Princ faysel
Open in Telegram
➜ ከዚህ ቻናል አንብባችሁ በተጠቀማችሁ ቁጥር፤ይህን ደካማ እና ስህተቱ ብዙ የሆነውን ወንድማችሁን በመልካም ዱዓችሁ አስታውሱት https://t.me/princfaysel
Show more2 640
Subscribers
-224 hours
-217 days
-9530 days
Posts Archive
2 640
የዐሹራ ቀን በሒጅራ አቆጣጠር የሙሐረም ወር 10ኛው ቀን ሲሆን፣ በእስልምና ታሪክ ትልቅ ቦታ አለው። ቀኑ አላህ ነቢዩላህ ሙሳን (ዐ.ሰ) እና ሕዝቦቻቸውን ከፈርዖን ጭቆና ያዳነበት በመሆኑ ነቢዩ ሙሐመድ ﷺ ራሳቸው ጾመውታል፤ ሰሃባዎችንም እንዲጾሙ አዘዋል።
በሶሒሕ ሙስሊም ሐዲስ መሠረት፣ የዐሹራን ቀን መጾም ያለፈውን የአንድ ዓመት (ትንንሽ) ወንጀሎችን ያስምራል። ሱናውን በተሟላ መልኩ ለመተግበር የሙሐረም 9ኛ እና 10ኛን ወይም 10ኛ እና 11ኛን ቀናት አብሮ መጾም ይመረጣል። ከጾም ባለፈም ቀኑን በዱዓ፣ በዚክር፣ በቁርኣን ንባብ እና በመልካም ሥራዎች ማሳለፍ ይወደዳል። ይህ ዕለት በአስቸጋሪ ጊዜያት ሁሉ የአላህ እርዳታና እዝነት እንደማይለየን የሚያስታውስ ታላቅ ቀን ነው።
ዐሹራን ፁም ሌሎችንም አስታውስ!
2 640
አንተ ሀብታም አይደለህም
አላህ ሰቶህ እንጂ
አንተ የምችል አልነበርክም
አላህ ስላገዘህ እንጂ
አንተ አዋቂ አልነበርክም
አላህ አሳወቀህ እንጂ
ስኬቶችን የራስህ አታድርግ እያንዳንዱ ነገርህ የአላህ ትሩፍት እንደሆነ አትርሳ ።
2 640
በልብህ ውስጥ መቼም የማይተኙ 4 ሌቦች እንዳሉ ታውቃለህ?
ኢማም አል-ገዛሊ (ራ. ዓ)እንዳብራሩት እነዚህ ሌቦች መሣሪያ አይታጠቁም፣ ነገር ግን የልብህን ብርሃን በዝምታ ይሰርቁታል። እነሱም: —
1.ስሜት (ሻህዋ)፦ ደስታን ቃል ይገባል፣ ግን መቼም አይረካም።
2.ቁጣ፦ በፍጥነት ካልጠፋች ቀድማ ያንተን ልብ የምታቃጥል እሳት ናት።
3.የዝና ፍቅር፦ ለአላህ የሚሰራን ንጹህ ስራ ይሰርቃል፤ የሰዎችን አድናቆት ብቻ እንድትሻ ያደርጋል።
4.የሀብት ፍቅር፦ ገንዘብን መሣሪያ ማድረግ ሲገባህ የልብህ ግብ ሲሆን ባሪያ ያደርግሃል።
★መፍትሄው
እነዚህ ሌቦች የውስጥ ሰላምን ያውካሉ፣ ኢባዳን የተራራ ያህል ያከብዳሉ። ፈውሳቸው ዘወትር ራስን መመርመር ሲሆን፥ ይህም ስሜትን በመቃወም፣ ቁጣን በትዕግስት በመስበር፣ ክብርን ለአላህ ብቻ በመስጠት እና ሀብትን በእጅ እንጂ በልብ ውስጥ ባለማስቀመጥ ይገለጻል።
