የኮንስትራክሽን ዲዛይን ግንባታና ማማከር ድርጅት
Ir al canal en Telegram
1 875
Suscriptores
-324 horas
-27 días
+7530 días
Archivo de publicaciones
+4
የጎንዮሽ ህገወጥ የቤት ኪራይ ውል የአከራይ ተከራይ አዋጅን የሚፃረርና በህግ የሚያስጠይቅ ነው
የጎንዮሽ ህገወጥ የመኖሪያ ቤት ኪራይ ውል የወጣውን የአከራይ ተከራይ አዋጅ የሚፃረር መሆኑንና በህግም እንደሚያስጠይቅ የአዲስ አበባ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ቅድስት ወልደ ጊዮርጊስ አሳሰቡ።
ቢሮው በከተማዋ ካሉ የጋራ መኖሪያ ቤቶች ማህበራት ተወካዮች ጋር ውይይት አድርጓል።
"የአከራይ ተከራይ ግንኙነትን በህግ ማዕቀፍ በመምራት የጋራ ተጠቃሚነትን እናረጋግጣለን" በሚል መሪ ሀሳብ በተደረገው ውይይት ከሁሉም ክፍለ ከተሞች የተውጣጡ ከ1 ሺህ በላይ የጋራ መኖሪያ ቤት ማህበራት ተወካዮች ተገኝተዋል።
የአዲስ አበባ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ቅድስት ወ/ጊዮርጊስ በህገወጥ ደላሎች አነሳሽነት የጎንዮሽ ህገወጥ ውሎች እየተፈፀሙ እንደሚገኙ ከመንግስት ድብቅ እንዳልሆነ ጠቅሰዋል።
ይህ ድርጊት ግን የታሰበውን የጋራ ተጠቃሚነት እንደማያረጋግጥና በህግም እንደሚያስጠይቅ አስጠንቅቀዋል።
በቅርቡ የአከራይ ተከራይ አዋጅን መነሻ በማድረግ የአዲስ አበባ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ ጣራው 11.5 በመቶ የሆነ የመኖሪያ ቤት ኪራይ ማሻሻያን ማፅደቁ ይታወሳል።
ANN
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የልማት ድርጅቶች አስተዳደር ባለስልጣን የፕሮጀክቶች አፈፃፀም ክትትል ቡድን በድርጅታችን በመገኘት የክትትል፣ድጋፍና የምልከታ ስራ አከናወነ፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግሥት ልማት ድርጅቶች አስተዳደር ባለሥልጣን የፕሮጀክቶች አፈጻጸም ክትትል ቡድን በኮንስትራክሽን ዲዛይን ግንባታና ማማከር ድርጅት በመገኘት ለሁለት ቀናት የቆየ የክትትልና ድጋፍ ሥራ አከናውኗል።
ቡድኑ በ2018 በጀት ዓመት የታቀዱ ተግባራት አፈጻጸም፣ የአፈጻጸም ውስንነት ያላቸውን ስራዎችን እንዲሁም የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ዝግጅትን ለመገምገም በተቋሙ ዋና ዋና የሥራ እንቅስቃሴዎች ላይ ምልከታ አድርጓል።
