en
Feedback
Abrsh News አብርሽ ኒውስ🌎

Abrsh News አብርሽ ኒውስ🌎

Open in Telegram

📈 Analytical overview of Telegram channel Abrsh News አብርሽ ኒውስ🌎

Channel Abrsh News አብርሽ ኒውስ🌎 (@habesha_cryptoo) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 24 718 subscribers, ranking 4 959 in the Cryptocurrencies category and 1 352 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 24 718 subscribers.

According to the latest data from 19 June, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by -1 182 over the last 30 days and by -37 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 1.79%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 0.70% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 443 views. Within the first day, a publication typically gains 172 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 3.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
Creator @Futurecryptoholder @habesha_second Buy Ads: https://telega.io/c/Habesha_Cryptoo

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 20 June, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Cryptocurrencies category.

24 718
Subscribers
-3724 hours
-2677 days
-1 18230 days
Posts Archive
📌 ቦሌ ቡልቡላ 👉ሱቅ ከ 12 ካሬ ጀምሮ ጠቅላላ ዋጋ 💥2,958,000 ብር ወይም ቅድመ ክፍያ 15% =522,000ብር 💥አፓርትመንት 🏢115ካሬ ባለ2 መኝታ=13.2ሚሊዮን ብር 👉15%ቅድመ
📌 ቦሌ ቡልቡላ 👉ሱቅ ከ 12 ካሬ ጀምሮ ጠቅላላ ዋጋ 💥2,958,000 ብር ወይም ቅድመ ክፍያ 15% =522,000ብር 💥አፓርትመንት 🏢115ካሬ ባለ2 መኝታ=13.2ሚሊዮን ብር 👉15%ቅድመ ክፍያ =1,983,750 ብር   🏢130ካሬ ባለ2 መኝታ=14.9ሚሊዮን ብር 👉15%ቅድመ ክፍያ  =2,242,500 ብር 🏢155ካሬ  ባለ3 መኝታ17.8ሚሊዮን ብር 👉15%ቅድመ ክፍያ =2,673,750 ብር   💥 ቀሪዉ በ14 ዙር ረጅም ጊዜ አከፋፈል ያለ ምንም ዋጋ ጭማሪ 💥Building facilities ✅የከርሰ ምድር ውሃ ✅ Hotel Standard ጂም እና ስፖ ✅Back up Generator ✅CCTV - Camera ✅ 2 Escalator  ✅ 8 ዘመናዊ ሊፍቶች ✅ 4 ቤዝመንት Smart Parking ከ ኤሌትሪክ መኪኖች ቻርጂንግ ቦታ ጋር ✅ ላይብረሪ ✅ የልጆች መጫወቻ ☎️ለበለጠ መረጃ ይደውሉ 👇👇👇👇👇👇 +251937341286 +251714558361 📲👇በ WhatsApp ማግኘት ከፈለጉ https://wa.me/251937341286 📲Channel: https://t.me/Jenboro_RealEstateSales 📲Telegram : @AbrhamRealEstateConsultant

የአሜሪካ ቢ-52 (B-52) ወታደራዊ ቦምብ ጣይ አውሮፕላን በካሊፎርኒያ ተከሰከሰ ሰኞ ሰኔ 8 ቀን 2018 ዓ.ም የአሜሪካ አየር ኃይል ንብረት የሆነ ግዙፍ የቢ-52 (B-52) የረጅም ርቀት ቦምብ
የአሜሪካ ቢ-52 (B-52) ወታደራዊ ቦምብ ጣይ አውሮፕላን በካሊፎርኒያ ተከሰከሰ ሰኞ ሰኔ 8 ቀን 2018 ዓ.ም የአሜሪካ አየር ኃይል ንብረት የሆነ ግዙፍ የቢ-52 (B-52) የረጅም ርቀት ቦምብ ጣይ አውሮፕላን በካሊፎርኒያ ከሚገኘው ኤድዋርድስ አየር ኃይል ጦር ሰፈር ለመነሳት በሞከረበት ወቅት ተከስክሷል። በአደጋው የደረሰው የሰው ሕይወት ጉዳትም ሆነ የአደጋው መንስኤ እስካሁን በይፋ ያልታወቀ ሲሆን፣ የአደጋ ጊዜ ሠራተኞች በስፍራው ተሰማርተው ክትትል እያደረጉ ይገኛሉ። እያንዳንዳቸው 110 ሚሊዮን ዶላር የሚያወጡትና የኑክሌር መሣሪያዎችን ጭምር የመሸከም አቅም ያላቸው እነዚህ አውሮፕላኖች ለአሜሪካ አየር ኃይል ስትራቴጂካዊ የጦር መሣሪያዎች መሆናቸው ይታወቃል።

