en
Feedback
Abu Hessan - አቡ ሐሳን - قناة أبي حسان

Abu Hessan - አቡ ሐሳን - قناة أبي حسان

Open in Telegram
9 475
Subscribers
+1224 hours
+537 days
+61730 days
Posts Archive
ስህተቴን ባሳወቀኝ ሙስሊም ሁሉ የአ'ሏህ እውነት ይሁን። ነገርግን እኔ በምመዝንበት ሚዛን ካልተመዘንክ፣ በምሰፍርበት መስፈሪያ ካልተሰፈርክ ከሆነ «لا ناقة لي فيها ولا جمل» አይመለከተኝም። https://t.me/Abu_Hessan

🎁 በደምብ ይነበብ። ✅ሼርም ይደረግ።

✅የሰለዮች ትብብር አስፈላጊነቱ! — ሸይኽ ሙቅቢል ኢብኑ ሃዲ አል-ዋዲዒይ -ረሒመሁ'ሏህ- ሱዑዲያ ሂደው ሸሪዓዊ ትምህርት ተምረው ወደ ሀገራቸው "የመን 🇾🇪 اليمن" ሲመለሱ ከራፊዳዎችም ሆነ ከ
የሰለዮች ትብብር አስፈላጊነቱ! — ሸይኽ ሙቅቢል ኢብኑ ሃዲ አል-ዋዲዒይ -ረሒመሁ'ሏህ- ሱዑዲያ ሂደው ሸሪዓዊ ትምህርት ተምረው ወደ ሀገራቸው "የመን 🇾🇪 اليمن" ሲመለሱ ከራፊዳዎችም ሆነ ከሌሎች ሙብተዲዖች ብዙ ተጋፍጠዋል። በርካታ ስቃዮችንም አሳልፈዋል።" — "በስተመጨረሻም አ'ሏህ መንገዱን አመቻችቶላቸው ሰለፊየን ከየመን ውጪ ባሉ ሀገራቶች ራሱ በሰፊው ለማሰራጨት ችለዋል። ለማለት የፈለግኩት ሸኽዬው ብዙ ተሞክሮዎች አላቸውና ምክራቸው በደምብ ትኩረት ሊሰጠው ይገባል።" — ታላቁ ዓሊም ሸይኽ ሙቅቢል -ረሒመሁ'ሏሁ ተዓላ- እንዲህ አሉ፦ ጉዳዩ ትብብርን ይፈልጋል፤ ካልሆነ ወ'ሏሂ በእርግጥም ተዘምተናል (+) በእርግጥም ተዘምተናል። — ነጋዴ በንብረቱ እንዳይሰስት። ወደ አ'ሏህ ተጣሪ (ዳዒ) በራሱም ሆነ በደሙ እንዳይሰስት። እንደዚሁም የክብር ባለቤት በክብሩ እንዳይሰስት። — የልቅናው ጌታ በተከበረው መፅሀፉ እንዲህ ይላል፦ «በበጎ ነገርና አ'ሏህን በመፍራት ተረዳዱ፡፡ በወንጀልና ድንበር በማለፍ አትረዳዱ፡፡» [አል-ማኢደህ 2] ጥራት ይገባውና እንዲህም ይላል፦ «እናንተ ያመናችሁ ሆይ! የአላህ ረዳቶች ሁኑ፡፡» [አስ-ሶፍ 14] — ከኛ የአ'ሏህን ዲን መርዳት ይፈለጋል። ካላደረግነው ግን ፂማችን ይጎትታል (አህሉል ቢደዖች ፂምህ ይነጫል!)። — ለማንኛውም አሁሉስ-ሱናዎች በመሃከላቸው ባለው ነገር መዘያየርና መተባበር ያስፈልጋቸዋል። ካልሆነ ወ'ሏሂ የኢስላም ጠላት ይውጠናል።" 📚 ቀምዑል ሙዓኒድ (1) ከ 42 - 47 ባለው። — ወገን ምክሩ ለኛ ለሰለፊዮች ነው። ነገርግን ከነዚህ ወርቀማና ተሞክሯዊ ምክሮች የት ነው ያለነው!? እኔንም እንተንም ሁሉንም የሚመለከት አባታዊ ምክር ነውና ስሌላ ሰው እንደተወራ አስመስለን ነፍሳችንን አደጋ ላይ አንጣል።" — ሁላችንም እራሳችንን እንታዘብ። ሁሌም ለዲናችን (ለሰለፊያ) እንኑር። የግል ችግር እንደ ግል ታይቶ ይፈታ። ነገርግን ዲናችን ኢኽላስን መሰረት ያደረገ ሸሪዓዊ ትብብር ይፈልጋልና አንድነታችን ይጠንክር።" — የሰለፊያ ጉዳይ አሳስቧቸው ሰለፊያን በምን በልኩ ማሰራጨት እንደምንችል የሚያውቁ መሻዪኾችን በማማክር ቁርኣንና ሐዲሥን በሰለፎች አረዳድ በተደገፈው ስምሪታቸው እንስተማራ ስሜታችንን እንግታ።" وحق للشيخ الوادعي أن يقول: فلقدْ نصحتُكَ إنْ قبلتَ نصيحتي ... فالنُّصحُ أغلى ما يُباعُ ويُوهَبُ 💭 ትርጉም፦⬅️ምክሬን ከተቀበልክ በእርግጥ መክሬሃለሁ። ምክር ከሚሸጥና ከሚጀባ ነገር ሁሉ ውድ ነው።" አሏህ በችሮታው ይወፍቀን።➡️ ✅ ከከፊል ጭማሪ ጋር በድጋሚ የተለጠፈ። || የቴሌግራም ቻናል፦ https://t.me/Abu_Hessan https://t.me/Abu_Hessan

