en
Feedback
Ďaŵud Apologetics◍﷽

Ďaŵud Apologetics◍﷽

Open in Telegram

▫️ወደ ኸይር ነገር ሰውን ያመላከተ እነሱ የሰሩትን አጅር በሙሉ ያገኛል ከሰሪዎቹ አንድ አጅር ሳይቀነስ {ሰ.ዐ.ወ} ✅ስለዚህ እኔም በዚህ ቻናል የተለያዩ:– #ቁርአናዊ አስተምሮቶች #ኢስላማዊ ታሪኮችና ሀዲሶች #የንፅፅር እና የአቂዳ ትምርቶች #quote & ጥያቄና መልስ #ጠቃሚ ንግግሮችን እለቃለው ሀሳብ ካለ👇 @ibnu_Jemal7 Share for friends 👇

Show more
5 618
Subscribers
-224 hours
-297 days
-14130 days
Posts Archive
የቂያማ ቀን የሚሰጥህ መፅሀፍ ደራሲው አንተ ነህ 🌱 @TewhedandSuna

🔆ቁርአን ከቃኢዳ ጀምሮ እንዲሁም አጫጭር                          👉ኪታቦች  መቅራት የምትፈልጉ ☑️በቴሌግራም ቀጥታ (live) እና ☑️በኢሞ በቀጥታ (live) በተጅዊድ ከፈተና  ጋር መቅራት የምትፈልጉ         በዚህ አናግሩን 👇👇      👉@Umu_asiya65          👆በዚህ ኑ

🆕📲 አዲስ አፕልኬሽን ተለቀቀ ↩️اسـم الكتـاب፡- ➘➷➴ ⬅️ تنبيهات على أحكام تختص بالمؤمنات ↪ የኪታቡ ስም፦➘➷➷ ➡️ ተንቢሀት አላ ኣህካሚን      ተኽተሱ ቢልሙእሚናት 🎙 ደርሱ የተሰጠው፦ በኡስታዝ አቡል በያን ኑርአዲስ ሲራጅ አላህ ይጠብቀው! 🎁 የእህታችን_ስጦታ ነው የኡስታዝ አቡልበያን ሌሎቹ ትምህርቶች ለማግኘት በዚ ሊንክ ይግቡ https://t.me/Nuraddissiraj https://t.me/Nuraddissiraj የቡታጀራ አልበያን የሱና መስጂድ  መደረሳ ለመረዳት  በታቹ ሊንክ ይግቡ https://t.me/albeyanbutajiragroup https://t.me/albeyanbutajiragroup 🎙  ከነ ሊንኩ ሼር መድረግን አትርሱ ⁉️ስለ አወራረዱ https://t.me/jj_app_developer/219 መሰል ስራዎችን ለማሰራት👇 @JJ_selfy_app_developer ከመቶ በላይ አፖችን ለማግኘት ቻናለችንን ይቀላቀሉhttps://t.me/jj_app_developer https://t.me/jj_app_developer

"በቅሎ አባትሽ ማነው ቢሏት፣ፈረስ አጎቴ ነው አለች..." ​ እንደሚታወቀዉ በቅሎ የምትወለደው ከአህያና ከፈረስ ነው፤ነገር ግን አህያን ዝቅ አድርጋ ስለምታስብ፣ አባቷ አህያ መሆኑን ደብቃ ከፍ ያለውን ፈረስ "አጎቴ ነው" በማለት ትመካለች።

🔶# የአልከሶ መውሊድ ቀን የትልቁ ሺርክ ቀን ነው ክፍል2 🔶በማዕከላዊ ኢትዮጲያ ክልል በስልጤ ዞን በአልቾ ውሪሮ ወረዳ በኩተሬ አል'ዋህዳ መስጂድ የተደረገ ሙሐደራ። 🎙በኡስታዝ ሻኪር ቢን ሱልጣን (ሀፊዘውላህ) 📌 ትምህርቱን ለመከታተል ይህን ቻናል ይቀላቀሉ 👇👇👇 🌐 https://t.me/shakirsultan

