7 213
Subscribers
No data24 hours
-107 days
-8030 days
Posts Archive
+1
🌸🌸 ንዒ ኀቤነ ሙዳይነ 🌸🌸
ሙዳየ ግእዝ ቍጥር ፩ እኅት አገኘች።
ለግእዝን በርቀት ከ፩ኛ ዙር እስከ ፲፬ ዙር ለተማራችኹና ለምትማሩ ወንድሞቼና እኅቶቼ ዅሉ
ሙዳየ ግእዝ ቍጥር ፩ ብቻዋን ትኾን ዘንድ አልወደደችምና በዕድሜ ታናሿን በይዘት ታላቋን እኅት ይወለድላት ዘንድ ለሰፊዉ ባቀረበችው አቤቱታ መሠረት፣ አቤቱታዋ ተሰምቶ እኅቷን ከጎኗ ለማድረግ ቀናት ብቻ ይቀሯታል።
ሙዳየ ግእዝ ቍጥር ኹለት በእግዚአብሔር መልካም ፈቃድ በአእምሮ ከመመላለስ ዐልፋ አካል ነሥታ በእጃችን ልትገባ ቀናት ብቻ ቀሯት።
እግዚአብሔር ይመስገን።
ለኹለት ዓመታት በስፋትና በጥልቀት፣
ተዘጋጅታ ግሩም በኾነ መልኩ በአራት ምዕራፋት ተዋቅራ፣ በቂ ምሳሌዎችንና ማብራሪያዎችን ይዛ ዕውቀት ብርሃኗን ለዓለም ኹሉ ለማዳራስ ሞልታ እየፈሰሰች በሽፋኗ ታይታለች።
አራት በሙያው ውስጥ ባሉ ምሁራን፣ ታይታና ተገምግማ በማለፏ በዕድሜ ታላቋን ካልበለጥኩሽ እያለች ነው።
ታላቄን የያዛችኹ ያለእኔ ሙሉ አትኾኑም፥
ልዩ ነገር ይዣለኹና፥ ከጎኗ አስቀምጡኝ
እያለች በሰውኛ ዘይቤ መልእክቷን ታስተላልፋለች።
እንደታላቅ እኅቴ በብዛት አልታተምኩም፣
ርሷን የገዛችኹ ዅሉ እንኳን እንውሰድሽ ብትሉኝ መዳረስ አልችልምና የቀደመ ይውሰደኝ የምትልም ይመስላል።
በእውነት በሙዳየ ግእዝ ቍጥር ፩
ካገኘነው የግእዝ ማእድ በተጨማሪ
የግእዝ ቋንቋ ዕውቀታችንን በእጅጉ
ከፍ የሚያደርግ፣ በይዘቱ የተለየ፣
ጠለቅና መጠቅ ያለ፣ ግእዝን ፍንትው አድርጎ የሚያሳይና የሚያጠግብ ማእድ በውስጧ ይዛለች።
"ንዒ ኀቤነ ሙዳይነ" ልንላት ይገባል።
ከኢትዮጵያ ውጭ ለምትኖሩ ከታች
ስማቸውና ስልካቸው ለተጠቀሱት በፈቃደኝነት ለሚያስተባብሩ ወንድሞችና እኅቶች በመደወል "ንዒ ኀቤነ ሙዳይነ" ማለት ትችላላችኹ።
▪ በአሜሪካ ለምትኖሩ
◦ ብርሃኑ ኃይሌ ➺ ሲያትል፣ ዋሽንግተን
(+1 206-973-9333 )
◦ ነጻነት አርጋው ➺ ማሳቹሴት
(+1 617-785-4716)
◦ ኮከብ ብሩህ ➺ ሲያትል፣ ዋሽንግተን
( +1 206 412 4534)
◦ ዲ/ን ተስፋ ሚካኤል ➺ ተክዊላ (ደቡብ ሲያትል)
( +1 571-732-9940 )
◦ ወላንሳ
( +1 206-753-9686 )
▬▭▬▭▬
▪ በጀርመን( Germany) ለምትኖሩ
◦ ዳዊት ጌታቸው
(+4915212996246 )
▬▭▬▭▬
▪በስዊድን (Sweden) ለምትኖሩ
◦ ናሆም ግርማይ
( +46760882705 )
▬▭▬▭▬
▪ በኖርወይ (Norway) ለምትኖሩ
◦ ዓባይነሽ በላይ
( +4748389991 )
በተጠቀሱት ሀገራትም ኾነ በሌሎች ሀገራት መጽሐፉን የሚፈልጉ አሉና "እኔም ለማገዝ ፈቃደኛ ነኝ" የምትሉ ወንድሞችና እኅቶች አለኹ ብትሉኝ ደስታዬ ወደር የለውም።
ኢትዮጵያ ውስጥ የምንኖር ደግሞ እንዴት እንደምናገኛትና ሌሎች መረጃዎችን ጨምሬ በቅርብ ቀን አሳውቃችዃለኹ።
ስለዅሉም ነገር እግዚአብሔር ይስጥልኝ።
🌸🌸 ንዒ ኀቤነ ሙዳይነ 🌸🌸
🌺🌺 ሙዳየ ግእዝ ቍጥር ፪ 🌺🌺
እንቋዕ ለመልአኩ ቅዱስ ሚካኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል በሰላም ወበጥዒና አብጽሐክሙ።
የተከበራችኹ የግእዝን በርቀት ተማሪዎች ወንድሞቼና እኅቶቼ እንደምን ከረማችኹ?
እኔ እግዚአብሔር ይመስገን በጣም ደኅና ነኝ።
እንደምታስታውሱት ሙዳየ ግእዝ ቍጥር ፩
በርካታ ቁም ነገሮችን ይዛ በ፳፻፲፬ ዓ.ም ወደ እናንተ ደርሳ ነበር። በወቅቱም መጽሐፏን ለግእዝን ተማሪዎች ለማሰራጨት ከእናንተው መካከል በፈቃደኝነት ተሰባስበው ትልቅ እገዛ ያደረጉልኝን ወንድሞቼና እኅቶቼን ዅል ጊዜም አመሰግናቸዋለኹ። እናንተም በሚገርም ርብርብ መጽሐፉን በመግዛት አግዛችዃል። ምስጋናዬ በልብና ከልብ ነው።
በወቅቱ ምንም እንኳን አብዛኛው የግእዝ ተማሪ መጽፏን የገዛ ቢኾንም የታተመው መጽሐፍ የተማሪውን ብዛት ታሳቢ ተደርጎ በብዙ ሺሕ የሚቆጠር ስለነበር ዛሬ ድረስ ገንዘብና ቦታ ይዞ ቤት ቤት ውስጥ ተቀምጧል።
አብዛኛው ማኅበረሰብ መጽሐፍ ሲገዛ የጸሓፊውን ዐዋቂነትና ታዋቂነት መሠረት አድርጎ በመኾኑ እኔ ደግሞ ዐዋቂም ታዋቂም ባለመኾኔ በመጽሐፏ ስርጭት ላይ የተወሰነ ተጽዕኖ ነበረው። ለነገሩ እኔም ታሳቢ ያደረግኩት የግእዝን በርቀት ተማሪዎችን ነበር። ይደግም ይነስም እናንተ የትምህርቱን ጥቅም ስለተረዳችኹት መጽሐፏን በምትችሉት ዐቅም ገዝታችዃል፣ ለሌላም ሰው ጠቁማችዃል።
የኾነ ኾኖ ከባለፈው ልምድ በመውሰድ
የቍጥር ኹለትን የኅትመት ብዛት ከመጀመሪያው ባነሰ መጠን ለማሳተም ዐስቤአለኹ።
በነገራችን ላይ ሙዳየ ግእዝ ቍጥር ፪
በብዙ ነገር ከመጀመሪያው ልምድ በመውሰድ በጥንቃቄ የተዘጋጀ ፣ ያልተዳሰሱትን የሚዳስስ በእኔ ዕይታ በጥሩ ኹኔታ አዘጋጅቼ ጨርሻለኹ። የሚቀረው ባጭር ቀናት ውስጥ ወደ ማተሚያ ቤት መውሰድ ነው። ወደማተሚያ ቤት ለመውሰድ ደግሞ የሚታተመውን የመጽሐፍ ብዛት መወሰን አለብኝ።
ይኽን ለማድረግ ደግሞ ቅድመ ኅትመት መረጃ መሰብሰብ አስፈላጊ ኾኗል። በመኾኑም እርስዎ ሙዳየ ግእዝ ቍጥር ፪ ሲታተም መጽሐፉ መግዛት ይፈልጋሉ?
ከዚኽ መረጃ ተነሥቼ ስንት ይታተም የሚለውን ወስኜ እንዲታተም አደርጋለኹ። (የመጽሐፉ ዋጋው ያው እንደ ብዛቱና እንደ ወቅቱ ስለሚወሰን የአገር ያኽል ነው የሚኾነው)።
በመኾኑም ከታች ባስቀመጥኩላችኹ ሊንክ በመግባት ያለችዋን ዐጭር ፎርም በመሙላት ፍላጎታችኹን እንድትገልጹልኝ በታላቅ ትሕትና
እየጠየቅኹ ቍጥር ፪ን ለማስተዋወቅ፣ ለማሰራጨትም ኾነ ለማስተባበር የምትፈልጉም ካላችኹም ጻፉልኝ። በተለይ ፲፩ኛ፣ ፲፪ኛ እና ፲፫ኛ ዙር ተማሪዎች በቍጥር ፩ ስላልተሳተፋችኹ ቍጥር ፪ እናንተን ትጠብቃለችና ቅረቧት። (ለቍጥር ፩ ያስተባበሩና ያሰራጩ ከ፩ኛ እስከ
፲ኛ ዙሮች ነበሩና።)
ከኢትዮጵያ ውጪ የምትኖሩም እንደቍጥር ፩ መጽሐፍ ባላችኹበት አገር ለመላክ ታስቧልና ከኢትዮጵያ ውጪ የሚለውን ፎርም ሙሉ።
⭕️ ከኢትዮጵያው ውጪ የምትኖሩ ይኽን ፎርም ሙሉ። https://forms.gle/LJ5hdpGtnBeNwFnw5
⭕️ ኢትዮጵያ ውስጥ የምትኖሩ ይኽን ፎርም ሙሉ። https://forms.gle/pP6STVHuAPV6nLuq5
በቅርብ ቀን ሙዳየ ግእዝ ቍጥር ፪ ታትማ ወጥታለች የሚል ዜና ይዤ እመጣ ዘንድ
የእግዚአብሔር መልካም ፈቃድ ፣ የእናንተ ጸሎት አይለየኝ።
▬▭▬▭▬▭▬▬▬▭▬▭▬▭▬
መልእክት ፪
ዕለቱን በተመለከተ በእንተ ቅዱስ ሚካኤል አንድ መዝሙር ላስደምጣችኹ ዐስብኩና አንዱን ብቻ ማሰቤ ንፉግነት ስለመሰለኝ ወደምንጩ ልወስዳችኹ ፈለግኹ።
እስካኹን እንደምታውቁት ከግእዙ ትምህርት ውጪ እንዲኽ አድርጉ የሚል ማስታወቂያ አስተላልፌ አላውቅም ምክንያቱም….