ድምጻዊ ሰማኸኝ በለው ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ ሰኔ 8/2018 (ገበያ ሚዲያ) ድምጻዊ ሰማኸኝ በለው (ሰሜ ባላገሩ) ባደረበት ሕመም በሕክምና ሲረዳ ቆይቶ በዛሬው ዕለት ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል፡
ድምጻዊ ሰማኸኝ በለው ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ ሰኔ 8/2018 (ገበያ ሚዲያ) ድምጻዊ ሰማኸኝ በለው (ሰሜ ባላገሩ) ባደረበት ሕመም በሕክምና ሲረዳ ቆይቶ በዛሬው ዕለት ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል፡፡ ድምጻዊ ሰማኸኝ በለው የተለያዩ ባህላዊ እና ሌሎች ይዘቶቸ ያሏቸው የሙዚቃ ሥራዎችን ለአድማጭ ተመልካች አበርክቷል፡፡ ድምጻዊ ሰማኸኝ በለው ባለትዳር እና የአራት ልጆች አባት እንደነበር ፋና ከቤተሰቦቹ አገኘሁት ያለው መረጃ ያመላክታል፡፡ ገበያ ሚዲያ ለቤተሰቦቹ፣ ለወዳጅ ዘመዶቹና ለአድናቂዎቹ መጽናናትን ይመኛል፡፡

ከደሴ ወደ አዲስ አበባ ሲጓዝ በነበረ ተሽከርካሪ ላይ በደረሰ አደጋ የ28 ሰዎች ሕይወት አለፈ ከደሴ ወደ አዲስ አበባ ሲጓዝ በነበረ ተሽከርካሪ በደረሰ አደጋ የ28 ሰዎች ሕይወት ማለፉን ፖሊስ አስታ
+1
ከደሴ ወደ አዲስ አበባ ሲጓዝ በነበረ ተሽከርካሪ ላይ በደረሰ አደጋ የ28 ሰዎች ሕይወት አለፈ ከደሴ  ወደ አዲስ አበባ ሲጓዝ በነበረ ተሽከርካሪ በደረሰ አደጋ የ28 ሰዎች ሕይወት ማለፉን ፖሊስ አስታውቋል። አደጋው የደረሰው ከደሴ እና ኮምቦልቻ ከተሞች መካከል በሚገኘው የሐረጎ መንገድ ላይ ነው። ዛሬ ሰኔ 8 ቀን 2018/ዓ.ም ማለዳ  ከደሴ ወደ አዲስ አበባ በመጓዝ ላይ የነበረ የሕዝብ አውቶቡስ በተለምዶ ሐረጎ  እየተባለ በሚጠራው መንገድ ላይ በደረሠበት  አደጋ እስካሁን የ28 ሰዎች ሕይወት ሲያልፍ በርካቶች ቀላልና ከባድ ጉዳት ደርሶባተቸዋል። የሕዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪው በግምት 100 ሜትር ጥልቀት ወዳለው ገደል ገብቶ አደጋው ደርሷል።በሕይወት የተረፉትን ወደ ሕክምና ቦታ ለማድረስ አሁንም ርብርብ እየተደረገ መኾኑን የገለጸው ፖሊስ የአደጋውን ምክንያት በመጣራት ላይ ይገኛል ብሏል። ምንጭ :- የአሚኮ

«እግዚአብሔር ቀን አለው» ከሚል የአመታት ተስፋ በኋላ «እግዚአብሔር ይመስገን» የምልበትን ቀን መጣ። አቦ ደስታዬ ደስ የሚላችሁ ደስ ይበላችሁ። ከዚህ በኋላ ተስፋ፣ ፀጋ እና ስኬት እንጂ ሌላስ ምን አለ?። ሁሉም ነገር ደህና መሆን ይጀምራል እኛ ደህና መሆን ስንጀምር°°😇