الفصل_المبين_في_دحض_شبهات_وتلبيسات_محمد_حامي_الدين.pdf3.23 KB

👎 የስራውን መጤነት የሀሳብህ ማማር አያሳምረው። ↘️አንድ ሰው አጅር አገኛለሁ ብሎ ለፍቶ፣ ጉልበቱን ጨርሶና፣ እድሜውን አቃጥሎ ወንጀል ሲያገኝ ምንኛ ያሳዝናል!? ዋናው ያንተ የሀሳብህና የኒያህ ማማር ሳይሆን የምትሰራው ዒባዳ ከነብዩ 🩷 መገኘቱ ነው።"ኢብኑ መስዑድ 🤎 የሆኑ ሰዎች የዚክሩን አባባል ከነብያችን 🩷 ከመጣው ቀይረው ሲያያቸው ተቃወማቸው እነሱም ኸይርን እንጂ አልፈለግንም አሉት፤ እሱም እንዲህ አላቸው፦ «وكم من مريد للخير لم يصبه» ስንትና ስንት ኸይርን ፈላጊ አለ ያላገኘው።" 🥲 يقول ربنا 🕋 : ((قُلْ هَلْ نُنَبِّئُكُم بِالْأَخْسَرِينَ أَعْمَالًا - الَّذِينَ ضَلَّ سَعْيُهُمْ فِي الْحَيَاةِ الدُّنْيَا وَهُمْ يَحْسَبُونَ أَنَّهُمْ يُحْسِنُونَ صُنْعًا)) ➡️ጌታችን 🕋 እንዲህ ይላል፦ «በሥራዎች በጣም ከሳሪዎቹን እንንገራችሁን» በላቸው፡፡ እነዚያ እነሱ ሥራን የሚያሳምሩ የሚመስላቸው ሲሆኑ በቅርቢቱ ሕይወት ሥራቸው የጠፋባቸው ናቸው፡፡ 📗(ሱረቱል-ከህፍ 103 -104) ▫️ የቴሌግራም ቻናል፦ https://t.me/Abu_Hessan https://t.me/Abu_Hessan

Repost from N/a
♦️| አዲስ ሙሓደራ ከ"ملتقى" ቁ.025 ርእስ፦ "መርከቧ ከመስመጧ በፊት" 🎙ኡስታዝ ሱልጧን ሐሰን (አቡ ኑዐይም) -ሐፊዞሁ'ሏህ- 🕌 በሰለፊዮች መገናኛ ግሩፕ የተደረገ ሙሓደራ! 🗓 ረቢዑል-አወል 22 - 1448 || #የመገናኛው_ግሩፕ፦ t.me/Multeqa_Ahlissuneh t.me/Multeqa_Ahlissuneh