ዛሬም ለማስተዋወቅ፣ እንዲኽ አድርጉ፤ ይኼን ውደዱ፣ ወዲያውም አጋሩ የሚል ተማፅኖ ለማቅረብ አይደለም፡፡ ውስጤ ደስ የተሰኘበትን የመዝሙር ስብስብ እናንተም ትሰሙት ዘንድ በዕለተ ቅዱስ ሚካኤል ለመጠቆም ብቻ ነው፡፡ ‹‹ልብን ያስደስታል›› የሚለው ቃል አይገልጸውም፡፡ ስለቅዱስ ሚካኤል ሙሉ መልእክት የሚያስተላልፍ በመኾኑ፣ ግእዝ በግእዝ በመኾኑ ጥንታዊውን የግእዝ መዝሙር ስለሚዘክር፣ ከዘማሪው አንዱ የዚኹ የግእዝን በርቀት የ፱ኛ ዙር ተማሪ የራሳችን ልጅ፣ የራሳችን ወንድም በመኾኑ ደረብረብ ባሉ ምክንያቶች መጠቆም ወደድኹ፡፡
በነገራችን ላይ ዲ/ን ቴዎድሮስ (ጸጋ ሥላሴ) በግእዝ ትምህርቱ የደረጃ ተማሪ፣ ዕውቀትን ከትሕትና ያጣመረ ተወዳጅ ተማሪዬ ነው፡፡ በመዝሙራቱም ያስተዋልኩት ይኼንኑ ነው፡፡
የራሴ ፎቶ ያለበትን ፎቶ ሳይ በቅድሚያ የራሴን የማየት ልምድ አለብኝና እኔም በቅርበት ስለማውቀው ስለ ጸጋ ሥላሴ ተናገርኩ እንጂ ዐብረውት የዘመሩት ከማሁ ነዮሙ።
ለኹሉም ዝማሬ መላእክትን ያሰማልን።
ከታች ባለው ማስፈንጠሪያ መዝሙራቱን አዳምጧቸው ትጠቀሙበታላችኹ፡፡
https://youtu.be/aorhTHIQl-g?si=7ni71sC4t009i0TY
ከማስታወቂያ ግን አትቁጠሩብኝ፡፡ ይኸን ሳልል ብቀር ውስጤ ዕረፍት ስለማያገኝ ስሜቴን ለማንጸባረቅ ብቻ ነው፡፡
ወንድማችኹ ግዛቸው ደጀኑ
ኅዳር ፲፪፥ ፳፻፲፯ ዓ.ም
🌺🌺 ሙዳየ ግእዝ ቍጥር ፪ 🌺🌺
➡️➡️➡️➡️➡️➡️➡️➡️➡️➡️
🔔 ግእዝን በርቀት ፲፬ኛ ዙር
ሰላም ለኹላችኹም ይኹን!
እንደሚታወቀው ግእዝን በርቀት እስከ ፲፫ኛ ዙር ላልተማሩ ዐዲስ ተማሪዎች የሚኾን ትምህርት በ፲፬ኛ ዙር ለመጀመር በእናንተ ቀስቃሽነት በርካታ ተማሪዎች ተመዝግበዋል።
የተማሪው ቍጥር እንደስካኹኑ ብዙ ባይኾንም ያሉትን ተማሪዎች በአግባቡ ተቀብሎ ማስተማር ስለሚገባኝ ትምህርቱን በቅርቡ ለመጀመር አስቤአለኹ።በመኾኑም እስካኹን ያልገቡ ካሉ
በማሳሰብና የመመዝገቢያ ጊዜውንና ትምህርቱ የሚጀመርበትን ጊዜ በማሳወቅ የተለመደ ተግባራችኹን ታከናውኑ ዘንድ በትሕትና እጠይቃለኹ።
● ግእዝን በርቀት ፲፬ኛ ዙር ምዝገባው የሚጠናቀቀው ዐርብ ጥቅምት ፲፭, ፳፻፲፯ ዓ.ም ከምሽቱ ፲፪ ሰዓት ነው።
● ትምህርቱ የሚጀመረው ደግሞ ሰኞ ጥቅምት ፲፰, ፳፻፲፯ ዓ.ም ሲኾን ወደ ትምህርቱ ቻናል መግቢያው @geezdistance14 ነው።
➡️➡️➡️➡️➡️➡️➡️➡️➡️➡️
🔥🔥2️⃣0️⃣1️⃣7️⃣ ዓ🔤ም 🔥🔥
እንቋዕ እምዘመነ ቅዱስ ዮሐንስ ኀበ
ዘመነ ቅዱስ ማቴዎስ በሰላም ወበጥዒና አዕደወክሙ።
የ፳፻፲፯ ዓ.ም ተዘዋዋሪ በዓላትና አጽዋማት
፩) ጥንተ ዮን
◌ 2017 ፥ 28 =72 ቀሪ 1
2017 ዓ.ም ማለት 72 ኛው ዐውደ ፀሓይ
ተፈጽሞ 73 ኛው ዐውደ ፀሓይ ከተጀመረ 1ኛው ዓመተ ፀሓይ ላይ ነው ።
◌ ምርያ ➾ 1
◌ ሠግር = አልቦ
◌ ጥንተ ዮን = ምርያ + ሠግር
= 1 + 0 = 1
ጥንተ ዮን = 1 = ረቡዕ
መስከረም 1, 2017 ዓ.ም ➾ ረቡዕ
▬▬▬▬🌼▬▬▬▬
፪) ወንጌላዊው
ወንጌላዊው = (5500+2017) ፥ 4
= 7517 ፥ 4
= 1879 ቀሪ 1
ወንጌላዊው ➾ ቅዱስ ማቴዎስ
▬▬▬▬🌼▬▬▬▬
፫) ወንበር
◌ 2017 + 5500 = 7517
◌ 7517 ፥ 19 = 395 ቀሪ 12
2017 ዓ.ም 395 ኛው ዐውደ አበቅቴ
ተፈጽሞ 396 ኛው ዐውደ አበቅቴ ከተጀመረ 12ኛው ዓመተ አበቅቴ ላይ ነው።
◌ ዓመተ አበቅቴ ➾ 12
◌ ወንበር = ዓመተ አበቅቴ - 1
= 12-1
ወንበር = 11
▬▬▬▬🌼▬▬▬▬
፬) አበቅቴ
◌ አበቅቴ=(ጥንተ አበቅቴ*ወንበር)፥30
= (11* 11)፥ 30
= 121 ፥ 30
= 4 ቀሪ 1
አበቅቴ ➾ 1
▬▬▬▬🌼▬▬▬▬
መጥቅዕ + አበቅቴ = 30
፭) መጥቅዕ
◌ መጥቅዕ = 30 - አበቅቴ
= 30 - 1 = 29
መጥቅዕ ➾ 29
መጥቅዕ ➾ መስከረም 29
ነነዌ የምትውለው የካቲት ውስጥ ነው።
ምክንያቱም መጥቅዑ ላይ መጥቅዑ የዋለበት ተውሳክ ከ30 ይበልጣልና።
መስከረም 29, 2017 ዓ.ም የትኛው ዕለት ላይ ይውላል?
ጥ.ዕለት
= ዐጽፈ ወርኅ + ሠ.መዐልት + ጥ.ዮን
= 2 + 29 + 1
= 32 ➾ 32 ፥ 7 = 4 ቀሪ 4
ጥ. ዕለት = 4ኛ ቀን = ረቡዕ
(ከጥንተ ዕለት)
መጥቅዑ ( መስከረም 29, 2017 ዓ.ም)
የሚውለው ➾ ረቡዕ ነው።
የረቡዕ ተውሳክ ➾ 4
▬▬▬▬🌼▬▬▬▬
መባጃ_ሐመር
= መጥቅዕ + መጥቅዑ የዋለበት ዕለት ተውሳክ
= 29 + 4 = 33
መባጃ ሐመር = 3
▬▱▬▱▬▱▬▱▬▱▬▱
የ፳፻፲፯ ዓ.ም ተዘዋዋሪ በዓላትና አጽዋማት ትንሣኤን መሠረት በማድረግ ሲሰሉ
በዓለ ፍሥሕ
በዓለ ፍሥሕ በብሉይ ኪዳን ከሚከበሩ በዓላት አንዱ ሲኾን የስቅለት በዓል ምሳሌ ነው። በዓለ ፍሥሕ የሚውለው መጥቅዕ ከዋለበት ጀምሮ በ190ኛው ቀን ነው።
ፍሥሕ = መጥቅዕ +10
የ2017 ዓ.ም በዓላትና አጽዋማትን ለማስላት በቅድሚያ የ 2017 ዓ.ም ትንሣኤን ማግኘት አለብን። የ2017 ዓ.ም ትንሣኤን የምናገኘው ከፍሥሕ ነው። የጌታችን የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ትንሣኤ የሚውለው በዓለ ፍሥሕ ከዋለበት ቀጥሎ ባለው እሑድ ነው።
በዓላት/አጽዋማት ከትንሣኤ ለማስላት የበዓሉን/ የጾሙን ኢየዐርግ በትንሣኤ ላይ መደመር ነው።
ፍሥሕ = መጥቅዕ + 10
= 29 +10
= 39 ፥ 30 = 9
9 ማለት ሚያዝያ 9 ነው።
በመኾኑም የ2017 ዓ.ም በዓለ ፍሥሕ ሚያዝያ 9 ላይ ይውላል።
ሚያዝያ 9, 2017 ዓ.ም የሚውልበት ዕለት
ምንድን ነው?
