en
Feedback
የወልድያ ኦርቶዶክሳዊያን ሕብረት

የወልድያ ኦርቶዶክሳዊያን ሕብረት

Open in Telegram
358
Subscribers
No data24 hours
-27 days
-230 days
Posts Archive
“እርሱ ሊልቅ እኔ ግን ላንስ ያስፈልጋል።” በማለት ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ የመሰከረው ማነው?
Anonymous voting

በሽታ ከሰው ወደ ሰው እንደሚጋባ ሁሉ ጤንነትም ከሰው ወደ ሰው ይጋባል ጤናማ አስተሳሰብ ካላቸው ሰዎች ጋር መዋል ጤናማ ያደርጋል! መጽሐፍም እንዲህ ይላል “ከቸር ሰው ጋር ቸር ሆነህ ትገኛለህ ከቅን ሰው ጋር ቅን ሆነህ ትገኛለህ ከንጹሕ ጋር ንጹሕ ሆነህ ትገኛለህ ከጠማማም ጋር ጠማማ ሆነህ ትገኛለህ።” መዝሙር 18፥25-26 አብራችሁ የምትውሏቸው ሰዎች በእናተ ሕይወት ላይ በጎም ክፉም ተጽኖ አላቸው። ማንነታችሁ የሚወሰነው አብራችሁ በምትውሏቸው ሰዎች ነውና አብሯችሁ የሚውሉ ሰዎችን ምረጡ ። መልካም ነገር እንኳን ቢኖራችሁ “አትሳቱ ክፉ ባልንጀርነት መልካሙን አመል ያጠፋል።” 1ኛ ቆሮንቶስ 15፥33 እና ተጠንቀቁ ቴሌ ግራማችንን 👉 https://t.me/woldyyyyy

በወልድያ ከተማ ለምትኖሩ ኦርቶዶክሳዊያን ለጥቅምት 10/2017 ዓ.ም ማለትም እሁድ ከቀኑ 8:30 አዳጎ ፀደይ ባንክ ላይ ካለው አዳራሽ ለብርሃነ ዓለም ቅዱስ ጳውሎስ የጽዋ መርሐ ግብር እንድትገኙ ጠርተናችኋል እያንዳንዳችሁ ቢያንስ ሁለት ሁለት ሰዎችን በመጋበዝ ክርስቲያናዊ አደራችሁን እንድትወጡ ስል ጥሪ አስተላልፋለው። አደራ እንዳትረሱ!

የተከበራችው ወንድሞቼና እኅቶቼ እንደምን አላችሁ? ለጥቅምት 10/2017 ዓ.ም ማለትም እሁድ ከቀኑ 8:30 አዳጎ ፀደይ ባንክ ላይ ካለው አዳራሽ ለብርሃነ ዓለም ቅዱስ ጳውሎስ የጽዋ መርሐ ግብር እንድትገኙ ጠርተናችኋል እያንዳንዳችሁ ቢያንስ ሁለት ሁለት ሰዎችን በመጋበዝ ክርስቲያናዊ አደራችሁን እንድትወጡ ስል ጥሪ አስተላልፋለው። አደራ እንዳትረሱ!

​​ ✞ የፍቅር እናት ✞ የፍቅር እናት የሰላም /2/ ይናፍቀኛል ስምሽ ሳልጠራው ስቀር ማርያም በሕይወቴ ውስጥ በኑሮዬ ቅደሚ ከፊት ከኋላዬ ተደላደለ ልቤ አንቺ አለሽና ካጠገቤ ምኞቴም ይስመር ትልቅ ሕልሜ ልለፍ ወደፊት ተቋቁሜ የጌታዬ እናት ነሽ ኃይልን ያረጋል ጸሎትሽ እንዴት ቀራለው ከመንገድ አደራ እናቴ አስቢኝ ከሚያስጨንቀኝ ጠላት ለሚያሳድደኝ አትስጪኝ ትላንትም ዛሬም አመስጋኝ ነኝ የለም ለነገ የሚያስፈራኝ ሜዳ ይሆናል ተራራ ልጅሽ ስላለ ከኔ ጋራ

