en
Feedback
ግእዝን በርቀት ፲፫ኛ ዙር መጋቢት ፳፻፲፮ ዓ.ም

ግእዝን በርቀት ፲፫ኛ ዙር መጋቢት ፳፻፲፮ ዓ.ም

Closed channel
7 213
Subscribers
No data24 hours
-107 days
-8030 days

Data loading in progress...

Similar Channels
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Tags Cloud
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Incoming and Outgoing Mentions
---
---
---
---
---
---
Attracting Subscribers
November '25
November '250
in 0 channels
October '250
in 0 channels
Get PRO
September '250
in 0 channels
Get PRO
August '250
in 0 channels
Get PRO
July '250
in 0 channels
Get PRO
June '250
in 0 channels
Get PRO
May '250
in 0 channels
Get PRO
April '250
in 0 channels
Get PRO
March '250
in 0 channels
Get PRO
February '250
in 0 channels
Get PRO
January '250
in 0 channels
Get PRO
December '240
in 0 channels
Get PRO
November '240
in 0 channels
Get PRO
October '240
in 0 channels
Get PRO
September '240
in 0 channels
Get PRO
August '240
in 0 channels
Get PRO
July '240
in 0 channels
Get PRO
June '240
in 0 channels
Get PRO
May '240
in 0 channels
Get PRO
April '240
in 0 channels
Get PRO
March '24
+2 780
in 0 channels
Get PRO
February '24
+2 194
in 0 channels
Get PRO
January '24
+6 423
in 2 channels
Date
Subscriber Growth
Mentions
Channels
23 November0
22 November0
21 November0
20 November0
19 November0
18 November0
17 November0
16 November0
15 November0
14 November0
13 November0
12 November0
11 November0
10 November0
09 November0
08 November0
07 November0
06 November0
05 November0
04 November0
03 November0
02 November0
01 November0
Channel Posts
