en
Feedback
አፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ

አፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ

Open in Telegram
5 084
Subscribers
+1124 hours
-157 days
-7730 days
Posts Archive
የአማራን  ፋኖ የትጥቅ ትግልና የህዝብ ተሳትፎን ያጠናከረ ህዝባዊ ውይይት በአንፆኪያ ገምዛ ክላስተር ተካሄደ!!         ሰኔ 27/2018 ዓ.ም። በአንፆኪያ ገምዛ ክላስተር ዋሻ ንገት ቀበሌ የአማራ ፋኖ የትጥቅ ትግልን በማጠናከር እና መሠረተ ልማቶችን ከጥቃት በመጠበቅ ዙሪያ ያተኮረ ሰፊ ህዝባዊ ውይይት ተካሂዷል። በውይይት መድረኩ ላይ የአካባቢው ነዋሪዎች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የአስቴ ጎማ ክፍለጦር አመራሮች እና የአማራ ፋኖ ብሄራዊ ንቅናቄ ወታደራዊ ቃል አቀባይ አርበኛ አበበ ሙላቱን ጨምሮ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ተገኝተዋል። ​በመድረኩ ላይ ማህበረሰቡ ከፋኖ መዋቅር ጎን በፅናት በመሰለፍ እያጋጠሙ ያሉትን የፀጥታና የደህንነት ፈተናዎች በተደራጀ መንገድ ሊመክት እንደሚገባ የፋኖ አመራሮች አሳስበዋል። በተለይም በከሚሴ (ምድረገኝ) ዙሪያ እየተስተዋለ ያለውን የወረራ እንቅስቃሴ ለመከላከል፣ ማህበረሰቡ ከፋኖ ጋር በመቀናጀት የአካባቢውን ደህንነት በዘላቂነት ለማስጠበቅ ዝግጁ እንዲሆን ሰፊ ግንዛቤ ተፈጥሯል። ​ከፀጥታ ጉዳዮች ባለፈ የልማትና የመሠረተ ልማት ጥበቃ ጉዳይም የውይይቱ አካል ነበር። ነባር የህዝብ መገልገያ ተቋማትን ከማንኛውም ውድመትና ዝርፊያ በባለቤትነት ስሜት መጠበቅ እንደሚገባ የተገለጸ ሲሆን፤ ህዝቡና ፋኖ አቅማቸውን በማስተባበር አዳዲስ የልማት ስራዎችን ማከናወን በሚችሉበት መንገድ ላይም ተመክሯል። ​በሌላ በኩል የአካባቢው አርሶ አደር የዕለት ተዕለት የግብርና ስራውን ከህዝባዊ የትጥቅ ትግሉ ጋር አቀናጅቶ ማስኬድ እንዳለበትና፣ የሰላም እሴቶችን በመጠቀም አካባቢውን ነቅቶ መጠበቅ እንደሚኖርበት አቅጣጫ ተቀምጧል። ​መድረኩ ቀጠናውን በከፍተኛ ሁኔታ እየፈተነ ባለው የወጣቶች ስደት ዙሪያ ላይም በሰፊው መክሯል። ወጣቶች አደገኛ ከሆነው ስደት በመቆጠብ፣ ሀገር ጥለው እንዲሰደዱ ምክንያት የሆነውን ጨቋኝ ስርአት በትጥቅ ትግሉ በመሳተፍ መታገል እንጂ ስደት አማራጭ ሊሆን እንደማይገባ ተመላክቷል። ​በማጠቃለያውም የአማራ ፋኖ ብሄራዊ ንቅናቄ ወታደራዊ ቃል አቀባይ አርበኛ አበበ ሙላቱ፤ ማህበረሰቡ ለትግሉና ለአካባቢው ህልውና እያደረገ ላለው ከፍተኛ አስተዋጽኦ ምስጋና አቅርበዋል። አክለውም በመድረኩ የተቀመጡ አቅጣጫዎችን ወደ ተግባር በመቀየር ድልን በአስተማማኝ ሁኔታ ለማስቀጠል ሁሉም የድርሻውን እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል። ክብርና ሞገስ ለትግሉ ሰማዕታት!!   ድል ለአፋብን!!  ድል ለአማራ ህዝብ!!  ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!    ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!! የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ      ሰኔ 27/2018 ዓ.ም።