[በሰለዋት የደመቀ በመልካም ስራ የታጀበ ጁምዓ ይሁንላቹ
2 640
+1
በአንድ ሰው ህይወት ውስጥ fit ለማድረግ ብላችሁ don't change ur vibe, don't change ur self, sometimes የምንጣጣረው ለመኖር ሳይሆን survive ለማረግ ይሆናል, Try to be someone who's able to survive,able to handle all the messes መበርታት እና ችግሮቻችንን መፍታት is one of God's examination in our life እና ከማንችለው በላይ የማያሸክመን ፈጣሪ አለን plus የተፈጠርንበትን አላማ እስካልረሳን ድረስ፣በGod እስከተማመንን ድረስ ምንም አንሆንም እንበርታ🙏🏾
2 640
ደሃም ሆነህ ቅጥርም ጠልተህ አብረው አይሄዱም:: ወላጆችህ ድህነት አውርሰውህ ይሆናል:: ያው እነርሱም እንደ ማንኛውም ምእመን ወርሰው ወይም ችግሮች ተደራርበውባቸው ነው:: ሀገሪቷም ድሃ ነች:: Well, ታዲያ አንተም ድህነትን ማውረስ አለብህ ወይ? ከተባለ ማንም አይፈልግም:: ጅል ጥያቄ ነው:: ድሃ ከሆንክ የመጀመሪያው step መቀጠር ነው:: ስትቀጠር ደመወዙን ታርጌት ካደረግህ ለመውጣት ጊዜ ይፈጅብሃል:: የቅጥር ትልቁ ጥቅም ልምድ መቅሰም ነው:: አንዳንድ ቦታማ ደመወዝ ቀንሰህም ልትቀጠር ትችላለህ:: ከልምድ ባሻገር ሰዎችን ትተዋወቅበታለህ:: በዚህ ወቅት ትምህርትም ጠልተን ቅጥርም ጠልተን ግን ሀብታምነት መመኘት የማይሆኑ ነገሮች ናቸው:: ፌሚኒዝምን በጣም የጠጡ ወይም በጎረቤቶቻቸው ባለትዳሮች ኑሮ ተበሳጭተው ትዳር እና ባል የሚባል ነገር ጠልተው ግን በልጅ ፍቅር የሚነድዱ ሴቶች እንደማለት ነው:: ልጅ ፍለጋ "አንዴ ተሳሳትብኝ" የሚሉ ትዳር ጠይ ልጅ ወዳጅ አይጠፉም:: ገንዘብ ደግሞ አይሳሳትም:: እንደ ገንዘብ ዘመዱን የሚወድ አይቼ አላውቅም:: ይኖራል ግን የገንዘብ ዘመድ አወዳደድ ይለያል:: አንድ ገንዘብ ... ገንዘብ የሌለበት ቦታ አይሄድም:: ስለዚህ በበሩ በኩል ግባ:: ትምህርት, አጫጭር የሙያ ስልጠና ውሰድ:: ተቀጠር:: ሁሉንም የወጪ በር ዝጋና ቋጥር:: ከዚያ ወደ ሁለተኛው ኳድራንት ትሻገራለህ:: የሽግግሩ ጊዜ ነቅለህ ከቅጥር አትወጣም:: ቅዳሜና እሁድ, ንጋትና ማታ ላይ ትሞክራለህ:: ብልጥ የወንዝን ጥልቀት በሁለት እግሩ አይፈትሽም ይባላል::
2 640
የዝምታ ሰፈር!