መዝሙር 22 እግዚአብሔር እረኛዬ ነው የሚያሳጣኝም የለም። በለመለመ መስክ ያሳድረኛል  በዕረፍት ውኃ ዘንድ ይመራኛል። ነፍሴን መለሳት  ስለ ስሙም በጽድቅ መንገድ መራኝ። በሞት ጥላ መካከል እንኳ ብሄድ አንተ ከእኔ ጋር ነህና ክፉን አልፈራም!። በትርህና ምርኵዝህ እነርሱ ያጽናኑኛል። በፊቴ ገበታን አዘጋጀህልኝ። በጠላቶቼ ፊት ለፊት ራሴን በዘይት ቀባህ  ጽዋዬም የተረፈ ነው። ቸርነትህና ምሕረትህ በሕይወቴ ዘመን ሁሉ ይከተሉኛል ፥ በእግዚአብሔርም ቤት ለዘላለም እኖራለሁ 🙏🏽          

ኢራን የኑክሌር መሣሪያ ላለማምረት ከአሜሪካ ጋር ከስምምነት ላይ ደረሰች! ኢራን ከአሜሪካ ጋር በደረሰችው የረቂቅ ስምምነት መሠረት የኑክሌር መሣሪያዎችን ላለማምረትም ኾነ ላለመታጠቅ መስማማቷን አንድ
ኢራን የኑክሌር መሣሪያ ላለማምረት ከአሜሪካ ጋር ከስምምነት ላይ ደረሰች! ኢራን ከአሜሪካ ጋር በደረሰችው የረቂቅ ስምምነት መሠረት የኑክሌር መሣሪያዎችን ላለማምረትም ኾነ ላለመታጠቅ መስማማቷን አንድ ከፍተኛ የኢራን ባለሥልጣን ለሮይተርስ የዜና ወኪል ገልጸዋል። ቴህራን በረቂቅ የመግባቢያ ሰነዱ ላይ ባስቀመጠችው ስምምነት ማንኛውንም ዓይነት የኑክሌር መሣሪያ ከማምረት እና ከማግኘት ሙሉ በሙሉ ትቆጠባለች።። ስማቸው ያልተጠቀሰ አንድ ከፍተኛ የኢራን ባለሥልጣን ይኸው ከአሜሪካ ጋር የተደረገው የረቂቅ ስምምነት ሂደት መቋጫ ማግኘቱን ለሮይተርስ አረጋግጠዋል።

ነገ ሰኔ 7 ቀን የጥገና ሥራ የሚከናወንባቸውና የኃይል አቅርቦት የሚቋረጥባቸው አካባቢዎች ​🕐 ከጠዋቱ 2፡00 – 8፡30 ​አፍንጮ በር መስጊድ፣ ደጃች ውቤ፣ ጊዮርጊስ እሳት አደጋ፣ ችሎት አደባባይ፣ ዘበኛ ሰፈር እና ሾላ፣​ኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት፣ ሰሜን ሆቴል ጫፍ፣ ቀለመወርቅ ት/ቤት፣ ዶሮ ተራ እና ራስ ደስታ አካባቢ፣​አርበኞች ት/ቤት፣ ዕንቁላል ፋብሪካ አደባባይ እና አካባቢያቸው። ​🕐 ከጠዋቱ 2፡00 – 9፡30 ​ጎፋ ካምፕ ኮንዶሚኒየም፣ ጀርመን አደባባይ፣ ጉራጌ ሰፈር፣ ትግሬ ሰፈር እና ካፍ ነዳጅ ማደያ ጀርባ፣​ሀግቤስ አራት መንታ፣ ጎጃም በረንዳ ጫፍ፣ ጅንአድ፣ አበበች ጎበና እና ቄጤማ ተራ ፣​ፓስተር አደባባይ፣ አቤት ሆስፒታል፣ ቅዱስ ዮሐንስ ቤ/ክ፣ ዳትሰን ሰፈር፣ ሰን ሆቴል፣ 3ኛ ፖሊስ ጣቢያ፣ አዲስ አበባ ሜዲካል ኮሌጅ እና አካባቢያቸው። ​🕐 ከጠዋቱ 3፡00 – 9፡30በከፊል እና አከባቢው፦ ድሬ ከአስፋልት በታች፣ ጉዳ፣ ኬላ፣ ጉዮ፣ ታጠቅ ኢንዱስትሪ መንደር (በከፊል)፣ ቶልቻ፣ ሰንጎታ እና ገፋርሳ ሰብስቴሽን ​በአዳማ፦ አዳማ ሆስፒታል፣ ፖስታ ቤት አካባቢ፣ ሁሩታ ከተማ፣ ሰኞ ገብያ እና አካባቢያቸው። ​🕐 ከጠዋቱ 2፡00 – 10፡30በመቀሌ፦ ኢትዮ-ሸዊት ብረት ስራ እና አካባቢዎቻቸው። የኢትዮጵያ ኤሌትሪክ ኃይል አገልግሎት

