የኮንስትራክሽን ዲዛይን ግንባታና ማማከር ድርጅት
Open in Telegram
1 888
Subscribers
-124 hours
-37 days
No data30 days
Posts Archive
የኅብር ቀን
ኢትዮጵያችን በሀገር በቀል እሴቶቿ፤ የነገውን ብሩህ ተስፋዋን በገዛ እጆቿ እየቀረጸች ትገኛለች!
በትውልድ ቅብብሎሽ ያገኘናቸውን ድንቅ የሀገር በቀል እሴቶቻችንን በማጎልበት እና በመደመር ፍልስፍና በመመራት፣ ለጽኑ ኅብረብሔራዊ አንድነታችን የማይናወጥ መሠረት ጥለናል። ታሪካዊውን ሀገራዊ ምክክር የመጀመር የታሪክ እጥፋት ተነስተን፣ የሁሉም ዜጎቻችንን ሕይወት ከሚለውጡ ሰው-ተኮር የኮሪደር ልማታችን፣ የበጎ ፈቃድ ስራዎቻችን እንዲሁም የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃግብርን በተግባር እውን እስከማድረግ ድረስ፤ ሁላችንም በአንድነት ስንቆም የጋራ ትርክቶቻችን ወደ ጋራ ስኬት እንደሚያሻግሩን በተግባር አሳይተናል።
እኛ የምንገነባው አካታች የሆነች፣ በኢኮኖሚ ራሷን የቻለች፣ የአብሮነትና መረዳዳት ባህል የጎለበተባት ጠንካራ ሀገር ብቻ ሳይሆን የሁሉንም ኢትዮጵያውያን የጋራ ታላቅነትና እምቅ አቅም በተግባር እያረጋገጥን እንገኛለን። በአንድነት ወደ ብልጽግና ጉዟችን እንቀጥላለን።
አንድ ህዝብ፣ ታላቅ ሀገር ኢትዮጵያ!
#EthiopiaPrevails
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
ዻጉሜን 3 “የጽናት ቀን”
የዻጉሜን 3 “የጽናት ቀንን” የኮንስትራክሽን ዲዛይን ግንባታና ማማከር ድርጅት አመራሮችና ሰራተኞች አክብረዋል፡፡
በዚህ ክብረ በዓል ላይ የድርጅቱ የጽ/ቤት ሃላፊ ወ/ሮ አዳነች አሰፋ፣ በከተማው አስተዳደር የዻጉሜን 5ቱ ቀናት በተለያዩ ሃገራዊ ሁነቶች የሚከበሩ መሆኑን ገልፀው፣ በድርጅታችንም በዛሬው እለት ለሚከበረው የዻጉሜን 3 “የጽናት ቀን” እንኳን በሰላም አደረሳችሁ ብለዋል፡፡
በዚህ መርሃ ግብር ላይ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ክቡር ዶ/ር አቢይ አህመድ፣ የዻጉሜን 3 “የጽናት ቀንን” አስመልክተው ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ ያስተላለፉት መልእክት በንባብ ቀርቧል፡፡
በመጨረሻም በበዓሉ ተሳታፊዎች የኢትዮጵያ ህዝብ መዝሙር ተዘምሮ የበዓሉ ፍፃሜ ሆኗል፡፡
የቢዝነስ ዴቨሎፕመንት ዳይሬክቶሬት
ዻጉሜን 3 ቀን 2018 ዓ.ም
ዻጉሜን 2 “የማንሰራራት ቀን”
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2018 ዓ.ም የጳጉሜን ወር አምስቱ ቀናት የተለያዩ ስያሜዎችን በመያዝ በተለያዩ ሁነቶች በመከበር ላይ ይገኛሉ።