በክትትልና ድጋፍ መድረኩ ላይ እንደ IFRS፣ ERP፣ GPS እና የጣት አሻራ (Biometric) ያሉ የቴክኖሎጂና ዘመናዊ አሠራሮች አጠቃቀም የተገመገመ ሲሆን፤ በግንባታና ልማት ዘርፍ የብሎኬት ማምረቻ ማሽን፣ የጋራዥ ግንባታ፣ የውኃ ቁፋሮ እና የነዳጅ ማደያ ሥራዎች ያሉበት ደረጃ ተዳስሷል። በተጨማሪም የቢሮ ዕድሳት፣ የጨረታ ሂደት እና ከፕሮጀክት በፊት የቅድመ-ጥናት አፈጻጸምን የመሳሰሉ የግዢ አስተዳደር ሥራዎች የተቃኙ ሲሆን፣ መጪውን የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ስኬታማ ለማድረግ የሚያስችለው የፋይናንስ ምንጭ ዝግጅት ላይም አስተያየት ሰጥተዋል።
በድርጅቱ ስትራቴጂክ ካውንስል አመራር አባላትና በሚመለከታቸው የክፍል ኃላፊዎች በተገኙበት በተደረገው በዚህ መድረክ፤ የታዩ ጥንካሬዎችና መሻሻል ያለባቸው ጉዳዮች ላይ የቃል ግብረ-መልስ ተሰጥቷል።
የድርጅቱ ም/ዋና ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር መስፍን መኮንን ለተደረገው ድጋፍ አመስግነው፣ የተለዩ ክፍተቶችን በቀጣይ እንደሚያሻሽሉ ገልጸዋል። አክለውም የተሻለ ተቋም ለመፍጠር የባለሥልጣኑ ድጋፍ ውጤት በሚያመጡ አሠራሮች ላይና ቀጣይነት ያለው እንዲሆን አሳስበዋል።
የክትትል ቡድኑ አባላት በበኩላቸው በቀጣይም ተቋሙን ሊደግፍ በሚችል መንገድ የጽሑፍ ግብረ-መልስ የሚሰጡ መሆኑን በመግለጽ ውይይቱ በጋራ መግባባት ተጠናቋል።
በቢዝነስ ዴቨሎፕመንት ዳይሬክቶሬት
ሰኔ 4 ቀን 2018 ዓ.ም
ቀበና
ለህፃናት መቦረቂያ ፣ለአዋቂዎች መንፈስ ማደሻ !
የዘመናት ትዝታችን ብቻ ሆኖ፣ በቆሻሻና በጥሻ ተከቦ የነበረው የቀበና ወንዝ፤ ዛሬ ላይ ለህፃናት መቦረቂያ፣ ለአዋቂዎች የመንፈስ ማደሻና የጐቢኚዎች መዳራሻ ሆኗል።
መዲናችን አዲስ አበባን በእውነትም እንደ ስሟ "አዲስና ዉብ አበባ" ካደረጉት አስደናቂ ለዉጦች አንዱ ሆኗል።
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
የኮንስትራክሽን ዲዛይን፣ ግንባታና ማማከር ድርጅት ለ2018 በጀት ዓመት የንብረት ቆጠራ ሥራን በይፋ አስጀመረ
የኮንስትራክሽን ዲዛይን፣ ግንባታና ማማከር ድርጅት የ2018 በጀት ዓመት የሚከናወነውን የንብረት ቆጠራ ሥራን ዛሬ ሐምሌ 1 ቀን 2018 ዓ.ም. በይፋ ጀምሯል። ከሥራው ማስጀመሪያ ጋር በተያያዘም ለ6ቱ የቆጠራ ቡድን መሪዎችና ለቆጠራ ኮሚቴ አባላት የግንዛቤ ማስጨበጫ ተሰጥቷል፡፡
የግንዛቤ ማስጨበጫ መርሃ-ግብሩን በይፋ ያስጀመሩት የድርጅቱ ም/ዋና ስራ አስኪያጅ/ምርትና ማሽነሪ ዘርፍ/ ኢ/ር መስፍን መኮንን እንደገለጹት የንብረት ቆጠራው በትክክልና በጥራት መከናወኑ የድርጀቱን የንብረት አስተዳደር ለማጠናከር፣ ተጠያቄነትንና ግልጽነትን ለማሳደግ፣ የበጀት ዓመቱን ሂሳብ በትክክል ለመዝጋት እንዲሁም የድርጅቱን ሀብት በብቃትና በቀልጣፋ ሁኔታ ለማስተዳደር መሠረታዊ ጠቀሜታ እንዳለው ገልጸዋል፡፡