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬ ማንሣት መጣልማ ዓለምም ታነሣለች ትጥላለች። ኑ እንደ ግእዝ ቋንቋ ተማሪነታችን ምክንያታዊ ኾነን እናንሣ ምክንያታዊ ኾነን እንጣል። ባለፈው እንደጻፍኩላችኹ በዐዲሱ ዓመት በደረጃ ፩ እና ፪  የተማርናቸውን ትምህርቶች በማካተት ከዘወትር ጸሎት በመነሣት ወደሌሎችም እያደገ የሚኼድ ጸሎቱንም የቋንቋውንም ሕግ ጎን ለጎን በጥልቀትና በስፋት ለማስተማር ታስቧል። ትምህርቱ ○ ለዚኽን ያኽል ወራት ተብሎ የሚገደበ አይኾንም። ተማሪዎች መማር እስከፈለጉበት ጊዜ ድረስ ለረጅም ጊዜ የሚቈይና ተከታታይነት የሚኖረው ይኾናል። ○ በጽሑፍና በድምፅ ማብራሪያ የሚታገዘ ሲኾን  በዋናነት በቀጥታ ውይይት ይሰጣል። ○ ከእያንዳንዱ ተማሪ ጋራ ለመወያየት በቂ ጊዜ ይኖረኝ ዘንድ የተማሪውን ለውጥም በቅርበት በመከታተል ለማብቃት ያስችለኝ ዘንድ የተማሪዎች ቍጥር ትንሽ እና የተገደበ ይኾናል። ○ ከዚኽ በፊት የተሰጡትን ትምህርቶች በደንብ ላልተረዱትና ለጀማሪዎች ልዩ ትኵረትና እንክብካቤ ይደረጋል። ○ ግእዝ ተምሬአለኹ ለማለት ሳይኾን በትክክል መረዳት ለምትፈልጉ ይኽ መርሐ ግብር ለእናንተ ነው። ○ ትምህርቱን መስከረም ወር ላይ ለመጀመር ታስቧል። በመኾኑም የግእዝን ቋንቋ ሰዋስው ለማወቅና በተጨማሪም የጸሎት ክፍሎች ውስጥ የሚገኙ ቃላት ተነሥተው ወይም ተጥለው የሚነበቡበትን ምክንያት ለማወቅና ለማንበብ የእያንዳንዱን ቃላት ምንነትና አወቃቀር በጥልቀት ለመማር እፈልጋለኹ የምትሉ ኑ የማውቀውን ላሳውቃችኹ። ማሳሰቢያ፦ ትምህርቱ ከፍተኛ ትኵረትና ጊዜ የሚፈልግ በመኾኑ ከእስካኹኑ በተለየ መልኩ ወርኃዊ ክፍያ ይኖረዋል። የክፍያውን መጠን ለመወሰን ግን የሚማረው የተማሪ ቍጥር መታወቅ ስላለበት ከታች ባለው አድራሻ በመደወል ወይም ቴሌግራም ላይ በመጻፍ እየከፈላችኹ መማር ለምትፈልጉ ተጨማሪ መረጃ ማግኘትና መመዝገብ ትችላላችኹ። በስልክ ፦  +251911727529 በቴሌግራም፦  @Elias238 በቀጣይ ደግሞ በግልም ኾነ በቡድን፣ ለልጆችም ኾነ ለዐዋቂዎች፣ ላጭርም ኾነ ለረጅም ጊዜ ለጀማሪዎች ቋንቋውን መማር ለሚፈልጉ ዅሉ ለማስተማር ዝግጅት እየተደረገ ይገኛል።            ግዛቸው ደጀኑ      ( ነሐሴ ፲፱፥ ፳፻፲፯ ዓ.ም.) ▬▬▬▬▬▬▬▬▬

2
🌼 ▬▬▬ ባሕረ ሐሳብ ▬▬▬ 🌼 እግዚአብሔር አምላካችን ቢፈቅድና ብንኖር በዚኽ ዓመት መጨረሻ፣ በወርኀ ጳጕሜን በ፳፻፲፰ ዓ.ም. በዓላትና አጽዋማት የሚውሉባቸውን ቀናት ከሙሉ ማብራሪያ ጋራ በቀላል አቀራረብ ለማቅረብ ታስቧል። ይኽ ብቻ አይደለም በአንድ ገጽ ላይ የተዘጋጀ የኢትዮጵያ የዘላለም የቀን መቍጠሪያ የተሰኘ ( እኔ ከዚኽ በፊት ሌላ ቦታ ሰምቼው፣ አንብቤው የማላውቀው) ዐዲስ ትምህርት ከአራት ወራት በፊት በአሜሪካ ሀገር በሚኖሩ የ፸፮ ዓመት የዕድሜ ባዕለ ጸጋ ገለጻ ተደርጎልን በጣም ገርሞኝ ነበር። እናንተም ይኼን አቈጣጠር ትማሩት ዘንድ እርሳቸውንም እጋብዛለኹ። ትምህርቱ የሚሰጠው በዐምስቱ ቀናት ውስጥ " ግእዝን በርቀት የኹሉም ዙር ተማሪዎች " በሚገኙበት ቡድን ውስጥ ይኾናል።       👇 👇 👇 @geezinberiket           ☝️ ☝️ ☝️ 🌼 ▬▬▬ ባሕረ ሐሳብ ▬▬▬🌼
2 568
3
ግእዝን በርቀት ከትናንት እስከ ዛሬ.pdf
2 560
4
🌸 ▬▬  በእንተ ግእዝ ▬▬ 🌸                 ኢያረምም የተከበራችኹ የግእዝን በርቀት ከ፩ኛ እስከ ፲፭ኛ ዙር ተማሪዎች በእግዚአብሔር ቸርነት፥ በእኔ በደካማው የልብ መሻት በጣት የሚቈጠሩ ተማሪዎችን ይዞ ከስድስት ዓመታት በፊት በቫይበር የተጀመረው የግእዝን በርቀት ትምህርት ከቀን ወደቀን እያደገና በእናንተ ቀስቃሽነት የተማሪው ቍጥር እየጨመረ ያለምንም መሰናክል ዛሬ ላይ ደርሰናል። እግዚአብሔር ከእኔ ጋራ ኾኖ በሰው ሰውኛው በአንድ በኔ በደካማው አስተባባሪነት ብዙ ሺሕ ጠንካራ ተማሪዎችን በግእዝ ስም ለማሰባሰብ ተችሏል። ዅሉን ያደረገ እግዚአብሔር ነው። ይኽ ዅሉ የኾነው ግን አየር ላይ ነው። አያድርገውና ቴሌግራም ሙሉ በሙሉ ሥራውን ቢያቆም ወይም እኔ ሰው እንደመኾኔ አንድ ነገር ብኾን (ክፉውን ያርቅ) አየር ላይ መቅረታችን ነው። በመኾኑም መሬት እንድይዝ ጊዜው ደርሷል። የሚዳሰስ ፣የሚጨበጥ ተቋም ያስፈልጋል። በአስፈላጊነቱ ዙሪያ እኔ ሳላስብ እናንተ ቀድማችኹ ዐስባችኹ እንደነበር እኔም እናንተም አንዘነጋውም። በተለይ ፯ኛ እና ፱ኛ ዙሮች በራሳችኹ መንገድ ብዙ ርቀት ኼዳችኹ ጊዜው ስላልነበር ስሜታችኹ ተጎድቶ እኔንም ታዝባችኹኝ ተቀምጣችዃል። ሌሎች ዙሮችም እንዲኹ። መቼም እግዚአብሔር ዐብሮን አለ ብለን ስናምን ፈቃዱን መጠየቅ መጠበቅም ግድ ይላል። እግዚአብሔር ዐብሮት ያልኾነ ማንም ባይኖርም በተለይ በዚኽ መርሐ ግብር ላይ መኖሩ ሥራው በግልጥ ታይቷል። አንድ ምንም የማያውቅ ተራ ሰውን አስነሥቶ ብዙ ጠንካራ ተማሪዎችን ያፈራ እርሱ ነው። ለዓመታት ዅሉንም በታሰበው መልኩ ለመፈጸም አይደለም ማስታጎል ደቂቃ ሳላዛንፍ ትምህርቱን ማስተላለፌ በእርሱ ቸርነት ነው። ዛሬ አሞኛል፣ ዛሬ አልችልም ዛሬ እንዲኽ ችግር ገጥሞኛል ሳልል ዅልጊዜ በደስታና ባለመሰልቸት ከእናንተ ጋራ የኖርኩት በእግዚአብሔር ቸርነት ነው። ብዙ ኀጢአት ባለችበት በዚያ የእግዚአብሔር ጸጋ ትበዛለች የተባለው ለእኔ ብቻ እስኪመስለኝ ድረስ የእግዚአብሔር ጸጋው አልተለየኝም። በመኾኑም ለዅሉም ነገር የእርሱን ፈቃድ መጠየቅ መጠበቅም የግድ ኾኖብኝ ስለተቋም ስታነሱ እንዳልሰማ እንዳለየ ዝም ስል ኖርኩ። አኹን ግን እግዚአብሔር ፈቀደ መሰለኝ ልቤም ተቋሙን ሻተ። ከአየሩ በተጨማሪም መሬትም እንድንይዝ በእግር የምንሸከረከር በአየርም የምንበር እንድንኾን፣ በጽሑፍ እና በድምፅ ብቻ የምንተዋወቅ ሰዎች ዐይን ለዐይን እየተያየን ስለግእዝ እንድንመክር፣ እንድንማማር፣ ሰው ቢያልፍ ስለግእዝ ቋንቋ የሚያስቡ ሌሎች እልፎች እንዲተኩ ለማድረግ ተቋሙ ያስፈልጋል። ከአንድ ሰው ይኼን ያኽል ለግእዝ የሚያስብ ከተገኘ ከእናንተ ከብዙ ሺሖች መካከል ደግሞ ሺሕ ቅን ዐሳቢዎች ይገኛሉና ያላችኹን ሐሳብ፣ ዕውቀት ግብአት ትሰጡ በይፋ በድጋሚ ጥሪ ቀርቧል። እኔ አነሰም አደገም ተሰጥኦዬ የማውቃትን ማስተማሩ ላይ ነው። እናንተ ደግሞ ከማስተማሩ በተጨማሪ የእያንዳንዳችኹ ተሰጥኦ ልዩ ልዩ ነውና በኅሊና የታሰበውን ተቋም በተለያዩ መንገዶች ትደግፉ፣ ታግዙ ዘንድ ስጠይቅ በታላቅ ኵራትና መተማመን ነው። ምክንያቱም ጥያቄዬ አብሉኝ አጠጡኝ አይደለም። እግዚአብሔር ይመስገን የዕለት ጉርስ የዓመት ልብስ አላሳጣኝም፣ አያሳጣኝምም። ግን ከዚኽ በዘለለ ኅሊናችን የሚረካበት፣ የአባቶቻችን ታሪክ የምናስቀጥልበት፣ ዐሻራችንን አሳርፈን ስናልፍ የማያልፍ ታሪክን ለልጆቻችን የምናስተላልፈበት ተቋም ለመመሥረት ጋን የኾነውን ተቋም ዙሪያውን በጠጠር እንደግፈው ዘንድ ነው። በመኾኑም እኔ ዐዳዲስ ትምህርቶችን ለማስተማርና የነበረውን ለማስቀጠል ልበርታ። እናንተ ደግሞ ሰብሰብ በሉና ከኮሚቴዎች ጋራ ስለተቋሙ ምከሩ፣ እንዲኽ ቢኾን እንዲያ ቢኾን ብላችኹ ግብአት ስጡ፣ በየተማራችኹበት ዙር ተወያዩ። ባለፈው በጠየቅኹት ጥያቄ በፈቃደኝነት ምን እናግዝ ብለው የጠየቁኝን ጥቂት ተማሪዎች ዐበይት ኮሚቴዎች ብዬ ባንድ አድርጌ አሰባስቤአለኹ። አኹን ንኡሳን ኮሚቴዎችን ከእናንተ እጠብቃለኹ። ከየዙሩ በያንስ ኹለት ኹለት ተወካይ ቢገኝ መልካም ነው። በተለይ መደበኛ ሥራችኹ ከተቋም ምሥረታ፣ ከትምህርት ጋራ ተያያዥነት፣ ከአስተዳደር ጋራ፣ ሕግ ነክ፣ ሒሳብ አያያዝ፣ ተግባቦት ባለሙያዎች፣ አይቲ ባለሙያዎች፣ ለማስተባበር ፈጣን የኾናችኹ እና ሌሎችም እኔ በተቋሙ ምሥረታና አካኼድ ዙሪያ ዐሻሬዬን ላሳርፍ እችላለኹ የምትሉ ግእዝን በርቀት ደረጃ ፩ በተማራችኹበት መገናኛ ብትጽፉልኝ በአንድ ላይ ተሰባስባችኹ እንድትመክሩ አደርጋለኹ። በቀጣዩ  የተቋሙን ምሥረታ በተመለከተ ዐበይት ኮሚቴዎች እየተነጋገሩ የሚያዘጋጁት መርሐ ግብር ይኖራል። ስማቸውንና አድራሻቸውንም አሳውቃችዃለኹ። ለእኔ እንደ አንድ ግለሰብ እስካኹን ለግእዝ መስፋፋት ያደረግኹት በቂ ባይኾንም፣ ባልረካበትም ትንሽዬ ዐሻራዬን እንዳሳረፍኩ ይሰማኛል።   እናንተስ ❓❓❓ ግእዝ ሞቷል? ወይስ አልሞተም? 🌸 ▬▬  በእንተ ግእዝ ▬▬ 🌸                 ኢያረምም
2 551
5
▬▬▬ @geezinberiket ▬▬▬ ሰላም ለእናንተ ይኹን። " ግእዝን በርቀት የኹሉም ዙር ተማሪዎች"          @geezinberiket የሚለውን ቻናል ተቀላቅለዋል? የኹሉም ዙር ተማሪዎች የሚሰባሰቡት፣ ከዚኽ ቀደም በርካታ ቁም ነገሮች የተላለፈበት ወደፊት ትምህርቶችና መልእክቶች የሚተላለፉበት ነውና እስካኹን ወደቻናሉ ካልገቡ ወደቻናሉ ቢገቡ ይጠቀሙበታል። ወደፊት ስለሚሰጡ ትምህርቶችም መልእክት በየዙሩ ከማስተላለፍ በአንድ ቻናል ማስተላለፍ ለእኔም ይቀለኛልና በተቀመጠው የመግቢያ ሊንክ ወደዚያ ትሰባሰቡ ዘንድ በትሕትና እጠይቃለኹ። ▬▬▬ @geezinberiket ▬▬▬
2 572
6
No text...
0
7