Repost from ISLAMIC POST
ሱረቱል ካህፍ‼️ ▬ ▬ ▬ ▬ ▬ ▬ ✍በእለተ ጁምአ ሱረቱል ካህፍን መቅራት ሱና ነው፣ በዚህ ውድ ቀን ውስጥ ስለተከሰቱ ዋና ዋና ክስተቶች እና ቱሩፋቶች እንዲሁም በሱረቱል ካህፍ ውስጥ የተወሱ አንዳንድ ሁነቶችን ለማንሳት ያክል: እለተ ጁምዓ:- ✔️ አባታችን አደም የተፈጠረበት እለት፣ ✔️ ጀነት የተፈጠረበት እለት፣ ✔️ አደም ና ሀዋ ምድር ከወረዱ በሗላ የተገናኙበት እለት፣ ✔️ ቂያማ የሚቆምበት እለት፣ ✔️ የሰው ልጆች ጀነት የሚገቡበት እለት፣ * ሱረቱል-ከህፍ:- ✔️ በምስጋና የሚጀምር ምእራፍ - የዋሻው ሰዎች (አስሀቡል ካህፍ)፣ ✔ የወጣቶቹን ገድል ታሪክ የሚዘክር ምእራፍ፣ ✔️ የኸድር እና ሙሳን ታሪክ የሚያወሳ _ ነቢዩላህ ሙሳ ከኸድር የቀሰሟቸው ትምህርቶችን ይዘረዝራል፣ _ አዋቂ እንኳን ብንሆን ከእኔ በላይ አዋቂ የለም ማለት ከኢስላማዊ አደብ (ስነ-ምግባር) አንፃር ተገቢ እንዳልሆነ፣ _ ኸድር ነቢዩላህ ሙሳን (ዓለይሂ ሰላም) አስተባብረው የየቲሞችን ቤት ከመውደቅ እንደታደጉ፣ በዚህም ድርጊታቸው ለመላው የሰው ዘር ታሪካቸው አስተማሪ ይሆን ዘንድ በሱረቱል ካህፍ ውስጥ መካተቱ፣ ✔️ የሁለት ባለ እርሻ ታሪክ ይተርካል፣ በሀብት መወዳደር መጨረሻው "ውድመት" እንደሆነ ያትታል። ✔️ የዙልቀርነይን ታሪክ ምድርን ስለገዛው ገናና ንጉስ በምእራብ በምስራቅ በሰሜን አቅጣጫ የዙፋኑን መዳረሻ ስላደረገው ቅኑ መሪ ያወሳል፣ ስለያእጁጅ እና መእጁጅ አስፈሪ ድባብና የዙልቀርነይን የብረት ግድብ መፍትሄ ይጠቅሳል። ✔️በመጨረሻም በአላህ ያመኑ ሰዎች መልካምን የሰሩ ሰዎች ማረፊያቸው በፊርደውስ ከተማ እንደሆነ ይዘረዝራል፣ ከአላህ ጋር መገናኘትን የፈለገ ሰው አላህን ያለ አጋር በአሀዳዊነት (በብቸኝነት) መገዛት እንዳለበት እና ከባእድ አምልኮ መራቅ እንዳለበት በመናገር ምእራፉን ይቋጨዋል። እነዚህን ሁሉ ከመጀሪያ እስከ ፍፃሜ ከታሪክ ማስተማር እስከ ምክር ድረስ የሚዘክር ምዕራፍ በየሳምንቱ ቢያንስ አንዴ ጁሙዓን እንኳን ቀርተን የማስተንተን ልቦና ከሌለን ከባድ ነው። አላህ ከሚያስተነትኑትና ልቦና ከሰጣቸው ባሮቹ ያድርገን። * "አላሑመ ሶሊ ወሰሊም ወባሪክ ዓላ ነቢይና ሙሀመድ" ﺍﻟﻠَّﻬُــﻢَّ ﺻَﻞِّ ﻭَﺳَـــﻠِّﻢْ ﻭَﺑَﺎﺭِﻙْ ﻋﻠﻰ ﻧَﺒِﻴِّﻨَـــﺎ ﻣُﺤﻤَّﺪﷺ ﺍﻟﻠَّﻬُــﻢَّ ﺻَﻞِّ ﻭَﺳَـــﻠِّﻢْ ﻭَﺑَﺎﺭِﻙْ ﻋﻠﻰ ﻧَﺒِﻴِّﻨَـــﺎ ﻣُﺤﻤَّﺪﷺ || መልካም ጁምዓ‼

Repost from ISLAMIC POST
በ ጁምአ ሌሊት እና በጁምአ ቀን በእኔ ላይ አብዝታቹ ሰለዋት አውርዱ ይህንን ላደረገ በእለተ ቂያማ መስካሪ እና አማላጅ እሆንለታለው ረሱል (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም)

የ(ض)ዷድ ቋንቋ በመባል የሚታወቀው ቋንቋ ማነው❓
Anonymous voting

السلام عليكم ورحمة الله وبركاته             የደርስ መጀመሪያ ጊዜ ማስታወቂያ    እንሆ በሰሜን ወሎ ዞን ከውቢት ሀራ ከተማ መስተዳደር በመስጂደል ፉርቃን ከአረፋ በፊት ሲሰጥ የነበረው እና በአረፋ ምክኒያት ተቋርጦ የነበረው የሸይኽ ሙሀመድ ሀያት የነህውና ፊቅህ እንዲሁም የሀዲስና የሌሎችም ፈን ቂራአቶች ሊጀመሩ ነው ። ነባር ማዶች(ቂረአቶች) ዛሬ ዙልሂጃ 16 የጀመሩ ሲሆን በአላህ ፈቃድ ቂርአቱ ሙሉ በሙሉ የሚጀመረው ዙል–ሂጃ 20 ሁሉም ደረሳ ( ተማሪ ) እንዲገባ ስንል ጥሪያችንን እናቀርባለን !           ማሳሰቢያ      ማንኛውም ወደ መድረሳ የሚመጣ ተማሪ ማንነቱን የሚገልፅ የታደሰ መታወቂያ ይዞ መምጣት ይኖርበታል ።                 የሸይኽ ሁሰይን ከረም ደርስ     በዛው በሀረ ከተማ በመስጂደል ሂጅራ በሸይኽ ሁሰይን ከረም ሲቀራ የነበረው የሶርፍና ተያያዥ የሉጛ ደርሶችም ነባር ደርሶች የተጀመሩና አዳድስ ማዶችም የሚጀመሩ መሆናቸውን እናስታውሳለን !                የሸይኽ ሰይድ ደርስ     በመስጂድ አቡበክር  ሲሰጥ የነበረውም የሸይኽ ሰይድ የፊቅህ የዐቂደና ሌሎችም ደርሶች በተመሳሳይ የሚቀጥሉ ይሆናል ። በተጨማሪ ከዓረፋ በአል በፊት ሲያስሞጥሉ የነበሩ አሞጣዬችም ብዙዎች ስለገቡ (በመድረሳው ስለሚገኙ) ፈጠን ብለው ወደ ውቢቷ ሀራ ከተማ በመምጣት ይህን ታላቅ የእውቀት ማዕድ ይቋደሱ። ለተጨማሪ መረጃ፣በነዚህ ስልኮች በመደዎል መረጃ ማግኘት ይችላሉ ኢብኑ ኢድሪስ: 0919988236 ዘይኑ ዲን 0987924450 https://t.me/SheikMohmmedHyatHara

🔆ቁርአን ከቃኢዳ መቅራት የምትፈልጉ ☑️በቴሌግራም ቀጥታ (live) እና ☑️በኢሞ በቀጥታ (live) በተጅዊድ ከፈተና  ጋር መቅራት የምትፈልጉ በዚህ አናግሩን 👇👇      👉@Umu_asiya65          👆በዚህ ኑ

ስለ ሂጅራ አቆጣጠር ምን ያሃል ያቃሉ❓ የሂጅራ ዘመን አቆጣጠር ከመጀመሩ በፊት በአረቢያ ምድር እንደ አሁኑ ወጥ የሆነ ቁጥር ያለው ዓመታዊ የቀን መቁጠሪያ አልነበረም። ይልቁንም አረቦች ዘመናትንና ዓመታትን የሚቆጥሩት በአካባቢያቸው በተከሰቱ ታላላቅ እና ታሪካዊ ክስተቶች (Major Historical Events) ስም በመሰየም ነበር። በወቅቱ የነበረውን የአቆጣጠር ዘዴ የሚያሳዩ ዋና ዋና ነጥቦች የሚከተሉት ናቸው፦ --- ### 1. በታዋቂ ክስተቶች የመሰየም ልማድ (Event-Based Calendar) አንድ ትልቅ ክስተት ሲፈጠር ያ ዓመት በዚያ ክስተት ስም ይጠራና፣ ቀጣዮቹ ዓመታት "ከዚያ ክስተት በኋላ አንደኛው ዓመት፣ ሁለተኛው ዓመት..." እየተባሉ ይቆጠራሉ። ሌላ ትልቅ ክስተት ሲመጣ ደግሞ አቆጣጠሩ ይለወጣል። በታሪክ በጣም የታወቁት የዓመት ስሞች የሚከተሉት ነበሩ፦ * ዓመተል ፊል (عام الفيل - የዝሆን ዓመት)፦ አብርሃ የተባለው የየመን ገዥ ዝሆኖችን አስከትሎ ካዕባን ለማፍረስ የመጣበት እና በአላህ ተአምር የጠፋበት ዓመት ነው። ነቢዩ ሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) የተወለዱት በዚህ ዓመት ነው። በመሆኑም ሂጅራ ከመጀመሩ በፊት ሰዎች "ነቢዩ የተወለዱት ከዝሆን ዓመት በኋላ ነው" ወይም "ይህ ነገር የሆነው ከዝሆን ዓመት 5 ዓመት በኋላ ነው" ይሉ ነበር። * ዓመተል ፊጃር (የፊጃር ጦርነት ዓመት)፦ በአረቦች መካከል ከባድ ጦርነት የተካሄደበት ዓመት። * የካዕባ እድሳት ዓመት፦ የቁረይሽ ነገዶች ካዕባን በጋራ ያደሱበት ዓመት። ### 2. ከእስልምና በኋላ (ከሂጅራ በፊት የነበሩ የዳዕዋ ዓመታት) የእስልምና ዳዕዋ ከተጀመረ በኋላም ቢሆን፣ ሂጅራ ከመደረጉ በፊት የነበሩት ዓመታት በነቢዩ (ሰ.ዐ.ወ) ሕይወት ውስጥ በተከሰቱ ክስተቶች ይታወቁ ነበር። ለምሳሌ፦ * ዓመተል ሑዝን (عام الحزن - የሀዘን ዓመት)፦ የነቢዩ (ሰ.ዐ.ወ) ባለቤት እጅግ የተወደዱት ኸዲጃ (ረ.ዐ) እና ጠባቂያቸው የነበሩት አጎታቸው አቡ ጧሊብ የሞቱበት 10ኛው የነብይነት ዓመት ነው። --- ### 💡 የሂጅራ አቆጣጠር እንዴት ተጀመረ? የሂጅራ አቆጣጠር በቁጥር ደረጃ በይፋ የተጀመረው በነቢዩ (ሰ.ዐ.ወ) ዘመን ሳይሆን፣ በሁለተኛው የሊቀ-ሙስሊማን (ኸሊፋ) ዑመር ኢብኑል ኸጧብ (ረ.ዐ) ዘመነ መንግሥት (በ638 እ.ኤ.አ / በ17ኛው የሂጅራ ዓመት) ላይ ነው። የእስልምና አስተዳደር እየሰፋ ሲሄድ ከተለያዩ አገራት የሚመጡ ደብዳቤዎች ላይ ቀኑና ዓመቱ በግልጽ ባለመጻፉ ግራ መጋባት ተፈጠረ። በመሆኑም ዑመር (ረ.ዐ) ሰሃባዎችን ሰብስበው መከሩ። * አንዳንዶች በነቢዩ (ሰ.ዐ.ወ) የልደት ቀን እንጀምር አሉ። * ሌሎች ደግሞ ነብይነት በተሰጣቸው ዓመት እንጀምር አሉ። * በመጨረሻም በታላቁ ሰሃባ ዓሊ ኢብኑ አቢ ጧሊብ (ረ.ዐ) አቅራቢነት፡- ሙስሊሞች ከጨለማ ወደ ብርሃን የተሻገሩበት፣ የእስላማዊ መንግሥት መሰረት የተጣለበት ነቢዩ (ሰ.ዐ.ወ) ከመካ ወደ መዲና የተሰደዱበት (ሂጅራ ያደረጉበት) ዓመት የአቆጣጠሩ መነሻ (ዓመተ 1) ሆኖ እንዲመዘገብ ተወሰነ። ወሮቹ ግን (ከሙሐረም እስከ ዙልሒጃ ያሉት 12 ወራት) ከእስልምና በፊትም በአረቦች ዘንድ የሚታወቁና የሚሰሩባቸው ነበሩ፤ የጎደለው የዓመታት መቁጠሪያ ቁጥር ብቻ ነበር።