አያይዘውም ሁሉም የቆጠራ ኮሚቴ አባላት ተግባራቸውን በከፍተኛ ኃላፊነት፣ በታማኝነትና በሙያዊ ሥነ-ምግባር በመፈጸም የድርጅቱን የንብረት መረጃ ትክክለኛና ተዓማኒ እንዲሆን በኩላቸውን አስተዋጽዎ እንዲያበረክቱ አሳስበዋል፡፡
በመርሃ-ግብሩ የተሰጠው የግንዛቤ ማስጨበጫ ያቀረቡት የድርጅቱ የውስጥ ኦዲት ቡድን መሪ በወ/ሮ ኤልሳ ተ/ማርያም ሲሆኑ የቆጠራው ዓላማ፣ የአፈጻጸም ሂደት፣ የኮሚቴ አባላት ኃላፊነትና ተግባር የሪፖርት አዘገጃጀትሥርዓት እንዲሁም የግልጽነትና ተጠያቂነት መርሆዎች ዝርዝር ማብራሪያ ሰጥተዋል።
በመጨረሻም በዚህ የቆጠራ ሥራ ላይ ከኦዲት ሰርቪስ ኮርፖሬሽን የውጭ ኦዲተር የሆኑት አቶ ካሳሁን ማሞ በታዛቢነት የተገኙ ሲሆን፣ የ2018 በጀት ዓመት የንብረት ቆጠራ ስራን በይፋ አስጀምረዋል፡፡
የቢዝነስ ዴቬሎፕመንት ዳይሬክቶሬት
ሐምሌ 1 ቀን 2018 ዓ.ም
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ፤ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 30ኛው መደበኛ ስብሰባ ላይ በሰላምና ደህንነት፣ ኢኮኖሚ፣ ጤና፣ ትምህርት፣ የውጭ ግንኙነትን ጨምሮ በሌሎች ዘርፎች ዙሪያ የመንግሥትን አፈጻጸም እና የቀጣይ እቅዶች አብራርተዋል።
የፕሪቶሪያው ስምምነት ጦርነቱን ለማቆም የተደረገ መሆኑን ጠቅሰው፣ በአሁኑ ወቅት በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደርና በክልሉ የሚታዩ አዳዲስ ውጥረቶችን እንዲሁም የክልሉን ሰላም ለማደናቀፍ የሚደረጉ እንቅስቃሴዎችን አንስተዋል። በማኅበራዊ ጉዳዮች ላይ ደግሞ፣ በኢትዮጵያ የሚከሰቱ ግጭቶች የሃይማኖት ወይም የብሔር ሳይሆኑ በፖለቲካና በኢኮኖሚ ጥቅም ሳቢያ የሚነሱ መሆናቸውን ገልጸዋል። በመሆኑም ሕዝቡ የጥላቻ ቅስቀሳዎችን በመቃወም ሃገራዊ ተቋማትን እንዲደግፍ ጥሪ አቅርበዋል።
የሀገር በቀል ኢኮኖሚ ማሻሻያ ፕሮግራም የዋጋ ንረትን ለመቆጣጠር፣ የግሉን ዘርፍ ለማበረታታት፣ ግብርና እና ቱሪዝምን ለማነቃቃት እንዲሁም የውጭ ምንዛሬ ገቢን ለማሳደግ አስተዋጽዖ እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል። በግብርና 29 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በማረስ 1.3 ቢሊዮን ኩንታል ምርት መሰብሰቡን፣ ዘርፉም 7.7 በመቶ ማደጉን ጠቅሰዋል። በኢንዱስትሪ የማኑፋክቸሪንግ አቅም ከ47 በመቶ ወደ 67 በመቶ ማደጉን፣ አዳዲስ ኢንዱስትሪ ፓርኮች መገንባታቸውን እና በሀገር ውስጥ ምርትን በማስፋፋት እስከ 5 ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ የውጭ ምንዛሬ መቆጠቡን ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ 21 ሚሊዮን