​💎 እውቀት የነቢያት ውርስ ነው! ​አሁኑኑ ይቀላቀሉን! 👇

🫱 አጓጊው ፕሮግራም ተጀመረ! 🎤ኡስታዝ ሱልጧን ሐሰን (አቡ ኑዐይም) -ሐፊዞሁ'ሏህ- ⏺ርእስ፦ "መርከቧ ከመስመጧ በፊት" 📎| ሊንኩን በመንከት ተከታተሉ፦ https://t.me/Multeqa_Ahlissuneh?videochat=db14b6a0777ab514fd

✅ማልድ ትደርሳለህ — የአ'ሏህ መልእክተኛ 🩷 እንዲህ አሉ፦ (مَنْ خَافَ أَدْلَجَ، وَمَنْ أَدْلَجَ بَلَغَ الْمَنْزِلَ، أَلَا إِنَّ سِلْعَةَ اللَّهِ
✅ማልድ ትደርሳለህ — የአ'ሏህ መልእክተኛ 🩷 እንዲህ አሉ፦ (مَنْ خَافَ أَدْلَجَ، وَمَنْ أَدْلَجَ بَلَغَ الْمَنْزِلَ، أَلَا إِنَّ سِلْعَةَ اللَّهِ غَالِيَةٌ، أَلَا إِنَّ سِلْعَةَ اللَّهِ الْجَنَّةُ) — “የፈራ ይማልዳል (በጠዋት ተነስቶ ይወጣል)። በጠዋት የተንቀሳቀሰ ደግሞ ያሰበበት ይደርሳል። አዋጅ! የአላህ እቃ (ሸቀጥ) ውድ ናት። አዋጅ! የአላህ ሸቀጥ ደግሞ ጀነት ነች።” (📚 ቲርሚዚይ ሶሂህ ብለውታል 2450) ▫️ የቴሌግራም ቻናል፦ https://t.me/Abu_Hessan https://t.me/Abu_Hessan

✔️የእንሴኖ ሰለፊዮች ጥሩ እንቅስቃሴ ላይ ዋናው። 🫱⬅️የእንሴኖ ሰለፊዮችን አድ ሼር.. በማድረግና የአቅማችሁን አስተውፅኦ በማድረግ ተባበሯቸው።➡️ 🕌 ሰለፊያ መስጂድ...፦ ✈️ @Enseno_Se
✔️የእንሴኖ ሰለፊዮች ጥሩ እንቅስቃሴ ላይ ዋናው። 🫱⬅️የእንሴኖ ሰለፊዮችን አድ ሼር.. በማድረግና የአቅማችሁን አስተውፅኦ በማድረግ ተባበሯቸው።➡️ 🕌 ሰለፊያ መስጂድ...፦ ✈️ @Enseno_Selefiya_Madrasah 🕌 አል-ፉርቋን መድረሳ፦ ✈️ t.me/Enssenofurkanmedresa 🕌 ኢማሙ'ሻፊዒይ መስጂድ፦ ✈️ @Ensenoimamushafiymesjid