ጥ. ዕለት
= ዐጽፈ አውራኅ+ሠርቀ መዐልት+ጥ. ዮን
= 16 + 9 + 1
= 26
= 26 ፥ 7 = 3 ቀሪ 5
በጥንተ ዕለት 1ኛ ዕለት ማለት #ኀሙስ ነው።
በዓለ ፍሥሕ ➳ ኀሙስ ሚያዝያ 9, 2017 ዓ.ም
ትንሣኤ በዓለ ፍሥሕ ከዋለበት ቀጥሎ ያለው እሑድ ይውላል። ይኸውም ማለትም ሚያዝያ 12, 2017 ዓ.ም ይውላል።
በዓል/ጾም = ትንሣኤ + የበዓሉ/ጾሙ ኢየዐርግ
▬▱▬▱▬▱▬▱▬▱▬▱
🌼 ነነዌ
= ትንሣኤ + የነነዌ ኢየዐርግ
= 12 + 21
= 33 ➝ 3
ነነዌ ➝ ሰኞ የካቲት 3
🌼 ዐቢይ ጾም
= ትንሣኤ + የዐቢይ ጾም ኢየዐርግ
= 12 + 5
= 17
ዐቢይ ጾም ➝ ሰኞ የካቲት 17
🌼 ደብረ ዘይት
= ትንሣኤ + የደብረ ዘይት ኢየዐርግ
= 12 + 2
= 14
ደብረ ዘይት ➝ እሑድ መጋቢት 14
🌼 ሆሳዕና
= ትንሣኤ + የሆሳዕና ኢየዐርግ
= 12 + 23
= 35 ➝ 5
ሆሳዕና ➝ እሑድ ሚያዝያ 5
🌼 ስቅለት
= ትንሣኤ + የስቅለት ኢየዐርግ
= 12 + 28
= 40 ➝ 10
ስቅለት ➝ ዐርብ ሚያዝያ 10
🌼 ረክበ ካህናት
= ትንሣኤ + የረክበ ካህናት ኢየዐርግ
= 12 + 24
= 36 ➝ 6
ርክበ ካህናት ➝ ረቡዕ ግንቦት 6
🌼 ዕርገት
= ትንሣኤ + የዕርገት ኢየዐርግ
= 12 + 9
= 21
ዕርገት ➳ ኀሙስ ግንቦት 21
🌼 ጰራቅሊጦስ
= ትንሣኤ + የጰራቅሊጦስ ኢየዐርግ
= 12 + 19
= 31 ➝ 1
ጰራቅሊጦስ ➝ እሑድ ሠኔ 1
🌼 ጾመ ሐዋርያት
= ትንሣኤ + የጾመ ሐዋርያት ኢየዐርግ
= 12 + 20
= 32 ➝ 2
ጾመ ሐዋርያት ➳ ሰኞ ሠኔ 2
🌼 ጾመ ድኅነት
= ትንሣኤ + የጾመ ድኅነት ኢየዐርግ
= 12 + 22
= 34 ➝ 4
ጾመ ድኅነት ➝ ረቡዕ ሠኔ 4
▬▱▬▱▬▱▬▱▬▱▬▱
ፀሓየ ጽድቅ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በተወለደበት በ፩ ዓ.ም ዘመኑ ዘመነ ማቴዎስ ፥ ጥንተ ዮኑ ፩ (መስከረም ፩ ረቡዕ) ነበር። ይህም ዓመት ከዓመተ ፍዳ፣ ከዓመተ ኵነኔ ወደ ዓመተ ምሕረት የተሻገርንበት ዓመት ነው።
፳፻፲፯ ዓ.ም ዘመኑ ዘመነ ማቴዎስ፥
ጥንተ ዮኑ ፩ (መስከረም ፩ ረቡዕ) ነው።
ዐዲሱን ዓመት የምሕረት፣ የምሕረት፣ የምሕረት ዘመን ያድርግልን።
▬▱▬▱▬▱▬▱▬▱▬▱
ወንድማችኹ ግዛቸው ደጀኑ
መስከረም ፩, ፳፻፲፯ ዓ.ም
▬▱▬▱▬▱▬▱▬▱▬▱
🔥🔥2️⃣0️⃣1️⃣7️⃣ ዓ🔤ም 🔥🔥
▬▬▬▬▬▬🌸▬▬▬▬▬▬
የተከበራችኹ የግእዝን በርቀት የ፲፫ኛ ዙር ተማሪዎች ( የዚህ ቻናል አባላት)
የ፲፫ኛ ዙር ትምህርትን ስንማማር እኔና እናንተ የምንጻጻፍበት፣ መልመጃ/ፈተና የምትልኩበት፣ ሌሎች መልእክቶችንም በግል የምንጻጻፍበት @geezachew13 የሚለው አካውንቴ በመጥፋቱ እና እስካኹን ሊስተካከል ባለመቻሉ
ከእኔ ጋራ መገናኘት ብትፈልጉ እንደምትቸገሩ በማሰብ በተለያዩ ምክንያቶች እኔን ማግኘት ስትፈልጉ @geezachew12 የሚለውን አካውንት መጠቀም እንደምትችሉ መግለጽ እየገለጽኹ ስትጽፉ የ፲፫ኛ ዙር ተማሪዎች መኾናችኹን እየገለጻችኹ፣ ከቻላችኹ ደግሞ
deleted account የሚል አካውንት ፈልጋችኹ በግል የተጻጻፍናቸውን ወደ @geezachew12 Forward ብታደርጉልኝ ደስ ይለኛል። ምክንያቱም ለነበረን ቈይታ ማስታወሻዬ ናቸውና። ይህ መልእክት የደረጃ ፪ ትምህርትን እየተማራችኹ ያላችኹትን አይመለከትም።
ግዛቸው ደጀኑ
ነሐሴ ፳፫, ፳፻፲፮ ዓ.ም
▬▬▬▬▬▬🌸▬▬▬▬▬▬
🌼🌼ግእዝን በርቀት ፲፬ኛ ዙር🌼🌼
ግእዝን በርቀት ፲፬ኛ ዙር በክፍያ
[ ግማሽ ለሥጋ ፥ ግማሽ ለነፍስ]
የተከበራችኹ የግእዝን በርቀት ተማሪዎች
እንደምን አላችኹ? እንደምታውቁት ግእዝን በርቀት በሚል መነሻነት የማውቃትን ትንሽ የግእዝ ዕውቀት
ለወገኔ ምንን አደረግኹ? ለሚለው ጥያቄ መልስ ለመስጠት እና ከእግዚአብሔርም ዋጋ ለማግኘት፣ በተጨማሪም የዕውቀት ዐሥራት በኵራት ለማውጣት በማሰብ ለዐምስት ዓመታት ለብዙ ሺሕ ተማሪዎች እስከ ፲፫ኛ ዙር ድረስ፣ ዕውቀት በገንዘብ ባይተመንም ዩኒቨርሲቲ ገብቼ በክፍያ የተማርኹትን፣ ያገኘኹትን ዕውቀት #በነጻ ለማስተማር ጥረት አደርጌአለኹ።
ይህን ሳደረግ ከእግዚአብሔር እንጂ ከሰው ምላሽን ሳልጠብቅ ደስ ብሎኝ በፍቅርና በትጋት በመኾኑ ብዙ ርቀት እንድጓዝ ረድቶኛል። በዚህም እግዚአብሔርን አመሰግናለኹ።
ከዚህ በኋላ ደግሞ እስካኹን ካደረግኹት ይልቅ አብዝቼና አስፍቼ ተቋማዊም አድርጌ ለመቀጠል
አስባለኹና እንደስካኹኑ ለመቀጠል ያሉት ነባራዊ ችግሮች ስለማይፈቅዱልኝ ከ፲፬ኛ ዙር ጀምሮ ሙሉ በሙሉ ነጻ መኾኑ ቀርቶ በተመጣጣኝ ክፍያ
ትምህርቱን ለማስቀጠል አስቤአለኹና እንዳስካኹኑ ከጎኔ ኾናችኹ የግእዝ ትምህርቱ በዓለም ኹሉ እንዲዳረስ የእናንተ ድጋፍ ያስፈልገኛል።
እንደምታውቁት እኔ በግሌ ወደትምህርቱ የምጋብዛቸው በጣት የሚቈጠሩ ተማሪዎች ናቸው። እነዚህን ኹሉ ተማሪዎች ያመጣችዃቸው እናንተ ናችኹ። እኔ ግእዝን በቀላሉ ተምሬአለኹና #ኑ ተማሩ እያላችኹ በመጋበዝ ነው። በመኾኑም እኔ ትምህርቱን በማስተማር እናንተ ደግሞ ተማሪዎችን በማምጣት ተጋግዘን ለዚህ ኹሉ ተማሪ መማር ድርሻችንን ተወጥተናል።
አኹን ደግሞ ግእዝን በርቀት ፲፬ኛ ዙርን በክፍያ ለመጀመር ስላሰብኹ እንደተለመደው ተማሪዎችን እንድትጋብዙ ስጠይቅ በታላቅ ትሕትና ነው።
ክፍያውን በተመለከተ
◎ ክፍያው ማንንም የማያስጨንቅ፣ ኹሉም በነጻነት እንዲማር፣ የምከፍለው የለኝም ብሎ ሳይማር እንዳይቀር የሚያበረታታ ይኾን ዘንድ ከአንድ ብር ጀምሮ እንደየተማሪው ዐቅም የሚከፈል ይኾናል። መቼም በዚህ ዘመን አንድ ብር መክፈል የማይችል አይኖርምና ዐማርኛው ኹሉም ይማር ነው።
◎ ትምህርቱ የሚሰጠው ለኹለት ወራት ሲኾን ክፍያው የሚፈጸመው ሲጀምሩ ሳይኾን ትምህርቱ ግማሽ ( ፩ ወር ) ላይ ይኾናል።
እናም በዚህ የሚስማሙና ለመማር ፈቃደኛ የኾኑ፣ ከዚህ ቀደም ግእዝን በርቀት (ከ፩ኛ እስከ ፲፫ኛ ዙር) ያልተማሩ ጀማሪ ተማሪዎችን በራሳችኹ መንገድ በየማኅበራዊ መገናኛው እየጻፋችኹ እንድትጋብዙና እናንተ የቀመሳችኹትን የግእዝ ትምህርት እንዲቀምሱ ታደርጉ ዘንድ በታላቅ ትሕትና እጠይቃለኹ።
▬▬▬▬▬▬🌼▬▬▬▬▬▬
እግዚአብሔር ቢፈቅድና ቢረዳኝ በቀጣይ ላደርጋቸው የማስባቸው፦
፩) ሙዳየ ግእዝ ቍጥር ፪ን ማሳተም።
፪) ግእዝን በርቀት የተሰኘውን ተቋማዊ ማድረግ
፫) ዐዲስ አበባ ውስጥ ለሚኖሩ የግእዙን ትምህርቱ ለተወሰኑ ተማሪዎች በአካል(ገጽ ለገጽ በክፍል ውስጥ) ማስተማር። አካል ውስን ነውና።
፬) ከኢትዮጵያ ውጪ ለሚኖሩ በተለያዩ አማራጮች በመጠቀም የአካል( ገጽ ለገጽ) ትምህርቱን ሊተኩ በሚችሉ አማራጮች የተወሰኑ ተማሪዎችን ማስተማር
፭) ተተኪ መምህራን ሊኾኑ የሚችሉ
ተማሪዎችን መመልመልና ማሠልጠን
፮) ዩ ቲዩብ የሚባለውን መገናኛ ዘዴ በመጠቀም ከመደበኛ ትምህርቱ ለየት ያሉ አነቃቂ ትምህርቶችን ማቅረብ።
፯) ዕድሜአቸው ለትምህርት የደረሱ
ሕፃናትን ለእነሱ በሚመጥን መልኩ በማስተማር ሕፃናት ላይ መሥራት እና ሌሎችንም ጉዳዮች ለመሥራት አስባለኹና ለዚህ መድረሴ ምክንያትና አጋዥ የኾናችኹኝን ይዤ ከእስካኹን በተሻለ ግእዙን ለማዳረስ እገዛችኹ አይለየኝ።
ዐቅም ፣ ኀይል፣ ዕውቀት፣ ጥበብ አልባውን እንደ ዐቅሜ ኃይሉን፣ ብርታቱን፣ ዕውቀቱን ሰጥቶ እስከዚህ ዕለት የረዳኝ እግዚአብሔር ከዚህ የበለጠ ሥራ እንድሠራ እንደሚረዳኝ በመተማመን ከላይ የጠቅስዃቸውን ከእናንተ ጋራ በቅርበት እየተወያየኹ ለመሥራት አስባለኹ።
ግእዝን በርቀት የ፲፬ኛ ዙር መግቢያ ሊንኩ የሚከተለው ነው።
@geezdistance14
ነሐሴ ፲፯, ፳፻፲፮ ዓ.ም
🌼🌼ግእዝን በርቀት፲፬ኛ ዙር🌼🌼
▬▬▬▬🌸🌸🌸🌸🌸▬▬▬▬
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።
ሰላም ለእናንተ ይኹን!