ተጓዦችን ማጓጓዙን፣ ከ200 በላይ ዓለም አቀፍ ጉባኤዎች በሀገሪቱ መካሄዳቸውን እና የአገልግሎት ዘርፉ 9.8 በመቶ ማደጉን ጠቅሰዋል። በጤና ዘርፍ፤ የሀገር ውስጥ የመድኃኒት ምርት ከ4 በመቶ ወደ 44 በመቶ ማደጉን፣ አዳዲስ ሆስፒታሎች መገንባታቸውን፣ የወባ መከላከል እና የክትባት ተደራሽነት መስፋፋቱን አብራርተዋል። በትምህርት፤ 35 ሺህ የመዋዕለ ሕፃናት ትምህርት ቤቶች እና 35 ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መገንባታቸው የትምህርት ጥራትን ለማሻሻልና ኩረጃን ለማስወገድ እየተደረገ ያለውን ጥረት ያሳያል። በመኖሪያ ቤት ዘርፍ፤ ባለፉት ሰባት ዓመታት 1.2 ሚሊዮን ቤቶች መገንባታቸውን እና በቀጣይ 1.5 ሚሊዮን ተጨማሪ ቤቶች ለመገንባት ዕቅድ መያዙን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ በመቋቋም፣ መጠቀም እና መግራት በተባሉ ሶስት መርሆች ላይ የተመሰረተ መሆኑን ገልጸው በማንኛውም ብሔራዊ ውሳኔ ላይ የውጭ ጣልቃ ገብነት እንደማንቀበል አስረድተዋል። በተጨማሪም የኢትዮጵያ ሉዓላዊነት ሊደፈር እንደማይችልና ይህንን ለማስጠበቅ አቅም እየተገነባ መሆኑን አስታውቀዋል።
በአጠቃላይ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሰላም ማስፈን፣ ኢኮኖሚን ማሻሻል፣ በምግብ ራስን መቻል፣ የትምህርት ጥራትን ማሻሻል፣ ኢንዱስትሪና አገልግሎትን ማሳደግ፣ የሀገሪቱን ሉዓላዊነት በማስከበር እንዲሁም ሌሎች ማኅበራዊ አገልግሎቶችን በማስፋፋት የተገኙ ውጤቶችን በመዘርዘር የቀጣይ ትኩረትም እነዚህን ስኬቶች በማስቀጠል ዘላቂ ልማትና መረጋጋትን ማጠናከር እንደሚሆን አስገንዝበዋል።
#የጠሚሩምላሾች
#PMOEthiopia
የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት በተመለከተ፦
ጠላቶቻችን ‘3መ’ን መርህ አድርገው ይከተላሉ፤ አንደኛው ‘መ’ መካድ ነው፤ ኢትዮጵያ ድልብ ሀብት ያላት መሆኗን፣ አልገዛም ያለ ህዝብ ያላት መሆኗን፣ ኢትዮጵያን ማንበረከክ ቀላል አለመሆኑን ቢያውቁም ግን ይክዳሉ። ሁለተኛው ‘መ’ መርሳት ነው፤ ስልታዊ ጥልቀት ያላት ሀገር መሆኗን፣ የወጣት ሀገር መሆኗንና ከከፋም እራሱንና ሀገሩን መከላከል እንደሚችል እንዲሁም የሀገሪቷ አቀማመጥም ሆነ ተቋማዊ ልምምድ ቀላል አለመሆኑን መርሳት፤ ስለእኛ ሲያስቡ እምቢ ባይነታችንን ይዘነጋሉ። ሶስተኛው ምኞት ነው፤ ያለፈበት ስልት እስረኛ የመሆን ምኞት፤ ሀገር ውስጥ ያሉ ጽንፈኞች ከውጪ ጠላቶች ጋር በመተባበር ኢትዮጵያን አሸንፋለው ብሎ መመኘት። እውነታው ግን ማንም ቢመጣ በኢትዮጵያ ሉዓላዊነት ላይ ቅንጣት ታክል ስጋት የለብንም፤ ያንንም ለማረጋገጥ የሚያስችል አቅም እየገነባን ነው!