ዓፄ ዳዊት ክፍለ ጦር በመርሀቤቴ አውራጃ በሬማ ከተማ በፈፀመው ልዩ ኦፕሬሽን ጠላት ሲደመሰስ፥ ጠላት ንፁሀንን ደብድቦ ረሸነ!!      ሰኔ 27 ቀን 2018 ዓ.ም የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ዓፄ አምደጽዮን ኮር ዓፄ ዳዊት ክፍለ ጦር በትጥቅ ትግሉ መስመር ወታደራዊ የበላይነትን እያረጋገጠ የሚገኘው የፋኖ ኃይል፣ በመርሀቤቴ አውራጃ በምትገኘው ሬማ ከተማና ዙሪያዋ ላይ ድንቅ የተቀናጀ ወታደራዊ ኦፕሬሽን መፈጸሙን የዓፄ አምደጽዮን ኮር ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ክፍል አስታወቀ። ትላንት ሰኔ 26 ቀን 2018 ዓ.ም በአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ስር የሚንቀሳቀሰው የዓፄ ዳዊት ክፍለ ጦር፣ የአገዛዙ ወታደራዊ አቅም መገለጫ ነው በሚባለው 101ኛ አየር ወለድ ክፍለ ጦር ላይ ያነጣጠረ ጠንካራ ጥቃት ሰንዝሯል። ከቀኑ 6:00 ጀምሮ እስከ ምሽቱ 12:00 ሰዓት ድረስ ለተከታታይ ስድስት ሰዓታት በዘለቀውና በፋኖ ከፍተኛ አመራሮች በተመራው በዚህ የአውደ ውጊያ ኦፕሬሽን፣ የፋኖ ሰራዊት ወራሪውን ኃይል ሙሉ በሙሉ ከበባ ውስጥ በማስገባት ስልታዊ የበላይነትን ተቀዳጅቷል። የክፍለ ጦሩ አናብስቶች በአራዲት ቀበሌ፣ በቆሮ፣ በአፈር ባይኔ ቀበሌ እንዲሁም በከተማዋ ሰሜን አቅጣጫ በጠጠር አምባ መስመር በኩል ወደ መሀል ከተማ በመዝለቅ በፈጸሙት የተቀናጀ ጥቃት፦ ከ 17 በላይ የሚሆኑ የ101ኛ አየር ወለድ ክፍለ ጦር (ቀይ ቦኔት ለባሽ) አባላት ሙሉ በሙሉ ተደምስሰዋል። በርካታ ቁጥር ያላቸው የጠላት ኃይሎች መቁሰላቸውንና ከፍተኛ ወታደራዊ፣ ቁሳዊና ሰብአዊ ኪሳራ ማስተናገዳቸውን የግንባ መረጃዎቻችን አረጋግጠዋል። ይሁን እንጂ በአውደ ውጊያው አይቀሬ ሽንፈት የገጠመውና በፋኖ ክንድ የደነገጠው የአገዛዙ ኃይል፣ የተለመደውን የጦር ወንጀል በንፁሃን ዜጎች ላይ በመፈጸም ፀረ-ሕዝብነቱን  አሳይቷል። በመደበኛ ስራው ላይ የነበረውን የአፈር ባይኔ ቀበሌ ነዋሪ ወጣት ሀብታሙ በላይሁን የመከላከያ ዩኒፎርም በማልበስና የሀሰት ድራማ በመስራት በአሰቃቂ ሁኔታ የረሸኑት ሲሆን፣ በሬማ ከተማ መንገዶች፣ ግሮሰሪዎችና የህዝብ መሰብሰቢያዎች የነበሩ ንፁሃን ዜጎች ላይም የፈሪ በትራቸውን በማሳረፍ ከፍተኛ ድብደባ ፈጽመዋል። የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ይህንን ወታደራዊ ድል በማብሰር፣ በትጥቅ ትግሉ መስመር የሕዝብን ህልውና በተባበረ ክንድ የማስከበሩ ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥልና ለሰማዕታት የሚገባው ክብር ሁሉ እንደሚሰጥ በፅኑ አረጋግጧል። "ክብር ለትግሉ ሠማዕታት! "ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ!!

አፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ወቅታዊ መግለጫ! ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯"""""""""¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ​“የአማራን ሕዝብ በሴራና በክህደት የማንበርከክ ዕቅድ በቆራጥነት ይመከታል‼” ​ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ፣ በተለይም ለተከበርከው የአማራ ሕዝብ ገዥው ሥርዓት የአማራን ሕዝብ የህልውና ትግል ለማደናቀፍ በሃይልም ሆነ በውስጥ ሴራ ለማዳከም ሌት ከቀን እየሰራ መሆኑ ይታወቃል። ​የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የስርዓቱን አጠቃላይ #የክረምት ስልታዊ ዕቅድና የወታደራዊ ቅኝት እንቅስቃሴን በጥብቅ በመከታተል፣ መረጃዎችን አደራጅቶ ለፀጥታ መዋቅሩና ለሕዝቡ የሚከተለውን ወቅታዊ መግለጫና ጥሪ ያቀርባል። 