🌸▬▬▬  ቦ ጊዜ ለኵሉ ▬▬▬ 🌸 እንኳን ለመልአኩ ቅዱስ ሚካኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል በሰላምና በጤና አደረሳችኹ። ( ወአውሥአቶ አፎምያ ለዲያብሎስ ወትቤሎ አስኬማከ ሠናይ ወቃልከሰ እኩይ ወኢሠናይ ውእቱ። ድርሳነ ሚካኤል ዘወርኀ ሠኔ። ) ▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬        ለኹሉም ጊዜ አለው። በእግዚአብሔር መልካም ፈቃድ ከ፳፻፲፩ ዓ.ም. ጀምሮ በደረጃ ፩ ትምህርት በ፲፬ ዙሮች፣ በደረጃ ፪ ትምህርት ለ፯ ዙሮች እና በደረጃ ፫ ለ፯ ዙሮች በብዙ ሺሕ የሚቆጠሩ ተማሪዎችን ከግእዝ ቋንቋ ጋራ ለማስተዋወቅ ጥረት አድርጌአለኹ። በእነዚኽ ዓመታት ብዙ ውጣ ውረዶችን ያየኹ ቢኾንም ብዙዎቹ መልካምና የኅሊና ርካታን ያገኘኹባቸው ነበሩ። ወደፊት በተለያዩ አጋጣሚዎች የምተርክላችኹ ብዙ አጋጣሚዎችም አሉኝ። በእግዚአብሔር ሙሉ ርዳታ በዐሥር ጣቶቼና  በኦጅ ስልክ አንዱ እኔ ለብዙ ሺሖች ያለችኝን ዕውቀት በደረጃ ፩ ትምህርት ያለምንም ክፍያና ሽልማት ይልቁንም በመሸለምና በማበረታታት ያለኝን ዅሉ ሳካፍል ቆይቻለኹ።  በዚኽም የኅሊና ርካታና ለወገኔ ምንን አደረግኹ? ለሚለው ጥያቄ ጥቂትም ቢኾን መልስ አግኝቼበታለኹ። ከብዙ ሺሕ ተማሪዎች ጋራ ብቆይም በራሴ መንገድ ተጉዤ የልቤን ሐሳብ ፈጽሜአለኹ፤ ለነፍሴ ሐሴትን አግኝቻለኹ፣ ባደርግ ብዬ የማስበውን ዅሉ ያለምንም ዕንቅፋትና መሰናክል በእግዚአብሔር ርዳታ አድርጌአለኹ። ሰው እንደመኾኔ የሥጋ ድካም፣ የአእምሮ ዝለት ገጥሞኝ እስካኹን ካደረግኹት በላይ ወደፊት ላደርገው የሚገባኝን ሳላደርግ እንዳልቀር በዐሥር ጣቶች እና ባንድ ስልክ ሲሰጥ የነበረውን የግእዝ ቋንቋ ትምህርት ለማስቀጠልና ተቋማዊ ለማድረግ ጊዜው አኹን እንደኾነ ይሰማኛል። ከ፮ ዓመት በላይ ከእናንተ ጋራ የነበረኝን የቴሌግራም ጉዞ በቀጣይ ደግሞ በተደራጀ መልኩ በተቋም ደረጃ ለማስቀጠልና እንዲኾኑ የምመኛቸውን፣ የማስባቸውን ጉዳዮች ለመፈጸም ግእዝን በርቀትን #ወደ_ተቋም  ለማሳደግ ካሰብኩ ብቆይም ምንም ነገር ያለጊዜውና ያለፈቃደ እግዚአብሔር አይኾንምና እስከዚች ሰዓት ሳይተገበር ቆይቷል። አኹን ግን ጊዜው ደርሷል መሰለኝ አፍ አውጥቼ ለእናንተ በይፋ ለማሳወቅ ብቅ ብያለኹ። ከእስካኹኑ በበለጠ የግእዝን ቋንቋ ለብዙኃኑ ተደራሽ ለማድረግ ጊዜው አኹን ነው። በቀጣይ ከእናንተ በማጋኛቸው ግብአቶች ተቋሙ ተመሥርቶ ሊሠሩ ስለሚገባቸው ጉዳዮች እስካሳውቃችኹ ድረስ በተቋሙ መመሥረት ድጋፋችኹን ታሳዩኝ ዘንድ በታላቅ ትሕትና እጠይቃለኹ። በመኾኑም ይነስም ይደግም ከግእዝ ቋንቋ ጋራ የተዋወቅንበት ይኽ ግእዝን በርቀት የተሰኘ የቴሌግራም መርሐ ግብር አድጎ ተቋም ይኾን ዘንድ በሐሳብ (እንዲኽ ቢኾን እንዲያ ቢኾን) ፣ በዕውቀት (ተቋሙን በተለያዩ ዘርፎች በዕውቀት ለመደገፍ) ፣ በሙያዊ ድጋፍ፣ በማማከር ፣ በገንዘብ (ለተቋሙ መመሥረት የሚያስፈልጉ ግብአቶችን ለማሟላት) ፣ በጸሎትና በሌሎች መንገዶች ዅሉ የእርስዎን ድርሻ ያደርጉ ዘንድ ስጠይቅ በታላቅ ወንድማዊ ፍቅር ነው። ከላይ በተጠቀሱት በማናቸውም መንገዶች ልታግዙኝ ከፈለጋችኹ ከዚኽ በፊት ትምህርቱን ስትማሩ በምንጻጻፍበት በነበረው የቴሌግራም አድራሻዬ በጽሑፍም ኾነ በድምፅ ሊያገኙኝ የሚችሉ መኾኑን በታላቅ ክብርና ትሕትና እገልጻለኹ።። ከግእዝን በርቀት ወንድማችኹ  ግዛቸው ደጀኑ መኰንን           ሠኔ ፲፪ ፥ ፳፻፲፯ ዓ.ም. 🌸▬▬▬  ቦ ጊዜ ለኵሉ ▬▬▬ 🌸