#የጠሚሩምላሾች
#PMOEthiopia
የትግራይን አሁናዊ ሁኔታ በሚመለከት፦
የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት በርካታ ጥቅሞችን ያስገኘ ቢሆንም፣ ለምን ተስማማችሁ በሚል ያኮረፉ በርካታ ኃይሎች ተፈጥረዋል። ከሕወሓት ባሻገር፤ በትግራይ ላይ ጥፋት ሊቀጥል ይገባ ነበር ብለው የሚያስቡ አካላት በማኩረፍ ከእኛ የራቁ ሲሆን በተቃራኒው ደግሞ እርስ በእርስ ለመተባበር የሞከሩበት ሁኔታ አለ።
አሁን ላይ በትግራይ ባሉ ኃይሎች በየቀኑ አዳዲስ ግጭቶችንና ጦርነትን ሊቀሰቅሱ የሚችሉ ትንኮሳዎች እየተፈጸሙ ይገኛሉ። ከሁሉ በላይ የሚያሳዝነውና የከፋው ጉዳይ ግን በአሁኑ ወቅት በርካታ የትግራይ ወጣቶች በጉልበት ታፍሰው በሱዳን እየተካሄደ ላለው ጦርነት እንዲሰለፉ መደረጉ ነው። እነዚህ ወጣቶች በማያውቁትና በማይመለከታቸው ጉዳይ በሱዳን ጦርነት ውስጥ ሕይወታቸውን እያጡ ይገኛሉ። በኢትዮጵያ ውስጥ ያለው ችግር ሳይበቃ፣ ጉዳዩ ወደ ሱዳንም ተሻግሯል።
በዚህ ሁሉ ሂደት ውስጥ የትግራይ ሕዝብ የችግሩ ፈጣሪ ሳይሆን፣ የችግሩ ገፈት ቀማሽ ነው። የትግራይን ሕዝብ ይበልጥ የጎዳውና ጉዳቱን ያባባሰው የማይታይ የውስጥ ቁስል መኖሩ ሲሆን እንዲህ ዓይነቱ የውስጥ ቁስል ደግሞ በቀላሉ የማይሽር ነው። እንደ እውነቱ ከሆነ፣ ዛሬ በትግራይ ውስጥ ከሚኖረው ይልቅ በደሴ፣ በጎንደር፣ በአዲስ አበባ እና በአዳማ በሰላም እየኖረና ያለምንም ስጋት ወጥቶ የሚገባው የትግራይ ተወላጅ ቁጥር ይበልጣል።
#የጠሚሩምላሾች
#PMOEthiopia
ኢንዱስትሪን በሚመለከት፦
የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ዘርፍ ከፍተኛ ለውጥ እያሳየ ይገኛል። አጠቃላይ የማኑፋክቸሪንግ አቅም ከነበረበት 47 በመቶ ወደ 67 በመቶ ከፍ እንዲል ሰፊ ጥናቶች እና የድጋፍ ስራዎች ተከናውነዋል። ይህ እድገት ከነባሮቹ የኮምቦልቻ፣ የመቐለ እና የሐዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርኮች በተጨማሪ አስር አዳዲስ የኢንዱስትሪ ፓርኮችን በመገንባት ከ80 በመቶ በላይ የውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንትን መሳብ ተችሏል። በተጨማሪም የውጭ ምርቶችን በሀገር ውስጥ ምርት የመተካት ስትራቴጂ ተግባራዊ ተደርጓል። በዚህም ሲሚንቶ፣ ብረት፣ ብርጭቆ እና ሴራሚክስን የመሳሰሉ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በማምረት ብቻ ወደ 5 ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ የውጭ ምንዛሬ መቆጠብ ተችሏል። ዘርፉ እያስመዘገበ ባለው ፈጣን እድገትም በማዕድን ዘርፍ 24 በመቶ፣ በማኑፋክቸሪንግ 20.3 በመቶ እና በኢነርጂ ዘርፍ ደግሞ 23 በመቶ ጭማሪ ታይቷል። ለወደፊቱም ይህን ስኬት ዘላቂ ለማድረግ ትኩረት የተደረገ ሲሆን፣ በሚቀጥለው ዓመት በኢንዱስትሪ ፓርኮች ብቻ የ12.7 በመቶ እድገት እና ከኢንዱስትሪ ምርቶች ኤክስፖርት የ1 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ለማግኘት ታቅዷል።