#የነብዩ_ﷺ_ክልከላዎች!! 1. ሴትን ልጅ ያለ ባሏ ፍቃድ ማናገር። 2. ከመስጂድ በሮች ላይ መሽናት። 3. ከቆመ ውኃ ላይ መሽናት። 4. ሻወር ቤት ውስጥ መሽና። 5. መስጂድ ውስጥ መፎካከር። 6. ሰይፉን ከሰገባው አውጥ ማቀበል። 7. ሳያስፈቅዱ በሁለት ሰዎች መካከል መቀመጥ። 8. በፀሃይ እና በጥላ መካከል መቀመጥ። 9. በአጥንት እና በፍግ ማበስ። 10. ቁሞ መጠጣት። 11. ተንጋሎ እግርን ማቆላለፍ። 12. የጁሙዓን ቀን ለብቻው መፆም። 13. ሰውን አስነስቶ መቀመጥ። 14. እንስሳትን አስሮ መግደል። 15. ቀብር ላይ መቀመጥ። 16. ቀብር ላይ መገንባት። 17. ቀብር ላይ መፃፍ። 18. ብልትን በቀኝ እጅ መንካት። 19. በአንድ ጫማ ብቻ መሄድ። 20. ወኃ መከልከል። 21. ቁሞ መጫማት። 22. መጠጥ ላይ መተንፈስ። 23. ምግብ ላይ መተንፈስ። 24. የቤት አህያ ስጋ መብላት። 25. ሶላት ላይ ሽንጥን መያዝ። 26. በወርቅ እና በብር እቃ መብላት። 27. አለማግባት። 28. ለእንግዳ መቸገር። 29. በቁርአን መከራከር። 30. አስካሪ ከሚጠጣበት ቦታ መቀመጥ። 31. ኹጥባ እየተደረገ ቁጢጥ ብሎ መቀመጥ። 32. ውሸት መዋሸት። 33. መስጂድ ውስጥ መግዛትና መሸጥ። 34. መስጂድ ውስጥ የጠፋን ማፈላለግ። 35. ወደ ቀብር ዙሮ መስገድ። 36. ፎቶ ማንሳት። 37. በፈስ መሳቅ። 38. ጊዚያዊ ጋብቻ። 39. ስለት መግባት። 40. ከዒሻእ በፊት መተኛት። 41. ሙሾ ማውረድ። 42. ለብቻ ማደር። 43. ንቅሳት። 44. ፀጉር መቀጠል። 45. ፍራፍሬ ሳይበስል መሸጥ። 46. ትርፍ ውኃን መሸጥ። 47. ነብር መጋለብ። 48. ሙታኖችን መሳደብ። 49. የዒድ ቀን መፆም። 50. ጉንዳን መግደል። 51. አስካሪ መጠጥን ሁሉ። 52. ሸበቶን መንጨት። [ሶሒሑል ጃሚዕ (1151-1171)]