👉 ሙሐመድ ሓሚዲን የሰይድ ቁጥብ ጠበቃ ! ክፍል ሁለት — የሶሓቦችን ክብር የመንካትና የመዝለፍ ብይኑ :– ሙሓመድ ሓሚዲን ሰይድ ቁጥብ ከነብዩ ሶሓቦች ውስጥ የብዙዎችን ክብር ከማጉደፉና ከማብጠልጠሉ በተጨማሪ ሙዓዊያንና አጋሮቹን በኒፋቅ ፣ በማታለልና በመሰሪነት ይፈርጃል ። የዚህ አይነቱ የኢስላም ጠላቶች በእስልምና ላይ ተአማኒነት እንዳይኖር ያስተላለፉትን ሶሓቦች ማነወር የሚሉትን መርህ ተከትሎ ሶሓቦችን የማብጠልጠል ስራ በተዋጣለት መልኩ ሰርቶ ከራፊዳዎች ሽልማት የተቸረውን ሰይድ ቁጥብ ተግባር ቀለል በማድረግ ነው የሚያጣፋው ጠበቃው ሙሐመድ ሓሚዲን ። የሰይድ ቁጥብን በሶሓቦች ላይ ዘመቻ ክብደት ለማወቅ ሶሓቦች በኢስላም ያላቸውን ቦታ ማወቅ ግድ ይላል ። የሶሓቦች ክብር በቁርኣን ውስጥ : – { مُّحَمَّدٌ رَّسُولُ اللَّهِ ۚ وَالَّذِينَ مَعَهُ أَشِدَّاءُ عَلَى الْكُفَّارِ رُحَمَاءُ بَيْنَهُمْ ۖ تَرَاهُمْ رُكَّعًا سُجَّدًا يَبْتَغُونَ فَضْلًا مِّنَ اللَّهِ وَرِضْوَانًا ۖ سِيمَاهُمْ فِي وُجُوهِهِم مِّنْ أَثَرِ السُّجُودِ ۚ ذَٰلِكَ مَثَلُهُمْ فِي التَّوْرَاةِ ۚ وَمَثَلُهُمْ فِي الْإِنجِيلِ كَزَرْعٍ أَخْرَجَ شَطْأَهُ فَآزَرَهُ فَاسْتَغْلَظَ فَاسْتَوَىٰ عَلَىٰ سُوقِهِ يُعْجِبُ الزُّرَّاعَ لِيَغِيظَ بِهِمُ الْكُفَّارَ ۗ وَعَدَ اللَّهُ الَّذِينَ آمَنُوا وَعَمِلُوا الصَّالِحَاتِ مِنْهُم مَّغْفِرَةً وَأَجْرًا عَظِيمًا } الفتح (29) " የአላህ መልክተኛ ሙሐመድ እነዚያም ከእርሱ ጋር ያሉት (ወዳጆቹ) በከሓዲዎቹ ላይ ብርቱዎች በመካከላቸው አዛኞች ናቸው ፡፡ አጎንባሾች፣ ሰጋጆች ኾነው ታያቸዋለህ፡፡ ከአላህ ችሮታንና ውዴታን ይፈልጋሉ ፡፡ ምልክታቸው ከስግደታቸው ፈለግ ስትኾን በፊቶቻቸው ላይ ናት ፡፡ ይህ በተውራት (የተነገረው) ጠባያቸው ነው ፡፡ በኢንጂልም ውስጥ ምሳሌያቸው ቀንዘሉን አንደአወጣ አዝመራና ፣ (ቀንዘሉ) እንዳበረታው፣ እንደወፈረምና ፣ ገበሬዎቹን የሚያስደንቅ ኾኖ በአገዳዎቹ ላይ ተስተካክሎ እንደ ቆመ (አዝመራ) ነው ፡፡ (ያበረታቸውና ያበዛቸው) ከሓዲዎችን በእነርሱ ሊያስቆጭ ነው ፡፡ አላህም እነዚያን ያመኑትንና ከእነርሱ በጎዎችን የሠሩትን ምሕረትንና ታላቅ ምንዳን ተስፋ አድርጎላቸዋል "፡፡ { وَالسَّابِقُونَ الْأَوَّلُونَ مِنَ الْمُهَاجِرِينَ وَالْأَنصَارِ وَالَّذِينَ اتَّبَعُوهُم بِإِحْسَانٍ رَّضِيَ اللَّهُ عَنْهُمْ وَرَضُوا عَنْهُ وَأَعَدَّ لَهُمْ جَنَّاتٍ تَجْرِي تَحْتَهَا الْأَنْهَارُ خَالِدِينَ فِيهَا أَبَدًا ۚ ذَٰلِكَ الْفَوْزُ الْعَظِيمُ } التوبة (100) " ከስደተኞቹና ከረዳቶቹም ሲኾኑ የመጀመሪያዎቹ ቀዳሚዎች እነዚያም በበጎ ሥራ የተከተሏቸው አላህ ከእነሱ ወዷል ከእርሱም ወደዋል ፡፡ በሥሮቻቸውም ወንዞች የሚፈሱባቸውን ገነቶች በውስጣቸው ዘለዓለም ነዋሪዎች ሲኾኑ ለእነርሱ አዘጋጅቶላቸዋል ፡፡ ይህ ታላቅ ዕድል ነው "፡፡ لِلْفُقَرَاءِ الْمُهَاجِرِينَ الَّذِينَ أُخْرِجُوا مِن دِيَارِهِمْ وَأَمْوَالِهِمْ يَبْتَغُونَ فَضْلًا مِّنَ اللَّهِ وَرِضْوَانًا وَيَنصُرُونَ اللَّهَ وَرَسُولَهُ ۚ أُولَٰئِكَ هُمُ الصَّادِقُونَ ለእነዚያ የአላህን ችሮታና ውዴታውን የሚፈልጉ፣ አላህንና መልክተኛውንም የሚረዱ ኾነው ከአገሮቻቸውና ከገንዘቦቻቸው ለተወጡት ስደተኞች ድኾች (ይስሰጣል)፡፡ እነዚያ እነርሱ እውነተኞቹ ናቸው፡፡ وَالَّذِينَ تَبَوَّءُوا الدَّارَ وَالْإِيمَانَ مِن قَبْلِهِمْ يُحِبُّونَ مَنْ هَاجَرَ إِلَيْهِمْ وَلَا يَجِدُونَ فِي صُدُورِهِمْ حَاجَةً مِّمَّا أُوتُوا وَيُؤْثِرُونَ عَلَىٰ أَنفُسِهِمْ وَلَوْ كَانَ بِهِمْ خَصَاصَةٌ ۚ وَمَن يُوقَ شُحَّ نَفْسِهِ فَأُولَٰئِكَ هُمُ الْمُفْلِحُونَ እነዚያም ከበፊታቸው አገሪቱን መኖሪያ ያደረጉት እምነትንም የለመዱት ወደእነርሱ የተሰደዱትን ሰዎች ይወዳሉ፡፡ (ስደተኞቹ) ከተሰጡትም ነገር በልቦቻቸው ውስጥ ቅሬታን አያገኙም፡፡ በእነርሱ ላይ ችግር ቢኖርባቸውም በነፍሶቻቸው ላይ ሌላውን ይመርጣሉ፡፡ የነፍሱንም ንፍገት የሚጠበቅ ሰው እነዚያ እነሱ ምኞታቸውን አግኚዎች ናቸው፡፡ وَالَّذِينَ جَاءُوا مِن بَعْدِهِمْ يَقُولُونَ رَبَّنَا اغْفِرْ لَنَا وَلِإِخْوَانِنَا الَّذِينَ سَبَقُونَا بِالْإِيمَانِ وَلَا تَجْعَلْ فِي قُلُوبِنَا غِلًّا لِّلَّذِينَ آمَنُوا رَبَّنَا إِنَّكَ رَءُوفٌ رَّحِيمٌ እነዚያም ከበኋላቸው የመጡት «ጌታችን ሆይ! ለእኛም ለእነዚያም በእምነት ለቀደሙን ወንድሞቻችን ምሕረት አድርግ፡፡ በልቦቻችንም ውስጥ ለእነዚያ ለአመኑት (ሰዎች) ጥላቻን አታድርግ፡፡ ጌታችን ሆይ! አንተ ርኅሩህ አዛኝ ነህና» ይላሉ፡፡ الحشر (10–8) { وَاعْلَمُوا أَنَّ فِيكُمْ رَسُولَ اللَّهِ ۚ لَوْ يُطِيعُكُمْ فِي كَثِيرٍ مِّنَ الْأَمْرِ لَعَنِتُّمْ وَلَٰكِنَّ اللَّهَ حَبَّبَ إِلَيْكُمُ الْإِيمَانَ وَزَيَّنَهُ فِي قُلُوبِكُمْ وَكَرَّهَ إِلَيْكُمُ الْكُفْرَ وَالْفُسُوقَ وَالْعِصْيَانَ ۚ أُولَٰئِكَ هُمُ الرَّاشِدُونَ } الحجرات (7) " በውስጣችሁም የአላህ መልክተኛ መኖሩን ዕወቁ ፡፡ ከነገሩ በብዙው ቢከተላችሁ ኖሮ በእርግጥ በተቸገራችሁ ነበር ፡፡ ግን አላህ አምነትን ወደናንተ አስወደደ ፡፡ በልቦቻችሁም ውሰጥ አጌጠው ፡፡ ክህደትንና አመጽንም እንቢተኛነትንም ወደናንተ የተጠላ አደረገ ፡፡ እነዚያ (እምነትን የወደዱና ክሕደተን የጠሉ) እነርሱ ቅኖቹ ናቸው "፡፡ እነዚህ የቁርኣን አንቀፆች በመቶዎች ከሚቆጠሩት ውስጥ ጥቂቶቹ ናቸው ። የነብዩ ባልደረቦች ( ሶሓቦች) ደረጃቸው ቢለያይም ባጠቃላይ ፍትሓዊና ከኒፋቅና ኩፍር የጠሩ ለመሆናቸው በአላህ የተመሰከረላቸው ናቸው ። አንድ ከገጠር የመጣ ገበሬ ከነብዩ ጋር ተገናኝቶ በሳቸው አምኖ በዛው ኢማን ላይ ከሞተ ከዛ በኋላ ከሚመጣ ትውልድ ውስጥ የፈለገው የዒልም ደረጃ ላይ ቢደርስ ከዛ በላይ ለላኢላሃ ኢልለላህ ብሎ መስዋእት ቢሆን በደረጃ ከገጠር መጥቶ ካመነው ሶሓብይ ጋር አይገናኝም ። የሶሓብይነት ደረጃ ማንም ላይደርስበት በሩ ተዘግቷል ። እነዚህን አላህ የመሰከረላቸው ብርቅዬ የነብዩ ባልደረቦችን መተቸትና ክብራቸውን መንካት የመጨረሻው ደረጃ ሙብተዲዕ ያደርጋል ።