#የጠሚሩምላሾች
#PMOEthiopia
ግብርና እና የምግብ ሉዓላዊነትን በተመለከተ፦
በዘንድሮው የምርት ዘመን 29 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በማረስ 1.3 ቢሊዮን ኩንታል ምርት መሰብሰብ መቻሉ እንዲሁም ዘርፉ የ7.7 በመቶ ዕድገት ማስመዝገቡ፤ የኢትዮጵያ ግብርና እያሳየ ላለው መዋቅራዊ ሽግግር ግልጽ ማሳያ ነው። በሀገር አቀፍ ደረጃ የተተገበረው የ‘ሌማት ትሩፋት’ መርሃ-ግብር አስደናቂ ውጤቶችን ያስመዘገበ ሲሆን፣ በተለይም አቮካዶን ወደ ውጭ በመላክ ከአፍሪካ 2ኛ ደረጃን መያዝ መቻሉ ለሀገሪቱ ተጨማሪ ከፍተኛ ገቢ በማስገኘት አስደናቂ ድል እንዲመዘገብ አስችሏል። ከዚህም በላይ ለረጅም ጊዜ በከባድ ድርቅ ይጎዳ የነበረው የቦረና ቀጣና ዛሬ በሰፊ የስንዴ ልማት ተሸፍኖ ማየት መቻሉ የስትራቴጂያዊ ግብርና ስራችንን ስኬታማነት ያረጋግጣል። ምንም እንኳ የዓለም አቀፍ ጫናዎች ቢበዙም፣ የማዳበሪያ እና የነዳጅ ዋጋ ቢንርም፣ በቁርጠኝነትና በጠንካራ ስራ በምግብ ራሳችንን ለመቻልና በአፍሪካ ላይ የተለጠፈውን የረሃብ ታሪክ ለመቀየር በተግባር እየሰራን እንገኛለን፤ ምክንያቱም ምርጫችን ለምኖ መኖር ሳይሆን ሰርቶ ማደር ነው!
#የጠሚሩምላሾች
#PMOEthiopia
+2
ከ100 በላይ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ሥራ ጀምረዋል - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ ላይ ተገኝተው ማብራሪያ የሰጡት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፣ በኢትዮጵያ ከ100 በላይ የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎቶች በይፋ ሥራ መጀመራቸውን አስታውቀዋል።
የኢትዮጵያን የዲጂታል ጉዞና የቴክኖሎጂ ሽግግር አስመልክተው በሰጡት ሰፊ ማብራሪያ፣ በሀገራችን ከ5 ሚሊዮን በላይ ወጣቶችን በኮደርስ ሥልጠና ላይ በመመዝገብ በዚህም ትልቅ ስኬት መመዝገቡን ገልጸዋል።
የቴክኖሎጂ ልማቱ በኢኮኖሚውና በማኅበራዊ ዘርፉ ላይ እያመጣ ያለውን ዘርፈ-ብዙ ለውጥ የጠቀሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ በአሁኑ ወቅት የሞባይል ባንኪንግ አገልግሎት በከፍተኛ ደረጃ እያደገ እንደሚገኝና የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) ዩኒቨርሲቲ መዋቅርም በጥሩ ሁኔታ ላይ መሆኑን አስረድተዋል።
አክለውም በተለይም በስታርት አፖች (አዳዲስ የፈጠራ ሥራዎች)፣ በሥራ ዕድል ፈጠራ፣ በገቢ አሰባሰብ እንዲሁም በአጠቃላይ የአገልግሎት አሰጣጥ ሥርዓት ላይ ቴክኖሎጂ ከፍተኛና ስትራቴጂካዊ ሚና እየተጫወተ እንደሚገኝ በአጽንኦት ገልጸዋል።
የውጭ ጉዳይና ሉዓላዊነትን በተመለከተ፦
