en
Feedback
ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት

ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት

Open in Telegram

በአሰላ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። የቴሌግራም ቻናል:-  @Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- @FinoteWongel27 የቲክቶክ ገፅ:- https://www.tiktok.com/@finotewongel27 Youtube:- https://www.youtube.com/@Finote_Wongel ©ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት

Show more
669
Subscribers
-224 hours
+57 days
+130 days
Posts Archive
ለሦስት ቀናት ከልኂቅ እስከ ደቂቅ ሁላችንም ጠዋትና ማታ በየቤተክርስቲያኑ ዐውደ ምሕረት እየተገኘን በንስሓ በዕንባ በጸሎት በምህላ የእግዚአብሔርን ምሕረትና ይቅርታ እንድንጠይቅ። ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ
+5
ለሦስት ቀናት ከልኂቅ እስከ ደቂቅ ሁላችንም ጠዋትና ማታ በየቤተክርስቲያኑ ዐውደ ምሕረት እየተገኘን በንስሓ በዕንባ በጸሎት በምህላ የእግዚአብሔርን ምሕረትና ይቅርታ እንድንጠይቅ።          ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት        እንኳን ለጾመ ነነዌ በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ! እግዚአብሔር አምላካችን ምሕረቱን ይቅርታውንና ሰላሙን ለሀገራችንና ለቤተክርስቲያናችን  ይስጠን ምህላችንንም ይቀበልልን።

🍁🍁🍁✨✨✨🍂🍂🍂✨✨✨🍁🍁🍁 #የካቲት_2 የገዳማዊያን አለቃ ለሆነ #ለአባ_ጳውሊ የአመታዊ መታሰቢያ እንኳን አደረሳችሁ፡፡ 🍁🍁🍁✨✨✨ አባ ጳዊሊ የማይቆጠር እጅግ ባለ ጸጋ የኾነ አባት በእስክድርያ ሀገር ነበረው፡፡ጳውሊን ለትምህርት ሲደርስ ለመምህር ሰጥቶ ብሉይ ሐዲስ እንዲሁም ሥርዐተ ቤተ ክርስቲያንን ተምሮ በሕግ በሥርዐት አደገ፡፡ ተጨማሪ ያንብቡ..

እሑድ ማለት"አሐደ" ከሚለው የግዕዝ ቃል የወጣ ሲኾን ትርጉሙ የመጀመሪያ እንደማለት ነው። ይኽች ዕለት በመጽሐፍ ቅዱስ "ከሳምንቱ በፊተኛው ቀን " በመባል ትታወቃለች። ዮሐንስም በራዕዩ "የጌታ ቀን"
እሑድ ማለት"አሐደ" ከሚለው የግዕዝ ቃል የወጣ ሲኾን ትርጉሙ የመጀመሪያ እንደማለት ነው። ይኽች ዕለት በመጽሐፍ ቅዱስ "ከሳምንቱ በፊተኛው ቀን " በመባል ትታወቃለች። ዮሐንስም በራዕዩ "የጌታ ቀን" ያላት ናት (ራዕይ 1፥10) ቅዱስ ያሬድም በድጓው ላይ "ዕለተ እግዚአብሔር" የሚላት ዕለተ እሑድ ናት። መልካም ዕለተ ሰንበት ይኹንልን 🙏🙏🙏

