en
Feedback
ዋን ፕላኔት ሚዲያ - One Planet Media

ዋን ፕላኔት ሚዲያ - One Planet Media

Open in Telegram

እያዝናና፣ እያሳወቀ እያስተማረ ለዓለም መሻሻል የሚተጋ ሚዲያ!! JOIN Request ላኩ 👇👇👇

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel ዋን ፕላኔት ሚዲያ - One Planet Media

Channel ዋን ፕላኔት ሚዲያ - One Planet Media (@timihrt_minister22) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 31 565 subscribers, ranking 6 031 in the Education category and 1 073 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 31 565 subscribers.

According to the latest data from 28 June, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by -1 406 over the last 30 days and by -30 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 0.63%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects N/A% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 198 views. Within the first day, a publication typically gains 0 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 1.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
እያዝናና፣ እያሳወቀ እያስተማረ ለዓለም መሻሻል የሚተጋ ሚዲያ!! JOIN Request ላኩ 👇👇👇

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 29 June, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Education category.

31 565
Subscribers
-3024 hours
-2787 days
-1 40630 days
Posts Archive
ትምህርት ቤት ወይስ የለውጥ ማዕከል? ‘’በበሻሌ ትምህርት ቤት የፈለቀው ሕይወት" ሚያዝያ 30፣ 2018 ዓ.ም | አዲስ አበባ ዋን ፕላኔት ሚዲያ "ውኃ ሕይወት ነው፤ ትምህርት ደግሞ የሕይወት መሠረት!" ትምህርት ቤት ማለት በግድግዳዎች የታጠረ የዕውቀት መቅሰሚያ ብቻ ሳይሆን፣ የማህበረሰብን ቁስል የሚፈውስና ጥማትን የሚቆርጥ የለውጥ ማዕከል መሆኑን ዋን ፕላኔት ኢንተርናሽናል ትምህርት ቤት ዳግም በተግባር አስመስክሯል። በቅርቡ 20ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን በደመቀ ሁኔታ ያከበረው ተቋሙ፣ በዓሉን ያደመቀው በቃላት ብቻ ሳይሆን በበሻሌ አጸደ ሕፃናትና አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ውስጥ የሚታየውን የመጠጥ ውኃ እጥረት በዘላቂነት የሚፈታ የከርሰ ምድር ውኃ በማስመረቅ ነው። ይህ በበሻሌ ምድር የፈለቀው የሕይወት ምንጭ ለተማሪዎቹ የጤና ዋስትና፣ ለወላጆቻቸው ደግሞ የአዕምሮ እረፍት ሆኖ ተገኝቷል። ከአገልግሎት ባሻገር የተተከለ አሻራ ዋን ፕላኔት ላለፉት ዓመታት ለዚሁ ትምህርት ቤት ያበረከታቸው ስራዎች ቁጥራቸው በርካታ ነው፦ ዘመናዊ የአጸደ ሕፃናት ክፍሎች እና ቤተ መጻሕፍት፤ የምርምር አድማስን የሚያሰፉ የአይሲቲ እና የሳይንስ ቤተ-ሙከራዎች፤ የተማሪዎችን አካላዊ ጥንካሬ የሚገነቡ የስፖርት ሜዳዎች፤ እንዲሁም ለኑሮ ተግባራዊ ዕውቀት የሚሰጡ የችግኝ ማፍያ እና የዶሮ ማርቢያ ቤቶች። ዛሬ ደግሞ እነዚህን ሁሉ አገልግሎቶች የሚያለመልም የውኃ ፕሮጀክት በማስመረቅ፣ ተቋሙ "ችግር ፈቺ ትውልድን መቅረጽ" የሚለውን መርህ መሬት ላይ አውርዶታል። የጋራ ፍቅር ውጤት በምርቃቱ ስነ-ስርዓት ላይ የተገኙት የለሚኩራ ክፍለ ከተማ ምክትል ሥራ አስፈፃሚ አቶ ልመንህ  ምህረቱ፣ ተቋሙ ለማህበረሰቡ እያበረከተ ያለውን ተከታታይ ድጋፍ በማድነቅ "ይህ የውኃ ፕሮጀክት ከጤና ባለፈ ለትምህርት ጥራት መሻሻል ቁልፍ ሚና አለው" ብለዋል። የትምህርት ቤቱ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ዘላለም አማረ በበኩላቸው፣ ይህ ስኬት የተገኘው በተናጠል ሳይሆን በወላጆች፣ በተማሪዎች እና በአጋዥ ተቋማት የጋራ "የፍቅር ድምር" መሆኑን ገልጸዋል። አቶ ዘላለም አክለውም፣ "ትምህርት ቤት ማለት የህንፃዎች ስብስብ ሳይሆን የማህበረሰብ ለውጥ ማዕከል ነው፤ እኛም ይህንን አርአያነት ያለው ስራ ወደፊትም አጠናክረን እንቀጥላለን" ሲሉ የላቀ ራዕያቸውን አጋርተዋል። ይህ በበሻሌ ምድር የፈለቀው የሕይወት ምንጭ፣ ለነገዎቹ የሀገር ተረካቢ ህጻናት ተስፋን ያበሰረ እና ዋን ፕላኔት ኢንተርናሽናል ትምህርት ቤት በ20 ዓመት ጉዞው ካስመዘገባቸው ደማቅ የታሪክ ምዕራፎች መካከል አንዱ ሆኖ ተመዝግቧል።

የዋን ፕላኔት የ20 ዓመታት የብርሃን እና የፅናት ጉዞ! በዋን ፕላኔት ሚድያ አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ— ዋን ፕላኔት ኢንተርናሽናል ስኩል እ.ኤ.አ በ2006 ዓ.ም በአዲስ አበባ በአንዲት አነስተኛ ጊቢ ውስጥ በ30 ህጻናት ብቻ የጀመረው ጉዞ፣ “እያንዳንዱ ልጅ ለዓለም ብርሃን የመሆን አቅም አለው” በሚል ትልቅ ራዕይ ታጅቦ ነበር። ባለፈው አርብ ግን ይህ ህልም እውን ሆኖ በአፍሪካ ሕብረት (AU Hall) ታላቅ አዳራሽ ውስጥ የድል ዝማሬ ሆኖ ተደምጧል፡፡ የስነ-ምግባር እና የእውቀት ጥምረት “የ20 ዓመታት የትምህርት ጉዞ በተግባር፦ ማህበረሰቡን ማገልገልና ማብቃት” በሚል መሪ ቃል የተከበረው ይህ በዓል፣ ትምህርት ቤት ከማስተማር ባለፈ ስብዕናን የመቅረጽ ተልዕኮ እንዳለው ያስመሰከረ ነበር። በትምህርት ቤቱ መስራችና ዋና ስራ አስፈጻሚ በአቶ ዘላለም አማረ እና በባለቤታቸው ወ/ሮ ጌይል አማረ የተመሠረተው ይህ ተቋም፣ የቀድሞዋ የትምህርት ሚኒስትር አምባሳደር ገነት ዘውዴን ጨምሮ የተለያዩ ሃገራት ዲፕሎማቶች እና ታዋቂ የትምህርት ባለሙያዎች በተገኙበት ታሪኩን በደማቅ ቀለም መዝግቧል። “ትምህርት ቤቱን ስንመሰርት ቀዳሚ ዓላማችን ከሂሳብና ከንባብ በፊት ለሥነ-ምግባር ቅድሚያ መስጠት ነበር” ሲሉ አቶ ዘላለም በንግግራቸው አስታውሰዋል። “ምክንያቱም እያንዳንዱ ልጅ በውስጡ ያለውን ብርሃን ካበራ፣ የአካዳሚክ እውቀቱ ለማህበረሰቡ የተሻለ ለውጥ ማምጫ መሣሪያ እንደሚሆን እናምናለን።” “የዓለም ብርሃን” በታሪክ መዝገብ በክብረ በዓሉ ላይ ሌላ ልዩ ትኩረት ስቦ የነበረው በትምህርት ቤቱ መስራች በአቶ ዘላለም አማረ የተጻፈው "The Light of the World" (የዓለም ብርሃን) የተሰኘው መጽሐፍ ምርቃት ነበር። መጽሐፉ በአማርኛ እና በእንግሊዘኛ ቋንቋ የተፃፈ ሲሆን የጸሐፊውን የግል የሕይወት ታሪክ ጉዞ እና ትምህርት ቤቱ ያለፈባቸውን አስቸጋሪ ፈተናዎች፣ አነቃቂ ስኬቶች እና የሁለት አስርተ ዓመታት ታሪካዊ ጉዞዎችን በዝርዝር የሚያስቃኝ ሲሆን፣ በዘርፉ ለተሰማሩ ባለሙያዎችም እንደ አርአያነት ቀርቧል። የአንድነት እና የልህቀት ውጤት በዕለቱ በተካሄደው የፓናል ውይይት፣ የቀድሞ እና የአሁኑ ተማሪዎች እንዲሁም ወላጆች መምህራን እና የትምህርት ባለሙያ ስለ ትምህርት ቤቱ ማህበራዊ ተፅዕኖ ምስክርነታቸውን ሰጥተዋል እንዲሁም ለወደፊት የተቋሙ ጉዞው አመላካች ሃሳቦች ተንሸራሽረዋል። ተቋሙ ለአካዳሚክ ልህቀት ብቻ ሳይሆን፣ ለሌሎች ማሰብን ለሚያውቁ የነገ መሪዎች መፍሪያ መሆኑን አሳይቷል። ኢትዮጵያ በትምህርት ዘርፍ ሰፊ ማሻሻያ እያደረገች ባለችበት በዚህ ወቅት፣ ዋን ፕላኔት ኢንተርናሽናል ስኩል ላለፉት 20 ዓመታት ያሳየው ስኬት ለዘርፉ እንደ ተምሳሌት ተጠቅሷል። አቶ ዘላለም በቀጣዮቹ ሁለት አስርተ ዓመታት ጥራት ያለው ትምህርትን በቴክኖሎጂ በማገዝ ለኢትዮጵያ ገጠራማ አካባቢ ህጻናት በነፃ ተደራሽ የሚያደርግ የዲጂታል ፕላትፎርም በቅርቡ ይፋ እንደሚያደርጉና፣ የጂኦግራፊያዊ አቀማመጥ ለትምህርት እንቅፋት የማይሆንበትን አዲስ የተስፋ ምዕራፍ እንደሚከፍት ገልጸዋል። ዋን ፕላኔት ኢንተርናሽናል ስኩል ዛሬ ከ1,200 በላይ ተማሪዎችን የሚያስተምር እና 250 ሰራተኞችን የያዘ የትምህርት ማዕከል ለመሆን በቅቷል። ከ20 ዓመት በፊት የበራው ያ ትንሽዬ ሻማ፣ ዛሬ የብዙዎችን መንገድ የሚያበራ ታላቅ ችቦ ሆኗል፡፡

የዛሬው መነፅር ፖድካስት! https://youtu.be/agpJvNHuMG0

ውድ የዋን ፕላኔት ሚዲያ ቤተሠቦች የዛሬውን ዝግጅታችንን እነሆ ብለናል:: https://youtu.be/Ui7GMYaM9xE

የዓለም መሻሻል ላይ ትኩረት የሚያደርገው 'ዓለም ታማለች' ፕሮግራም፣ ለአራት ተከታታይ ሳምንታት በሚቀርበው ዶክመንተሪ ድራማና ውይይት ሁለተኛ ክፍል፣ ከዝግ በሮች በስተጀርባ የሚፈጸመውን የቤት ውስጥ የህጻናት ጥቃት ጉዳይ ወደ እናንተ ያቀርባል። ይህ ፕሮግራም የህጻናት ጥቃት ሰለባ የሆኑ ህጻናትን እውነተኛ ታሪክ የሚያሳይ ነው። እያንዳንዱ ክፍል ከጥቃቱ የስሜት ስቃይ አንስቶ የመፈወስን ጉዞ ያሳያል። የፕሮግራሙ ዋና አላማ የጥቃቱን የስነ-ልቦናዊ ጉዳት መግለጽና ለተስፋና ለለውጥ የሚበራውን ብርሃን ማሳየት ነው። ይህን ጠቃሚ ፕሮግራም ሁላችሁም እንድትመለከቱና የዋንፕላኔት ሚዲያ ቤተሰብ እንድትሆኑ በአክብሮት እንጋብዛችኋለን። https://youtu.be/K3fM3NCQAmA