ሰበር-መረጃ‼️ የኢራን ሰላም ስምምነት ነገ ይፈረማል - ትራምፕ። ስምምነቱ እንደተፈረመ የሆርሙዝ ስርጥ ወዲያውኒ ሙሉ ለሙሉ ይከፈታል ብለዋል። ነገሮች ሲረጋጉ አሜሪካ ወደ ኢራን ገብታ ለኑክሌር የበ
ሰበር-መረጃ‼️ የኢራን ሰላም ስምምነት ነገ ይፈረማል - ትራምፕ። ስምምነቱ እንደተፈረመ የሆርሙዝ ስርጥ ወዲያውኒ ሙሉ ለሙሉ ይከፈታል ብለዋል። ነገሮች ሲረጋጉ አሜሪካ ወደ ኢራን ገብታ ለኑክሌር የበለፀገውን የዩራኒየም አቧራ እንወስዳለን ብለዋል። ከኢራን ጋር አሁን ላይ የተሻለ ግንኙነት አለን ያሉ ሲሆን ከመሬት በታች ምሽግ ደርማሽ ቦንብ በመጣል የሚታወቀውን የአሜሪካ B-2 የጦር አውሮፕላን አመስግነዋል። ነገ የኢራን እና የአሜሪካ አመራሮች በመይነመረብ ስብሰባ ያደርጋሉ፣ፊርማው ኤሌክትሮኒካሊ ይፈረማል። ኢራን አልስማማም ካለች ይህን እድል መቼም እንደማታገኘው አስጠንቅቀዋል።

ይህን ግዙፍ ሀብት በ100 ዓመት ዕድሜ ውስጥ አውድሞ ለመጨረስ በቀን 59.5 ሚሊዮን ዶላር፣ ወይም በየሰዓቱ 2.48 ሚሊዮን ዶላር፣ አልያም በየደቂቃው 41,360 ዶላር ማውጣት ይጠይቃል። በሌላ ስሌ
ይህን ግዙፍ ሀብት በ100 ዓመት ዕድሜ ውስጥ አውድሞ ለመጨረስ በቀን 59.5 ሚሊዮን ዶላር፣ ወይም በየሰዓቱ 2.48 ሚሊዮን ዶላር፣ አልያም በየደቂቃው 41,360 ዶላር ማውጣት ይጠይቃል። በሌላ ስሌት፣ በቀን አንድ ሚሊዮን ዶላር እንኳ ቢወጣ ሀብቱ ለ3,000 ዓመታት ይዘልቃል። በተጨማሪም ይህ ገንዘብ በዓለም ላይ ላለ እያንዳንዱ ሰው ቢከፋፈል እያንዳንዳችን 132 ዶላር መድረስ ይችላል።

ታሪካዊ ክስተት፡ ኢሎን ማስክ የአለማችን የመጀመሪያው ትሪሊየነር (Trillionaire) ሆነ! ይህ ሰው በቃ ሊቆም አልቻለም! የቴስላ እና ስፔስ ኤክስ ባለቤት የሆነው ቢሊየነሩ ኢሎን ማስክ (Elon
ታሪካዊ ክስተት፡ ኢሎን ማስክ የአለማችን የመጀመሪያው ትሪሊየነር (Trillionaire) ሆነ! ይህ ሰው በቃ ሊቆም አልቻለም! የቴስላ እና ስፔስ ኤክስ ባለቤት የሆነው ቢሊየነሩ ኢሎን ማስክ (Elon Musk) የሀብት መጠኑ 1 ትሪሊየን ዶላር በማለፍ በሰው ልጅ ታሪክ የመጀመሪያው ትሪሊየነር መሆን መቻሉ ተሰማ። ይህ ሊሆን የቻለው የጠፈር ምርምር ኩባንያው SpaceX ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ አክሲዮን ገበያ (IPO) በይፋ መግባቱን ተከትሎ የኩባንያው የአክሲዮን ዋጋ በከፍተኛ ሁኔታ በመናሩ ነው። ይህም የኩባንያውን አጠቃላይ ዋጋ ከ2 ትሪሊየን ዶላር በላይ አድርሶታል። ስፔስ ኤክስ "SPCX" በሚል መለያ ስም ወደ አክሲዮን ገበያ የገባ ሲሆን፥ የቀረበው የአክሲዮን ፍላጎት ከተጠበቀው በላይ እስከ 3 እጥፍ በመጨመሩ በታሪክ ትልቁ የገበያ መግቢያ (IPO) መሆን ችሏል። ኢሎን ማስክ በኩባንያው ውስጥ ያለው የ38% ድርሻ ብቻ አሁን ላይ 800 ቢሊዮን ዶላር የደረሰ ሲሆን፥ ይህ ስኬት ከቴስላ ካለው ሀብት ጋር ሲደመር የፎርብስ መጽሔት ማስክን የአለማችን የመጀመሪያው ትሪሊየነር አድርጎ እንዲመዘግበው አስችሎታል። ኢሎን ማስክ ኩባንያው ወደ አክሲዮን ገበያ የገባው ለቀጣይ ትልልቅ ፕሮጀክቶች የሚሆን የፋይናንስ አቅም ለመገንባት መሆኑን ገልጿል። ከነዚህም መካከል የስታርሊንክ የሳተላይት ኢንተርኔት አውታረ መረብን በከፍተኛ ደረጃ ማስፋፋት፣ በጠፈር ላይ የሰው ሰራሽ አስተዋፅኦ (AI) ዳታ ማዕከላትን መገንባት እና በወደፊት የጠፈር ቴክኖሎጂዎች ላይ በሰፊው ኢንቨስት ማድረግ ይገኙበታል። Via The National