እኛ ሰዎች ዛሬም በየሰዓቱ ብቻ ሳይሆን በየደቂቃው እግዚአብሔርን የሚያስቆጣ አበሳ እንደምንፈጽም ማወቅ ኣለብን፣ አበሳውና ኃጢኣቱ ሲበዛ እግዚአብሔር እውነተኛ ዳኛ ነውና ወደ ዳኝነት ተግባሩ ይገባል፤ይህ ደግሞ በሰብአ ትካት በሰዶምና በጎሞራ ያስተላለፈውን ዳኝነት ያስታውሰናል፤ አሁን ያለንበት ዘመን ዓመተ ምሕረት በመሆኑ እግዚአብሔር ለጊዜው ቢታገሠንም በኃጢኣታችን የምንጠየቅበት ጊዜ አዘጋጅቶአል፤ ዛሬም ቢሆን የማናስተውለው ሆነን ካልሆነ በስተቀር እግዚአብሔር ተግሣጹን ማስተላለፍ አላቆምም፤ በምድራችን ላይ በምናደርሰው የተዛባ ተግባር በጐርፍ፣ በድርቅ፣ በመሬት መንቀጥቀጥና በአየር መዛባት እየገሠጸን እንደሆነ ማስተዋል አለብን፤ እግዚአብሔር ከጥንቱ ከጠዋቱ ጀምሮ ምድርን እንድንከባከባት፤ እንድናበጃት፣ እንድናጠብቃትና እንድናለማት አዞናል፤ ሆኖም ይህን ትእዛዙን ገሸሽ አድርገን በኬሜካልና በመርዛም ጋዝ ምድርን በመበከል፣ደንዋን በመመጠርና ራቁቷን በማስቀረት በምናደርገው ድርጊት አበሳ እየፈጸምን እንደሆነ ያወቅነው አይመስልም፤ በዚህም ምክንያት በጐርፍ፣ በድርቅ ለሰው ልጆች በማይመች የኣየር ፀባይ ወዘተ . . . ስጋት ውስጥ እየወደቅን ነው፤    በሌላም በኩል በምናወሳስበው የአስተዳደር ርእዮትና መሳሳብ የእግዚአብሔር ገንዘብ የሆነውን ሕዝብ እርስ በርሱ እንዲጋጭና ያላስፈላጊ አደጋ ላይ እንድወድቅ እያደረግን ነው፤ በዚህም ጠንቅ ሰላም እየደፈረሰ፣ ፍቅርና አንድነት እየላላ የሃይማኖት ክብርና ልዕልና እየተነካ ራሳችንንም እየጐዳን ነው፤በዚህ ሁሉ ተግባራችን  እግዚአብሔርን እያሳዘንን ነው፤ ይህ ሊገባንና ሊቈረቁረን ይገባል፤   የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት ለችግሮች ሁሉ መፍትሔ አላቸው፤ መፍትሔውም የሚገኘው ከእግዚአብሔርና ከእኛ ነው፤ ከእኛ በንስሓ ተመልሰን ከልብ እግዚአብሔርን ይቅርታ መጠየቅና ከክፉ ተግባራችን በእውነት መጸጸት ይጠበቃል፤ እግዚአብሔር ደግሞ ይህንን ዓይነቱ ንስሓ ከኛ መኖሩ ሲመለከት ምሕረትና ይቅርታን ይለግሰናል፤በዚህም መፍትሔና ፈውስ ይገኛል፤ ከዚህ አንጻር በአሁኑ ጊዜ ለሀገራችንና ለዓለማችን ስጋት የሆኑ የጦርነት ክሥተቶች፣ የመሬት መንቀጥቀጥ፣ የአየር መዛባት፣የድርቅ መከሠት፣የጎርፍ መጥለቅለቅ የሰላም መደፍረስ፣ የሰላማውያን ወገኖች መጎዳት፣ የፍቅርና የአንድነት መላላት ወዘተ. . . . ከምድራችን ተወግደው ፍጹም ምሕረትና ሰላም እናገኝ ዘንድ በኃጢኣታችን ተጸጽተን በምህላ ንስሓ መግባት አለብን፤ ከዚህ አኳያ ከጥንት ጀምሮ በቤተክርስቲያናችን ቀኖናዊ ሥርዓት መሠረት በየዓመቱ የሚጾመው ጾመ ነነዌ ለዚህ አመቺ ጊዜ ስለሆነ ከየካቲት ፫ ቀን ፳፻፲፯ ዓመተ ምሕረት ጀምሮ  ለሦስት ቀናት ከልኂቅ እስከ ደቂቅ ሁላችንም ጠዋትና ማታ በየቤተክርስቲያኑ ዐውደ ምሕረት እየተገኘን በንስሓ በዕንባ በጸሎት በምህላ የእግዚአብሔርን ምሕረትና ይቅርታ እንድንጠይቅ፤ እንደዚሁም በሀገራችንና በውጭ ያላችሁ ሊቃውንተ ሕዝብ ቀኖናውን ጠብቃችሁ ይህንን በማስፈጸም ምህላውን በቀኖናው መሠረት እንድታከናውኑ በእግዚአብሔር ስም አባታዊ መልእክታችንን እናስተላልፋለን፤ እግዚአብሔር አምላካችን ምሕረቱን ይቅርታውንና ሰላሙን ለሀገራችንና ለዓለማችን ይስጠን፤ ምህላችንንም ይቀበልልን፤    “እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ” ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን!!                አባ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስምወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት            ጥር ፳፱ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም                አዲስ አበባ ኢትዮጵያ © የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

ለሦስት ቀናት ከልኂቅ እስከ ደቂቅ ሁላችንም ጠዋትና ማታ በየቤተክርስቲያኑ ዐውደ ምሕረት እየተገኘን በንስሓ በዕንባ በጸሎት በምህላ የእግዚአብሔርን ምሕረትና ይቅርታ እንድንጠይቅ። ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ
+2
ለሦስት ቀናት ከልኂቅ እስከ ደቂቅ ሁላችንም ጠዋትና ማታ በየቤተክርስቲያኑ ዐውደ ምሕረት እየተገኘን በንስሓ በዕንባ በጸሎት በምህላ የእግዚአብሔርን ምሕረትና ይቅርታ እንድንጠይቅ። ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት የ2017 ዓ.ም የጾመ ነነዌ የሰላምና የጸሎት አዋጅ መግለጫ ሙሉ መልእክት የሚከተለው ነው፡፡ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ የተላለፈ የምህላ ሱባዔ፡- ‹‹ቀድሱ ጾመ ወስብኩ ምህላ አስተጋብኡ ሕዝበ ሊቃውንተ ሕዝብ፤ ጾምን ቀድሱ፣ጉባኤውንም አውጁ፤ሽማግሌዎችንና በምድር የሚኖሩትን ሁሉ ወደ ኣምላካችሁ ወደ እግዚአብሔር ቤት ሰብስቡ፤ ወደ እግዚአብሔርም ጩኹ (ኢዩ ፩÷፲፬)     ሁላችንም እንደምናውቀው ያለንበት ዓለም የመከራ ዓለም ነው፣ መከራው በኛ ስሕተትና ክፋት የመጣና እየሆነ ያለ መሆኑም ይታወቃል፤ እኛ የምንፈጽመው ጥቃቅንና ትላልቅ ግብረ ኃጢአት እግዚአብሔርን እንደሚያስቈጣ በቅዱስ መጽሐፍ ተረጋግጦ ያደረ ነው፤ ለዚህም ከነነዌ ነዋሪ ሕዝብ የበለጠ ማስረጃ የለንም፤ የነነዌ ከተማ ነዋሪዎች በፈጸሙት ግብረ ኃጢአት እግዚአብሔርን አስቈጥተዋል፤ ድርጊታቸው እግዚአብሔርን የሚያስቆጣ ቢሆንም እሱ ምሕረቱን ማስቀደም ስለፈለገ በዮናስ በኩል አስጠን ቅቆአቸዋል፤ የነነዌ ነዋሪዎችም በዮናስ በኩል የደረሳቸውን የንስሓ ጥሪ ወዲያውኑ ተቀብለው በምህላ፣ በጾም፣ በጸሎት ንስሓ ስለገቡ እግዚአብሔር ፍጹም ይቅርታ አድርጎላቸዋል፤ •  የተወደዳችሁ ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያን ልጆቻችንና ወገኖቻችን !