የተከበራችኹ የግእዝን በርቀት የ፲፫ኛ ዙር ተማሪዎች ወንድሞቼና እኅቶቼ።
ግእዝን በርቀት ደረጃ ፪ ትምህርትን በዚህ ክረምት አስተምራለኹ የሚል ዕቅድ አልነበረኝም። ነገር ግን በክረምት ልሠራቸው ያሰብዃቸው አንዳንድ ጉዳዮች ቀደም ብለው በማለቃቸው፣ ወደፊትም ከሚኖረኝ ጊዜ አኹን ያለኝ ጊዜ የተሻለ ኾኖ ስላገኘኹት ቀደም ብዬ ሳላሳውቅ ድንገት መምጣቴ ለእኔም ብዙ አላሳመነኝም።
ይኹን እንጂ መዘግየቱ ከመቅረት ይሻላል በሚል መጥቻለኹ። እናንተንም በዐጭር ጊዜ እንድትመዘገቡ በመጠየቄ ይቅርታ እየጠየቅኹ፣ መልእክቱን አይታችኹ ፈጣን ምላሻችኹን በመስጠት ግእዝን በደረጃ ፪ ለመማር የተመዘገባችኹትን በርካታ ተማሪዎችን አመሰግናለኹ፤ እግዚአብሔር አክብርልኝ።
ትምህርቱ ነገ ሐምሌ ፲፭ ጧት ፲፪ ሰዓት እንደሚጀመር እየገለጽኹ ለመማር ፈቃደኛ ነን ብላችኹ መረጃውን ሞልታችኹ ለላካችኹልኝ፣ የደረጃ ፩ ትምህርትን ማጠናቀቃችኹንና የላካችኹት መረጃ ትክክል መኾኑን እያረጋገጥኹ ወደቻናሉ መግቢያ ሊንክ ለእያንዳንዳችኹ ልኬአለኹ። ምናልባት ዘንግቼ ያልላክኹላችኹ ካላችኹ እንድታሳስቡኝ እየጠየቅኹ የምዝገባ ጊዜው ግን ዛሬ ሐምሌ ፲፬ ማታ ፲፪ ሰዓት ላይ የሚጠናቀቅ መኾኑን በትሕትና እገልጻለኹ።
ሐምሌ ፲፬, ፳፻፲፮ ዓ.ም
▬▬▬▬🌸🌸🌸🌸🌸▬▬▬▬
የተከበራችኹ የግእዝን በርቀት የ፲፫ኛ ዙር ተማሪዎች እንደምን አላችኹ?
የደረጃ ኹለት ትምህርትን ለመማር የምትፈለጉ ትመዘገቡ ዘንድ በቀረበው ጥሪ መሠረት በርካታ ተማሪዎች ተመዝግባችዃል። እግዚአብሔር ያክብርልኝ። የተመዘገበው የተማሪ ቍጥር በቂ ቢኾንም የደረጃ ፩ ትምህርትን ካጠናቀቃችኹት የተማሪዎች ብዛት አንጻር ግን ጥቂት የሚባል ነው። ይህም በኹለት ምክንያቶች ይኾናል ብዬ አሰብኹ።
አብዛኛው ተማሪ ትምህርቱ ካለቀ በኋላ ቻናሉን ስለማይከታተል መልእክቱን ላያየው ይችላል። በመኾኑም እናንተ መልእክቱን ያያችኹት አብረዋችኹ ለተማሩት በተለያየ መንገድ እንድታሳውቁልኝ በትሕትና እየጠየቅኹ
በተለይ የቡድን ተጠሪዎች በየቡድናችኹ ያሉ ተማሪዎችን ስልክ በመደወልም ቢኾን መልእክቱን ሳያዩት የምዝገባ ጊዜው እንዳያልፍባቸው ብታሳውቋቸው መልካም ነው። ከእናንተ በኋላ ሌላ ደረጃ ፩ የተማረ ስሌለለ ከዚህ በኋላ ደረጃ ፪ ላይኖር ይችላል፣ ቢኖርም እንኳ ረጅም ጊዜ ሊቈይ ይችላልና ይኼንን ዕድል መጠቀሙ የተሻለ ነው ብዬ አስባለኹ።
መቼም በክፍያ ነው ስለተባለ በዚህ ምክንያት የሚቀር ተማሪ ያለ አይመስለኝም። ምክንያቱም ከአንድ ብር ጀምሮ መክፈል ትችላላችኹ የሚል
ነጻ ፈቃድ ተሰጥቷችዃልና። አንድ ብር የመክፈል ዐቅም የሌላችኹ ትኖራላችኹ ብዬ ደግሞ አልገምትም። ካላችኹም ብታሳውቀኝ እኔ ለመክፈል ዝግጁ ነኝ።
በዚህም አለ በዚያ ደረጃ ፩ ያጠናቀቃችኹ ኹሉ ይህን ትምህርት ትማሩ ዘንድ ፍላጎቴ ነው።
እኔም ያለኝ ነጻ ጊዜ ክረምቱ በመኾኑ፣ ሌሎቻችኹም እንዲሁ ይመቻችዃል ብዬ በማሰብ ጊዜው እየኼደ ነውና ትምህርቱን ቶሎ መጀመር የተሻለ ነው።
በመኾኑም የምዝገባ ጊዜው እስከ
እሑድ ሐምሌ ፲፬ , ፳፻፲፮ ዓ.ም
ማታ ፲፪ ሰዓት ድረስ ብቻ ሲኾን ትምህርቱ
ደግሞ እንደ እግዚአብሔር መልካም ፈቃድ
ሰኞ ሐምሌ ፲፭, ፳፻፲፮ ዓ.ም
ጧት ፲፪ ሰዓት ይጀመራል።
እስካኹን ደረጃ ፩ አጠናቃችኹ የተጠየቀውን መረጃ ሞልታችኹ ለላካችኹልኝ ከዚህ ሰዓት ጀምሮ እስከ እሑድ ማታ ድረስ የደረጃ ፪ መማሪያ ቻናል ሊንክን ለእያንዳንዳችኹ የምልክ ይኾናል።
ማሳሰቢያ፦
የደረጃ ፩ ትምህርትን ሳታጠናቀቅ ብዙ ተማሪዎች
የእንማር ጥያቄ ልካችዃል። ትምህርቱ የደረጀ ፩ ቀጣይና በይዘቱም ጠንከር ያለ በመኾኑ ደረጃ ፩ን ሳያጠናቅቀቁ መቀጠል ይከብዳልና ትምህርቱ የሚፈቀደው የደረጃ ፩ ትምህርትን ላጠናቀቁና ከ ፻ ውጤት ላላቸው ብቻ መኾኑን እገልጻለኹ።
እግዚአብሔር አምላክ ሰኞ ለምንወደው የግእዝ ትምህርት በሰላም ያገናኘን።
@geezachew13
የደረጃ ፪ ትምህርትን ለመማርና በፈቃደኝነት ከአንድ ብር ጀምሮ የዐቅሜን ከፍዬ ለመማር ፈቃደኛ መኾኔን እየገለጽኹ የሚያስፈልጉ መረጃዎችን እንደሚከተለው ልኬአለኹ።
◎ ስም------------------------
◎ የሚኖሩበት አገር --------------
◎ በደረጃ ፩ የተማርኹበት ዙር-----
◎ የደረጃ ፩ መለያ ቍጥር-------
◎ የደረጃ ፩ ከ፻ ውጤት -----------
@geezachew13
🌸🌸🌸🌸 ደረጃ ፪ 🌸🌸🌸🌸
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
ግእዝን በርቀት ደረጃ ፪
የተከበራችኹ የ፲፫ኛ ዙር የግእዝን በርቀት ተማሪዎች እንደምን ከረማችኹ?