በፌስቡክ እና በሌሎች የሜታ (Meta) አገልግሎቶች ላይ መስተጓጎል አጋጠመ! ዛሬ ሰኔ 5 ቀን 2018 ዓ.ም. (June 12, 2026) በዓለም ዙሪያ የሚገኙ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ የፌስቡክ፣ የኢንስታግራም እና የሜሴንጀር ተጠቃሚዎች ከፍተኛ የአገልግሎት መቋረጥ እያጋጠማቸው መሆኑን ሪፖርት እያደረጉ ይገኛሉ። ምን ተከሰተ? ብዙሃኑ ተጠቃሚዎች ከበይነ-መረብ አካውንቶቻቸው በራሱ ጊዜ Log out እየሆኑባቸው ሲሆን፥ ተመልሰው ለመግባት በሚሞክሩበት ወቅትም የሚከተሉትን የስህተት መልዕክቶች እያዩ መሆናቸውን ገልጸዋል፦ - Something went wrong” የሆነ የተሳሳተ ነገር ተከስቷል) *Query error” (የጥያቄ ስህተት) ከተለመደው የፌስቡክ መተግበሪያ በተጨማሪ የ Messenger እና የInstagram አገልግሎቶችም ተመሳሳይ እክል እንደገጠማቸው ታውቋል። ምን ማድረግ ይኖርብዎታል? ችግሩ ከእርስዎ ስልክ ወይም የኢንተርኔት ግንኙነት ጋር የተያያዘ ሳይሆን ከራሱ ከሜታ (Meta) ሰርቨር የመነጨ በመሆኑ፦ 1. አይደናገጡ፦አካውንቴ ተጠለፈ (Hack ተደረገ) ብለው እንዳይሰጉ። 2. ይጠብቁ፦የሜታ የቴክኒክ ባለሙያዎች ችግሩን ቀርፈው አገልግሎቱን ወደ ነበረበት እስኪመልሱ ድረስ በትዕግስት መጠበቅ ብልህነት ነው። Viaጉርሻ Page

ጥቃቱ ተሰርዟል-ትሬምፕ‼️
👉ኢራን ወደ ስምምነት መጥታለች ብለዋል።
ትራምፕ በዛሬው ዕለት ኢራን ላይ ሊፈፀም የነበረውን ከባድ ጥቃት መሰረዛቸውን አስታወቁ። በድርድሩ የመጨረሻ ነጥቦች ላይ መላው የአረብ ሀገራትን ጨምሮ በሁሉም አካላት ተቀባይነት አግኝተዋል ያሉ ሲሆን ከኢራን ጋር የሚደረገው የስምምነት መፈረሚያ ጊዜ እና ቦታ በቅርቡ ይፋ ይሆናል' ብለዋል። ስምምነቱ እስከሚፈረም በኢራን ላይ የተጣለው የባህር ላይ እገዳ ይቀጥላል ብለዋል።

