የለተሞ መንጋን በመረጃ ማፈራረስ
Open in Telegram
የለተሞ መንጋን ማፈራረስ ሲባል የተፈራረሰውን ግልፅ ማድረግን ነው የተፈለገበት በአሏህ ፍቃድ የመንሀጅ ስህተቶቻቸውን በመረጃ ግልፅ እናደርጋለን በአላህ ፍቃድ።
Show more4 723
Subscribers
+324 hours
+97 days
+5230 days
Posts Archive
4 723
ሸሪዓዊ ህግ ጉራጌ /ጉንችሬ ሲሆንና አዲስ አበባ ሲሆን ይለያያል እንዴ! ?
ባህሩ ተካ ብዙ አቋሞቹ ላይ ጉንችሬ ሲሆንና ሌላ ቦታ ሲሆን የተለያየ አቋም ያንፀባርቃል ።
4 723
ያ ጀመዓ!
በእስልምና ሚዛን የሚከተሉትን መሠረታዊ ልዩነቶች ማወቅና መለየት ያስፈልጋል፦
ጥፋት (ወንጀል) እና ቢድዓ ይለያያሉ፦
ጥፋተኛ መሆን እና "ሙብተዲዕ" ተብሎ መፈረጅ ይለያያሉ፦ አንድ ሰው በሆነ ነገር ላይ ተሳስቶ ጥፋተኛ ሊሆን ይችላል፤ ነገር ግን የሸሪዓ መስፈርቶች ሳይሟሉ እና ከልካይ ነገሮች (እንደ አለማወቅ፣ በስህተት መረዳት) ሳይወገዱ ሰዎችን ወዲያውኑ "ሙብተዲዕ" ብሎ መፈረጅ ድንበር ማለፍ ነው።
እነዚህን መሠረታዊ የሸሪዓ ልዩነቶች ሳያውቁና ሳይረዱ ሰዎችን በጅምላ መፈረጅ የመንሃጅ ጥልቀት ማጣትን ያሳያል።
4 723
ለለተሞ ጀመዓዎች ጥያቄ፦
" የ መርከዝ ኢብኑ መስዑድ የተወሰኑ ሸይኾችና ኡስታዞች ጥፋት አጠፉ ብላችሁ 'ሙብተዲዕ' ስላላችሁ ፦
በገጠር፣ በከተማ፣ በሀገር ውስጥም ሆነ ከሀገር ውጭ ያለውንና ከእናንተ ጋር ያልሆነን ሙስሊም ሁሉ—ምንነቱን ሳታውቁ፣ የሸሪዓ መስፈርቶች ሳይሟሉና ከልካይ ነገሮች ሳይወገዱ—በጅምላ 'ሙብተዲዕ' ብላችሁ የመፈረጅን አካሄድ ከየትኛው የሰለፎች ድንጋጌ አገኛችሁት?"
በአጭሩ፦
የአንድ አካል ጥፋት ወደ ሌሎች በማስተላለፍና ምንም የማያውቀውን ድፍን ሙስሊም በጅምላ "ሙብተዲዕ" በማለት መፈረጅ፣ ከሰለፊያ መንሃጅና ከኡለሞች መንገድ ሙሉ በሙሉ የወጣ ድንበር አላፊነት ነው።
በሸሪዓ ሚዛን ግለሰብም ሆነ ቡድን ላይ ፍርድ የሚሰጠው መስፈርቶች ሲሟሉ እና ከልካዮች ሲወገዱ ብቻ እንጂ፤ በግሩፕ አባልነትና በጅምላ ፍረጃ አይደለም።
ይህ አካሄዳችሁ የመንሃጅ ጥልቀት ማጣታችሁንና የራሳችሁን ስሜት የመከተላችሁ ግልጽ ማሳያ ነው።
4 723
"ቢድዓ ከመስራት ወንጀል መስራት ይሻላል!" — የለተሚዮች የተዛባ አስተሳሰብ ሌላው ማሳያ
የለተሞ ጀመዓዎች በድንበር አላፊ አስተሳሰባቸው ምክንያት የት ደረጃ ላይ እንደደረሱ የሚያሳይ አንድ ታሪክ፦
ቡታጅራ ላይ የሚገኝ አንዱ የለተሞ ጀመዓ አባል ከረንቡላ ቤት ይከፍታል፤ መስጊድ መምጣቱንም ይተዋል።
ወንድሞች ሁኔታው አሳስቧቸው ሄደው፦ "ለመሆኑ ለምን ከረንቡላ ቤት ከፈትክ? መስጊድስ ለምን ጠፋህ?" ብለው ሲጠይቁት፤
አፉን ሞልቶ፦ "ቢድዓ ከመስራት ወንጀል መስራት ይሻላል ብዬ ነው!" ብሎ ይመልስላቸዋል።
በእሱ ቤት መረጃና ሸሪዓዊ ምክንያት ማቅረቡ ነው!