«ለአንድ ሰው አልኩት፤ ሐሜት የማይናገሩ፣ ምቀኝነት የሌለባቸው፣ ጥላቻም የማይያዙ ሰዎች የሚኖሩበት ሰፈር አጠገብ ቤት እፈልጋለሁ።
እርሱም ወደ መቃብር ይዞኝ መጣና እንዲህ አለኝ፦“እነሆ እዚህ ነው”።»
2 640
የዛሬ ቀን ትልቁ ዚክር
" لا إله إلا الله وحده لا شريك له، له الملك وله الحمد
وهو على كل شيء قدير "
" ላ ኢላሃ ኢል ለላህ ወሕደሁ ላ ሸሪከ ለሁ ለሁል ሙልኩ ወለሁል ሐምዱ ወሁወ ዓላ ኩሊ ሸይኢን ቀዲር "
ይህ ዚክር በዛሬው የዐረፋ ( የሐጅ ሰዎች ዐረፋት ላይ በሚቆሙበት) በጣም ተወዳጅ ዚክር ነው ። የአላህ መልእክተኛ በዛው ቀን ይህ ዚክር ( ዱዓእ) በጣም ተወዳጅና በላጭ ሲሆን እኔና ከኔ በፊትም የነበሩት ነብያቶች ያልነው ነው ይሉናል በነፍሳችን ላይ አንሰስት ።
እንደሚታወቀው የዛው ቀን ከዓለም የተሰባሰቡ ሙስሊሞች በዐረፋት ሜዳ ላይ ፈሰው መዳፋቸውን ዘርግተው ወደ ላይ አንስተው ያ አላህ የሚሉበት ቀን ነው ። አላህ በመላኢካዎች ለእነዚህ ባሮቹ ምህረት የለገሳቸው መሆኑን የሚያስመሰክርበት ቀን ነው ። ባሮቹ የከፈን ጨርቅ ለብሰው አምላካቸው ፊት ቆመው የርሱ እዝነትና ምረት ካልደረሰላቸው ጠፊዮች መሆናቸውን በእንባ እየታጠቡ የሚናገሩበትና ራሳቸውን ለጌታቸው ዝቅ የሚያደርጉበት ቀን ነው ። በዚህ ተግባራቸው አምላካቸው የሚደሰትበት ቀን ነው ። ታዲያ እኛ ለዚህ ያልታደልን ወይም ወረፋ ያልደረሰን የሱ ባሮች በዚህ ዚክር እየታገዝን አምላካችንን ምህረት እንለምን አንዘናጋ ።
2 640
ነገ ዓረፍ ነው
16 ሰዓታት መፃም የሁለት አመት ወንጀል ን ያስምራል (730 ቀን) ማለት ነው ።
فاللهم بلغنا عرفة ووفقنا لصيامه، وتقبّله منا، واغفر لنا فيه ما مضى وما هو آتٍ.
2 640
ኃጥያቴ ቢበዛም ለበይከ ጌታዬ… አንተን የተጠጋ ልብ እድለቢስ ሆኖ አያውቅምና። በቅዱሱ ስፍራ ከሁጃጆች መሀል ሆኜ ባልጠራህም … ካለሁበት ቦታ አቤቱ እልሃለሁ። ልቤ ደርቆ ስምህን ደጋግሜ ባላነሳም… መመለሻዬ አንተ ብቻ ነህና ለበይከ ረቢ። ቤትህን ከሚወዱን ከምንወዳቸው ጋር የምንዘይርም አድርገን ያ አላህ።
2 640
🕋 የነገው የዐረፋ ቀን ምን ልስራ?
1⃣ዛሬ አዳሩን በመተኛትህ አጅርን
ማግኘትን ሌሊት ቶሎ ለመነሳት
በሚል ንያ ቶሎ ተኛ.
2⃣ነገን ለመፆም ለስሁር ከፈጅር
በፊት ቀድመህ ተነስተህ ስሁር
ቅመስ ምክንያቱም አላህና
መላኢኮች ስሁር በሚበሉ ሰው
ላይ ሰለዋት ያወርዳሉ
3⃣የሌሊትም ሰላት ቢያንስ አራት
ያህልን ስገድ ስትሰግድም በሱጁድህ
ላይ ሆነህ የዱንያም የአኼራም
መልካምን ነገር ለጌታህን
በመዋደቅ ተለማመጠው
4⃣ፈጅር ሊደርስ ሲልም እዚያው
በተቀመጥክበት ለተወሰነ ደቂቃ
አላህን ምህረትን ጠይቀው
5⃣ ከሰላት ቡሀላ የሚባሉትን
ዚክሮችን እንዲሁም ተክቢራ
እንዳትዘናጋ
6⃣ከቻልክ ፈጅርን ሰግደህ የሰገድክበት
ቦታም ላይ ፀሀይ እስክትወጣ ደርስ
ቁጭ ብለህ አላህን አውሳ ወይም
ቁርአንን ቅራ የጠዋትን ዚክርም
ለማለት ሞክር
7⃣ፀሀይ ወጥቶ የተወሰነ ከፍ ካለ
ቡሀላ ሁለት ረከዐ መስገድ ፈፅሞ
እንዳንረሳ ይህ ካደረክ ሀጅና ኡምራ
ያደረገ ሰው ያህል አጅር ታገኝበታለክ
አደራህን እንዳያመልጥህ
8⃣ከተቻለክ ፀሀይ ከወጣበት ሰአት
ጀምረህ ፀሀይ እስኪገባ የነገዋን
ቀን ላለመተኛት ሞክር
በዚክር በዱዐ በርታ ዱዐህም ምላሽ
እንደሚያገኝ እርግጠኛ ሁን
9⃣ረፋድ ላይ የሚሰገደወወ የዱሀን
ሰላትንም መስገድ እንዳትዘነጋ
🔟 ይህም 👇👇👇👇👇ዚክር ከዱአህ በፊትም ሆነ ቡሀላ
: لا إله إلا الله وحده لا شريك له له الملك وله الحمد وهو على كل شيئ قدير
በጣም አብዝተህ በለው ምክንያቱም የዐረፋ ቀን ከሚባሉ ዚክሮች ሁሉ የሚበልጥ ዝክር ነውና
1⃣1⃣የግዴታ ሰላቶችህን ሁሉም
ወቅቱን ጠብቀህ ከመስገድ
እንዳትዘናጋ ከፊትና ከሀላቸው
ያሉት የጠበቁት ሱና ሰላቶችንም
እንዲሁ ስገድ
1⃣2⃣ከአሱር ሰላት ቡሀላም ፀሀይ
ለመግባት እስክትቀርብ ቁጭ
ብለህ ቁርአንን አንብብ ከዚየም
በዱዐህ ችክ ብለህ አላህን
ተለማመጥ በዱዐህም ሀገራችንም
ላይ ከሀገር ውጭ የሉ ደካሞችን አካት
1⃣3⃣በስተመጨረሻም ቀን ሙሉ
የሰራህውን ኢባዳህ አላህ
እንዲቀበልህና ፅናቱንም
እንዲሰጥህ ተለማመጠው
ዱዐህም ተቀባይነት እንዲኖረው
እርግጠኛ ሁን
1⃣4⃣መግሪብ አዛን ሲልም ቶሎ አፍጥር
በድጋሚ አላህን ከመለማመጥ
እንዳትዘነጋ ምክንያቱም ለፆመኛ
አላህ የማይመልስበት ዱዐ አለውና
وباالله التوفيق
አደራ እኔንም በዱዐ እንዳትረሱኝ
2 640
.
እስካሁን ስላላገባህ አላህን አመስግንና ቤትህ ተኝተህ እረፍት አድርግ....😁
ካልሆነማ አሁን እሷ ጋር ገበያ መሃል ቆመህ፣ ከጫማዋ_ቀለም ጋር የሚመሳሰል ሂጃብ ፍለጋ ትዞር ነበር¡🥲
2 640
ምሽቱ ጁምዓ ነው። ድምቀቱም በሰለዋት ነው።
ሰው ሁሉ በሀሳብና ጭንቀት የተዳከመበት ዘመን ላይ ነው ያለነው
ትልቁ መድሃኒት ሰለዋት ማብዛት ነው።
አልሏሁምመ ሶልሊ ወሰሊም ወባሪክ ዐለይሂ ።