👉 ሙሐመድ ሓሚዲን የሰይድ ቁጥብ ጠበቃ ! ክፍል አንድ ሶሞኑን ሙሐመድ ሓሚዲን የእውቀት ቅርስ በሚል ፕሮግራም ላይ ቀርቦ ስለ ሰይድ ቁጥብ የተለያዩ ጥያቄዎች ቀርቦለት በጣም አሳፋሪ በሆነ ሁኔታ የነብያቶችን ክብር የሚያጎድፈውን የነብዩ ባልደረቦችን የሚያዋርደውንና የሙስሊሙን አለም ማህበረሰብ በግልፅ የሚያከፍረውን የሰይድ ቁጥብን ጥመቶች እንደ ተራ ጥፋት በመቁጠር ስሌት ሰርቶ ሙዋዘና በሚባለው ሸውራራ ሚዛን እየለካ ያ ጥፋት በዚህ ይጣፋል በሚል አይነት አንድምታ ያለው ዑዝር እየሰጠ ሲያልፍ ሰምተናል ። ከዚህ ጎን ለጎን የሰይድ ቁጥብን ስህተቶች በመረጃ በማጋለጥ ለነብያቶችና ለነብዩ ባልደረቦች ክብር ዘብ የቆሙትን ዑለሞች ወሰን አላፊዮች በሚል የንግግር ቃና ወርፏል ። በዚህ ሳያበቃ ለሸውራራ ፍርዱ ይረዳው ዘንድ ከዘመናችን ዑለሞች ውስጥ ስለግለሰቡ ሳያውቁ በፊት የተናገሯቸውን ንግግሮች በማምጣት ባጢልን ሐቅ ለማስመሰል ሞክሯል ። እዚህ ጋር አንባቢያን ሊያውቁት የምፈልገው የሰይድ ቁጥብ ስህተቶች ተራ ስህተቶች ሳይሆኑ አንዱ እንኳን ከእስልምና የሚያወጣ አይነት ለተራራ የከበዱ ቅጥፈት የተሞላባቸው ከባባድ ወንጀሎች መሆናቸውን ነው ። ከእነዚህ ውስጥ እንደማሳያ የነብያትን ክብር መንካት ፣ ሶሓቦችን በኒፋቅ መወረፍ የኢስላሙን አለም ማህበረሰብ በግልፅ ማክፈር የሚሉት ይገኙበታል ። እንደነዚህ አይነት ስህተቶች የኢስላም ሊቃውንቶች ዘንድ ያላቸው ብይን ባለቤቱ ይከፍራል ወይስ አይከፍርም የሚል ነው ። በሱና ዑለሞች ዘንድ ፋሲቅና ሙብተዲዕ ለመሆኑ ኺላፍ የለም ። አላህ ካለ ወደፊት በሚመጡ ክፍሎች በዝርዝር በመረጃ የምናያቸው ይሆናል ። ለዛሬ ለመግቢያ ይሆን ዘንድ ስለነብያትና ሰለሶሓቦች ክብር የተወሰነ እንይ :– — ነብያቶች በአላህና በፉጡራኖቹ መካከል አገናኝ እንዲሆኑ ፉጡራኖችን ከኩፍር ጨለማ ወደ ኢማን ብርሀን እንዲያሸጋግሩ አላህ መርጦ የላካቸው ምርጥ ባሮቹ ናቸው ። ይህን አስመልክቶ አላህ በተከበረው ቃሉ እንዲህ ይላል : – { وَإِذَا جَاءَتْهُمْ آيَةٌ قَالُوا لَن نُّؤْمِنَ حَتَّىٰ نُؤْتَىٰ مِثْلَ مَا أُوتِيَ رُسُلُ اللَّهِ ۘ اللَّهُ أَعْلَمُ حَيْثُ يَجْعَلُ رِسَالَتَهُ ۗ سَيُصِيبُ الَّذِينَ أَجْرَمُوا صَغَارٌ عِندَ اللَّهِ وَعَذَابٌ شَدِيدٌ بِمَا كَانُوا يَمْكُرُونَ} الأنعام (124) " ተዓምርም በመጣቻቸው ጊዜ ፡- «የአላህ መልክተኞች የተሰጡትን ብጤ እስክንሰጥ ድረስ በፍጹም አናምንም» አሉ ፡፡ አላህ መልክቱን የሚያደርግበትን ስፍራ ዐዋቂ ነው ፡፡ እነዚያን ያመጹትን ሰዎች ይዶልቱ በነበሩት ነገር አላህ ዘንድ ውርደትና ብርቱ ቅጣት ያገኛቸዋል "፡፡ በዚህ አንቀፅ ላይ እንደምናየው አላህ ለከሀዲያኖች መልስ ሲሰጥ " አላህ መልእክቱን የሚያደርግበትን ስፍራ ዐዋቂ ነው " ይላቸዋል ። መልእክቱንም ከሰዎች ውስጥ ነብያቶችን መርጦ ልባቸውን ለመልእክቱ ማስቀመጫ ስፍራ አደረገው ። እነዚህን አላህ መልእክቱን ሊያስቀምጥባቸው የመረጣቸውን ነብያቶች ክብር መንካት ያከፍራል ። ይህ ሲባል የአንድ ነብይ ክብር መንካት ያጠቃላይ ነብያቶች ክብር መንካት ማለት አይደለም የሚል የሸረሪት ድር አይነት ሹብሀ የሚያነሱ ስለማይጠፉ አላህ ይህን በር በሚቀጥለው አንቀፅ ዘግቶታል : – { قُلْ آمَنَّا بِاللَّهِ وَمَا أُنزِلَ عَلَيْنَا وَمَا أُنزِلَ عَلَىٰ إِبْرَاهِيمَ وَإِسْمَاعِيلَ وَإِسْحَاقَ وَيَعْقُوبَ وَالْأَسْبَاطِ وَمَا أُوتِيَ مُوسَىٰ وَعِيسَىٰ وَالنَّبِيُّونَ مِن رَّبِّهِمْ لَا نُفَرِّقُ بَيْنَ أَحَدٍ مِّنْهُمْ وَنَحْنُ لَهُ مُسْلِمُونَ} آل عمران (84) «በአላህ አመንን ፡፡ በእኛ ላይ በተወረደውም (በቁርኣን) ፣ በኢብራሂምና በኢስማዒልም፣ በኢስሓቅም፣ በያዕቆብም ፣ በነገዶችም ላይ በተወረደው ፤ ለሙሳና ለዒሳም ለነቢያትም ሁሉ ከጌታቸው በተሰጠው (አመንን) ፡፡ ከእነርሱ መካከል አንድንም አንለይም ፡፡ እኛ ለእርሱ ታዛዦች ነን» በል ፡፡ በዚህ አንቀፅ ላይ እንደምናየው አላህ ከመልእክተኞች መካከል መለየት እንደማይቻል እንዲህ ብሎ ነገረን " ከእነርሱ መካከል አንድንም አንለይም " ። እኛ ለነርሱ ታዛዦች ነን በል " ። ብሎ በሁሉም ነብያቶች ማመን ግዴታ መሆኑ ነግሮናል ። ከዚህ በመነሳት የኢስላም ሊቃውንቶች አላህ ከላካቸው መልእክተኛች ውስጥ የአንዱንም ክብር መንካት የሁሉንም ክብር መንካት እንደሆነ በተለይም ደግሞ ዑሉል ዐዝም የተባሉትን ክብር መንካት የወንጀሉን ክብደት እንዲጨምር እንደሚያደርገው ይስማማሉ ። ለዚህ ነው ከእስልምና መሰረታዊ የኢማን ክፍሎች ( አርካኑል ኢማን) አንዱ በነብያት ማመን የሆነው ። የነብያትን ክብር መንካት በነብያት ማመንን ይፃረራል ። ሰይድ ቁጥብ የሚያቋሽሻቸው ነብዩላሂ ሙሳ ከዚህ ለየት ባለ መልኩ አላህ ለኔ መርጨሃለሁ ያላቸው መሆኑን በሚቀጥለው አንቀፅ እንመልከት : – { وَاصْطَنَعْتُكَ لِنَفْسِي} طه (41) «ለነፍሴም (በመልእክቴ) መረጥኩህ ፡፡ ይህ ስለነብያቶች ከመጡ መረጃዎች ከባሕር እንደ ጠብታ ሲሆን ለጮሌ ማመላከት ይበቃዋልና ልብ ያለው ልብ ይበል ። እኝህን አላህ መርጦ ያከበራቸውና መልእክተኛው አድርጎ ወደ ሰው ልጆች የላካቸውን የአላህ መልእክተኛን ነው ሰይድ ቁጥብ ክብራቸውን በመንካት የሚያዋርዳቸው ። አላህ ካለ በሚቀጥለው ክፍል ስለ ሶሓቦች ደረጃና ክብር እንዲሁም እነርሱን የመሳደብና ክብራቸውን የመንካት ብይን እናያለን ። https://t.me/bahruteka