2 592
8
@geezdistance15
@geezdistance15
2 520
9
የተከበራችኹ የግእዝን በርቀት የ፲፫ኛ ዙር ተማሪዎች እንደምታውቁት ለኹለት ወራት በደረጃ ፩ ትምህርት ተምራችዃል። ከእናንተ በፊት የነበሩት እንዲኹም ከእናንተ ጋራ በ፲፫ኛ ዙር የተማሩ የደረጃ ኹለትን ተምረዋል። ከርሱም ዐልፈው በሦስተኛ ዙር ባሕረ ሐሳብ የተማሩም አሉ። በመኾኑም ከዚኽ ቀደም የተሰጠውን የደረጃ ፪ ያልተማራችኹ በደረጃ ፪ ጠለቅ ያሉና መሠረታዊ ትምህርቶችን ተምራችኹ የግእዝ ዕውቀታችኹን ከፍ ታደርጉ ዘንድ የደረጃ ፪ ትምህርት ለመስጠት ታስቧል። የተማሪው ቍጥር የሚፈለገው ቍጥር ከደረሰ በዚኽ ክረምት ለመጀመር ታስቧል። እርስዎም እስካኹን ካልተመዘገቡ ከላይ ያለውን መልእክት በማንበብና የሚጠይቀውን በመሙላት ትመዘገቡ ዘንድ እጋብዛለኹ። ስለትምህርቱ ይዘት በተዘጋጀው የትምህርቱ መስጫ ቻናል ይገለጻል። ግእዝን በርቀት የኹሉም ዙር ተማሪዎች ቡድን ውስጥ እስካኹን አባል ካልኾኑ በሚከተለው ሊንክ መግባት ይችላሉ። https://t.me/geezinberiket እናንተ የተማራችኹትን ዐይነት የደረጃ ፩ ትምህርት መማር የሚፈልጉ ጓደኞቻችኹ ካሉ ደግሞ @geezdistance15 በሚለው ሊንክ እንዲገቡ ጠቁሟቸው።
3 477
10
ገና እጅግ ብዙ ከግእዝ ቋንቋ ጋራ ያልተዋወቁ ወገኖች አሉን። ግእዝን በርቀት እንድትማሩ ማን ጋበዛችኹ? በነበረኝ ቆይታ ብዙዎች የጋበዛቸውን ሰው ሲያመሰግኑ እሰማ ነበር። እናንተስ ሰው እንዲያስታውሳ
ገና እጅግ ብዙ ከግእዝ ቋንቋ ጋራ ያልተዋወቁ ወገኖች አሉን። ግእዝን በርቀት እንድትማሩ ማን ጋበዛችኹ? በነበረኝ ቆይታ ብዙዎች የጋበዛቸውን ሰው ሲያመሰግኑ እሰማ ነበር። እናንተስ ሰው እንዲያስታውሳችኹ አትፈልጉም? በሉ ቢያንስ ለአንድ ሰው የ፲፭ኛ ዙርን በመጋበዝና መግባቱን በማረጋገጥ ለርሱም፣ ለእኔም፣ ለግእዝ ትምህርቱም ማደግ ዐሻራችኹን አሳርፉ።        @geezdistance15 ግእዝን በርቀት በ፲፭ኛ ዙር አንድ ተማሪ አስገብቻለኹ። ካስገባችኹ🙏 የምትለዋን ምልክት በመጫን አረጋግጡልኝ።
3 843
11
https://t.me/geezinberiket/8608
4 150
12
▬▬▬▬▬🌸🌸🌸▬▬▬▬▬                  ልደታ ለማርያም እንኳን ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም የልደት በዓል በሰላምና በጤና አደረሳችኹ። ቅድስት፣ ስብሕት፣ ውድስት፣ ቡርክት፣ ጽንዕት፥ ብፅዕት፥ ምልእት፣ ፍጽምት፣ ክብርት፥ ልዕልት፥ ስርጉት፥ ንጽሕት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ረድኤትሽ፣ በረከትሽ ይደርብን፤ ጥበቃሽ፣ አማላጅነትሽ አይለየን። ▬▬▬▬▬🌸🌸🌸▬▬▬▬▬ 