ዓለም ሊካድ በማይችል ሁኔታ ተለዋዋጭ በሆነችበት በዚህ ወቅት፤ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም፣ የውጭ ፖሊሲ እና ሉዓላዊነትን ለማስከበር በስትራቴጂካዊ ራስን መቻል ላይ የተመሠረቱ ሦስት ዋና ዋና መርሆችን እንከተላለን፤ የመጀመሪያው መቋቋም ሲሆን፤ ይህም የውጭ ተጽዕኖዎችን በራስ አቅም ለመቋቋም የሚያስችል ጠንካራ ተቋማዊ አቅምን መገንባት ላይ ያተኩራል። ሁለተኛው መጠቀም ሲሆን፤ ይህም ማንኛውንም የሚያጋጥም ፈተና ወደ ስትራቴጂካዊና መልካም የልማት ዕድል የመቀየር ብቃትን ያካትታል። ሦስተኛው ደግሞ መግራት ሲሆን፤ ይህም ሀገሪቱ የራሷን ብሔራዊ አጀንዳ ቀርጻ ዓለም አቀፋዊ ሁነቶችን በልበ ሙሉነት እንድትጋፈጥና እንድትመራ ያስችላታል። በእነዚህ ሦስት ምሰሶዎች በመመራት በማንኛውም ብሔራዊ ውሳኔያችን ላይ የትኛውንም የውጭ አካል ጣልቃ ገብነት ፍጹም አንፈቅድም።
#የጠሚሩምላሾች
#PMOEthiopia
የትምህርት ዘርፍ ጥራት እና ለውጦችን በተመለከተ፦
የትምህርት ዘርፍ ጥራትን ለማረጋገጥ በተሰሩ ስራዎች ከፍተኛ ለውጥ እየመጣ ነው። ባለፉት ዓመታት ተማሪዎች በራሳቸው ተማምነው ፈተና የሚወስዱበት አሰራር ተተግብሯል፤ በዚህም የኩራጃ ባህልን ማስረቀት ተችሏል። ትምህርት ከታች ካልተሠራ ከላይ መሥራት ውጤታማ አያደርግም፤ ለመዋዕለ ህጻናት ማስፋፊያ በተሰጠው ትኩረት 35 ሺህ መዋዕለ ሕጻናትን መገንባት ተችሏል። የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ፣ ኩረጃን ለማስቀረት፣ ትምህርትን በቴክኖሎጂ ለማስፋፋት እየተደረገ ያለው ሙከራ ተስፋ ሰጪ ነው። የአንደኛ እና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችም ደረጃቸውን የጠበቁ እጅግ አበረታች ግንባታዎች እየተከናወኑ ይገኛል።
#የጠሚሩምላሾች
#PMOEthiopia
ሀገራዊ ምክክርን በተመለከተ
“ይህንን ሰፊ ሀገራዊ እድል በመጠቀም፣ ካለፉት እሰጥ አገባዎች ወጥተን በሰለጠነ መንገድ መወያየት ይኖርብናል። በሕገ መንግሥቱ ውስጥ ያሉትን አወንታዊ እሴቶች ይዘን እንቀጥል፤ ማሻሻያ የሚያስፈልጋቸውን ነጥቦች ደግሞ ማንንም በማይጎዳ፣ የሁሉንም መብት በሚያከብርና አንድነታችንን በሚያጠናክር መልኩ እናሻሽላለን።ዋናው መገንዘብ ያለብን ነጥብ፦ አሁን የምንመክረው የአንድን ጊዜያዊ ገዥ ፓርቲ ስህተት ለማረም ብቻ አይደለም። ይልቁኑ ለዘመናት የተከማቹ ስር የሰደዱ ሀገራዊ ችግሮቻችንን በጋራ ጠረጴዛ ዙሪያ ፈትተን፣ ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ የሚበጅ አዲስ ማህበራዊ ውል ለመፈረም ነው። ይህ ምክክር በመወያየት፣ በመነጋገርና በመተማመን እንዴት አብሮ መኖር ይቻላል ለሚለው ታሪካዊ ጥያቄ ዘላቂ ምላሽ የምንሰጥበት ብቸኛው መንገድ ነው!”
#የጠሚሩምላሾች
#PMOEthiopia
ሰላምና መረጋጋትን በተመለከት
“በኢትዮጵያ በተለያዩ አከባቢዎች የተፈጠሩ አለመረጋጋቶችን ለመፍታት መንግሥት ከ4000 በላይ የምክክር መድረኮችንና በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን በማሳተፍ በኢትዮጵያ ታሪክ ትልቁን የብሔራዊ መግባባት ምእራፍ ተሻግረናል። ባንዳዎችንና ጽንፈኞችን የምናሸንፈው በተጠናክረ ውይይት ብቻ ነው።”
#የጠሚሩምላሾች
#PMOEthiopia