ብሂለ አበው "ሰማዕትነት ስር ነው፡፡ ክርስቲያኖች ደግሞ ከዚኽ ስር የሚያቆጠቁጡ ምርጥ ዘሮች ናቸው፡፡ ብዙ ዛፍ የሚያቆጠቁጥበት ስር በለም አፈር ስለሚሸፈን አይታይም፡፡ ከዚያ በሚያቆጠቁጡ ዛፎች ግን ስሩ እንዴት እንደተመቸው ይታወቃል፡፡ ሰማዕታትም በግዙፉ ዓይናችን እንደምን ያለ አክሊል ሽልማት እንደተቀበሉ አይታየንም፡፡ ፍሬያቸው ግን እነርሱን መስለው እነርሱን አኽለው በሚጋደሉ ምርጥ ዘሮች ይታወቃል፡፡" ✍ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ

✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨ ✨️ባሎች ለሚስቶቻቸው ሊያሳዩአቸው የሚገባ            ፍቅር ✨ ቤተ ክርስቲያን ለክርስቶስ እንደምትገዛ ሚስትህ ለአንተ ትገዛልህ ዘንድ ትሻለህን? ክርስቶስ ለቤተ ክርስቲያን እንዳደረገላት አንተም እንዲሁ ለሚስትህ አድርግላት፡፡ ሕይወትህን ስለ ርሷ አሳልፈህ መስጠት ካለብህ ስለርሷ ሕይወትህን አሳልፈህ ስጥ፤ መከራም መቀበል ካለብህ መከራን ለመቀበል አትሰቀቅ፡፡ አንተ ይህን ብትፈጽመው ስንኳ ክርስቶስ ለቤተ ክርስቲያን ካደረገላት ጋር ሲነጻጸር የሚወዳደር አይደለም፡፡ ምክንያቱም አንተ ይህን ያደረግኸው ከአንተ ጋር ፈጽማ ለተዛመደችህ ለአንዲት ሴት ነው፡፡ “እርሱ ግን ከእርሱ ለተመለሰችውና ለጠላቸው ራሱን አሳልፎ ሰጠ፡፡” ርሱ ከርሱ የተመለሰችውንና የጠላችውን እንዲሁም ያቃለለችውን ገንዘቡ ሲያደርጋት በማስፈራራት፣ በማስገደድ ወይም ይህን በመሳሰሉ ነገሮች አልነበረም፤ ነገር ግን ኀዘን ባልተቀላቀለበት ፍጹም በሆነ ፍቅር በመሆን ነበር፡፡ አንተም ለሚስትህ እንዲሁ አድርግላት አዎን! ምናልባት ሚስትህ አንተን ልታመናጭቅህ፣ ልትንቅህ፣ ልታፌዝብህም ትችላለች፤ ቢሆንም ግን አንተ ለርሷ ካለህ አርቆ አሳቢነት ንጹሕ ፍቅርና ኀዘኔታ የተነሣ ልትታገሣት ይገባሃል፡፡ ከሰው ሁሉ ጋር ተስማምቶ ለመኖርም ከእነዚህ የተሻሉ ነገሮች ፈጽሞ አናገኝም፡፡ በተለይም ለባልና ለሚስት፡፡ አንድ ሰው አገልጋይ ባሪያውን በማስፈራራት ለመግዛት ቢሞክር ለጥቂት ጊዜአት ሊገዛለት ይችላል፡፡ ሆኖም ይህ ባሪያ እንዲህ ዓይነት አገዛዝ ስለማይመቸው ከእርሱ ፈጥኖ ይሸሻል፡፡ ነገር ግን አንድ ሰው የሕይወቱን አጋር፣ የልጆቹን እናት፣ የደስታው ሁሉ ምንጭ የሆነችውን ሚስቱን በፍቅርና በፍጹም አክብሮት እንጂ ልክ እንደ ባሪያ በፍርሃት ሰንሰለት በማሰር ወይም በማስጨነቅ ርሷን ሊገዛት መሞከር አይገባውም፤ ሚስት በባልዋ ምክንያት የምትሸበር ከሆነ አንድነታቸው ምን ዓይነት አንድነት ነው? ከባሪያ ጋር እንደ መኖር ከሚስት ጋር መቀመጥ ለባል የሚፈጥርለት ምን ዓይነት ደስታ  ነው? አዎን ይልቁኑ አንተ ስለ ርሷ ስትል ብዙ መከራዎችን መቀበል ሲገባህ በተቃራኒው በቁጣ ርሷን በማስጨነቅና በማሸበር ታስፈራራታለህን? ክርስቶስ እንዲህ አላደረገም፡፡ “በውኃ መታጠብና ከቃሉ ጋር አንጽቶ አንዲቀድሳት ስለ ርሷ (ስለ ቤተ ክርስቲያን) ራሱን አሳልፎ ሰጠ ፡፡ ከቃሉ እንደምንረዳው ቤተ ክርስቲያን (እኛ) አስቀድማ ንጽሕት አልነበረችም፤ ጉድፍ ነበረባት፤ መልከ ጥፉም ነበረች፡፡ ስለዚህም ለእርሱ የተገባች አልነበረችም፡፡ አንተ እንደ ቤተ ክርስቲያን የሆነችውን ሴት ሚስትህ ትሆን ዘንድ አትመርጥም፡፡ ቤተ ክርስቲያን ከክርስቶስ የተለየችውን ያህል ከአንተ ፈጽማ የማትስማማውን ሴት ሚስትህ ትሆን ዘንድ ወደ አንተ አታቀርባትም፡፡ እርሱ ግን እጅግ መልከ ጥፉ ብትሆንም አልጠላትም፣ አልተጸየፋትም፣ ስለ መልከ ጥፉነቷ የተጻፈውን መስማት ትፈልጋለህን? ቅዱስ ጳውሎስ ስለ ርሷ ምን እንደሚል ስማ “ቀድሞ ጨለማ ነበራችሁ” (ኤፌ.፭፡፰) አላት፤ የገጽታዋን መጥቆር ትመለከታለህን? ከጨለማስ የበረታ ጥቁረት ምን አለ? የአመሏን መክፋት ደግሞ ስማ “በክፋትና በምቀኝነት” ይልና “የምንኖር” ይላል፤ ስለ ነውሮቿ ደግሞ “የማንታዘዝና የምንስት ለልዩ ልዩ ተድላ እንደ ባሪያዎች የምንገዛ” ይላታል (ቲቶ.፫፡፫)፡፡ ነገር ግን ለርሷ ስለተደረገላት በጎነት ምን ማለት ይቻለኛል? ርሷ ስንፍናን የተሞላችና ክፉ አንደበት የነበራት እንዲሁም በነውሮቿ ሁሉ ያደፈች ብትሆንም እነዚህ ሁሉ ጠባዮቿ ከርሷ አላራቀውም፡፡ ነገር ግን ልክ የደስ ደስ እንዳላት ልጃገረድ በአፍቃሪም ዘንድ ለምትወደድ ውብ ሴት እንደሚደረገው ርሱ ስለ ርሷ ራሱን አሳልፎ የሰጠ አይደለምን? ይህንንም በማድነቅ ቅዱስ ጳውሎስ “ስለጽድቅ የሚሞት በጭንቅ ይገኛልና ስለ ቸር ሰው ግን ሊሞት ስንኳ የሚደፍር ምናልባት ይገኛል” ይልና
“ነገር ግን ኃጢአተኞች ሳለን ክርስቶስ ስለ እኛ ሞቷልና”(ሮሜ.፭፥፯-፰)
ብሎአል፡፡ በዚህ መልክ ርሷ ለርሱ  ትሆን ዘንድ አቀረባት፤ በመንፈሳዊ ውበትም አስጌጣት፤ ንጽሕት አደረጋት፤ ስለ ርሷም ራሱን አሳልፎ ለመስጠት ስንኳ የጨከነ ሆነ፡፡ 📚የትዳር አንድምታ እንደ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ አስተምህሮ 📝በመምህር ሽመልስ መርጊያ ✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿

በዛሬው እለት በሻሸመኔ ከተማ ስለ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ዶግማ እና ስርዓት ሲሉ ሰማዕትነት የተቀበሉ የሻሸመኔ ሰማዕታት መታሰቢያ ነው። የማይረሳ ቁስል !!! በዚህች እለት ጥር 27 እለት የሻሸመኔ
በዛሬው እለት በሻሸመኔ ከተማ ስለ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ዶግማ እና ስርዓት ሲሉ ሰማዕትነት የተቀበሉ የሻሸመኔ ሰማዕታት መታሰቢያ ነው። የማይረሳ ቁስል !!! በዚህች እለት ጥር 27 እለት የሻሸመኔዎቹ ሰማእታት የተሰዉበት እለት ነች 2ኛ ዓመታቸውን በዚች እለት እንዘክራቸዋለን። ሰማዕታት የዚህችን ዓለም ጣዕም በእውነት ናቁ ፤ ደማቸውን ስለ እግዚአብሔር አፈሰሱ ፤ ስለ መንግስተ ሰማያት መራራ ሞትን ታገሱ" ውዳሴ ማርያም ዘሐሙስ ቁ፮ በረከታቸው ይድረሰን🙏

መድኀኔዓለም ክርስቶስ ሆይ ክቡዱንና ግዙፉን ዕፀ መስቀል በመሸከም ምንኛ ድካምንና መከራን ልትታገስ ቻልክ። ለዚህ ረቂቅ ትህትናህ አንክሮ ይገባል። ✝መልክዐ መድኃኔዓለም✝
መድኀኔዓለም ክርስቶስ  ሆይ ክቡዱንና ግዙፉን ዕፀ መስቀል በመሸከም ምንኛ ድካምንና መከራን ልትታገስ ቻልክ። ለዚህ ረቂቅ ትህትናህ አንክሮ ይገባል።      ✝መልክዐ መድኃኔዓለም

"ሁለቱም አንድ አካል ይኾናሉ ፤ ይህ ነገር ጥልቅ ፤ ረቂቅ ምሥጢር ነው ፤ እኔም ለክርስቶስና ለቤተክርስቲያን ምሳሌ አድርጌ እናገረዋለሁ፡፡" ሃይማኖተ አበው ዘስምዓት ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ ጥር 2
"ሁለቱም አንድ አካል ይኾናሉ ፤ ይህ ነገር ጥልቅ ፤ ረቂቅ ምሥጢር ነው ፤ እኔም ለክርስቶስና ለቤተክርስቲያን ምሳሌ አድርጌ እናገረዋለሁ፡፡" ሃይማኖተ አበው ዘስምዓት ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ ጥር  25 ቀን 2017 ዓ.ም በስርዓተ ቤተ ክርስቲያን ጋብቻችሁን የፈጸማችሁ ወጣት ደምስ እና ወ/ት ምህረት አስራት እንኳን ለዚህ ቀን አበቃችሁ፤ እንኳን ደስ ያላችሁ ። የአብርሃምንና የሣራን ፤ የይሰሐቅንና የርብቃን ጋብቻ የባረከ አምላክ አንድነታችሁን  ይባርክ እመብርሃን በአማላጅነቷ አትለያችሁ ፤ ቅዱስ ዮሐንስ ከፊት ይምራችሁ ከኋላ ይከተላችሁ እያለች  ፍኖተ ወንጌል ሰ/ት/ቤት መልካም የትዳር ሕይወት ትመኝላችኃለች። " ጋብቻ ንጹሕ ነው የወንድና የሴት አንድ መሆንንም እግዚአብሔር አክብሮታል "                           መጽሐፈ ዲድስቅልያ የቴሌግራም ቻናል:-  T.me/Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel27