📌   ግእዝን በርቀት ፲፭ኛ ዙር የተከበራችኹ የግእዝን በርቀት ተማሪዎች እንደምን አላችኩ? እንደምታውቁት እስካኹን በደረጃ ፩ ትምህርት ከ፩ኛ ዙር እስከ ፲፬ኛ ዙር ፣ በደረጃ ፪ ትምህርት ደግሞ ለሰባት ዙሮች፣ እንዲኹም በደረጃ ፫ ለሰባት ዙሮች በድምሩ በ፳፰ ዙሮች ብዙ ሺሕ ተማሪዎችን በተለያዩ ደረጃዎች ከግእዝ ቋንቋ ጋራ ለማስተዋወቅ ጥረት ተደርጓል። አኹንም ዐዳዲስ የሚማሩ ተማሪዎች ለመማር ጥያቄዎችን እያቀረቡ በመኾኑ በደረጃ ፩ ለዐሥራ ዐምስተኛ ጊዜ፣ በደረጃ ፪ ደግሞ ለ፰ኛ ጊዜ ለማስተማር ታስቧል። በመኾኑም ከዛሬ ጀምሮ ምዝገባ የተጀመረ በመኾኑ እናንተ የተማራችኹትን ትምህርት ሌሎችም እንዲማሩ የግእዝን ቋንቋ መማር ለሚፈልጉ ኹሉ መልእክቱን በማስተላለፍና እንዲመዘገቡ በመጋበዝ የተለመደ ትብብራችኹን በትሕትና እጠይቃለኹ። ፩) ዐሥራ ዐምስተኛ ዙር ትምህርቱ ከዚኽ በፊት ግእዝን በርቀት ከ፩ኛ እስከ ፲፬ኛ ባለው ላልተማሩ ዐዳዲስ ተማሪዎች ታስቦ የሚዘጋጅና ኹለት ወራትን የሚፈጅ ነው። ትምህርቱ የሚሰጠው በክፍያ ነው። ወደትምህርቱ የመግቢያ ሊንከ         @geezdistance15 ▪▪▪▪▪▪▪ ፪) ደረጃ ፪ እስካኹን የደረጃ ፩ ትምህርትን ላጠናቀቁ ተማሪዎች ብቻ የሚሰጥ በይዘቱ ከደረጃ ፩ ከፍ ያለ ለኹለት ወራት የሚሰጥ ትምህርት ሲኾን እስካኹን ከ፩ኛ እስከ ፲፬ኛ ዙር ባለው ተምራችኹ ደረጃ አንድን ያጠናቀቃችኹ የደረጃ ኹለትን መማር ትችላላችኹ። ትምህርቱ በክፍያ ነው። ትምህርቱን ለመማር ፈቃደኛ የኾናችኹ የሚከተለውን መረጃ በመሙላት @geezachew12 ላይ ጻፉልኝ ። ◦ የደረጃ ፩ መለያ ቍጥር ◦ የተማራችኹበት ዙር ◦ ሙሉ ስም ◦ የደረጃ ፩ ከ100 ውጤት ማስታወሻ ለዐሥራ ዐምስተኛ ዙርም ይኹን ለደረጃ ፪ ትምህርት ክፍያ ቢኖረውም ክፍያው ማንንም የማያስጨንቅና የማያሳስብ፣ ኹሉም እንደየዐቅሙ ለመክፍል ዕድል የሚሰጥ መኾኑን መግለጽ እወዳለኹ።        እኁክሙ ግዛቸው ደጀኑ        ግንቦት ፩ ፣ ፳፻፲፯ ዓ.ም ▭▰▭▰▭▰▭▰▭▰▭▰▭▰
4 669
13
🌸 🌸 🌸 🌸 🌸 🌸 🌸 ◎ ክርስቶስ ተንሥአ እሙታን                   ➾ በዐቢይ ኀይል ወሥልጣን ◎ አሰሮ ለሰይጣን  ➾ አግዐዞ ለአዳም ◎ ሰላም    ➾  እምይእዜሰ ◎ ኮነ        ➾ ፍሥሓ ወሰላም 🌸🌸🌸 እንቋዕ ለበዓለ ትንሣኤሁ ለእግዚእነ ወመድኀኒነ ኢየሱስ ክርስቶስ በሰላም ወበጥዒና አብጽሐክሙ። ሠናይ በዓለ ትፍሥሕት ይኩን ለኵልክሙ። እኁክሙ  ግዛቸው 🌸 🌸 🌸 🌸 🌸 🌸 🌸
3 710
14
ሰላም ለዅላችኹም ይኹን። የተከበራችኹ ወንድሞቼና እኅቶቼ እንደምን ከረማችኹ? በአሜሪካ ሀገር የምትኖሩ፣ ግእዝን በርቀት ከደረጃ ፩ እስከ ፫ ከተሰጠው ትምህርት ውስጥ ቢያንስ የደረጃ አንድን ትምህርት ተምራችኹ ያጠናቀቃችኹ ትምህርቱን ስትማሩ መልመጃ/ፈተና በምትልኩበት አድራሻዬ እስከ የካቲት ፲ ፳፻፲፯ ዓ.ም. ማታ ፲፪ ሰዓት ድረስ ትጽፉልኝ ዘንድ በትሕትና እጠይቃለኹ። ግዛቸው ደጀኑ
2 870
15
No text...