👉 ​1. ለፀጥታ ኃይሉ (ሚሊሻ፣ ፖሊስና ሰላም አስከባሪ) የቀረበ አጣዳፊ የህልውና ጥሪ፦ ባለፉት ሁለት ቀናት ውስጥ የአማራ ክልል ፀጥታ ቢሮ ም/ኃላፊ አቶ ደጀኔ ልመንህ የሰ/ሸዋ ዞን እና ደ/ብርሀን ሜትሮ ፖሊታን ከተማ የብልፅግና ካድሬን አስቸኳይ ስብሰባ ጠርቶ  ያስተላለፈው ውሳኔ፣ ከሰሜን ሸዋ  ከየወረዳ የሚውጣጣ 370 ከደ/ብርሀን 150 በድምሩ=520 ፖሊስ፣ ከሰሜን ሸዋ ከየወረዳ የሚውጣጣ 1700 እና ከደ/ብርሀን 800 በድምሩ =2500 ሚኒሻ በአጠቃላይ ከ3000 በላይ ሚኒሻና ፖሊስ ከነ ሙሉ ትጥቁ ተመልምሏል። ይህ ፕሮግራም በአማራ ክልል በሁሉም ዞኖች የሚደረግ ሲሆን የምስራቅ አማራው ቡርቃ፣ የጎንደር ፣ የጎጃም በሚል በሶስት ማእከል ሰልጥኖ ካጠናቀቀ በኋላ ከመከላከያ ጋር ተፐውዞ በራሱ ማህበረሰብ ላይ ሊዘምት መዘጋጀቱን ከውስጥ የመረጃ ምንጫችን አረጋግጠናል። ​መልእክታችን ወንድሞቻችን የሆናችሁ የሚሊሻ፣ የፖሊስና የሰላም አስከባሪ አባላት! በእናንተ ላይ የተጣለባችሁ “ወደ ስልጠና ማዕከላት ገብቶ የመሰልጠን” አስገዳጅ ትዕዛዝ፣ ዓላማው እናንተን ለማብቃት ሳይሆን በገዛ ወገኖቻችሁ ላይ እንድትዘምቱና ለወንድማማች የዘር ፍጅት እርስ በእርስ እንድትጨራረሱ የተደገሰላችሁ የሞት ወጥመድ መሆኑን ከወዲሁ እንድትገነዘቡት እንፈልጋለን። ሥርዓቱ የራሱን ዕድሜ ለማራዘም እናንተን እንደ ጭዳ ከፊት አሰልፎ በገዛ እናትና አባቶቻችሁ፣ በገዛ ወንድሞቻችሁ ላይ ሊያዘምታችሁ ቆርጦ ተነስቷል። ​ስለሆነም ለዚህ እኩይና የክህደት ተግባር ፍጹም ተባባሪ እንዳትሆኑ ይህንን የጥፋት መዋቅርና የስርዓቱን ሰንሰለት በመበጠስ ከወዲሁ በመውጣት ወደ ወገን ዘመዳችሁ፣ የአብራካችሁ ክፋይ ወደሆነው የፋኖ ኃይልና ወደ ሕዝባችሁ እንድትቀላቀሉ #ጥሪ እናቀርባለን። ሕዝባችሁና የህዝብ ልጅ የሆነው ፋኖ ሁልጊዜም እቅፋቸውን ከፍተው ሊቀበሏችሁ ዝግጁ ናቸው። 👉 ​2. በሴራና በገንዘብ የህልዉና ታጋዩን የመከፋፈል ሙከራን በተመለከተ፦ የጠላት ቀጣይ ዕቅድ በቢሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ በመመደብ በፋኖ የድርጅት የኮር አመራሮችና በታችኛው መዋቅር ውስጥ ሰርገው የሚገቡ ሰላዮችን በመመልመል በመካከላችን ጥርጣሬንና መከፋፈልን መፍጠር እንደሆነ በግልጽ አውቀነዋል። #መልእክታችን ፦ የአሳምነው ዕዝ አመራሮችና የፋኖ አባላት ከመቼውም ጊዜ በላይ የተሳሰሩና የአማራን ሕዝብ ጥያቄ በፅናት የሚያስከብሩ እንጂ በገንዘብ የማይደለሉ መሆናቸውን እናረጋግጣለን። በውስጣችን ሰርጎ ገቦችን ለመለየትና የጠላትን የውስጥ ሴራ ለማክሸፍ የደህንነት መዋቅራችን በንቃት እየሰራ ይገኛል። 👉 ​3. የአመራሮችን እንቅስቃሴ ለይቶ የማጥቃት ስልትን በተመለከተ፦ ​ ጠላት የፋኖ አመራሮች የሚያድሩበትንና የሚንቀሳቀሱበትን ቦታዎች በመለየት ከፍተኛ መስዋዕትነት ከፍሎም ቢሆን ከበባ በማድረግ የመግደልና በቅርብ ሰዎቻቸው የማስመታት ጥቁር ዕቅድ ቀርጿል። #መልእክታችን፦ ለሁሉም የዕዛችን አመራሮችና ታችኛው መዋቅር ጥብቅ የወታደራዊና የደህንነት ጥንቃቄ እንዲያደርጉ መመሪያ አስተላልፈናል። የአንድ አመራር መውደቅ ትግሉን እንደማያቆመው ጠላት ሊያውቀው ይገባል። ይልቁንም ይህ ዓይነቱ የጭካኔ ዕቅድ ይበልጥ እንድንጠነክርና እንድንደራጅ ያደርገናል። 👉 ​4. በስርዓቱ መዋቅር ውስጥ ያሉ ደጋፊዎቻችንን የማጽዳት ዘመቻ፦ ስርዓቱ በመዋቅሩ በፖለቲካ አመራሩና በባለሀብቱ ውስጥ ለፋኖ መረጃና ሎጂስቲክስ የሚያቀርቡትን የውስጥ አርበኞች የማሰርና የማጥፋት ዘመቻ ለመጀመር አቅዷል። #መልእክታችን፦ ከጎናችን ለቆማችሁና መረጃ ለምታቀብሉን የቁርጥ ቀን የአማራ ልጆች በሙሉ፦ ጠላት ሊያደርግ የሚችለውን አፈና በመገመት ከፍተኛ ጥንቃቄ እንድታደርጉና የደህንነት አሠራራችሁን እንድትቀይሩእናሳስባለን።                                                                               ክብር ለትግሉ ሰማዕታት!       ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! ✊ ​አፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሰኔ 26 ቀን 2018 ዓ.ም