እንደምታስታውሱት የደረጃ አንድ ትምህርታችንን ካጠናቀቅን በኋላ ለወራት ዝምታን መርጠን ቈይተናል።
ይኸውም በኹለት ምክንያቶች ነበር።
አንደኛው በኔ በኩል የራሴ ትምህርትና ሌሎች የሥራ ጫናዎች ስለነበሩብኝ፣ ሲኾን ኹለተኛው ደግሞ እናንተም የተማራችኹትን ትምህርት በቂ ጊዜ ወስዳችኹ በደንብ ትረዱት ዘንድ በማሰብ ነበር።
እንደምታስታውሱት በደረጃ ፩ ስንማር በርካታ ርእሶችን አኹን ላይ አንማራቸውም ፣ጊዜው አይደለም፣ ለጀማሪ አይኾኑም እያልን ያልተማርናቸው በርካታ መሠረታዊ የግእዝ ትምህርቶች ነበሩ። እነዚህ የቀሩን ትምህርቶች በደረጃ ፪ የሚዳሰሱ ሲኾኑ ትምህርቱ ከባለፈው የሚቀጥል፣ በይዘቱ ጠለቅና ጠንከር ያለ ፣ ለጀማሪ የሚኾነውን የግእዝ ትምህርትን ለተማሩ የሚሰጥ ትምህርት ነው።
በመኾኑም በተለይ ለጀማሪዎች የግእዝ ዕውቀታቸውን ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ እና
ከሞላ ጎደል የግእዝ ቋንቋን ተምሬአለኹ ለማለት የሚያስችል የደረጃ ፪ ትምህርት ተዘጋጅቷል።
ትምህርቱ እንደተለመደው የሚሰጠው ለዚሁ ዐላማ በሚዘጋጅ የቴሌግራም ገጽ ሲኾን የቈይታ ጊዜው ለኹለት ወራት ይኾናል።
የደረጃ ኹለት ትምህርቱን መማር የሚችሉት ከዚህ በፊት በ፲፪ኛ/፲፫ኛ ዙር የደረጃ አንድ ትምህርትን ተምረው ያጠናቀቁ፣ ከ፻ ውጤት ያላቸውና ስማቸው በውጤት መመዝገቢያ ዝርዝር ውስጥ የተካተቱ ብቻ ናቸው።
የደረጃ ፪ ትምህርትን በአግባቡ ለሚጨርሱም የደረጃ ፩ና ፪ ትምህርትን ማጠናቀቃቸውን የሚገልጽ የምስክር ወረቀት የሚዘጋጅ ይኾናል።
እግዚአብሔር በሕይወቴ ካደረገልኝ በርካታ መልካም ነገሮች አንዱ የግእዝ ቋንቋን በመጠኑ እንድረዳውና የማውቀውን ያኽል ለወገኖቼ እንዳካፍል ስለረዳኝ ነው። እኔም የሰጠኝን ዕውቀት በማሰብ እስካኹን ለ፭ ዓመታት፣ በ፲፫ ዙሮች በብዙ ሺሕዎች የሚቈጠሩ ተማሪዎችን በነጻ በማስተማር የዕውቀት ዐሥራት በኵራት ለማውጣት ሞክሬአለኹ።
ከዚህ በኋላ ደግሞ ለእኔ ግማሽ ለነፍስ ግማሽ ለሥጋ በሚኾን መልኩ፣ ተማሪውንም በማይጎዳና በፈቃደኝነት ላይ በተመሠረተ በተመጣጣኝ ክፍያ የግእዝ ቋንቋን ለማስተማር አስቤአለኹ።
በክፍያ ይኾን ዘንድ የታሰበበት ምክንያት፦
፩) እኔ በክፍያ የተማርኹትን የግእዝ ትምህርት ያለክፍያ በማስተማር የዕውቀት ዐሥራት በኵራትን ለማውጣት፣ ይነስም ይደግሞ እኔ ያየኹትን የዕውቀት ብልጭታ ለወንድሞቼ ለእኅቶቼ ለማሳየትና በሕይወት ዘመኔ አንዲት መልካም ነገር ለማድረግ እስካኹን ያደረግኹት ብዙ ባይኾንም በእኔ በደካማው እይታ በቂ ነው ብዬ ስላሰብኹ እና በቀጣይ በተጠናከረ መልኩ ለማስቀጠል ገንዘብ አስፈላጊ በመኾኑ
፪) ከዚህ በፊት በነጻ የተማሩት ተማሪዎች በደረጃ ፪ ትምህርት ሳይሳቀቁ በነጻነት ከፍዬ ነው የተማርኹት ብለው እንዲያስቡና ለከፈሉበትም ትምህርት ትኩረት ሰጥተው እንዲማሩ በማሰብ
፫) በኹለት ወራት የማስተማር ጊዜ ውስጥ ለተለያዩ ወጪዎችና የትምህርቱ ጊዜ የሥራ ጊዜን ስለሚሻማና እጅግ በጣም አድካሚም በመኾኑ እርሱን ለማካካስ የሚያስችል ገቢ መኖር ስላለበት እና የግእዝ ቋንቋ የትምህርቱን አሰጣጥ አኹን ካለበት ከፍ ለማድረግና በቅርቡም ተቋማዊ ለማድረግ ስለታሰበ ለርሱም ደግሞ ገንዘብ ስለሚያስፈልግ የግእዙን ትምህርትን በክፍያ ለማድረግ ታስቧል።
ክፍያውን በተመለከተ፦
ክፍያው የሚያስጨንቅ እንዳይኾን እያንዳንዱ ተማሪ በዐቅሙ ከአንድ ብር ጀምሮ የወደደውን / የፈቀደውን ሳይቸገር ይከፍል ዘንድ መጠኑ መወሰን አስፈላጊ ኾኖ አላገኘኹትም።
በተጨማሪም ክፍያው በቅድሚያ እንዳይኾንና የትምህርቱን ጥቅም አመዛዝኖ ለዚሁ ዐላማ በሚዘጋጅ የባንክ አካውንት በትምህርቱ አጋማሽ/መጨረሻ ላይ የሚከፈል በመኾኑ ነጻነትን የሚሰጥ እንደኾነ አምናለኹ።
በመኾኑም ከላይ የተጻፈውን ተረድታችኹ የደረጃ ፪ ትምህርትን በክፍያ ለመማር ፈቃደኛ የኾናችኹ ከዚህ በታች ያለውን ፎርም በመሙላት @geezachew13 ላይ ከዚህ ሰዓት ጀምሮ እንድትልኩልኝ በትሕትና እየጠየቅኹ የምዝገባ ጊዜ መጠናቀቂያና ትምህርቱ የሚጀመርበትን ቀን በቅርቡ የማሳውቃችኹ ይኾናል።
ወንድማችኹ ግዛቸው ደጀኑ
ሐምሌ ፬ ,፳፻፲፮ ዓ.ም
🌸🌸🌸🌸 ደረጃ ፪ 🌸🌸🌸🌸
🌸🌸 የመጨረሻዋ መልእክት🌸🌸
ይድረስ ለ፲፫ኛ ዙር ግእዝን በርቀት ተማሪዎች ወንድሞቼና እኅቶቼ በቅድሚያ ኹሉን ባሰብነው መልኩ እንድንፈጽም ለረዳን ለአምላካችን ለእግዚአብሔር ምስጋና ይኹን። ከዚህ በፊት አላውቃችኹም እናንተም አታውቁኝም። እኔንም እናንተንም የሚያውቀን ፈጣሪያችን እግዚአብሔር የእኔን የማስተማር፣ የእናንተን የመማር ፍላጎት አይቶ አገናኘን።
መማማር ከጀመርንበት አንሥቶ እስከ ዛሬዋ ዕለት በሙሉ ፍላጎት፣ ፍቅርና፣ በብዙ ድካም እኔ ምንም የማላውቀውን ፣ እግዚአብሔር በገለጠልኝ መጠን ግእዝን ለእናንተ ለማሳወቅ ያለ የሌለ ዐቅሜን ፣ጊዜዬን ተጠቅሜ የቻልኹትን ያኽል ዘርቻለኹ። የልፋቴንም ውጤት በተለያየ ጊዜ በሰጠኋችኹ ፈተና እና መልመጃ ውጤት አይቻለኹ።
ለማስተማር ሳስብ ይጨንቀኛል። እኔ ምን ዐውቄ ነው? ስንት ሊቃውንት ባሉባት አገር እኔ ግእዝን ላስተምር? ብዬ ከራሴ ጋር እሟገታለሁ። ደግሞ እንዳልተወው ውስጤ ዕረፍት ይነሣኛል። ምን አለበት! እኔ የማውቃትን ያኽል ለሌሎች ባካፍል! የግእዝን መንገድ ባሳያቸው እልና ይኸኛው ዐሳቤ ያሸንፋል። አሸንፎም ይኸው እናንተን የመሰሉ የተደበቁ ዕንቊ የግእዝ ሰራዊትን ለማግኘት ቻልኹ።
ያለምንም ማጋነን ኹላችኹም እጅግ በጣም በጣም ጎበዞች፣ ታታሪዎች፣ ታማኞች ቁርጠኛ የግእዝ ወዳጆች መኾናችኹን ዐይቻለኹ። ግእዝን በእንዲኽ ዐይነት ውጤት መጨረሳችኹ ያስቀናኛል። ታማኝነታችኹ፣ ታዛዥነታችኹ ወደር የለውም። እኔን አክብራችኹ የምላችኹን ኹሉ እሽ እያላችኹ ስታደርጉ ነበርና።
በየቀኑ ለኹለት ወራት፣ አይደለም ለመረዳት ለማንበብ እንኳን የሚያዳግተውን ጽሑፌን ባላችኹበት የስደት አገር ከሥራ ጋር፣ ከአገር ናፍቆት ጋር፥በአገር ውስጥ ያላችኹም ከኑሮ ጋር ትግል በኾነበት፣ የሚያስጨንቁ ነገሮች በበዙበት ዘመን ፥ እናንተ ግን ትግላችኹን ከግእዝ ጋር አድርጋችኹ አብራችኹኝ እስከ መጨረሻው ስለዘለቃችኹ ከልብ አመሰግናችኋለኹ።
የግእዝ ቋንቋ ሞቷል፣ የቄስ ቋንቋ ነው ወዘተ... ይባል የነበረው እናንተን ከግእዝ ጋር በማገናኘቴ፣ መንገዱን በማሳየቴ ፣ የማውቀውን በማካፈሌ በሺሕዎች የሚቈጠሩ የግእዝ ሰራዊትን በማፍራቴ በሕይወቴ ውስጥ ትልቁን የሕሊና ርካታን አግኝቼበታለኹ። እናንተም የግእዝ ቋንቋ የኹሉም መኾኑን አስመስክራችኋል። በመቀጠል ታናሽም
ብኾን ጥቂት ምክር ልለግሳችኹ።
▪ ግእዝን ዐውቀናል ብላችኹ እንዳትዘናጉ፣ ቋንቋውን በደንብ ለመረዳት የሚቀራችኹ አለና። ግእዝን አናውቅም ብላችኹ እንዳትሳቀቁ፥ ግእዝን በቀላሉ መማር እንደሚቻል አይታችዃልና በትምህርቱ ግፉበት። የነብራን ጅራት ከያዙ አይለቁ፣ ከለቀቁ... እንዲሉ ጅራቱን አስጨብቻችዃለኹና እንዳትለቁ።
▪ የፊደላትን ነገር አደራ። ቢያንስ በተለያዩ ትምህርቶቻችን ያየናቸውን ተጠንቅቃችኹ ጻፉ። ሊቃውንትን ጠይቁ፣ መጻሕፍትን አንብቡ።ለኔ ግእዝን ማወቅ ሰዋሰው ማወቅ ብቻ አይደለም። ፊደላትን ጠንቅቆ መጻፍም እንጂ!