#መልሰኝ 😭😭😭 ጌታ ሆይ እንድትወደኝ እለምንሃለሁ ብዬ በፍጹም አልጠይቅህም እንደ ምታፈቅረኝ  እስከ ኃጢአቴ እንደ ተሸከምከኝ ጠንቅቄ አውቃለሁና። አባቴ ሆይ እኔ የምለምንህ አንተ መፍቀር የሚችል ልብ እንድታድለኝ ብቻ ነው። ጌታ ሆይ አንተን መውደድ ልቤን በፍቅርህ መሙላት እፈልጋለሁ። ከንቱ ነገሮች የሞሉትን ልቤን አጽድተህ የፍቅርህ ዙፋን አንተን በመውደድ እንድታስጌጠው እማጸንሃለሁ። ጌታ ሆይ ለአንተ ምኑን እደብቅሃለሁ ከአንተ ይልቅ የምወዳቸው ብዙ ኃጢአቶች አሉ። ሕይወቴን የተቆጣጠረው ዓለማዊነት በእርኩሰት ፍቅር ጥሎኛል። ኃጢአት ሰላሜን ቢነሳኝም እርሱን ከመስራት ግን ወደ ኋላ ብዬ አላውቅም። በአመጽ መንገድ እርቄ ከመሄዴ የተነሳ በነውሬ የማጌጥ ደንዳና የዲያብሎስ ባሪያ ሁኛለሁ። ኃጢአቴ እንደ ሰማይ ከዋክብት እንደ ምድር አሸዋ የበዛብኝ እኔ እጅጉን እፈራለሁ። በደሌን ባሰብኩ ጊዜ ልቦናዬ ይደነግጥብኛል። ወደ አንተም እማጸናለሁ። ተንበርክኬም እለምንሃለሁ ። የነጻነት ሕይወት ወደ ሚሰጥ ወደ ፍቅርህ ሙላት ከፍታ አውጣኝ። በኃጢአት ጨለማ የጠቆረ ልቤን በፍቅርህ ብርሃን አስጌጠኝ። ጌታ ኢየሱስ ሆይ እንካ እጄን ያዘኝ እኔ አቅም አጥቻለሁ በራሴ ጉልበት ከኃጢአት መውጣት አልችልም እባክህን ጎትተኝ። ለዓለማዊነት የተሰነፈውን እኔነቴን ፈውስ። ወደ ከፍታ ልወጣባቸው የተሰጡኝን ግን በኃጢአት የተሰበሩ ክንፎቼን ጠግን። ለምን እንደወደድከኝ በእድሜዬ ላይ ይችን ቀን ለምን እንደ ጨመርከኝ ሳስበው በጣም እገረማለሁ ይመለሳል ብለህ በትዕግሥት እኔን መጠበቅን ሳስብ እደነቃለሁ። ፍቅርህ ለእኔ ያለህ ውድ ከአእምሮ በላይ ነው። ለፍቅርህ የምመልሰው ጥቂት መልካም ምግባር የሌለኝ ከንቱ መሆኔን ሳስብ በራሴ እናደዳለሁ። ጌታ ሆይ እባክህ ተመለስ አትበለኝ ። እኔ በራሴ ከኃጢአት መመለስ የምችልበት አቅም የለኝምና ። በኃጢአት የደከምኩ ልምዝምዝ መሆኔን አንተ ታውቀለህ። ግን እንዲህ እልሃለሁ “ አንተ እግዚአብሔር አምላኬ ነህና መልሰኝ እኔም እመለሳለሁ።” ኤርምያስ 31፥18 ቴሌ ግራም https://t.me/Abelltefera

#የቅጠል_ጓደኞች በሕይወት ውስጥ ሦስት አይነት ጓደኞች ይኖራሉ። እነርሱም 1) የቅጠል ጓደኞች 2) የቅርንጫፍ ጓደኞች 3) ሥር የሰደዱ ጓደኞች ናቸው። ሰለ ሦስቱም የጓደኞች አይነቶች መስማት ትፈልጋለህ እንግዳውስ ተከተለኝ። #የቅጠል_ጓደኞች እነዚህ ሰዎች ወቅት ጠብቀው ወደ ሕይወትህ የሚመጡ ሰዎች ናቸው፡፡ ወቅት እንዳመጣቸው ወቅት ነው ከአጠገብህ የሚያጠፋቸው። እንደዚህ ጓደኞች ደካማ ስለሆኑ ልትደገፍባቸው አትችልም፡፡ ምን አልባት ደካማ መሆናቸውን ሳታውቅ ተደግፈሃቸው ከሆነ እንደ ሸንበቆ ሰለሆኑ በጣም ይጎዱሃል። የሚመጡት የሚፈልጉትን ለመውሰድ ሲሆን ነፋስ በመጣ ወቅት ይሸሻሉ። እነዚህ ሰዎች የሚወዱህ ሀብታም ጠንካራ ተፈላጊ በሆንክበት ጊዜ ብቻ ነው። መከራ የስብእና ስብራት ሐዘን ችግር በገጠመህ ወቅት ወይም ሕይወትህ የሚያመሰቃቅል ነፋስ ባገኘህ ጊዜ እነዚህ ቅጠሎችን በፍጹም አታገኛቸውም ። ቴሌ ግራም 👉 https://t.me/Abelltefera