​በአንፆኪያ ገምዛ የፋኖን ወቅታዊ ቁመናና የትግሉን ገፊ ምክንያቶች የገመገመ ታላቅ የህዝብ መድረክ ተካሄደ!! ​     ሰኔ 26 ቀን 2018 ዓ.ም። በይፋትና ጥሙጋ አውራጃ፣ አንፆኪያ ገምዛ ክላስተር፣ በአሰለሌ ቀለበት ወንበር ቀበሌ የፋኖን ወቅታዊ የትግል ቁመና እና ወቅታዊ የጠላትን አቋም የገመገመ ታላቅ የህዝብ ስብሰባ ተካሂዷል። "በአንፆኪያ ገምዛ ክላስተር የፋኖ ወቅታዊ ቁመና እና የትግሉ ገፊ ምክንያቶች" በሚል መሪ ቃል በተካሄደው በዚህ መድረክ ላይ የአካባቢው ማህበረሰብ በነቂስ ወጥቶ ተሳትፏል። ​በመድረኩ ላይ የአፋብን ወታደራዊ ቃል አቀባይ አርበኛ አበበ ሙላቱ፣ የመሀመድ ቢሆነኝ ኮር እና የአስቴ ጉማ ተራራ ክፍለጦር ከፍተኛ አመራሮች እንዲሁም የቀጠናው ህዝባዊ አስተዳደር ሃላፊዎች ተገኝተዋል። ​በዕለቱ በተካሄደው ሰፊ ውይይት የትግሉ መነሻ የሆኑ መሰረታዊ ገፊ ምክንያቶች በዝርዝር ቀርበዋል። የመሀመድ ቢሆነኝ ኮር ወታደራዊ ቃል አቀባይ ፋኖ መምህር መንግስቱ፤ አገዛዙ በአንፆኪያ ገምዛ ቀጠና ላይ አቅዶና አስልቶ ያደረሰውን ዘርፈ-ብዙ ጥፋት በማንሳት ለማህበረሰቡ ማብራሪያ ሰጥቷል። ​የአፋብን ወታደራዊ ቃል አቀባይ አርበኛ አበበ ሙላቱ በበኩሉ፣ የፋኖን ወታደራዊ ግስጋሴና በየግንባሩ የተመዘገቡ ድሎችን አብራርቷል። በተለይም "በዘመቻ አንሻ ሰይድ" አማካኝነት በአካባቢው ሊከናወን የታሰበውን ምርጫ ሙሉ በሙሉ ማስተጓጎል መቻሉ የትግሉ ትልቅ ስኬት መሆኑን ገልጾ፤ በአንጻሩ የጠላት ጦር መዋቅር እየፈረሰና ኃይሉ በየግንባሩ እየተበተነ መምጣቱን አስታውቋል። ​ይህ ህዝባዊ መድረክ የትግሉን ቀጣይ አቅጣጫዎች ከማስቀመጥ ባለፈ፣ ማህበረሰቡ ለነፃነት ትግሉ እያደረገ ያለውን አስተዋፅኦ ያበረታታበት ነበር። አርበኛ አበበ ሙላቱ በቁርጠኝነታቸው ለሌሎች አርአያ የሆኑ ግለሰቦችን መርጦ ልዩ የዕውቅና ሽልማት አበርክቷል። ​ከዚህ በተጨማሪም በትግሉ ነፃ የወጡ አካባቢዎችን ሰላምና ደህንነት በአስተማማኝ ሁኔታ ለመጠበቅና የህዝብ አገልግሎትን ለማስቀጠል የሚያስችል አዲስ የቀበሌ መዋቅርና የአስተዳደር አመራሮች ሹመት በይፋ ተከናውኗል። ​በመድረኩ ማጠቃለያ ላይ አርበኛ አበበ ሙላቱ ባደረገው ንግግር፣ የፋኖ የትግል ጉዞ በታላቅ ድል እንደሚጠናቀቅ በልበ-ሙሉነት ገልጿል። ​"የአንድነታችን ውጤት ወደፊት በስራ እና በተግባር የምናየው ይሆናል" በማለት የህዝብና የፋኖ የጋራ ክንድ ያለውን የጎላ ሚና ያብራራው አርበኛው፤ ለአሰለሌ ቀለበት ወንበር ቀበሌ ህዝብም "ጠንካራ ናችሁ በርቱ" በማለት የላቀ ምስጋናውንና አክብሮቱን አቅርቧል። ክብርና ሞገስ ለትግሉ ሰማዕታት!!   ድል ለአፋብን!!  ድል ለአማራ ህዝብ!!  ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!    ስር-ነቀል ለውጥ በተባበረ ክንዳችን!! የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ  ሰኔ 26 ቀን 2018 ዓ.ም።

​በአንፆኪያ ገምዛ የፋኖን ወቅታዊ ቁመናና የትግሉን ገፊ ምክንያቶች የገመገመ ታላቅ የህዝብ መድረክ ተካሄደ!! ​     ሰኔ 26 ቀን 2018 ዓ.ም። በይፋትና ጥሙጋ አውራጃ፣ አንፆኪያ ገምዛ ክላስተር፣ በአሰለሌ ቀለበት ወንበር ቀበሌ የፋኖን ወቅታዊ የትግል ቁመና እና ወቅታዊ የጠላትን አቋም የገመገመ ታላቅ የህዝብ ስብሰባ ተካሂዷል። "በአንፆኪያ ገምዛ ክላስተር የፋኖ ወቅታዊ ቁመና እና የትግሉ ገፊ ምክንያቶች" በሚል መሪ ቃል በተካሄደው በዚህ መድረክ ላይ የአካባቢው ማህበረሰብ በነቂስ ወጥቶ ተሳትፏል። ​በመድረኩ ላይ የአፋብን ወታደራዊ ቃል አቀባይ አርበኛ አበበ ሙላቱ፣ የመሀመድ ቢሆነኝ ኮር እና የአስቴ ጉማ ተራራ ክፍለጦር ከፍተኛ አመራሮች እንዲሁም የቀጠናው ህዝባዊ አስተዳደር ሃላፊዎች ተገኝተዋል። ​በዕለቱ በተካሄደው ሰፊ ውይይት የትግሉ መነሻ የሆኑ መሰረታዊ ገፊ ምክንያቶች በዝርዝር ቀርበዋል። የመሀመድ ቢሆነኝ ኮር ወታደራዊ ቃል አቀባይ ፋኖ መምህር መንግስቱ፤ አገዛዙ በአንፆኪያ ገምዛ ቀጠና ላይ አቅዶና አስልቶ ያደረሰውን ዘርፈ-ብዙ ጥፋት በማንሳት ለማህበረሰቡ ማብራሪያ ሰጥቷል። ​የአፋብን ወታደራዊ ቃል አቀባይ አርበኛ አበበ ሙላቱ በበኩሉ፣ የፋኖን ወታደራዊ ግስጋሴና በየግንባሩ የተመዘገቡ ድሎችን አብራርቷል። በተለይም "በዘመቻ አንሻ ሰይድ" አማካኝነት በአካባቢው ሊከናወን የታሰበውን ምርጫ ሙሉ በሙሉ ማስተጓጎል መቻሉ የትግሉ ትልቅ ስኬት መሆኑን ገልጾ፤ በአንጻሩ የጠላት ጦር መዋቅር እየፈረሰና ኃይሉ በየግንባሩ እየተበተነ መምጣቱን አስታውቋል። ​ይህ ህዝባዊ መድረክ የትግሉን ቀጣይ አቅጣጫዎች ከማስቀመጥ ባለፈ፣ ማህበረሰቡ ለነፃነት ትግሉ እያደረገ ያለውን አስተዋፅኦ ያበረታታበት ነበር። አርበኛ አበበ ሙላቱ በቁርጠኝነታቸው ለሌሎች አርአያ የሆኑ ግለሰቦችን መርጦ ልዩ የዕውቅና ሽልማት አበርክቷል። ​ከዚህ በተጨማሪም በትግሉ ነፃ የወጡ አካባቢዎችን ሰላምና ደህንነት በአስተማማኝ ሁኔታ ለመጠበቅና የህዝብ አገልግሎትን ለማስቀጠል የሚያስችል አዲስ የቀበሌ መዋቅርና የአስተዳደር አመራሮች ሹመት በይፋ ተከናውኗል። ​በመድረኩ ማጠቃለያ ላይ አርበኛ አበበ ሙላቱ ባደረገው ንግግር፣ የፋኖ የትግል ጉዞ በታላቅ ድል እንደሚጠናቀቅ በልበ-ሙሉነት ገልጿል። ​"የአንድነታችን ውጤት ወደፊት በስራ እና በተግባር የምናየው ይሆናል" በማለት የህዝብና የፋኖ የጋራ ክንድ ያለውን የጎላ ሚና ያብራራው አርበኛው፤ ለአሰለሌ ቀለበት ወንበር ቀበሌ ህዝብም "ጠንካራ ናችሁ በርቱ" በማለት የላቀ ምስጋናውንና አክብሮቱን አቅርቧል። ክብርና ሞገስ ለትግሉ ሰማዕታት!!   ድል ለአፋብን!!  ድል ለአማራ ህዝብ!!  ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!    ስር-ነቀል ለውጥ በተባበረ ክንዳችን!! የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ  ሰኔ 26 ቀን 2018 ዓ.ም።

የሸዋሮቢት ሰማዕታት 4ኛ አመት መታሰቢያ ! ይህ ቀን በታሪክ ማህደር ውስጥ በደምና በእንባ የተጻፈ፣ ነገር ግን የነጻነትና የጽናት ትልቅ ማሳያ የሆነ ታሪካዊ እለት ነው። የሸዋሮቢት ወጣቶችና መላው ህዝብ ያደረጉት ህዝባዊ እምቢተኝነት፣ የአማራን ህዝብ ህልውና ለማስከበር ለተቀጣጠለው የፀረ-ብልፅግና አብዮታዊ የትግል ጅማሮ ትልቅ መሰረት የጣለ የቁርጠኝነት ምዕራፍ ነው። በእለቱ ምንም አይነት መሳሪያ ሳይይዙ፣ በባዶ እጃቸው ለክብራቸው አደባባይ የወጡት የሸዋሮቢት ወጣቶች የከፈሉት የህይወት መስዋዕትነት የክፋትንና የጭካኔን ጥግ ለዓለም ያሳየበት ክስተት ነው። የታጠቁ የመንግስት ኃይሎች በገዛ ወገኖቻቸው ላይ የጭካኔ ምላጭ ሲስቡ፣ እነዚህ ወጣቶች ግን ለአላማቸው ፍርሃትን አሸንፈው በጽናት ቆመዋል። ህይወታቸው በአሰቃቂ ሁኔታ የተቀጠፈበት ያ እለት፣ ለገዳዮቻቸው የሞራል ሽንፈትን፣ ለህዝባዊ ትግሉ ደግሞ አዲስ ወታደራዊና ፖለቲካዊ ንቃተ-ህሊናን የሰጠ የታሪክ አዙሪት ሆኗል። ይህ አሳዛኝ ክስተት የገዥው ፓርቲ ጉዳይ አስፈጻሚ የነበረው የብአዴን (የአሁኑ አማራ ብልፅግና) የፖለቲካ ውድቀትና የ"ቤት ባሪያነት" አስተሳሰብ ፍንትው ብሎ የታየበት ነው። የገዛ ህዝብን ጥቅም ማስከበርና ከጥቃት መከላከል ሲገባው፣ የጌቶቹን ስልጣን ለማርዘምና ፍላጎት ለማስፈጸም ሲል የገዛ ህዝቡን ለጥቃት አሳልፎ የሰጠበት፣ በቁጭት የሚታወስ ጥቁር ጠባሳ ነው። ይህ የባርነት ስነ-ልቦና የወለደው ጭካኔ የህዝብን የፍትህ፣ የእኩልነትና የህልውና ጥያቄ በኃይል ለመደፍጠጥ የተደረገ አሳፋሪ ሙከራ ነበር። የሸዋሮቢት ህዝባዊ ትግልና የንጹሃን ደም መፍሰስ በከንቱ አልቀረም። ይልቁኑም በትውልዱ ውስጥ ከፍተኛ ቁጭትንና እልህን በመውለድ፣ የአማራ ህዝብ ዛሬ ለደረሰበት ሁለንተናዊ የህልውና እና የትጥቅ ትግል እንደ ትልቅ መነሻ ሆኖ አገልግሏል። ዛሬ ያ ቀን ሲታወስ በሀዘንና በልቅሶ ብቻ ሳይሆን፣ የጀመሩትን አላማ ዳር ለማድረስ ቃል ኪዳናችንን በማደስ ነው። ክንዶቼ ነፍሳችሁ ትረፍ ! አማራ ያሸንፋል።