"ሁለቱም አንድ አካል ይኾናሉ ፤ ይህ ነገር ጥልቅ ፤ ረቂቅ ምሥጢር ነው ፤ እኔም ለክርስቶስና ለቤተክርስቲያን ምሳሌ አድርጌ እናገረዋለሁ፡፡" ሃይማኖተ አበው ዘስምዓት ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ ጥር 2
"ሁለቱም አንድ አካል ይኾናሉ ፤ ይህ ነገር ጥልቅ ፤ ረቂቅ ምሥጢር ነው ፤ እኔም ለክርስቶስና ለቤተክርስቲያን ምሳሌ አድርጌ እናገረዋለሁ፡፡" ሃይማኖተ አበው ዘስምዓት ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ ጥር  25 ቀን 2017 ዓ.ም በስርዓተ ቤተ ክርስቲያን ጋብቻችሁን የፈጸማችሁ ወጣት ኢ/ር ፍሬዘር እና ወ/ት ትዕግሥት ወርቅነሕ እንኳን ለዚህ ቀን አበቃችሁ፤ እንኳን ደስ ያላችሁ ። የአብርሃምንና የሣራን ፤ የይሰሐቅንና የርብቃን ጋብቻ የባረከ አምላክ አንድነታችሁን  ይባርክ እመብርሃን በአማላጅነቷ አትለያችሁ ፤ ቅዱስ ዮሐንስ ከፊት ይምራችሁ ከኋላ ይከተላችሁ እያለች ፍኖተ ወንጌል ሰ/ት/ቤት መልካም የትዳር ሕይወት ትመኝላችኃለች። " ጋብቻ ንጹሕ ነው የወንድና የሴት አንድ መሆንንም እግዚአብሔር አክብሮታል "                           መጽሐፈ ዲድስቅልያ የቴሌግራም ቻናል:-  T.me/Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel27

ጥር ፳፪ በዚህች ዕለት ሊቀ መላእክት ቅዱስ ዑራኤል ከሰባቱ ሊቃነ መላእክት አንዱ በመሆን ከፍጥረተ ዓለም ጀምሮ በመብረቅና በነጎድጓድ ላይ ተሾመ፡፡ 🍁🍁🍁🍁🍁🍁🍁🍁🍁🍁🍁🍁 እምርተ ዕ
ጥር ፳፪ በዚህች ዕለት ሊቀ መላእክት ቅዱስ ዑራኤል ከሰባቱ ሊቃነ መላእክት አንዱ በመሆን ከፍጥረተ ዓለም ጀምሮ በመብረቅና በነጎድጓድ ላይ ተሾመ፡፡ 🍁🍁🍁🍁🍁🍁🍁🍁🍁🍁🍁🍁
እምርተ ዕለት በዓለ ሢመትከ ዛቲ። ድኅረ ዕረፍተ እም ኪዳነ እስመ ተወከፍከ ባቲ። ዑራኤል ሥዩም ካህነ መስቀል አሐቲ። ማኅበረነ ዕቀብ ኵለሄ እምቅኔተ ሰይጣን መስሐቲ ወጽዋዓ እዴከ ፈኑ ጽሙዓነ ታስቲ
ቅዱስ ዑራኤል ኾይ ይኽች የበዓል ሢመትኽ ዕለት እጅግ የከበረች የተመረጠች ዕለት ናት። ከድንግል ዕረፍት በኋላ ቃልኪዳን የተቀበልክባት ቀን ናትና። ቅዱስ ዑራኤል ኾይ በምዕመን መስቀል ላይ የተሾምክ ታማኝ አገልጋይ ካህን ነኽና። ከአሳሳች ነፃ አውጥተኽ ማኅበራዊ አንድነታችንን ለኹልጊዜ ጠብቅ። የሃይማኖት ጥመኖችንም ታጠጣ ዘንድ የእጅኽን ጽዋ ላክልን።" መልክአ ቅዱስ ዑራኤል የብርሃን መልአክ ከሣታ ምሥጢር የኾንከው  ቅዱስ ዑራኤል ኾይ ጥበቃህና የቃል ኪዳንህ ረድኤት ዘወትር አይለየን። አሜን🙏

✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ ጥር ፳፩ በዚህች ዕለት ለከበረች አምላክን ለወለደች ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የዕረፍቷ መታሰቢያ በዓል ነው። ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ "ሞትሰ ለመዋቲ ይደሉ ሞታ ለማር
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ ጥር ፳፩ በዚህች ዕለት ለከበረች አምላክን ለወለደች ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የዕረፍቷ መታሰቢያ በዓል ነው። ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ "ሞትሰ ለመዋቲ ይደሉ ሞታ ለማርያም የዐጽብ ለኲሉ" ትርጉም:- "ሞት ለሟች ይገባዋል የማርያም ሞት ግን ሁሉን ያስደንቃል"  ቅዱስ ያሬድ እግዚአብሔር አምላክ በእናቱ በእመቤታችን አማላጅነት ከመከራ ሥጋ ከመከራ ነፍስ ይሠውረን፡፡ አሜን!🙏 ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨

🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁 "እግዚአብሔር ሰው ይፈልጋል!" ልቡ ንጹሕ የኾነውን፣ አሳቡ የተቃናውን፣ ማግኘት የማይለውጠውን፣ ይቅርታ አድራጊውን፣ ለእውነት ተቆርቋሪውን፣ ተለሳልሶ የማይናደፈውን፣ ለፍቅር ዋጋ የሚከፍለውን፣ አድሮ የማይቀለውን፣ በየወንዙ አቋሙን የማይለውጠውን፣ ለጥፋቱ ሙሉ ለሙሉ ኃላፊነቱን የሚወስደውን፣ ለቆዳው ሳይኾን ለቅንነቱ የሚጨነቀውን፣ የሃይማኖት አባቶችን የሚያከብረውን፣ ለመታዘዝ ራሱን ያዘጋጀውን፣ ክስና ክርክርን የናቀውን፣ በገርነት የሚያዳምጠውን፣ ትጋትና ትዕግስትን የያዘውን፣ ለመንገዱ ግብ ያለውን ሰው ይፈልጋል፡፡" "ልጄ ኾይ ሰው ኹን" ፩ነገ ፪፥፪ 🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿 መልካም ቀን ይሁንላችሁ ።

ወንድሞች ሆይ ሁላችን እንሞታለን። በዚህ ዓለም ሳለን እርስ በርሳችን የማንዋደድ ከሆነ ከባድ ይሆንብናል። ከጠላቶቻችን ጋር ፈጥነን  የማንታረቅ ከሆነ ያስቀየምናቸውንም ወገኖች ይቅርታቸውን የማናገኝ ከሆነ አንዱ ሌላውን የሚኮንን ከሆነ ይቅርም ካላልነው ችግር ይፈጠርብናል። በሚመጣውም ዓለም ዘላለማዊ ሕይወትን አናገኝም። ሰማያዊው አባታችን ኃጢአታችንን ይቅር አይለንም።    "ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ"        

የኤርትራ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ስድስተኛ ፓትርያርክ በዓለ ሢመት ተከናወነ ! ⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺ የኤርትራ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ስድስተኛው ፓት
+3
የኤርትራ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ስድስተኛ ፓትርያርክ በዓለ ሢመት ተከናወነ ! ⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺ የኤርትራ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ስድስተኛው ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ባስልዮስ በዓለ ሢመት በአሥመራ ቅድስት ማርያም በዛሬው ዕለት ተካሂዷል። በበዓለ ሢመቱ ላይ የኤርትራ ፕሬዚዳንት ኢሳይያስ አፈወርቅን ጨምሮ የኤርትራ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሊቃነ ጳጳሳት ፤ ከግብፅ ፣ ከሩሲያ ፣ ከግሪክ ፣ ከአርመን ፣ ከሶሪያ እና ከሕንድ የተውጣጡ የውጭ ሀገር ልዑካን ፣ የሀገሪቱ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ፣ የዲፕሎማቲክ ቡድን አባላት ፣ የሁሉም አህጉረ ስብከትና የዋና ዋና ገዳማት ተወካዮችና ምእመናን ተገኝተዋል። ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ባስልዮስ ታኅሣሥ 30 ቀን 2017 ዓ.ም የኤርትራ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ እንዲሆኑ መመረጣቸው ይታወሳል።

✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ ጥር አሥራ ስምንት በዚህች ቀን የሰማዕታት አለቃ የቅዱስ ጊዮርጊስ አፅሙ ተቃጥሎ ተደቁሶ ይድራስ በተሰኘ ተራራ ላይ የተበተነበት የመታሰቢያው ዕለት ነው፡፡ "ከመ ጸበል ዘነፍስ
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ ጥር አሥራ ስምንት በዚህች ቀን የሰማዕታት አለቃ የቅዱስ ጊዮርጊስ አፅሙ ተቃጥሎ ተደቁሶ ይድራስ በተሰኘ ተራራ ላይ የተበተነበት የመታሰቢያው ዕለት ነው፡፡
"ከመ ጸበል ዘነፍስ ዘረውዎ ደብረ ይድራስ ወወገርዎ ውስተ አዘቅት ይቡስ ለብፁዕ ወለቅዱስ ጊዮርጊስ አማን ፀሐየ ልዳ ኮከበ ፍርስ"።
ትርጉም፦ ነፍስ እንደሚበትው አቧራ (ትብያ አፈር) በይድራስ ተራራ ላይ በተኑት፡፡ ንዑድ ክቡር ቅዱስ ጊዮርጊስን ደረቅና ጥልቅ ወደሚሆን ጉድጓድ ውስጥ ጣሉት ንዑድ ክቡር ቅዱስ ጊዮርጊስ በእውነት የልዳ ፀሐይ የፋርስ ኮከብ። ሊቁ ቅዱስ ያሬድ በድጓው   ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ "ገድሉ የበዛ የተትረፈረፈ ኃያል፤ ተጋዳይ ብርቱ ሰው፤ በተዘረጋ ዙፋን ላይ ኃይልን ያሳየ በሰማይና በምድር መካከል ያለ የማይቆጠር የክብር ኮከብ፤ ተዓምሩ እንደ ባሕር አሸዋ የበዛ የኾነ፤ የፀሐየ ጽድቅ የኢየሱስ ክርስቶስ ሰማዕት ለኾነ ለቅዱስ ጊዮርጊስ ሰላምታ ይገባል።"                                     ተዓምኆ ቅዱሳን                         ዘአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ለእግዚአብሔር ምሥጋና ይኹን እኛንም በከበረ ቅዱስ ጊዮርጊስ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር🙏 አሜን።

🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨ ✨ሊኖሩበት የሚገባ መርህ ✨ በመንፈሳዊ አገልግሎት ውስጥ ከብጽዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ንግግር የተሻለ መርህ ለማግኘት ከባድ ነው። ይህንን መርህ ሁላችንም ብንከተል እግዚአብሔር የሰጠንን መክሊት ተጠቅመን ያለምንበት መድረስ እንችላለን። የአባት ምክር እነሆ:- "እግዚአብሔር ለእያንዳንዱ ሰው ሥራ ሰጥቶታል፤ ያንን መሥራት የእሱ ፈንታ ነው፡፡ ቢቻለው እሱን ማገድ የዲያቢሎስ ሥራ ነው፡፡ በእርግጥ ሥራው እግዚአብሔር እንደሰጠህ ያህል ሰይጣን ሊያግድህ ይጥራል፡፡ ሌላ ነገር በበለጠ ደስ የሚያሰኝ ሊያቀርብልህ ይጥራል፡፡ በዓለማዊ ተስፋዎች ያባብልሃል፡፡የሐሜት ጐርፍ ያስወርድብሃል፡፡ ደራስያን እንዲጠይቁህ፥ እጅግ ስመ ጥር ሰዎችም በክፉ እንዲናገሩብህ ይጠቀምባቸዋል፡፡ ጲላጦስ፣ ሄሮድስ፣ሐናንያ፣ ቀያፋ ሁሉም በአንተ ላይ ያድማሉ፡፡ ይሁዳም በአጠገብህ ቆሞ በሠላሳ ብር ሊሸጥህ ይከጅላል፡፡ ይሄ ሁሉ የደረሰብህ ሰይጣን በዚህ ከሥራህ ሊስብህና እግዚአብሔርን ከመታዘዝ ሊያሰናክልህ መሆኑን ልትገነዘብ አትችልምን? አንተ ግን ሥራህን ሥራ! አንበሳው ሲያጓራ ፍንክች አትበል፣ የሰይጣንን ውሻዎች ለመውገር አትቁም፡፡ ጥንቸሎቹንም በማባረር ጊዜህን አታጥፋ፡፡ ሥራህን ሥራ! ዋሾች ይዋሹ፣ ጠበኞች ይጣሉ፣ ማኀበሮችም ይወስኑ፣ ደራሲዎችም ይድረሱ፣ ሰይጣንም የፈለገውን ያድርግ፣ አንተ ግን ምንም ነገር እግዚአብሔር የሰጠህን ሥራ ከመፈጸም እንዳያግድህ ተጠንቀቅ፡፡ ገንዘብ እንድታተርፍ አልተላክም፣ እንድትበለጽግም አልታዘዝክም፣ ለክብርህ ተከላከል ብሎ አልነገረህም፣ ሰይጣንና አገልጋዮቹ የሚነዙትን የሐሰት ወሬ እንድታስተባብል አልተጠየቅክም፤ እነዚህን ሁሉ ነገሮች ብታደርግ ሌላ ሥራ ልትሰራ አትችልም። ይህም ብቻ ሳይሆን ለራስህ እንጂ ለእግዚአብሔር አልሠራህም፡፡ ዓላማህ እንደ ኮከብ የጸና ይሁን ፤ ተወው ዓለም እንደፈለገው ይነታረክ፣ ይጨቃጨቅ፣ ጥቃት ይደርስብህ ትበደል፣ ትሰደብ፣ ትታማ፣ ትቆስልና፣ ትናቅ ይሆናል፡፡ ኃይለኛ ያጐሳቁልህ፣ ወዳጆች ይተውህ፣ ሰዎችም ይንቁህ ይሆናል፡፡ አንተ ግን በጸና ውሳኔ የማያወላውል ቅናት በመጨረሻ ላይ ጸንተህ፣ የሰጠኸኝን ሥራ ፈጸምኩ ሃይማኖትንም ጠበቅሁ ለማለት እስክትችል ድረስ የሕይወትህን ዓላማ እና የተፈጠርክበትን ግብ ተከተል!" 📝ብጽዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ ✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿

🍂🍂🍂🌿🌿🌿✨✨✨✨🍂🍂🍂🌿🌿🌿✨✨✨✨ • ጊዜው ገና ነው • አንድ ምንጩ የማይታወቅ አስተማሪ የሆነ አፈ-ታሪክ አለ። በዚህ አፈ-ታሪክ መሠረት፥ ከእለታት በአንዱ ቀን አጋንንት ስብሰባ አደረጉ ይባላል። ይህንን ስብሰባ የጠራው የአጋንንቱ አለቃም “ዓለምን ሁሉ ከእኔ ጋር ለማሰለፍ እፈልጋለሁ። ምን ይደረግ? ማንንስ ልላክ?” ብሎ ጠየቀ። ከሥሩ ያሉትም አንድ በአንድ እየተነሱ አሳቦችን ማቅረብ ጀመሩ።  አንዱ ተነሳና፥ “እኔን ብትልከኝ፥ ፈጣሪ የለም ብዬ ሰዎችን ማሳመን እችላለሁ!” ብሎ ተናገረ። የአጋንንቱ አለቃ ግን፥ “እርሱ አይሠራም። ብዙዎቹ አያምኑህም። ፈጣሪ እንዳለ ያውቃሉ።” ብሎ መለሰ።  ሌላኛው ተነሳና፥ “እኔን ከላክኸኝ፥ ገነትም ሆነ ሲኦል የሚባል ቦታ እንደሌለ አሳምናቸዋለሁ!” አለ። የአጋንንቱ አለቃ ግን፥ “እርሱም አይሠራም። ብዙዎቹ ከሞት በኋላ ሕይወት እንዳለ ያውቃሉ።” ብሎ መለሰ።  ሌላው ደግሞ ተነሳና፥ “እኔን ላከኝ። ፈጣሪም አለ፥ ገነትም አለ፥ ሲኦልም አለ፤ ነገር ግን ስለዚህ ነገር ሁሉ ለማሰብ ጊዜው አሁን አይደለም ብዬ አሳምናቸዋለሁ።” አለ። የአጋንንቱ አለቃም ደስ እያለው “ይህ ጥሩ መንገድ ነው!” በማለት አሳቡን ተቀበለና ላከው ይባላል። ሰይጣን ማዘግየት ጥሩ ስልት መሆኑን ስለሚያውቅ፥ ለማዘግየት ይፋጠናል። በሐዲስ ኪዳን ላይ ቅዱስ ጳውሎስ
"ወደ እናንተ ልንመጣ ወደን ነበርና፥ እኔ ጳውሎስም አንድና ሁለት ጊዜ፥ ሰይጣን ግን አዘገየን።” (1 ተሰ 2:18)
ሲል እናገኘዋለን። ሰይጣን ላያስቀረን ይችላል፥ ግን ቢያንስ ሊያዘገየን ብዙ ይሞክራል። እርሱ ዓለማዊ ጓዞቻችንን ለአፍታ ስንኳ አውርደን ከእግዚአብሔር ጋር ስላለን ግንኙነት እንድናስብ አይፈልግም። ስለ ጸሎት ብታስብ፥ "አሁን ደክሞሃል። ጊዜው አይደለም። ሌላ ጊዜ ትጸልያለህ" ይልሃል። ለመጾም ብትዘጋጅ "አሁን ጉልበት ስለሚያስፈልግህ ብላ። የምትጾምበት ጊዜ አይደለም፤ ሌላ ጊዜ ትጾማለህ።" ይልሃል። ለመስገድ ብትዘጋጅ "ኧረ ተረጋጋ፤ ጊዜው አይደለም፥ ጾም ሲገባ ትሰግዳለህ" ይልሃል። ንስሃ ልትገባ ብትዘጋጅ "ቆይ እንጂ፥ ዘልለህ ጨርሰህ አንዴ ብትታጠበው አይሻልም?" ለማለት የሚቀድመው የለም። ቅዱስ ቁርባን ልቀበል ነው ካልክ "አንተኮ ገና ነህ፥ ለወደፊት ጣጣህን ስትጨርስ ቀስ ብለህ አመቻችተህ ትቆርባለህ" ብሎ ያዘናጋሃል። በዚህ ሁሉ መዘግየት ውስጥ መልአከ ሞት መቼ እንደሚመጣ ማን ያውቃል? ለመንፈሳዊ ነገር ስንነሳ፥ ሰይጣን "ጊዜው ገና ነው" ማለቱ አይቀርም። እኛ ደግሞ የእግዚአብሔር ቃል“
የተወደደው ሰዓት አሁን ነው፤ እነሆ፥ የመዳን ቀን አሁን ነው።” (2ኛ ቆሮ 6፥2)
እንደሚል እናስታውስ። ለመዳናችን ቀጥሮ አንስጥ። ✨✨✨ ✍️ መ/ር ፍሬሰንበት አድኃኖም የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ የዕብራይስጥ ቋንቋ መምህር 🌿️️️️🌿️️️️🌿️️️️✨✨✨🌿️️️️🌿️️️️🌿️️️️✨✨✨🌿️️️️🌿️️️️🌿️️️️✨✨✨

ፍቅረኛ ለመያዝ ቀና ልብ ይፈልጋል። ከዛ ደግሞ አስተዋይ መሆን አለብን። ምክንያቱም ዘው ብለን የምንገባው የሰው ህይወት ውስጥ ነው። ስንወጣ ደግሞ የሰውን ልብ እና ቅስሙን ሰባብረን... ህይወቱን አመሰቃቅለን ... ስሜቱን ጎድተን ተስፋ አስቆርጠን ነው የምንወጣው። ይህን ሁሉ በደል ከማድረሳችን በፊት እስክንበስል ፍቅረኛ አንያዝ። - ይኸውልሽ <አርግዣለሁ > ብለሽ ፍቅረኛሽን የመፈተን እድሜ ላይ ካለሽ ፍቅረኛ ይቅርብሽ። ምን አድርጌ ላስደስተው ብሎ ከመጨነቅ ይልቅ ምን ብዬ ላስጨንቀው የምትይበት እድሜ ላይ ከሆንሽ ይቅርብሽ። የእንትና ባል ለሷ እንዲ ያደርጋል አንተ ግን... ምናምን የሚል አስተሳሰብ ላይ ከሆንሽ ገና አልበሰልሽም። ፍቅር ማለት ካፌ ለካፌ ሬስቶራንት ለሬስቶራንት መንከራተት መስሎ የሚሰማሽ ከሆነ በቃ ይቅርብሽ። ፍቅሩን የገለፀልሽን ቴክስቶች ለሴት ጓደኞችሽ በማሳየት <እኔ እኮ እስከዚህም ነኝ .. > ብለሽ የማውራት ሞራል ላይ ከሆንሽ ይቅርብሽ። - ይኸውልህ። ስለፍቅረኛህ ለጓደኞችህ መናገር የምታፍርበት ጊዜ ላይ ከሆንክ ተወው ፍቅረኛ አትያዝ። <እኔ እኮ ለሷ እስከዚህም ነኝ ስለምታሳዝነኝ ነው ወይ ደግሞ እሷ ናት በደንብ የምታፈቅረኝ > ብለህ የምታወራበት እድሜ ላይ ካለህ አታፍቅር። አውቀህ ስልክ አለማንሳት ... ሚስኮሎቿን ለጓደኞችህ ለማሳየት የምትጣጣር እድሜ ላይ ካለህ ይቅርብህ። ጊዜ ያለመስጠት ... የማስቀናት... ሌላ ሴት የመደረብ ሞራል ላይ ከሆንክ ገና ስለሆንክ ፍቅረኛ አትያዝ። ስንት ልቦች የተሰበሩት... ስንት ተስፋዎች የተቆረጡት ...ስንት ቤቶች የተዘጉት ... ስንት ህይወቶች የጠፉት በግዴለሽ ፍቅር ነው። ፍቅርን ሁሉም ሰው ይፈልገዋል። የሰው ልጅ ሁሉ ይፈልገዋል። ግን በግዴለሽ አፍቃሪ ነን ባዮች አጥተውታል። ሰው ሁን ከሰውም ሰው ሁን ምንጭ ከሀሽማል ወመዘክር