🧑‍🦲ኻሊድ ክብሮን ቁርአንን የሚያብራራው መጽሐፍ ሆነ ሰው አያስፈልገውም። 💁‍♂ እኔ እና አንተ በሲራ ብለህ የቁርአን ትምህርት ቤት የከፈትከው ቲላዋ ለማስቀራት ነው?🤷

photo content

ጥያቄ ፦ እንደምታውቁት ለመላኢካዎችም ሆነ ለሰይጣናት በሰው የመመሰልን ሀይል አላህ ሰጥቷቸዋል ። ጅብሪል በሰው ተመስሎ ሲመጣና ኢብሊስ ተመስሎ ሲመጣ አጋጣሚዎቹም ታይተዋል ። ታዲያ ጅብሪል ተመስሎበት የሚመጣው ሶሃቢይ ማን ነበር ?  ሀ, አቡ ሚህጀን አልሰቀፊ ለ, ዱህያ አልከልቢይ ሐ, ኪላባ አል ጁሃኒ መ, ማሊክ ኢብኑ ዲናር

خطبة عيد الأضحى ሸይኽ ዩሱፍ አህመድ ١٤٤٧

تقبل الله منا ومنكم. = በግሌ እንኳን ለዒድ አል አድሓ አሏህ አደረሰህ እያላቹህ የምትፅፉልኝ ወንድም እህቶቼ በሙሉ እንኳንም አብሮ አደረሰን ከኛም ከናንተም አሏህ ይቀበለን أخوكم الذليل الراجي عفو ربه الجليل (أبو معاذ