ይህ አጋጣሚ የለተሞ ጀመዓዎች አስተሳሰብ ምን ያህል የተዛባ፣ ከዒልም ሚዛን የወጣ እና ዲኑን አላግባብ በመረዳት ሰዎችን ከስግደትና ከመስጊድ አርቆ ወደ ወንጀልና ወደ ከረንቡላ ቤት የሚነዳ ድንበር አላፊ አካሄድ መሆኑን ቁልጭ አድርጎ ያሳያል።
https://t.me/Menhaje_Selef/
4 723
የለተሞ ጀመዓ መረጃ አወሳሰድ ከዝንቧ ታሪክ ጋር ይመሳሰልብኛል
የለተሞ ጀመዓዎች መረጃን አጣሞ የመውሰድ፣ አውዱን ሳያገናዝቡ ለማይገናኝ ነገር አያያዞ ሰዎችን ከሱና የመግፋትና በቢድዓ የመፈረጅ አካሄድ፤ ሼኽ ረስላን ከተናገሩት አንድ አስገራሚ የተክፊሪዮች ታሪክ ጋር ተመሳስሎ ይገኛል።
ታሪኩ እንዲህ ነው፦
" ሁለት ጓደኛሞች አብረው ተቀምጠው ሳለ አንዲት ዝንብ መጥታ አዛ ታደርጋቸዋለች (ታስቸግራቸዋለች)።
ከሁለቱ አንደኛው፦ "እቺ ዝንብ እኮ ከፍራለች (ከእስልምና ወጥታለች)" ይላል።
ጓደኛውም በመገረም፦ "እንዴት ዝንብ ትከፍራለች?" ብሎ ሲጠይቀው፤
የመጀመሪያውም፦ "ምክንያቱም እቺ ዝንብ ምእመናንን አዛ አድርጋለች (አስቸግራለች)፤ አላህ ደግሞ በቁርኣን እንዲህ ብሏል፦
> وَالَّذِينَ يُؤْذُونَ الْمُؤْمِنِينَ وَالْمُؤْمِنَاتِ بِغَيْرِ مَا اكْتَسَبُوا فَقَدِ احْتَمَلُوا بُهْتَانًا وَإِثْمًا مُّبِينًا
> (ትርጉም፦ እነዚያም ምእመናንን እና ምእመናትን ባላደረጉት ጥፋት የሚያስቸግሩ በእውነት ታላቅ ቅጥፈትንና ግልጽ ወንጀልን ተሸክመዋል)
ስለዚህ ምእመንን ያዘነች ከፍራለች!" ሲል ድምዳሜ ላይ ይደርሳል።
ጓደኛውም አሁንም አልተዋጠለትምና፦ "ኧረ ዝንብ በሸሪዓ አትከፍርም!" ብሎ ሲከራከረው፤
ተክፊሪዩ ወዲያው ፊቱን ወደ ጓደኛው አዙሮ፦ "አንተም እኮ አሁን ከፍረሃል!" ይለዋል።
ጓደኛው ደንግጦ፦ "እኔ ደግሞ እንዴት ከፈርኩ?" ሲለው፤
"ካፊርን ካፊር ያላለ አካል ራሱ ካፊር ነው
(من لم يكفر كافراً فهو كافر)"
ብሎ እርሱንም ከእስልምና አስወጣው ይባላል።
የለተሚዮችና የታሪኩ ተመሳሳይነት፦
ይህ አያያዥ የለተሞ ጀመዓዎችን ትክክለኛ ምስል ቁልጭ አድርጎ ያሳያል፦
አውድ አልባ ትስስር፦ ለተሚዮችም በዲኑ ውስጥ ያላትን ቦታና አውድ ሳያገናዝቡ፣ ለማይገናኝ ነገር ቁርኣንና ሐዲስን እየመዘዙ፣ የራሳቸውን ስሜትና አተረጓጎም በመጨመር ሰዎችን ከሱና ያባርራሉ።
የፍረጃ ሰንሰለት፦ ልክ እንደ ታሪኩ ሰውዬ "እኔ የፈረጅኩትን ካልፈረጅክ አንተም ከሱና ወጥተሃል" በሚል የጅልነትና የድንበር አላፊነት መረብ ውስጥ ህዝቡን ሲያታግሉ ይኖራሉ።
በአጠቃላይ፣ የለተሞ ጀመዓዎች የዒልም ጥልቀት የሌላቸው፣ የመረጃ አወሳሰዳቸው የተዛባና ሰዎችን በከንቱ ምክንያት ከሱና አጥር ለማስወጣት የሚቸኩሉ ድንበር አላፊዎች መሆናቸውን ይህ ታሪክ ያመላክታል።