የኮንስትራክሽን ዲዛይን ግንባታና ማማከር ድርጅትም፣“የማንሰራራት ቀን” በሚል በተሰየመችው የዻጉሜን 2 ቀን ምክኒያት በማድረግ፣ የድርጅቱ አመራሮችና ሰራተኞች በተገኙበት ዕለቱን በተለያዩ ዝግጅቶች አክብሯል፡፡
በእለቱም የድርጅቱ ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር አብዶ ገለቶ እንኳን ለመጪው 2019 ዓ.ም አዲስ አመት በሰላም አደረሳችሁ ሲሉ ምኞታቸውን በመግለፅ የመክፈቻ ንግግር አድርገዋል፡፡
ኢንጂነር አብዶ ገለቶ በንግግራቸው፣ “የ2018 በጀት ዓመት እንደ ድርጅት እቅዶቻችንን ያሳካንበት፣በሃገር ደረጃም አዲስ መንግስት የተመረጠበት እንዲሁም የ2019 በጀት ዓመት ደግሞ ስራዎቻችንን ለማከናወን ያቀድንበት ጊዜ በመሆኑ የተለየ ትርጉም ይኖረዋል” ብለዋል፡፡
ኢንጂነር አብዶ አክለውም፣ድርጅቱ በየዘርፉ የያዛቸውን ስራዎች ይዞ እንዲያድግ የሚያስችለውን የ5 ዓመታት ስትራቴጂክ እቅድ ያዘጋጀና፣ እስከ 2023 ትልቅ ራእይ የሰነቀ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ አያይዘውም፣ ድርጅቱን ትልቅ ካምፓኒ ለማድረግ በዚህ በጀት ዓመት ውስጥ እቅዱ ተግባራዊ የሚደረግ በመሆኑ፣ ሰራተኞች የዚህ ራእይ ተካፋይ ናችሁ ሲሉ አፅንኦት በመስጠት ኢንጂነር አብዶ ንግግራቸውን አጠቃለዋል፡፡
በእለቱ የ2019 ዓ.ም አዲስ ዓመትን አብሳሪ የሆነውና የበዓሉ ድምቀት የነበረው፣“የአበባየሆሽ ለምለም” ባህላዊ ዜማ በድርጅቱ ሴት ሰራተኞች በኩል ቀርቧል፡፡ በተጨማሪም ከድርጅቱ ሰራተኞች መካከል በእድሜ አንጋፋ በሆኑ ወንድ ሰራተኞች በኩል የመልካም ምኞት መግለጫ የሆነው “ምርቃት” የተከናወነ ሲሆን፤ በሃገራችን ወግ መሰረትም ለሽማግሌዎች ጋቢ የማልበስ ስነ ስርዓትም ተካሂዷል፡፡
በሌላ በኩል በ2018 በጀት ዓመት በድርጅቱ በየሳምንቱ ሲካሄድ የነበረው “የወርቃማው የአብሮነት ቀን መርሃ ግብር” በሰራተኞች ላይ በተጨባጭ ያመጣውን ውጤት የተመለከተ የዳሰሳ ጥናት በሚመለከተው ክፍል ቀርቧል፡፡
የቢዝነስ ዴቨሎፕመንት ዳይሬክቶሬት
ዻጉሜን 2 ቀን 2018 ዓ.ም
ጳጉሜን 1- "የእመርታ ቀን"
የድርጅቱ አመራሮችና ሰራተኞች የጳጉሜን 1- "የእመርታ ቀንን " አስመልክቶ የግንባታ ፕሮጀክቶችን በመጎብኘት አከበሩ ።
የኮንስትራክሽን ዲዛይን ግንባታና ማማከር ድርጅት አመራሮችና ሰራተኞች፣ በዛሬው "የእመርታ ቀን" በድርጅቱ ስራ ተቋራጭነት በተለያዩ ሳይቶች በመገንባት ላይ የሚገኙ የግንባታ ፕሮጀክቶች አፈፃፀምንና ያሉበትን ደረጃ ተዘዋውረው በመጎብኘት ቀኑን አክብረዉ ውለዋል።
በዚህ የጉብኝት መርሐ-ግብር ላይ ከየፕሮጀክቶቹ ስራ አስኪያጆች በግንባታዎች አፈፃፀም ዙሪያ ለጉብኝቱ ለተሳታፊዎች ሠፊ ገለፃና ማብራሪያ ተሰጥቷል።