ሰላም ለኪ እያለ(2) ሃርና ወርቁን ስታስማማ የገብርኤል ድምጽ ተሰማ ተሰማ የመላኩ ድምጽ ተሰማ ተሰማ የገብርኤል ድምጽ ተሰማ አዝ፥ ውሃ ስትቀጂ ክንፉን እያማታ ሊያበስርሽ የመጣው በታላቅ ደስታ ከሞገስሽ ብዛት ከሞገስሽ ብዛት ሲታጠቅ ሲፈታ አቅርቦልሽ ነበር የክብር ሰላምታ አዝ፥ የምስራቹን ቃል ሚስጥር ተሸክሞ ገብርኤል ተላከ ሊያረጋጋት ደግሞ እርጋታ ተሞልታ እርጋታን ተሞልታ ነገሩን መርምራ የመላኩን ብስራት ሰማችው በተራ አዝ፥ ይደሰታል እንጂ መንፈሴ ባአምላኬ በምስጋና ሳድር ዘወትር ተንበርክኬ ሃሳቤ ለቅጽበት ሃሳቤ ለቅጽበት ሌላ መች ያስባል ለኔ ልጅን መውለድ እንዴት ይቻለኛል አዝ፥ ካአንቺ ሚወለደው ለዑል ነው ክቡር የተመሰገነ በሰማይ በምድር ሚስጥሩ ሃያል ነው ሚስጥሩ ሃያል ነው ይረቃል ይሰፋል ካንቺ በቀር ይሄን ማን ይሸከመዋል አዝ፥ እጹብ ነው ድንቅ ነው አንቺን የፈጠረ አንቺን በመውደዱ ሰውን አከበረ አለም ይባረካል አለም ይባረካል በማእጸንሽ ፍሬ ክብርሽን አልዘልቅም ዘርዝሬ ዘርዝሬ አዝ፥ ሰላም ለኪ እያለ(2) ሃርና ወርቁን ስታስማማ የገብርኤል ድምጽ ተሰማ ተሰማ የመላኩ ድምጽ ተሰማ ተሰማ የገብርኤል ድምጽ ተሰማ

አኮቴት ላንተ ይገባል ስብሃት ለአንተ ይገባል አምልኮ ላንተ ይገባል ስግደትም ላንተ ይገባል ቅድመ ዓለም የነበር በታላቅ ስልጣኑ ለኩነተ ስጋ የመጣው በፍቅሩ ደግሞም ይህን ዓለም የሚሳልፍ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ኃያል የእኛ አሌንታ በሥጋው ሲታመም ሲሞት በመስቀል በአብ ቀኝ የነበር በሰማይ ሳይጎል የአዳምን ባሕርይ ተዋሕዶ ሲያከብር በዚህ ይገለጣል የጌታችን ፍቅር ከቅድስት ሥላሴ የማይለኝ ምክሩ ጉድለት የለበትም ትክክል ነው ክብሩ የአብ ቃል ጥበቡ ክንዱ ስለሆነ ዓለምን ፈጠረ አዳምን አድነ ሊቃነ መላዕክት ኃይላቸው ነውና ያመሰግኑታል በታላቅ ትህትና ዘውዳቸው ክብራቸው ስለሆነ እርሱ ይኖራሉ ወልድን ስሙን ሲያወድሱ #ሊቀ_መዘምር_ይልማ_ኃይሉ ▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬ 🍇🍇🍇🍇🍇🍇🍇