የሁለቱን ዒዶች ስርኣት የሚመለከቱ ጥቂት ነጥቦች ከማስረጃዎቻቸው ጋር —————ክፍል 2 የተክቢራ አደራረግንና የዒድ ሶላት አሰጋገድን ያካተተ ክፍል 1 ለማግኘት ⤵️ https://t.me/IbnShifa/5118 ሴቶች የዒድ ሶላት ወደ ሚሰገድበት ቦታ ሲወጡ… »-» ሴቶች ሲወጡ ማንኛውም አይነት ማራኪ ሽታ ያለውን ነገር መቀባትና ጌጣ ጌጥ ያለውን ልብስ ለብሰው መውጣት ሀራም ይሆንባቸዋል። ኢብኑ ተይሚያ (ረሂመሁላህ) የሴቶችን ወደ ዒድ ቦታ መውጣት በተመለከተ ሲናገሩ እንዲህ ይላሉ:- “ሴቶች የዒድ ቦታ ላይ ማንኛውም አይነት ሽታ ያለውን ነገር ሳይጠቀሙ፣ የጌጣ ጌጥና የዝነኞችን ልብስ ሳይለብሱ ቢወጡ ችግር የለውም። ምክንያቱም ነቢዩ ﷺ እንዲህ ብለዋልና:- ምንም አይነት ሽታ ያለውን ነገር ሳይጠቀሙ ይውጡ…።” [ተውዲሁል አህካም ሸርህ ቡሉግ…] ይህ በሴቶች ላይ የተቀመጠ መስፈርት ነው። ይህን መስፈርት ስሜቴንና ሸይጧንን አሸንፌ ማሟላት አልችልም የምትል ሴት ከቤቷ ትቀመጥ!። ወደ ዒድ ቦታዎች እየወጣች ለጌታቸው ሊሰግዱና ጌታቸውን አላህን ሊያወድሱ የወጡ ወንዶችን ወንጀል ውስጥ እየጣለች ለራሷም ወንጀል ሸምታ ከመግባት ልትቆጠብ ይገባል!!። ሽቶ ተቀብተውና ተጋግጠው የሚወጡ እህቶች አላህን ሊፈሩት ይገባል!!። በደስታ ቀን አላህን ከማመፅ ሊቆጠቡ ይገባል። እህቴ ሆይ! በደስታ ቀን አላህን ካመፅሽ በዱኒያና ነገ በጭንቁ ቀን ጭንቀት እንዳይጨምርልሽና ስቃይሽን እንዳያበረታው ልትፈሪና ልትጠነቀቂ ይገባል!! እህቴ ወደ ዒድ ቦታ መውጣት ከፈለግሽ ሽቶና ዲዮድራንት… መሰል ነገሮችን ከመቀባት ርቀሽ፣ የሰውነት ቅርፅሽን የሚያሳዩ የተጣበቁና የተጋጌጡ ልብሶችን አሽቀንጥረሽ ጥለሽ ሰፋፊ ሸሪዓዊ አለባበስ ለብሰሽ ድምፅሽን አጥፍተሽ ወጥተሽ አምላክሽን አላህን አወድሰሽና አልቀሽ ለእርሱም ሰግደሽ ተመለሺ። ይህን ማድረግ ካልቻልሽ ግን አላህን ፈርተሽ ቤትሽ ይስፋሽ!!። »-» ወደ ዒድ ቦታ ሲኬድ ድምፅን ከፍ አድርጎ ተክቢራ ማለት ተደንግጓል። አምላካችን አላህ እንዲህ ብሏል:- وَلِتُكْمِلُوا الْعِدَّةَ وَلِتُكَبِّرُوا اللَّهَ عَلَىٰ مَا هَدَاكُمْ وَلَعَلَّكُمْ تَشْكُرُونَ «ቁጥሮችንም ልትሞሉ አላህንም ቅኑን መንገድ ስለመራችሁ ታከብሩትና ታመሰግኑት ዘንድ (ይህን ደነገግንላችሁ)፡፡» አል-በቀረህ 185 ከዐብደላህ ኢብኑ ዑመር (ረዲየላሁ ዐንሁማ) ተይዞ፣ የአላህ መልእክተኛ ﷺ በሁለቱ ዒዶች ከፈድል ኢብኑ ዐባስ፣ ከዐብደላህ፣ ከዐባስ፣ ከዐሊይ፣ ከጀዕፈር፣ ከሀሰንና ሁሰይን፣ ከኡሳማ ኢብኑ ዘይድ፣ ከዘይድ ኢብኑ ሃሪሰህ፣ ከአይመን ኢብን ኡሙ አይመን (ረዲየላሁ ዐንሁም) ድምፃቸውን ከፍ አድርገው ተክቢርና ተህሊል እያሉ ይወጡ ነበር። [በይሀቂይ የዘገቡት ሲሆን አልባኒ በኢርዋእ አልገሊል 3/123 ላይ ሶሂህ ነው ብለውታል።] የተክቢራውን አደራረግ በተመለከተ ከነቢዩ ﷺ የተረጋገጠ ሶሂህ የሆነ ዘገባ የለም። ዐብደላህ ኢብኑ መስዑድ ግን የሚከተለውን የተክቢራ አይነት ይጠቀም እንደነበር ተረጋግጧል:- “አላሁ አክበር አላሁ አክበር፣ ላ! ኢላሀ ኢለላህ፣ አላሁ አክበር አላሁ አክበር ወ ሊላሂል ሀምድ” [ኢብኑ አቢ ሸይባ በሶሂህ ሰነድ ዘግበውታል።] ዐብደላህ ኢብኑ ዐባስም እንደሚከተለው ይል እንደነበር ተዘግቧል:- “አላሁ አክበር አላሁ አክበር፣ አላሁ አክበር ወ ሊላሂል ሀምድ፣ አላሁ አክበር ወ አጀልሉ፣ አላሁ አክበር ዐላ ማ ሐዳና” [በይሀቂይ ሶሂህ በሆነ ሰነድ ዘግበውታል።] »-» የተክቢራ ጊዜን በተመለከተ የዒደል ፊጥር ተክቢራ የዒዱን ቀን ተሰግዶ እስኪያበቃ ነው። የዒዱል አድሃ ተክቢራ ደግሞ ከዐረፋ ንጋት ሶላት ጀምሮ በተከታታይ አያሙ ተሽሪቅ እስኪጠናቀቅ ድረስ ነው። (የውሙ ዐረፋ ማለት ከዙል ሒጃ 9ኛው ቀን ነው።) ይህ አጠቃላይ ሰለፎች፣ ሶሃባዎች፣ አራቱ መሪዎችና ፉቅሃዎች የተጓዙበት መንገድ ነው። [ሶሂህ ፊቅህ አስ-ሱና አቡ ማሊክ ከማል] »-» አንዳንድ ሰዎች ዒድ ሚሰገድበት ቦታ ሲደርሱ ሱና ብለው ይሰግዳሉ። ይህ ትልቅ ስህተት ነው። ለሁለቱም ዒዶች ከፊታቸውም ሆነ ከኋላቸው ሱና ሶላት የላቸውም። ነገር ግን ነቢዩ ﷺ ወደ ቤታቸው ከተመለሱ በኋላ 2ረከዓ ይሰግዱ ነበር። ከአቢ ሰዒድ አል-ኹድሪይ (ረዲየላሁ ዐንሁ) ተይዞ የአላህ መልእክተኛ ﷺ ከዒድ በፊት ምንም አይሰግዱም ነበር፣ ወደ ቤታቸው ከተመለሱ በኋላ ሁለት ረከዓ ይሰግዱ ነበር።” [ኢብን ማጀህ 1076 ላይ የዘገቡት ሲሆን አልባኒ ሀሰን ነው ብለውታል።] ለሁለቱም ዒዶች አዛንም ሆነ ኢቃም ማለት የለም። »-» የዒድ ሶላት የአሰጋገድ ሁኔታን በተመለከተ እንደሚከተለው ነው:- የዒድ ሶላት 2ረከዓ ነው። ዑመር ኢብኑል ኸጧብ (ረዲየላሁ ዐንሁ) እንዲህ ብሏል:- “የተጓዥ (የጉዞ) ሶላት 2ረካዓ ነው። የዒደል አድሃ ሶላትና የዒደል ፊጥር ሶላትም ሁለት ሁለት ረከዓ ነው። እርሱም አጥሮ ሳይሆን ሙሉው ነው 2ረከዓ በነቢያችሁ አንደበት የተደነገገ ነው።” [ነሳኢይ እና ኢማሙ አህመድ የዘገቡት ሲሆን ሀዲሱም ሶሂህ ነው።] » የመጀመሪያውን ረከዓ ልክ እንደሌላው ሶላት  በኢህራም ተክቢራ ይጀምራል። ከዚያ በኋላ ሰባት ጊዜ ተክቢራ ያደርጋል። ሰባቱ ተክቢራ በሚደረግበት ወቅ እጅ ማንሳቱ ከነቢዩ ﷺ የተረጋገጠ ነገር የለም። ነገር ግን ኢብኑል ቀይም (ረሂመሁላህ) ዐብደላህ ኢብኑ ዑመር የነቢዩን ﷺ ሱንና አጥብቆ የሚከተል ከመሆኑም ጋር በሰባቱም ተክቢራ ጊዜ እጁን ያነሳ ነበር ይላል። ሌላው በየ ተክቢራው መሃል የሚባል ዚክር ከነቢዩ ﷺ የተረጋገጠ ነገር የለም። ይሁን እንጂ ኢብኑ መስዑድ (ረዲየላሁ ዐንሁ) ነቢዩ ﷺ በየ ተክቢራው መሃል "አላህን ያወድሱም ያመሰግኑም ነበር” ብሏል። [በይሀቂ የዘገቡት ሲሆን ሰነዱ ሀሰን ነው።] ከሰባቱ ተክቢራዎች በኋላ ፋቲሃ ይቀራል ከዚያም ሱራዎች ይቀራሉ። ተወዳጅ ሱራዎች "ቃፍ፣ ወል ቁርኣኒል መጂድ፣ የሚለውና ኢቅተረበቲ ሰኣቱ… እንዲሁም ሰቢህ እስመ ረቢከል አዕላና ሐል አታከ ሀዲሱል ጋሺየህ…" ሱራዎች ናቸው። [ሙስሊምና ነሳኢይ ሌሎችም ዘግበውታል።] ከዚያም በሁለተኛው ረከዓ ተነስቶ ለመቆም ከሚለው ተክቢራ ውጭ አምስት ተክቢራዎችን ይላል። ከዚያ በኋላ ልክ በመጀመሪያው ረከዓ እንዳደረገው ፋቲሃን እና ሌሎችን ሱራዎች ይቀራል። ከዓኢሻ (ረዲየላሁ ዐንሃ) ተይዞ፣ “የአላህ መልእክተኛ ﷺ በዒደል ፊጥርና በዒደል አድሃ ሶላት በመጀመሪያው ረከዓ ሰባት ተክቢራዎችን በሁለተኛው ረከዓ ደግሞ አምስት ተክቢራዎችን ይሉ ነበር።” ብላለች። [አቡዳውድ የዘገቡት ሲሆን ሀዲሱም ሶሂህ ነው።] በመጨረሻም ከተሸሁድ በኋላ ያሰላምታል። »-» ወደ ዒድ ቦታ ከተጓዙባቸው መንገዶች በተቃራኒ መንገድ መመለስ ሱንና ነው። ከጃቢር ኢብን ዐብደላህ (ረዲየላሁ ዐንሁ) ተይዞ እንዲህ አለ:- “ነቢዩ ﷺ የዒድ ቀን ከሆነ በተቃራኒ መንገድ ይጓዙ ነበር።” [ቡኻሪ ዘግበውታል] አቢ ሁረይራ (ረዲየላሁ ዐንሁ) እንዲህ አለ:- “ነቢዩ ﷺ ወደ ዒድ መስገጃ ቦታ ከወጡ መጀመሪያ ከወጡበት መንገድ በተቃራኒው ይመለሱ ነበር።” [ኢብን ማጀህ ዘግበውታል] አላህ ዒዳችንን አላህን የምንታዘዝበትና አላህ በሚፈቅደው መልኩ የምንደሰትበት ዒድ ያድርግልን!!