በዚህ ጉብኝት ላይ ያነጋገርናቸው አንዳንድ ሠራተኞች፣ "ድርጅቱ በኮንስትራክሽን ዘርፍ የመፈፀም አቅሙን እያጎለበተ መምጣቱንና እያስመዘገባቸው የሚገኙ ስኬቶችንም በቦታው ተገኝተው በቅርበት ለማየት በመቻላቸው መደሰታቸውን" በሰጡት አስተያየት ገልፀዋል።
በመጨረሻም ይህ ጉብኝት በድርጅቱ እና በመሠረታዊ የሠራተኛ ማህበር ትብብር በጋራ የተዘጋጀ መሆኑ የወጣው የድርጊት መርሐ ግብር ያመለክታል።
የቢዝነስ ዴቨሎፕመንት ዳይሬክቶሬት
ጳጉሜን 1 ቀን 2018 ዓ.ም
"ነገን ዛሬ ላይ በፅኑ መሠረት እንገነባለን
የጳጉሜን አምስቱ ቀናት ስያሜዎች
ጳጉሜን 1 - "የእመርታ ቀን"
ጳጉሜን 2 - "የማንሰራራት ቀን"
ጳጉሜን 3 - "የጽናት ቀን"
ጳጉሜን 4 - "የኅብር ቀን"
ጳጉሜን 5 - "የነገ ቀን"
የቢዝነስ ዴቨሎፕመንት ዳይሬክቶሬት
ነሐሴ 29 ቀን 2018 ዓ.ም
በኮንስትራክሽን ዲዛይን ግንባታና ማማከር ድርጅት ለ25 አባወራዎች በበጎ ፍቃድ የተገነባው የG+4 የመኖሪያ ቤቶች ግንባታ ፕሮጀክት በመጠናቀቅ ላይ ይገኛል፡፡
ነሃሴ 28 ቀን 2018 ዓ.ም፡- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የልማት ድርጅቶች አስተዳደር ባለስልጣንና ተጠሪ የልማት ድርጅቶች፣ ማህበራዊ ፍትህንና የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት በሚያረጋግጡ ሰው ተኮር የበጎ ፍቃድ ስራዎች ላይ ጉልህ ተሳትፎ በማድረግ የበኩላቸውን ድርሻ በመወጣት ላይ ይገኛሉ፡፡
ከነዚህ የበጎ ፍቃድ ስራዎች ውስጥም በኮንስትራክሽን ዲዛይን ግንባታና ማማከር ድርጅት ስራ-ተቋራጭነት፣ በአዲስ ከተማ ክ/ከተማ በወረዳ 6 አስተዳደር ክልል ውስጥ ነዋሪ ለሆኑ ለ25 አባወራዎች አገልግሎት የሚሰጠውና፣ የግንባታ ስራውም በመጠናቀቅ ላይ የሚገኘው የበጎ ፍቃድ የG+4 የመኖሪያ ቤቶች ግንባታ ፕሮጀክት ይገኝበታል፡፡
ይህ በድርጅቱ በፍጥነትና በጥራት የተገነባው የበጎ ፍቃድ ፕሮጀክት አሁን ላይ፤ የስትራክቸራል፣ የብሎኬት እንዲሁም የጂብሰምና የኳርቴዝ ስራዎች ሙሉ በሙሉ ተጠናቋል፡፡
የመኖሪያ ቤቶቹን በአጭር ጊዜ ውስጥ አጠናቆ ለተጠቃሚዎች ለማስረከብም፤ የኤሌክትሪክ ፊቲንግ፣ የሳኒተሪና የሴራሚክ ስራዎች እንዲሁም የግድግዳ ቀለም የመቀባት ስራዎች በፍጥነትና በጥራት በመሰራት ላይ የሚገኙ መሆኑን ከሳይቱ ኢንጂነሮች የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡
ከዚህ በፊት የባለስልጣኑ መ/ቤትና ተጠሪ የልማት ድርጅቶች በልደታና በቂርቆስ ክ/ከተሞች በበጎ ፍቃድ ለዜጎች ቤት ገንብተው ማስረከባቸውና ማህበራዊ ሃላፊነታቸውን የተወጡ መሆኑም የሚታወስ ነው፡፡
የቢዝነስ ዴቨሎፕመንት ዳይሬክቶሬት