3 161
16
▬▬▬▬▬▬🌺▬▬▬▬▬▬ ሙዳየ ግአዝ ቍጥር ኹለት በገበያ ላይ (ከረቡዕ ታኅሣሥ ፳፫, ፳፻፲፯ ዓ.ም. ጀምሮ) መገኛ፦ ▪ ከሙዳየ ግእዝ ቍጥር ኹለት አስተባባሪዎች (ቀድሞ ከተለቀቀው ማስታወቂያ ላይ በ
▬▬▬▬▬▬🌺▬▬▬▬▬▬ ሙዳየ ግአዝ ቍጥር ኹለት በገበያ ላይ (ከረቡዕ ታኅሣሥ ፳፫, ፳፻፲፯ ዓ.ም. ጀምሮ) መገኛ፦ ▪ ከሙዳየ ግእዝ ቍጥር ኹለት አስተባባሪዎች (ቀድሞ ከተለቀቀው ማስታወቂያ ላይ በሚኖሩበት አካባቢ ላሉት አስተባባሪዎች በመደወል ማግኘት ይችላሉ።) ▪ 4 ኪሎ ቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ሕንጻ  ◦ ማዮን መጻሕፍት መደብር ◦ ልዩ መጻሕፍት መደብር (0901175520) ▪ በሌሎች የመጻሕፍት መሸጫ መደብሮች ▪ ከኢትዮጵያ ውጭ በተለይ አሜሪካና ጀርመን መጽሐፏ ስለተላከች በኹለት ቀናት ውስጥ ትደርሳለች። በመኾኑም እስካኹን ከአስተባባሪዎቹ ጋራ የተደዋወላችኹ በቅደም ተከተሉ መሠረት ያሳውቋችዃል። ሌላም ተጨማሪ የምትፈልጉ ለመላክ ያስችል ዘንድ ለአስተባባሪዎች አሳውቋቸው። በሌሎች ሀገራትም በቅርቡ የሚላክ ሲኾን በትዕግሥት እንድትጠብቁ በአክብሮት እጠይቃለኹ። 📌 ማስታወሻ ሙዳየ ግእዝ ቍጥር ኹለት ቢታተም ለመግዛት ፍላጎታችኹን ለገለጻችኹና ኢትዮጵያ ውስጥ የምትኖሩ ፎርሙን ለሞላችኹ ተማሪዎች ብቻ የተወሰነ የዋጋ ቅናሽ ተደርጓል። በመኾኑም ስማችኹንና የፈለጋችኹትን የመጻሕፍት ቍጥር ለብቻ ለይቼ 6 ኪሎ ቅዱስ ማርቆስ ቤተክርስቲያን ግቢ ውስጥ የሱቅ ቍጥር ፪ (+251978109058) አስቀምጣለኹና  ከረቡዕ ጧት ጀምሮ ራሳችኹም ኾነ ሌላ ሰው በመላክ በቅናሹ መግዛት የምትችሉ መኾኑን በትሕትና እገልጻለኹ። ▬▬▬▬▬▬🌺▬▬▬▬▬▬
2 792
17
No text...
2 806
18
ሰላም ለእናንተ ይኹን የተወደዳችኹ የግእዝን በርቀት ተማሪዎች! በናፍቆት እየጠበቅናት ያለችው ሙዳየ ግእዝ ቍጥር ኹለት መጽሐፍ ከኅትመት ለመውጣት በጣት የሚቈጠሩ ቀናት ቀርተዋታል ። ሙዳይዋ በእጃችን
ሰላም ለእናንተ ይኹን የተወደዳችኹ የግእዝን በርቀት ተማሪዎች! በናፍቆት እየጠበቅናት ያለችው ሙዳየ ግእዝ ቍጥር ኹለት መጽሐፍ ከኅትመት ለመውጣት በጣት የሚቈጠሩ ቀናት ቀርተዋታል ። ሙዳይዋ በእጃችን በእርግጠኝነት ትገባ ዘንድ ከታች ያለውን ፎርም በመሙላት እንተባበር! _+_-_+_-_+_-_+_-_+_-_+_-_+_-_+_ ⭕ ኢትዮጵያ ውስጥ የምትኖሩ ፦ 👇 https://forms.gle/pP6STVHuAPV6nLuq5 ⭕ ከኢትዮጵያ ውጭ የምትኖሩ ፦ 👇 https://forms.gle/LJ5hdpGtnBeNwFnw5 _+_-_+_-_+_-_+_-_+_-_+_-_+_-_+_ 🙏 ጥሪውን አክብረው ስለሞሉ እናመሰግናለን 🙏
3 008
19
No text...
3 955
20
🌸       ንዒ ኀቤየ ሙዳይየ     🌸 ሰላም ለዅላችኹም ይኹን። የሙዳየ ግእዝ ቍጥር ኹለት ፎቶ በጥያቄና መልሱ እና በእያንዳንዳችኹ የመወያያ ቡድን ውስጥ ስለተለቀቀ ከርሱ ላይ በማውረድ ፕሮፋይል ለመቀየር የምትችሉ እና ፈቃደኛ የኾናችኹ የግእዝን በርቀት ተማሪዎች ዅሉ መጽሐፋችኹን ዓለም ዅሉ እንዲመለከታት ታደርጉ ዘንድ በትሕትና እጠይቃለኹ። 🌸       ንዒ ኀቤየ ሙዳይየ     🌸
4 935