🔷የሰለፊዮች ዋና አላማ ምንድነው?

قال الشيخ مقبل بن هادي الوادعي رحمه اللّٰه: "إن المجتمع الإسلاميَّ في حاجة شديدة إلى المرأة الصالحة التي تهتم بأخواتها المسلمات؛ حتى لا يتخطَّفهنَّ دعاة الفساد والإفساد".
الانتصار لحقوق المؤمنات (٠٤).
▫️ ኪታቧን ለማግኘት፦ https://t.me/Abu_Hessan/4073

يشارك 🇸🇦 محمد بن هادي المدخلي حفظه الله في الدورة التأصيلية العلمية التي ستقام في مسجد الشيخ محمد بن إبراهيم بالجامعة الإسل
يشارك 🇸🇦 محمد بن هادي المدخلي حفظه الله في الدورة التأصيلية العلمية التي ستقام في مسجد الشيخ محمد بن إبراهيم بالجامعة الإسلامية بالمدينة النبوية حسب الجدول المرفق👆 ١- المحاضرة الافتتاحية بعنوان: فضل العلم وطلابه وبيان فضل العلماء. ٢- شرح (نخبة الفكر) للحافظ ابن حجر.

|| አዲስ በያን (መግለጫ) 🔗 «ከቀናት በፊት ተለቆ የነበረው የደርስ ድምጽ የፈጠረውን የተሳሳተ አረዳድ ማስተካከል!!» 🎙በታላቁ ሸይኽ ዐብዱልሀሚድ ያሲን አል-ለተሚይ (ሐፊዘሁላህ) https://t.me/abdulham/2853 https://t.me/abdulham/2853

🇪🇹የኢትዮጵያ ሰለፊዮችን ትክክለኛ ቻናል በቀላሉ ለማግኘት👉OPEN👈 ምትለዋን ብቻ ይጫኑ

🎁 ስጦታ ለእህቶች! 📚 አል-ኢንቲሷር ሊሑቁቂል ሙእሚናት 🖋 ኡሙ ሰለመህ አል-ዐባሲየህ ▫️ የቴሌግራም ቻናል፦ https://t.me/Abu_Hessan