የጀግናው አርበኛ አበባው ሠለሞን 1ኛ ዓመት መታሰቢያ መርሐ-ግብር ​ ሰኔ 24/2018 ዓ.ም ​የጀግናው አርበኛ አበባው ሠለሞን 1ኛ ዓመት መታሰቢያ መርሐ-ግብር በዛሬው ዕለት በደመቀ ሁኔታ ተካሂዷል። በመርሐ-ግብሩ ላይ የጀግናው ሁለገብ የሜዳ ላይ ተጋድሎ፣ የነበረው የላቀ የፖለቲካ ብስለት እና በትግሉ ውስጥ የነበረው የፊት አውራሪነት ሚና በሰፊው ተዘክሯል። ​ ​በዚህ የሰማዕቱ አርበኛ አበባው ሠለሞን የክብር መታሰቢያ ዕለት ላይ የአፋብን ከፍተኛ አመራሮች እንዲሁም የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ እና የአፄ ዘረያዕቆብ ፩ ኮር አመራሮች የተገኙ ሲሆን የአፄ ይኩኖ አምላክ ክፍለ ጦር ​ የሠራዊት አባላትም በፕሮግራሙ ታድመዋል። ​በመድረኩ ላይ በመገኘት ንግግር ያደረገው የአፋብን ወታደራዊ ቃል አቀባይ አርበኛ አበበ ሙላቱ፣ ለአርበኛ አበባው ሠለሞን ያለውን ጥልቅ አክብሮትና የትግል አጋርነት በመግለጽ ለተሰበሰበው አመራርና የሠራዊት አባል ብርቱ የትግል መልዕክት አስተላልፏል። ​"ጀግኖቻችን በአካል ቢለዩንም አልሞቱም፤ ሕዝባቸውን ከጭቆና እና ከበደል ነፃ ለማውጣት በሠሩት ታሪክ እና በከፈሉት የክብር መስዋዕትነት ሁሌም በልባችን ሕያው ሆነው ይኖራሉ።" ​አርበኛው አክሎም አሁን ስላለው የትግል ምዕራፍና ታሪካዊ ኃላፊነት ሲያብራራ "እኛ ዛሬ በሕይወት ያለነው አመራሮችና ታጋዮች፣ እነሱ የተሠዉለትን ታላቅና ቅዱስ ዓላማ ከዳር ለማድረስ ቃላችንን የምናድስበት ዕለት ነው። ለአማራ ሕዝብ ሕልውና እና መብት ስንል የማይተካ ነፍሳችንን ለመስጠት ምንጊዜም ዝግጁ መሆን አለብን" በማለት የቁርጠኝነት ጥሪ አቅርቧል። ​የአርበኛ አበባው ሠለሞን ታሪካዊ ሚና ​በዕለቱ እንደተገለጸው፣ አርበኛ አበባው ሠለሞን የጦር ሜዳ አርበኛ ብቻ አልነበረም። ​ሕዝብን በማደራጀት ረገድ ግንባር ቀደም መሪ መሆኑ፣ ​ትግሉን በማጠናከር እና መዋቅሩን በመገንባት ያሳየው ብቃት፣ ​በማስተባበር ረገድ የነበረው የፊት አውራሪነት ሚና የጎላ ነው። ክብር ለትጥቅ ትግሉ ሰማዕታት!! ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!! የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ

የአርበኛ አበባው ሰለሞን 1ኛ ዓመት መታሰቢያ:የህልውና ትግል አሻራና የማይጠፋው የነፃነት ታሪክ          ሰኔ 24/2018 ዓ.ም የአማራን ህዝብ ህልውና ለማረጋገጥና ጠላትን በትጥቅ ትግል ድል ለማድረግ በተካሄደው መራራ የምድር ላይ ተጋድሎ ውስጥ፣ ስማቸው በወርቅ ቀለም ከሚፃፉ ግንባር ቀደም የጦር መሪዎች መካከል አንደኛው አርበኛ አበባው ሰለሞን ነው። የቀድሞው የሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ ከፍተኛ ወታደራዊ አመራር የነበረው አርበኛ አበባው፣ በትጥቅ ትግሉ ታሪክ ውስጥ ታላቅ ስልታዊ  አሻራ ጥሎ ያለፈ እውነተኛ የህዝብ አለኝታ ነው። አርበኛ አበባው ሰለሞን በየቀጠናው ተበታትነው የነበሩ ብርጌዶችንና ክፍለጦሮችን በማቀናጀትና በአንድ ወታደራዊ ዕዝ ስር በማሰባሰብ፣ የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝን በፅኑ መሰረት ላይ ካቆሙት ቀዳሚ የጦር ስትራቴጂስቶች አንዱ ነበር። በትጥቅ ትግሉ ውስጥ ወታደራዊ ዲሲፕሊን፣ የወንድማማችነትና የአንድነት መንፈስ እንዲሰፍን በሁሉም የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አውራጃዎችና የጦር ግንባሮች እየተዘዋወረ፣ የህዝቡንና የሰራዊቱን የፖለቲካ-ወታደራዊ ንቃትና ዝግጁነት በማሳደግ ረገድ የማይተካ ሚና ተጫውቷል። በተለይም አማራ ለጋራ ህልውናው በጋራ እንዲቆም ከፍተኛ ጥረት ያደረገው ይህ ጀግና፣ በሸዋ ጠቅላይ ግዛት መርሐቤቴ አውራጃ በራስ አበበ አረጋይ የትውልድ ቀዬ ሞረትና ጅሩ የጀግናው መታሰቢያ በደመቀ ሁኔታ ተከብሮ ውሏል። ከሁሉም በላይ ወጣቱን የህብረተሰብ ክፍል በደፈጣ ውጊያና በትጥቅ ትግል ስልቶች በማደራጀት፣ ለአማራ ህዝብ ነፃነትና ክብር ግንባር ቀደም ተዋጊ ሆኖ እንዲሰለፍ በአካልም ሆነ በስነ-ልቦና (Military Psychology) በማሰልጠን፣ ለነፃነት የሚጋደል ቆራጥና ታጣቂ ትውልድ በመቅረጽ በኩል ግንባር ቀደም መሃንዲስ ነበር። ለቆመለት የትጥቅ ትግል ዓላማና ለተሰለፈለት ህዝብ ህልውና ቀን ከሌሊት በዱር በገደሉ ሳይታክት የደከመው አርበኛ አበባው ሰለሞን፣ አማራን በጦር ሜዳ ድል ለማውጣት በተጓዘበት የእውነተኛ ጉዞ ላይ እጅግ አሳዛኝ ክስተት ገጥሞት፣ ከጀርባው በተተኮሰ የከዳተኞች ጥይት ሰኔ 24/2017 ዓ.ም ውድ ህይወቱን በጦር ሜዳ ሰማዕትነት አሳልፎ ሰጥቷል። ይህንንም ዕለት የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሲያከብር፣ ጀግናው የተሰዋለትን ቅዱስ የትጥቅ ትግል ዓላማና ወታደራዊ ግብ ከእቅዱ ለማድረስ ቃል ኪዳን የማደሻና ክንድ የማጠናከሪያ መንገድ ጭምር በማድረግ ነው። ዛሬ እሱ በሰማዕትነት ያለፈበትን 1ኛ ዓመት ስንዘክር፣ እርሱ የጀመረውን ቅዱስ የነፃነት ተጋድሎ እስከ የመጨረሻው ድል ድረስ ለማስቀጠል ቃላችንን በአንድነትና በጦርነት ወኔ በማደስ ጭምር ነው። "አርበኛ አበባው ሰለሞን፤ ስምህ በታሪክ ማህደር፣ የጀግንነት ስራህ በትውልዱ የትግል ልብ ውስጥ ለዘላለም ይኖራል።"    "ክብር ለትጥቅ ትግሉ ሰማዕታት!   "ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! አፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

+4
የቀድሞው የሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ ከፍተኛ አመራር፣ የትግሉ ፈር ቀዳጅና የህዝብ አለኝታው፡ የአርበኛ አበባው ሰለሞን አንደኛ ዓመት መታሰቢያ🕯️🕯️ ሰኔ 24/2018 ዓ.ም የአማራን ህዝብ ህልውና ለማረጋገጥና ነፃነቱን ለማወጅ በተደረገው መራራ ትግል ውስጥ፣ ስማቸው በወርቅ ቀለም ከሚፃፉ ግንባር ቀደም የቁርጥ ቀን ልጆች መካከል አንደኛው የቀድሞው የሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ ከፍተኛ አመራር የነበረው አርበኛ አበባው ሰለሞን ነው። በየቀጠናው፣ የነበሩ ብርጌዶችንና ክፍለጦሮችን በማሰባባሰብ የሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝን መስራችና ትግሉ ላይ የአንድነትና የወንድማማችነት መንፈስን በማላበስ የራሱን አሻራ አሳርፏል። አርበኛ አበባው ሰለሞን በሁሉም የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አውራጃዎች እየተዘዋወረ፣ የህዝቡን የፖለቲካ ንቃት የፈጠረና ወገኑ ለጋራ ህልውናው እንዲታገል መንገድ የጠረገ እውነተኛ የህዝብ ልጅ ነው፣ ወጣቱን አሰባስቦ ለአማራ ህዝብ ነፃነት ከፊት ቀድሞ ይዋደቅ ዘንድ በአካልም በስነ-ልቦናም እያሰለጠነ ለነፃነት የሚጋደል ቆራጥ ትውልድ በመቅረጽ ትልቅ አሻራ ጥሎ አልፏል። ለቆመለትና ለተሰለፈለት የአማራ ህዝብ ህልውና ትግል ቀን ከሌሊት ደፋ ቀና ሲል የኖረው ሰማዕቱ አርበኛ አበባው ሰለሞን በመጨረሻም አማራን ነፃ ለማውጣት በተጓዘበት የሀቅ መንገድ ላይ ልክ እንደነ አክሊሉ ሀብተወልድ በከሃዲዎች ከጀርባው ተወግቶ አንድያ ነፍሱን ለሚወደውና ለደማለት፣ ብዙ መሰዋዕትነትን ለከፈለለት አማራ፣ ለተንከራተተለት ህዝቡ አንድያ ነፍሱን መስዋዕት አደረገ። አርበኛ አበባው ሰለሞን በአካል ቢለየንም ዛሬ ሰኔ 24/2018 ዓ.ም በከሀዲዎች በትር የተሰዋበትን አንደኛ ዓመት ስንዘክር፣ አርበኛው የጀመረውን የነፃነት ተጋድሎ ከዳር ለማድረስ ቃል በመግባት ነው❗️ ክብርና ሞገስ ለህዝባቸው ሲሉ ህይወታቸውን ለገበሩ ሰማዕታት!