▪ስለ ግእዝ ቋንቋ በየኼዳችኹበት ተናገሩ። በአጋጣሚዎች ኹሉ ግእዝ ግእዝ በሉ። ያልተማሩት ኹሉ እንዲማሩ ወደ ግእዝ መምህራን አድርሷቸው። በየጨዋታችኹ አጀንዳ አድርጉት። የተኛው ይነሣ፣ የፈዘዘው ይንቃ፣ የቆመው ይራመድ።በኛ ዘመን የግእዝ ትንሣኤ ኾኖ እናይ ዘንድ የምንችለውን ኹሉ እናድርግ።
▪ የተማራችኹትን አንድ በአንድ በተግባር ተለማመዱ፣ እርስ በርስ ተጠያየቁ፣ ተነጋገሩ የተማራችኹትን ወደኋላ ተመልሳችኹ ከተጨማሪ መጻሕፍት ጋር አንብቡ። አትለያዩ ኹሌም ፍቅራችኹ ጸንቶ ከኔ ጋር አንድ እንደነበርን አብራችኹ ቀጥሉ። እግዚአብሔር አንዴ አገናኝቶናልና። በስሜ የተከተፈተ በመኾኑ
ቡድናችኹን ለተከፈተበት ዐላማ በአግባቡ ተጠቀሙበት።
▪አንዳንድ ሰው ግእዝ ለ፪ ወር ተምሬ ጨረስኹ ብትሉት ምንም ላይመስለው ይችላል። ስላልገባው ነው። ለኛ ግን ክብራችን፣ የቤተክርስቲያናችን ልሳን፥ የጥበባት መገኛ፣ ብሔራዊ ኩራታችን በመኾኑ የበለጠ ክብር ልንሰጠው ይገባል።
▪ የትም ይኹን የትም ለቃላችኹ ታማኝ ኹኑ።
ማመን፣ መታመንን የመሰለ ጸጋ የለም።
እግዚአብሔርን አጋዥ አድርጋችኹ ጀምሩ
እሱ ያስፈጽማችኋልና። በማንኛውም ኹኔታና
ቦታ አድርጉ የተባላችኹትን በማድረግ ፣ አታድርጉ የተባላችኹትን ባለማድረግ ታዛዦች ኹኑ። ለራስ ታምኖ ለሰውም ታማኝ መኾን ትልቅ ጸጋ ነውና። ብዙዎች ወንድሞች እና እኅቶች ከእናንተ ጋር ጀምረው በተለያያ ምክንያት አቋርጠዋል። እናንተ ደግሞ እኩል ብትጠሩም በርትታችኹ ለፍጻሜ በመብቃታችኹ ፍሬን አፍርታችኋል። ይኽ የድካማችኹ ውጤት ነው። ያለ ድካም ዋጋ አይገኝምና። ለዚች ቀን ለመድረስ ብዙ ውጣ ውረዶችን አሳልፈናልና።
▪ ታናሽም ይኹን ታላቅ ሲያዝዟችኹ ታዘዙ፣
ጊዜአችኹን በአግባቡ ተጠቀሙ ከራሳችኹ አልፎ ለሌላውም ትጠቅማላችኹና፥በተሠማራችኹበት የሥራ መስክ፣በዋላችኹበት ውሎ ኹሉ ለሰው መልካምን ዐስቡ።
ሀበሻ ጊዜ አያከብርም የሚለውን አባባል አትቀበሉ ይልቁንም እናንተ ሰዓት አክባሪ ኾናችኹ ሀበሻ ሰዓት አክባሪ ለመኾኑ አብነት ኹኑ።
መልካምን ለሰው ልጅ ኹሉ አድርጉ። ታዲያ መልካም ነገር ስታደርጉ ከሰው ምንም አትጠብቁ፣ መልካምነታችሁን ያለ ዋጋ አድርጉት። የዘላለም ደስታን ታገኙበታላችኹና።
▬▱▬▱▬▱▬
በቈይታችን ከጥያቄ ውጪ ሌላ ነገር ምንም እንዳትጽፉ ተከልክላችኹ ነበር። ጊዜው ስላልነበረ ነው። አኹን ደግሞ ስለ ትምህርቱ ያላችኹን ማንኛውንም አስተያየት ትሰጡ ዘንድ ጊዜው ነውና ከትምህርቱ ያገኛችኹትን ጥቅም ካለ ፣ መጀመሪያ ስንጀምር የነበራችኹን ስሜትና መጨረሻ ላይ ያላችኹን ስሜት በዝርዝር @geezachew13 ላይ ብትጽፉልኝ መልስ ባልጽፍላችኹም ጊዜ ወስጄ አነበዋለኹ።
▬▱▬▱▬▱▬
በመጨረሻም እኔ ታናሽ ስኾን ከእናንተ ከታላላቆቼ ጋር እንደ ታናሽ ተጨቃጭቀናል፣ ተነጋግረናል፣ አዝዣችኋለሁ፣ መክሬአችኋለኹ፥ ተቈጥቻችኋለኹ።
ይህን ኹሉ ለማድረጌ ምክንያቴ አንድ እና አንድ ነበር ትምህርታችኹን በደንብ ተከታትላችኹ ለዚች ቀን ደርሳችኹ አይ ዘንድ ነበር። ሌላ ምንም ምክንያት አልነበረኝም። ከድካሜ የተነሣ ማገዝ ባለብኝ መጠን አላገዝዃችኹም፣ በፍቅር፣ በትሕትና አላስተናገድዃችኹምና እባካችኹን እንዳትሰናከሉብኝ። ይህ የኔ የግል ድክመት ነው።
በመኾኑም ባሳለፍናቸው የ፪ ወራት ቈይታችን በአንድም በሌላም ምክንያት ያስቀየምኳችኹ፣ የተቈጣኋችኹ፣ ቀና መልስ ያልመለስኹላችኹ፣ ያሳዘንኳችኹ በሙሉ በይቅር ባዩ በአምላካችን እግዚአብሔር ስም ይቅርታ ታደርጉልኝ ዘንድ በታላቅ ትሕትና እጠይቃለኹ።
ስብሐት ለእግዚአብሔር ወለወላዲቱ ድንግል ወለመስቀሉ ክቡር አሜን!!!
ትምህርታችን ስንጀምር በጸሎት ነበርና ስንፈጽምም በምስጋና ይኾን ዘንድ ይኽን ኹሉ ያደረገ አምላካችን ልዑል እግዚአብሔርን አባታችን ሆይ ብለን እናመስግነው።
ታናሽ ወንድማችኹ፦
ግዛቸው ደጀኑ መኰንን
ግንቦት ፭ , ፳፻፲፮ ዓ.ም
🌸🌸የመጨረሻዋ መልእክት🌸🌸
▬▬▬▬🌸🌸🌸🌸🌸▬▬▬▬
🌷በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ
ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን 🌷
የማጠቃለያ ውጤት
የተከበራችኹ ግእዝን በርቀት የ፲፫ኛ ዙር ተማሪዎች ወንድሞቼ እና እኅቶቼ
ለኹለት ወራት የተማማርነውን መሠረታዊ የግእዝ ቋንቋ ትምህርት (ለጀማሪዎች ) ፥ ምን ያኽሉን ዐውቀነዋል፣ ተረድተነዋል የሚለውን ለመገምገም በአራት ፈተናዎች እና መልመጃዎች ራሳችንን መዝነናል።ትምህርት ካለ ፈተና፣ ፈተና ካለ ውጤት ፣ ውጤት ካለ ደግሞ ደረጃ ይኖር የግድ ነውና ከ ፻ ያመጣችኹትን ውጤት ከዚኽ ቀጥሎ አያይዛለኹ።
ደጋግሜ እንደገለጽኹት በዚህ ዙር ውጤታችኹ የሠፈረው ሙሉ ትምህርቱን ተከታትላችኹ፣ ፈተናውን ተፈተናችኹ እና አርማችኹ የላካችኹትን ተማሪዎች ብቻ ነው።
ትምህርቱን ተምራችኹ፣ፈተናም ተፈትናችኹ ውጤት ያልላካችኹ ግን ስማችኹ አልተካተተም። ይህ ማለት አልተማራችኹም ማለት አይደለም ወደፊት በማንኛውም ጊዜ ውጤቱን ስትልኩ እኔ ሞልቼ ፋይል አድርጌ አስቀምጠዋለኹ።
እኔ በምችለው ዐቅም አሟልታችኹ የላካችኹልኝን ውጤት በትክክል ለመሙላት ጥረት አድርጌአሉኸ። ምናልባት እኔ ስጽፍ የተሳሳትኹት፣ ያልሞላኹላችኹ ካላችኹ ከወዲኹ ይቅርታ እየጠየቅኹ የሚስተካከል ካለ በግል @geezachew13 ብትጠቁሙኝ እኔ ጋር አስተካክዬ ሞልቼ አስቀምጠዋለኹ።
ከዚኹ ጋር ተያይዞ በታማኝነት ራሳችኹን ፈትናችኹ አርማችኹ፣ ውጤት ሞልታችኹ መላካችኹ ትልቅ ነገር ነው። በእውነት ከእናንተ ከተማርኹት ነገር ውስጥ #ታማኝነት እና #ታዛዥነት ዋና ዋናዎቹ ናቸው። ስለ ታማኝነታችኹ ሳላመሰግናችኹ አላልፍም። አድርጉ የምላችኹን ኹሉ አብዛኛዎቻችኹ ስታደርጉ ነበርና።
ግእዝን በርቀት በ፲፫ኛ ዙር ለመማር የተመዘገባችኹ ከ11,000 በላይ ብትኾኑም የተዘራው ኹሉ አይበቅልምና በተለያየ ምክንያት ጀምራችኹ ያቋረጣችኹ፣ የተወሰነ መንገድ ተጉዛችኹ ያቋረጣችኹ፣ እስከመጨረሻውም የጸናችኹ አላችኹ። ከአንድ በላይ ፈተና ያልተፈተኑ፣ ትምህርቱን ወጣ ገባ እያሉ የተማሩ፣ ውጤት አርመው ያልላኩ እጅግ በርካታ ናቸው። አጠቃላይ ያየኹት ውጤት እጅግ በጣም የሚያስደስት ሲኾን በዚህም ድካሜ ከንቱ እንዳልቀረ በቂ ማሳያ ኾኖኛል።
ከዚህ በመቀጠል ከ፲፫ኛ ዙር ግእዝን በርቀት ተማሪዎች መካከል እጅግ ከፍተኛ ውጤት ያመጡትን በደረጃ ከአንደኛ እስከ ሦስተኛ የወጡትን ማለትም (101 ፣ 100 እና 99 ) ያመጡትን እንደሚከተለው አሳውቃለኹ።
▪ ከነዳረጎቱ ፻፩ / ፻ በማምጣት
የየግእዙን ደረጃ በመያዝ ያጠናቀቀች
🥇919 ➝ አስካለ ገረመው ተሰማ
እኅታችን ከቡድን ፯ ናት።
▪ከመቶ መቶ(፻/፻ ) በማምጣት
በኹለተኛ ደረጃ ያጠናቀቁት ተማሪዎች
🥈153 ➝ ቅድስት እንየው
🥈726 ➝ መቅደላዊት ገብሬ ዓይናለም
🥈1080➝ ስንዱ አገኝ ዘሪሁን
🥈442 ➝ሃይማኖት ገብረ እግዚአብሔር
🥈921 ➝ ፋሲካው መልካሙ ወርቅነህ
🥈973 ➝ ናሆም አመለወርቅ ለማ
🥈1048 ➝ ያሬድ ወለላው ነገሠ
🥈413 ➝ መላኩ ደረሰ ጥጋቡ
🥈1105 ➝ ኤልያስ ውድነህ ታከለ
🥈310 ➝ አሸናፊ ውቡ ባዜ
▪ ከመቶ ዘጠና ዘጠኝ (፺፱/፻ ) በማምጣት በሦስተኛነት ያመጡ
🥉151➝ ብንያም ሲሳይ በላይ
🥉389 ➝በላይነሽ አዳሙ ጫኔ
🥉462 ➝ ደረጀ ጌታነህ አያሌው
🥉741 ➝እሴተ ሥላሴ(እሴተ አያሌው)
🥉868 ➝ አንዱዓለም ሰሎሞን ለገሰ
🥉992 ➝ መሉቀን አስፋው ኃይለ
🥉1177 ➝ ደስታ ዮሐንስ
▪▪▪▪▪▪▪▪
ትምህርቱ የግእዝ ቋንቋ ነው። እንዲህ ዐይነት ውጤት ማየት በእውነት ምንኛ ያስደስታል !!! የሚገርመውዋንጫውን የወሰደችው ሴት መኾኗ ነው። ይህ ላስተዋለው ትልቅ ትምህርት ነው።