Repost from ISLAMIC POST
እንኳን ለ1447ኛው የዒድ አል-አድሃ (ዓረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ! ይህ ታላቅ በዓል የደግነት፣ የራህማ (እዝነት) እና የጋራ መተሳሰብ ተምሳሌት ነው። አፍሪካ አካዳሚ እና አፍሪካ ቲቪ ለመላው
እንኳን ለ1447ኛው የዒድ አል-አድሃ (ዓረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ! ይህ ታላቅ በዓል የደግነት፣ የራህማ (እዝነት) እና የጋራ መተሳሰብ ተምሳሌት ነው። አፍሪካ አካዳሚ እና አፍሪካ ቲቪ ለመላው የዕምነቱ ተከታዮች በዓሉ የሰላም፣ የፍቅርና የበረከት እንዲሆን መልካም ምኞታቸውን ይገልፃሉ። መልካም በዓል! 🌙 #አፍሪካ_አካዳሚ #አፍሪካ_ቲቪ #የህይወት_ጎዳና #ዒድ_ሙባረክ #ዓረፋ1447

Repost from ISLAMIC POST
የዐረፋህ ቀን የምህረት ብስራት‼ ==================== ✍️ የዐረፋህ ቀን ሲደርስ፣ አንዳንዶች አላህ (ሱብሓነሁ ወተዓላ) የሚምረው በዐረፋህ ሜዳ ላይ ያሉትን ሑጃጆችን (أهل المشعر) ብቻ እንደሆነ ያስባሉ ወይም ያምናሉ። ነገር ግን እውነታው ከዚህም የላቀና ልብን በደስታ የሚሞላ ነው። የማይረሳው የነብዩ ﷺ የዐረፋህ ቀን ብስራት፡ በዚህ ቪዲዮ ላይ እንደተገለጸው፣ ልብን በፍርሃትና በተስፋ የሚያንቀጠቅጥ አንድ ታላቅ ሐዲሥ አለ። ነብያችን ሙሐመድ ﷺ በዐረፋህ ቀን በግመላቸው "አል-ቀሷእ" ላይ ተቀምጠው ሳለ፣ ቢላል (ረዲየላሁ ዐንሁ) ሰዎችን ጸጥ እንዲያደርግላቸው አዘዙት። በዙሪያቸውም እስከ 120,000 የሚደርሱ ሶሓቦች ነበሩ። ከዚያም ይህችን ታላቅ የምስራች ለሰዎች አበሰሩ፦ "እናንተ ሰዎች ሆይ! ጅብሪል (ዐለይሂ ሰላም) ከጌታዬ ዘንድ መጥቶ ሰላምታን አደረሰልኝና እንዲህ አለኝ፦ 'ሙሐመድ ሆይ! ሰዎችን አብስራቸው፤ አላህ ለዐረፋህ (ለሑጃጆች) እና በዐረፋህ ሜዳ ላይ ለቆሙት ሁሉ ምሯል!'" የዑመር (ረ.ዐ) ጥያቄና የነብዩ ﷺ አስደሳች ምላሽ፡ ይህን የሰሙት ዑመር ኢብኑል ኸጥ'ጧብ (ረዲየላሁ ዐንሁ) በደስታ ጮክ ብለው "ያ ረሱለላህ! ይህ ምህረት ለእኛ ብቻ የተወሰነ ነውን?" ሲሉ ጠየቁ። የአላህ መልዕክተኛም ﷺ ልብን በሀሴት የሚሞላውን ምላሽ ሰጡ፦ "አይደለም ያ ዑመር! ለእናንተም፣ ከእናንተ በኋላ እስከ ቂያማ ቀን ድረስ ለሚመጡትም (ይህ ምህረት ይደርሳቸዋል)!" ይህን የሰሙት ዑመር (ረዲየላሁ ዐንሁ) በከፍተኛ ድምፅ እንዲህ አሉ፦ "የጌታችን ኸይር (መልካም ነገር) በዛ! የጌታችን ኸይር በዛ!" ከዚህ ታሪክ የምንማረው ቁም ነገር፡ የአላህ እዝነት ስፋት፦ የአላህ ምህረትና እዝነት በዐረፋህ ሜዳ ላይ ባሉ ሐጃጆች ብቻ የተወሰነ አይደለም። ይልቁንም፣ በያሉበት ሆነው የዐረፋን ቀን በጾም፣ በዚክር፣ በዱዓእና በሶላት የሚያሳልፉትን ሁሉ ያጠቃልላል። የዐረፋ ቀን ጾም ትልቅነት፦ ይህ ሐዲስ ሐጅ ላይ ላልሆኑ ሰዎች የዐረፋን ቀን መጾምና በዒባዳ ማሳለፍ ያለውን ታላቅ ደረጃ ያሳያል። የነብዩ ﷺ ለኡመታቸው ያላቸው እዝነት፦ ይህ ብስራት ነብያችን ﷺ ለኡመታቸው የነበራቸውን ጥልቅ ፍቅርና እዝነት ያሳያል። ይህ ታሪክ በዐረፋህ ቀን የሚገኘውን ታላቅ ምህረት ተስፋ እንድናደርግና በዒባዳህ እንድንተጋ ያነሳሳናል። የዐረፋህ ቀን የአላህ እዝነትና ምህረት በስፋት የሚወርድበት ልዩ ቀን ነው። ሐጅ ላይ ያለነውም ሆነ በያለንበት ቦታ ሆነን ቀኑን በዒባዳ የምናሳልፈው፣ ሁላችንም የዚህን ታላቅ ምህረት ተካፋዮች እንድንሆን አላህ ይወፍቀን። የጌታችን ቸርነትና ልግስና በእርግጥም የበዛ ነው! || t.me/MuradTadesse