ዓፄ ይኩኖአምላክ ክፍለ ጦር የአመራርና መዋቅር ማሻሻያ ማድረጉን አስታወቀ!!                               ሰኔ 23 ቀን 2018 ዓ.ም በአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ስር የሚንቀሳቀሰው እና የዓፄ ዘርዓያዕቆብ ፩ኛ ኮር አካል የሆነው የዓፄ ይኩኖአምላክ ክፍለ ጦር፣ ለሦስት ቀናት የቆየ የ9 ወራት የሥራ ግምገማና የተሃድሶ መድረክ ማካሄዱን ገለጸ። ክፍለ ጦሩ ይህንን ስልታዊ ግምገማ ተከትሎ፣ የወደፊት ግስጋሴውን ለማፋጠንና አደረጃጀቱን ለማዘመን ያስችለኛል ያለውን አዲስ የአመራር መዋቅር ማሻሻያ ለሕዝብ ይፋ አድርጓል። የኮሩ የሕዝብ ግንኙነት ሪፖርተር በላከው መረጃ መሠረት፣ የተደረገው የአደረጃጀትና የአመራር ማሻሻያ በትግሉ ሂደት ውስጥ ክፍለ ጦሩን ይበልጥ ለማዘመንና በላቀ ዲሲፕሊን ለመምራት ያለመ ነው። በዚህም መሠረት የክፍለ ጦሩ አዲስ መዋቅራዊ ይዘት በሁለት ዋና ዋና ዘርፎች (በሲቪል/ፖለቲካ እና በወታደራዊ) የተከፋፈለ ሲሆን ዝርዝሩ እንደሚከተለው ቀርቧል፦ አወቃቀሩን፦ የሲቪል ፥ የፖለቲካና ወታደራዊ  መዋቅር ዘርፍ አካቷል። ይህ ዘርፍ በዋና ሰብሳቢ የሚመራ ሆኖ በሶስት(3) ንዑሳን የኃላፊነት ክፍሎች የተዋቀረ ነው። ፩. የሕዝብ አስተዳደር ኃላፊነት፦ በአደረጃጀት፣ በሰላምና ደህንነት እንዲሁም በሕግና ስነምግባር (ፍትሕ) ንዑሳን ክፍሎች የተዋቀረ። ፪. የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊነት፦ የሪፖርተር፣ የፋይናንስ እና የግዢ ንዑሳን ክፍሎችን ያካተተ። ፫. የወታደራዊ ዘርፍ መዋቅር ይህ ዘርፍ በዋና ወታደራዊ አዛዥ የሚመራ ሆኖ በሚከተሉት ሦስት ንዑሳን የኃላፊነት ክፍሎች የተዋቀረ ነው። [  ] የኦፕሬሽናል ኃላፊነት (በምክትል የሚመራ)፦ የመረጃና መሐንዲስ፣ የዋና ዘመቻ፣ የምክትል ዘመቻ እና የኦፕሬተር ንዑሳን ክፍሎችን የሚመራ። [  ] .የወታደራዊ አስተዳደር ኃላፊነት፦ የወታደራዊ ሕግ፣ የኦርዲናንስ እና የፐርሰኔል ንዑሳን ክፍሎችን የያዘ። [  ] የሎጀስቲክ ኃላፊነት (በምክትል የሚመራ)፦ የሕክምና እንዲሁም የቀለብና አልባሳት ንዑሳን ክፍሎችን የያዘ ነው። የኮሩ ሪፖርተር መግለጫ ማጠቃለያ  ይህ አዲስ የተዋቀረው የአመራር መዋቅር የተጀመረውን የሕልውና ትግል ወደ ላቀ ምዕራፍ ያሸጋግረዋል፤ በአውደ ውጊያው ላይ የተመዘገቡ ድሎችንም ይበልጥ ያጠናክራል የሚል ሙሉ እምነት አለን ሲል ለዕዙ ሕዝብ ግንኙነት አድርሷል። በዚሁ መሠረት በተለያዩ የኃላፊነት ቦታዎች ላይ የተመደቡት አመራሮች ቃለ መሐላ ፈጽመው ሥራቸውን በይፋ መጀመራቸውን የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ አረጋግጧል። "ክብር ለትግሉ ሰማዕታት!" "ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!" የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ!!