በአጠቃላይ ለእኅቶቻችንና ለወንድሞቻችንም እንኳን ደስ አላችኹ ማለት እፈልጋለኹ።
እግዚአብሔር በሚያውቀው ኹላችኹንም ብሸልም ምንኛ ደስ ባለኝ! ነገር ግን ዐቅሜ ውስን ኾነና መጀመሪያ ላይ በከፍተኛ ውጤት (ከ ፩-፫) የሚጨርሱትን እሸልማለሁ ብዬ ለራሴም ለእናንተም በገባኹት ቃል መሠረት ቃሌን ለመፈጸምና የተሰማኝን ደስታ ለመግለጽ ፻፩፥ ፻ እና ፺፱ ያመጣችኹትን ተማሪዎች እሸልም ዘንድ ይገባኛልና በአጠቃላይ ለ ፳፭ ተማሪዎች ሽልማትን በየስማችኹ አዘጋጅቻለኹ። እርሱንም #በየግል አድራሻችኹ አሳውቃችኋለኹ።
በተረፈ ለኹላችኹም የሚኾን የብራና መጻሕፍት ሽልማትን ደግሞ መጨረሻ ላይ አያይዛለኹ።
◼️በመጨረሻም በ፲፫ኛ ዙሮች ልዩ ተሸላሚዎች አሉኝ። እነሱም ዕድሜ ሳይገድባቸው፣ ከትምህርት ዓለም ከራቁ ቢቈዩም ከእናንተ ከወጣቶቹ ጋር እኩል ታግለው ግእዝን በመማር እና በከፍተኛ ሞራል በማጠናቀቅ እንዲኹም በውጤት ደረጃም ጥሩ ውጤት በማምጣት ላጠናቀቁ ዕድሜአቸው ከ 65 ዓመት በላይ የኾኑ አባቶቼንና እናቶቼን በክብር መሸለም እፈልጋለኹ። ለእኛ ለወጣቶችም አርኣያ ናቸውና።ጽናታችኹን፣ ትጋታችኹን አደንቃለኹ። እግዚአብሔር ረጅም ዕድሜና ጤና ይስጥልኝ። ዕድሜአችኹን በቅርብ ጠይቄ የላካችኹልኝ።
መ.ቍ ➝ ስም ➝ ዕድሜ
◎ 706 ➝ አሥራት ተስፋዬ ውቤ 75
◎ 1233 ➝ ጌታቸው በለጠ 67
◎ 186 ➝ ሕገመንግሥት ሠናይ ቦጋለ 65
◎ 725 ➝ ጣሰው በቀለ በላቸው 71
◎ 363 ➝ ወንድማገኘሁ ደምሴ 65
◎ 312 ➝ ዲ/ን ደቅስዮሶ ሽብሩ 67
◎ 961 ➝ አልማዝ ዘውዴ 65
እንዲኹም የሕፃንነት ዕድሜአችኹ ሳያታልላችኹ ጓደኞቻችኹ ሲጫወቱ እናንተ ግን ግእዝን እንማር ብላችኹ ከእናት ከአባት፣ ከአያቶቻችኹ ጋር ተምራችኹ በጥሩ ውጤት ላጠናቀቃችኹ የነገ አገር ተረካቢዎች፣ የቤተክርስቲያን ተስፋዎች፣ የመምህራን ተተኪዎች ዕድሜአችኹ 14 ዓመት እና በታች ለኾናችኹ የክብር ሽልማቴን አደርሳለኹ። ይህን ላደረጋችኹ ወላጆቻቸውም ልዩ ክብር አለኝ። በጧቱ ልጆቻችኹን ወደሚጠቅማቸው እየመራችዃቸኹ ናቸውና።
መ.ቍ ➝ ስም ➝ ዕድሜ
◎ 431 ➝ ረድኤት ተ/ሐዋርያት 14
እኛ እናልፋለን፤ እናንተ ደግሞ ትተካላችኹና ስለ ግእዝ ቋንቋ መነሣት በዘመናችኹ ኹሉ የምትችሉትን ኹሉ ታደርጉ ዘንድ አደራዬ የጸና ነው።
በመጨረሻም ግእዝን በርቀት እስካኹን በኹሉም ዙር የተማሩ የተሰባሰቡበት የቴሌግራም ቡድን አለ " ግእዝን በርቀት የኹሉም ዙር ተማሪዎች"። እናንተም ትምህርቱን ያጠናቀቃችኹ በቀጣዩ ሊንክ
https://t.me/geezinberiket
መቀላቀልና ዐብራችኹ መሳተፍ ትችላላችኹ።
▬▬▬▬🌸🌸🌸🌸🌸▬▬▬▬
▬▬▬▬🌸🌸🌸🌸🌸▬▬▬▬
ግእዝን በርቀት በ፲፫ኛ ዙር ከተማሩ ተማሪዎች መካከል እጅግ ከፍተኛ ውጤት በማምጣት በ፩ኛ ደረጃ ያጠናቀቀ/ያጠናቀቀች...
Loading ........ 😁
ዛሬ ማታ ከምሽቱ ፬ ሰዓት ላይ ጠብቁኝ።
▬▬▬▬🌸🌸🌸🌸🌸▬▬▬▬
▬▬▬▬▬🌸🌸🌸▬▬▬▬▬
የተከበራችኹ የግእዝን በርቀት የ፲፫ኛ ዙር ተማሪዎች
የማጠቃለያ ፈተና ውጤታችኹን እና ሌሎች ውጤታችኹን ባለፈው በፎርሙ ከላካችኹት ጋራ አያስተያየኹ የብዙዎቻችኹን በትክክል ለማደረጀት ሞክሬአለኹ። ትምህርቱን ከማስተማሩ በተጨማሪ ውጤት ማጠናከሩ በጣም ከባድ ነው። የበለጠ የሚያከብደው ደግሞ ተማሪዎች ውጤታችኹን በወቅቱ አርማችኹ ባለማስቀመጣችኹ፣ በፎርሙ እና ከ100 የላካችኹት መለያየቱ፣ እና በተጠየቃችኹበት ጊዜ የተሟላ መረጃ አለመስጠታችኹ ነው።
እውነቱን ስናገር እስካኹን ከ፩ኛ ዙር ጀምሮ እስከ ፲፫ ዙር ካስተማርዃቸው ተማሪዎች መካከል በትምህርት ቈይታዬም ኾነ ውጤትን በተመለከተ በጣም አድካሚና አስቸጋሪ የኾናችኹብኝ የ፲፫ኛ ዙር ተማሪዎች ናችኹ።
የተጻፈ አታነቡም፣ በተዛዛችኹት መሠረት አታደርጉም፣ .... ኹለት ዙር ላስተምርበት የምችለውን ዐቅሜን አባክናችኹበኛል።
ይህን ስል ኹላችኹንም አይደለም። ያው "ለኀጥኣን የወረደ ለጻድቃን ይተርፋል" ይባል የለ። እግዚአብሔር ይመስገን እንደምንም አልቋል።
ከሞላ ጎደል የእያንዳንዳችኹን የማጠቃለያ ውጤት አስገብቼ ወደማጠናቀቁ የደርስኹ ቢኾንም ከ120 በላይ ተማሪዎች የማጠቃለያ ፈተናውን ተፈትናችኹ ውጤቱን ግን እስካኹን ያልላካችኹልኝ አላችኹ። መቼም ተማሪ ስለኾንኹ የውጤትን ነገር አውቀዋለኹና ኹለት ወር ሙሉ የደከማችኹበት ውጤት ሳይመዘገብ፥ ስማችኹ ካጠናቀቁ ተማሪዎች ስም ዝርዝር ውስጥ ሳይካተት ከሚቀርባችኹ እስከ ዛሬ (ግንቦት ፭) ማታ ፲፪ ሰዓት ድረስ ብቻ ውጤት ያልላካችኹ ትልኩልኝ ዘንድ የመጨረሻ መልእክቴን አስተላልፋለኹ።
ከተጠቀሰው ሰዓት ውጪ ግን የተላኩልኝን ብቻ በስም ዝርዝር ውስጥ አካትቼ የአጠቃላይ የተማሪውን ውጤት የማሳውቅበት በመኾኑ ቀደም ብላችኹ ትልኩልኝ ዘንድ በትሕትና እጠይቃለኹ።
መልካም ጊዜ
▬▬▬▬▬🌸🌸🌸▬▬▬▬▬
▬▬▬🌸🌸🌸🌸🌸▬▬▬
ለመጨረሻ ጊዜ የሚሞላ መረጃ
በፎርሙ መሠረት የላካችኹልኝን ውጤት አስተካክያለኹ። ነገር ግን አንዳንድ ተማሪዎች ውጤት ስትሞሉ እኔ ከመዘገብኹት አንጻር ልዩነት አለው። በመኾኑም የመጨረሻ ማመሳከሪያ ይኾነኝ ዘንድ የሚከተለውን በትክክል ሞልታችኹ @geezachew13 ላይ ላኩልኝ።
◦ መለያ ቍጥር ----------
◦ ሙሉ ስም --------------
◦ ውጤት ድምር ከ 70--------
◦ ማጠቃለያ ከ30-----------
ድምር ከ 100 ----------
▪▪▪▪
ባለፈው ፎርሙን ላልሞላችኹ ደግሞ በቀጣዩ መሠረት ሞልታችኹ @geezachew 13 ላኩልኝ።
◦ መለያ ቍጥር ----------
◦ ሙሉ ስም --------------
◎ የፈተና ፩ ውጤት ከ20
◎ የፈተና ፪ ውጤት ከ20
◎ የቡድን መልመጃ ከ 10
◎ የፈተና ፫ ውጤት ከ20
◎ ድምር ከ 100 ----------
▬▬▬🌸🌸🌸🌸🌸▬▬▬
🌷በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን 🌷
🌸🌸 የማጠቃለያ ፈተና መልስ🌸🌸
ሰላም ለእናንተ ይኹን፡፡
በኢትዮጵያ ሰዓት አቈጣጠር ቅዳሜ ግንቦት ፫፥ ፳፻፲፮ ዓ.ም ማታ ፲፪ ሰዓት ነው። የማጠቃለያ ፈተና ትክክለኛ መልስ ከዚህ በታች የተዘረዘረው ሲኾን የሠራችኹትን በመልሱ መሠረት በኢትዮጵያዊ ጨዋነት፣ በታማኝነት ከ ፴ በማረም @Geezachew13 ላይ ላኩልኝ። ውጤቱን አርማችኹ ካልላካችኹ ግን መሙላት አልችልም።
▪▪▪▪▪▪▪▪▪▪
፩) ሐሰት
ስሞች ተሳቢ ለመኾን በሣልስ የጨረሱ የሚቀየሩት ወደ ኀምስ ፊደል እንጂ ወደግእዝ ፊደል አይደለም፡፡
፪) ሐሰት
በግስ ላይ እየወደቁ ግሱን ከማሰሪያ አንቀጽነት የማያስቀሩ አገባባት ንኡስ አገባባት ይባላሉ።
በግስ ላይ እየወደቁ ግሱን ከማሰሪያ አንቀጽነት የሚያስቀሩ አገባባት ዐቢይ አገባባት ይባላሉ።
፫) እውነት
ግስ የሚነሣባቸው ፊደላት ዐምስት ብቻ ናቸው፡፡ በካዕብና በሣልስ የሚነሣ መደበኛ ግስ የለም፡፡
፬) እውነት
፭) ሐሰት
ት የተባለውን ሥርወ ፊደል የሚጠቀሙ መራሕያን ዐምስት ናቸው፡፡ ይእቲ እና አራቱ 2ኛ መደብ መራሕያን ናቸው፡፡ ምንም እንኳን በአራቱ መራሕያን ትእዛዝ አንቀጽ ት ቢጎርድም በይእቲ ትእዛዝ አንቀጽ ግን አይጎርድም፡፡ ጥያቄው ት በሚጠቀሙ በኹሉም መራሕያን ስለሚል ሐሰት ይኾናል።
፮) እውነት
▱▱▱▱▱▱▱▱
ትእዛዝ ❷ ለሚከተሉት ጥያቄዎች ትክክለኛ መልስ የያዘውን ፊደል ምረጡ።
(እያንዳንዱ ጥያቄ ፩ ነጥብ ዋጋ አለው)
፯) በ ➝ ማእዜ
፰) ገ ➝ በአበገደ 20ኛ፣ በሀለሐመ 24ኛ
፱) በ) ➝ ኪያክን
ተሰሓቢያዊ ተውላጠ አስማት የሚባሉት ኪያሁ፣ ኪያሃ፣ ኪያሆሙ፣...