ኑ በብርሃኑ ተመላለሱ/2/ የፍቅርን ህይወት እንድትለብሱ ኑ በብርሃኑ ተመላለሱ ሁሉን በሚችል በአምላክ ጥላ በእረፍት ውሃ ስር አርፈናልና ሰላምና ፍቅር ሕይወት በሚሰጥ ወደ ጌታችን እንሂድ እንሩጥ ምህረትና ፍርድ በእጁ የያዘው የሰላም አባት መድሃኒዓለም ነው ሕይወት የሆነን በመስቀል ውሎ ብርሃን ሰጠን ጨለማን ሽሮ የሚያስደነግጥ የሚያስጨንቀን ይጠፋልና እርሱን ተማጽነን በቀን ከሚበር ፍላጻ ሁሉ ይታደገናል በቅዱስ ቃሉ እግርህ በድንጋይ እንዳይመታ በፈተና ውስጥ እንድትበረታ መቅሰፍት ከቤትህ እንዲከለከል ይጠብቀሃል ሌሊትና ቀን ስሙን ያወቀ ሕይወት መሆኑን ይመላለሳል ከሃይል ወደ ሃይል እረጅም እድሜ ይጠግባል እርሱ ብርሃን ይሆናል የፀጋ ልብሱ አቤቱ እንተ ተስፍ ነህና የምትመግብ የፍቅር መና ማዳንህ እኛን አስደስቶናል እንዲህ ያለ ክብር ከየት ይገኛል ▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬ 🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿 ነገር ግን እርሱ በብርሃን እንዳለ በብርሃን ብንመላለስ ለእያንዳንዳችን ኅብረት አለን፥ የልጁም የኢየሱስ ክርስቶስ ደም ከኃጢአት ሁሉ ያነጻናል።        1ኛ ዮሐንስ 1፥7 ▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬

የጽድቅን ሥራ የምንሠራበት ከኾነ አዲሱ ቀን ብቻ ሳይኾን አዲሱ ዓመት ለእኛ መልካም ነው፡፡ ኃጢአት የምንሠራበት ከኾነ ግን ቀኑ ብቻ ሳይኾን አዲሱ ዓመትም ክፉና መከራ የመላበት ይኾንብናል፡፡ አዲሱን ዓመት በበጐ ሥራ የምንጀምረው ከሆነ በዓመቱ በምናደርገው ማንኛውም ክንውን ላይ በጐ ተጽዕኖ ያሳድርብናል፡፡" ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ

ምንም እንኳን ምድሪቱን ያጎሳቆልን ዛፍ ብንሆንም በቸርነቱ ዘመንን የሚያቀዳጅ አምላክ መልካም ፍሬ እናፈራ እንደሆን ይህችን ዓመት ደግሞ (ተወን) ሰጠን። የበረከት ዘመን ይሁንልዎ። © ወንድማችሁ አቤል ተፈራ በላይ

ጸሎት የነፍስ ተራ ሰሜቶችን ፀጥ ያደርጋል የቁጣን ዓመጽ ያበርዳል ቅናትን ያጠፋል ክፉ ፍላጎቶችን ይበትናል የዓለማዊ ነገሮችን ፍቅር ያመነምናል ለነፍስም ታላቅ ሰላምና እርጋታን ያመጣል። ለመጸለይ ነገ ዛሬ አትበል ሰበብ አታብዛ። በቀን ሁለቴ በመጸለይ መጀመር ትችላለህ። በጠዋቱ የጸሎት ጊዜህ በእግዚአብሔር ፊት ስትቆም እንዲህ በል ፦ የጊዜያት ባለቤት እግዚአብሔር ሆይ የጨለማውን ግርማ ገፈህ ብርሃኑን እንድመለከት ሰለረዳሃኝ በኃጢአቴ ብዛት በሰውነቴ ክፋት ተስፋ ሳትቅርጥ በእድሜ ላይ ይችን ቀን ለንስሐ ሰለጨመርከኝ አመሰግንሃለሁ ። በመኝታዬም ስለጠበከኝ ከሞት ስለሰወርከኝ እጅ መንሳቴን ለአንተ አቀርባለሁ፡፡ ጌታ እግዚአብሔር ሆይ ቀኔ ያማረ በቅድስና የተዋበ ይሆን ዘንድ ባርክልኝ ከኃጢአት ሁሉ ጠብቀኝ አሜን ብለህ አባታችን ሆይ የሚለውን ጸሎት ከጨመርክበት ይህ እንደመጀመሪያ በቂ ነው። ይህንን ያለማቋረጥ ጠዋት ከእንቅልፍህ ስትነሳ ሰው ከማገኘትህ በፊት ወደ ሥራ ከመውጣትህ አስቀድሞ ያለመሰልቸት አድርገው ። እውነት እልሃለሁ በሕይወትህ ለውጡን ታየዋለህ። https://t.me/woldyyyyy

የወልድያ ኦርቶዶክሳዊያን ሕብረት https://t.me/woldyyyyy

destegna [997F87D].mp494.66 MB

የወልድያ ኦርቶዶክሳዊያን ሕብረት https://t.me/woldyyyyy