Give me image trump droped bonb in iral
Give me image trump droped bonb in iral

ብዙ ጊዜ በህይወታችን ውስጥ አዳዲስ ነገሮችን ከመሞከር የምንቆጠበው ውድቀትን ፈርተን አይደለም፥ ይልቁንም አሮጌውና የለመድነው መጥፎ ህይወት ስለሚመቸን ነው (Comfortable ስለሆነልን) ነው። አዕምሯችን ሁልጊዜ ከማይታወቅ አዲስ ስኬት ይልቅ፣ የሚታወቅና የለመደውን አሮጌ ስቃይ ይመርጣል። በህይወት ተሞክሮ ውስጥ ትልቅ ለውጥ የሚመጣው፣ ይህንን የለመድነውን የደህንነት ስሜት ጥሰን ስንወጣና አዳዲስ ፈተናዎችን ስንጋፈጥ ብቻ ነው።

433 Crypto ላይ ለ Abdi vote eyasderegu nw ሽልማት አዘጋጅተው

ሰበር ዜና‼️ ኢራን ወደ እስራኤል ሚሳይል ተኮሰች። እስራኤል ኢራን ለምትፈፅመው የሚሳኤል ጥቃት ዝግጁ ነኝ ማለቷን RT ዘግቧል። ሰሜናዊ የእስራኤል ግዛት በኢራን ሚሳይል ኢላማ ተደርጓል።
ሰበር ዜና‼️ ኢራን ወደ እስራኤል ሚሳይል ተኮሰች። እስራኤል ኢራን ለምትፈፅመው የሚሳኤል ጥቃት ዝግጁ ነኝ ማለቷን RT ዘግቧል። ሰሜናዊ የእስራኤል ግዛት በኢራን ሚሳይል ኢላማ ተደርጓል።

የህይወት ወርቃማ ህግ:- መቀየር ባልቻልከው ነገር አትበሳጭ ነገሩን እንዳለ ተቀበለው። የአየሩን ሁኔታ ለመቀየር አንሞክርም ነገርግን በቀላሉ እንዳየሩ ሁኔታ እንለብሳለን። ምርጡ ወንድ 🕴 ➱ ዘወትር
የህይወት ወርቃማ ህግ:- መቀየር ባልቻልከው ነገር አትበሳጭ ነገሩን እንዳለ ተቀበለው። የአየሩን ሁኔታ ለመቀየር አንሞክርም ነገርግን በቀላሉ እንዳየሩ ሁኔታ እንለብሳለን። ምርጡ ወንድ 🕴 ➱ ዘወትር ሌሊት 11:30 ይነሳል ➱ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ያደርጋል ➱ አልጋውን ያነጥፋል ➱ ቤቱን ያፀዳል ➱ በትጋት ይሰራል ➱ አልኮል ንክች አያደርግም ➱ ከኩሽና  አይጠፋም ➱ በየቀኑ ይጸልያል ➱ ያነባል ➱ ምሽት 9:00 አልጋው ላይ ያርፋል ጥያቄ:- እንደዚህ ያለ ምርጥ ወንድ የት ነው የሚገኘው? መልስ:- ማረሚያ ቤት😁

“ኢትዮጽያ ደሀ ሀገር ነች” ኤለን መስክ! ኤለን መስክ ስለ ኢትዮጵያ ያጋራው ነገር በዚህ ሰአት ላይ በጣም መነጋገሪያ ሆኗል። 1 ፖስት ላይ ሼር ያደረገው ኤለን መስክ ኢትዮጵያም ድሃ ሀገር ነች። ኮ
+1
“ኢትዮጽያ ደሀ ሀገር ነች” ኤለን መስክ! ኤለን መስክ ስለ ኢትዮጵያ ያጋራው ነገር በዚህ ሰአት ላይ በጣም መነጋገሪያ ሆኗል። 1 ፖስት ላይ ሼር ያደረገው ኤለን መስክ ኢትዮጵያም ድሃ ሀገር ነች። ኮሎናይዜሽን ሀገራትን ድሃ የሚያደርግ ቢሆን ኢትዮጵያ ሀብታም መሆን ነበረባት፤ ነገር ግን በጣም ድሃ ሀገር ነች። እንደዚሁም ደግሞ ቬትናም በፈረንሳይ ተገዝታለች፤ ነገር ግን አሁን ላይ ሀብታም ሀገር ነች። ስለዚህ ኮሎናይዜሽን ሀገራትን ድሃም ሀብታምም አያደርግም። እንደዚህ አይነት ነንሴንስ ነገር መቆም አለበት የሚለውን ፖስት ያጋራው ኤለን መስክ በኢትዮጵያ ጉዳይ ላይ መነጋገሪያ ሆኗል።

Marrying the right woman is the most important part of building wealth.
Marrying the right woman is the most important part of building wealth.