፲) በ) ➝ ከይሴ
ከይሲ(እባብ) ➛ ከይሴ (እባብን)
፲፩) ደ ➝ ሳኒታ ➺ ዛሬ
፲፪) በ ➝ ዘንጋዕኪ
ዘንገዐ የተባለው ግስ በ ዐ ፊደል በመጨረሱና ቅድመ መድረሻው ሳድስ በመኾኑ በአንቲ መራሒ ሲረባ ሳድሱ ወደ ራብዕ ተቀይሮ፣ የመጨረሻው ፊደል ሳድስ በማድረግ ኪ ፊደል መጨመር ነው፡፡ አንቲ ➝ ዘንጋዕኪ፡፡
፲፫) ገ ➝ አንበበ ፣ መጽሐፈ
፲፬) በ ➝ እለ
◦ ዘ ➛ለነጠላም፣ ለብዙም ቍጥር
◦ እለ ➛ ለብዙ ቍጥር ብቻ
◦ እንተ ➛ ለነጠላ ቍጥር ብቻ ይቀጸላሉ፡፡
፲፭) ደ ➝ ትንቢት አንቀጽ
ደንገፀ የተንበለ ቤት በመኾኑ እንደተንበለ ይረባል፡፡ በአንቲ መራሒ የተንበለ ትንቢት አንቀጹ ትተነብሊ በመኾኑ ትደነግፂ የሚለው ትንቢት አንቀጽ ነው፡፡
◦ ትተነብሊ ➛ ትተንብሊ ➛ ተንብሊ
◦ ትደነግፂ ➛ ትደንግፂ ➛ ደንግፂ
፲፮) አ ➝ አሳደገ
፲፯) በ ➝ መንኖ/መንኖት
የቀደሰ አርእስት ቀድሶ/ቀድሶት በመኾኑ የመነነ አርእስት መንኖ/መንኖት ይኾናል ማለት ነው፡፡
፲፰) አ ➝ ሲጋርድ
፲፱) በ ➝ ትንቢት አንቀጽ
ክህለ ➳ ይክህል ➳ ይክሀል ➳ ይክሀል
፳) ገ ➝ እንዲመጡ
፳፩) ሀ ➝ ኹሉም
፳፪) ደ ➝ መንግሥት
◦ መምህር ➳ የመሀረ ባዕድ ዘር ነው፡፡
◦ ክብር ➳ የከብረ ዘመድ ዘር ነው፡፡
◦ ቅዳሴ ➳ የቀደሰ ጥሬ ዘር ነው፡፡
◦ መንግሥት ➳ የነግሠ ባዕድ ከምእላድ ዘር ነው፡፡
◦ ሃይማኖት ➳ የሀይመነ ምእላድ ዘር ነው፡፡
፳፫) ገ ➝ አነ
፳፬) አ ➝ ኀደርክን
▱▱▱▱▱▱▱▱
ትእዛዝ ❸ ትክክለኛውን መልስ ጻፉ፡፡
(ዐሥራ ኹለቱ ጥያቄዎች 6 ነጥብ ዋጋ አላቸው፡፡ ይኸውም እያንዳንዱ ጥያቄ ½ ነጥብ ዋጋ አለው)
ሠለሰ ➾ ሦስት አደረገ
የቀደሰ ቤት
፩) ትንቢት ➝ ይሤልስ
፪) ዘንድ ➝ ይሠልስ
፫) ትእዛዝ ➝ ይሠልስ
፬) አርእስት ➝ ሠልሶ / ሠልሶት
፭) ሣልስ ቅጽል ለወ ➝ ሠላሲ
፮) ሣልስ ቅጽል ለብወ ➝ ሠላስያን
፯) ሣልስ ቅጽል ለሴት ➝ ሠላሲት
፰) ሣልስ ቅጽል ለብሴ ➝ ሠላስያት
፱) ሳድስ ቅጽል ለወ ➝ ሥሉስ
፲) ሳድስ ቅጽል ለብወ ➝ ሥሉሳን
፲፩) ሳድስ ቅጽል ለሴ ➝ ሥልስት
፲፪) ሳድስ ቅጽል ለብሴ ➝ ሥሉሳት
ማስታወሻ፦
፩) ኹሉም ጥያቄዎች የተዘጋጁት ከተማራችኹት ነውና በቀረበው መልስ ዙሪያ ተጨማሪ ማብራሪያ ከፈለጋችኹ ለእያንዳንዱ ጥያቄዎች በሰማያዊ ቀለም የተቀለመውን ስትጫኑት ወደትምህርቱ ይወስዳችዃል።
፪) አንድ ተማሪ ስሙ የ፲፫ኛ ዙር ተማሪዎች ስም ዝርዝር ውስጥ የሚካተተው ማጠቃለያ ፈተናውን ጨምሮ ኹሉንም ፈተናዎች የተፈተነ፣ መለያ ቍጥር ያለውና የፈተናዎችን ውጤት አርሞ የላከ ብቻ ነው። በመኾኑም ደጋግሜ እንደምለው በኋላ ስሜ ለምን አልተካተተም እንዳትሉ በወቅቱ የተፈተናችኹትን ውጤት በአስቸኳይ ላኩልኝ።
፫) አንዳንድ ተማሪዎች በፎርሙ ላይ የጻፋችኹት መለያ ቍጥር ትክክል አይደለም። ምንም መለያ ቍጥር ሳይሰጣችኹ በአንዱ መለያ ቍጥር የላካችኹ አላችኹ። አግባብነት፣ ተቀባይነት የለውም። ተማሪም ሳትኾኑ ሊንኩን ከየት እንዳገኛችኹት ባላውቅም ኹሉንም 20 ሞልታችኹ የላካችኹ አላችኹ። አሳዛኝ ነው። ለእኔም ይህን መለየት በጣም አድካሚ ቢኾንም እንዲህ ያደረጋችኹትን ለይቼ አውቄአለኹ።
፬) የቡድን ተጠሪዎች ለፈተና ዝግ ኾኖ የቈየውን ቡድናችኹን እንድትከፍቱ እየጠየቅኹ ከዚህ በኋላ ቡድኑን በኀላፊነት ማስተዳደር ሙሉ በሙሉ የእናንተ ድርሻ ነው። የምትጠቀሙበት ግእዝና ግእዝን በተመለከተ ብቻ ነው።
በስሜ ስለተከተፈተ ከዚህ የወጣ መልእክት እንዳይተላለፍበት በአግባቡ ትጠቀሙበት ዘንድ አደራ እያልኹ፣ አይ ከግእዙ ውጪ የፈለግነውን መጻጻፍ እንፈልጋለን ካላችኹ ደግሞ በራሳችኹ መንገድ ከእኔ ዕውቅና ውጪ የኾነ ገጽ ከፍታችኹ መጠቀም ትችላላችኹ።
ውጤታችኹን ቶሎ ለጥፌ እንሰነባበት ዘንድ ኹሉም ተማሪዎች ቶሎ አርመው እንዲልኩልኝ በየቡድናችኹ አነቃቁልኝ።
፭) በተለያየ ምክንያት ፎርሙን ያልሞላችኹ ከታች ያለውን ሞልታችኹ @geezachew13 ላይ በተለመደው መልኩ ላኩልኝ። ከዚህ ቀደም የሞላችኹ ደግሞ ከ70 እና ከ 100 የሚለውን ላኩልኝ። ምክንያቱም በፎርሙ እና እኔ በመዘገብኹት መካከል ብዙ ልዩነት አግኝቻለኹና።
፮) ትምህርቱን ተከታትላችኹ ያጠናቀቃችኹና ከ100 ውጤት ያላችኹ ዕድሜአችኹ 14 ዓመትና ከዚያ በታች እንዲኹም ዕድሜአችኹ 65 እና ከዚያ በላይ የኾናችኹ ተማሪዎች @geezachew13 ላይ ስማችኹንና ዕድሜአችኹን ላኩልኝ።
🌸🌸የማጠቃለያ ፈተና መልስ🌸🌸
