ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት
Open in Telegram
በአሰላ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። የቴሌግራም ቻናል:- @Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- @FinoteWongel27 የቲክቶክ ገፅ:- https://www.tiktok.com/@finotewongel27 Youtube:- https://www.youtube.com/@Finote_Wongel ©ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት
Show more669
Subscribers
No data24 hours
+27 days
No data30 days
Posts Archive
+1
ውድ የፍኖተ ወንጌል ፍሬዎች እንኳን ደስ አላችቹ።
ከታች ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።
▭▭▭▭▭▭▭▭▭ ◎⃝ ◎⃝ ⃟ ◎⃝ ◎⃝ ▭▭▭▭▭▭▭▭▭
ዛሬ ላይ ነገን ለማነጽ የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ድምጽ ልንገነባ ነው። #ሚዲያችንን_ይደግፉ
የአሰላ ደ/መ/መ/ዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት
🔎 የቴሌግራም ቻናል:- T.me/Finote_Wongel
🔎 የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel27
🔎 የቲክቶክ ገጽ:- tiktok.com/@finotewongel27
🔎 Youtube:- youtube.com/@Finote_Wongel
🔎 Instagram:- https://www.instagram.com/finote_wongel
🔎 Facebook:- https://www.facebook.com/profile.php?id=61558615513475
▭▭▭▭▭▭▭▭ @FinoteWongel1 ▭▭▭▭▭▭▭▭
ማስታወቂያ
📢
ወደ ሸንኮራ ደብረ መንክራት መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ቤተ ክርስቲያን የቅዱስ ዮሐንስን በዓለ ልደት ለማክበር እና ከመጥምቁ በረከትን ለማግኘት ወደ ስፍራው ለመጓዝ በሰንበት ት/ቤታችን የተመዘገባችሁ ሁላችሁም ነገ ጥዋት መኪና የሚነሳው 12:00 ሰዓት ስለሆነ ቀደም ብላችሁ እንድትገኙልን ስንል መልዕክታችንን እናስተላልፋለን ።
አባታችን እና አምላካችን ቸሩ መድኃኔዓለም ከፊት ከኋላ እየጠበቀን መንገዳችንን ያቅናልን!
በሰላም ይመልሰን🙏
🎲 Quiz 'Qophii Gaafii fii Deebii Daandii Wangeelaa. Carra Gaarii🛎🛎🛎'
🖊 5 questions · ⏱ 30 sec
🎲 Quiz 'ፍኖተ ወንጌል ልዩ የጥያቄና መልስ ውድድር "start the quiz"የሚለውን ሲጫኑ "i am ready"ሲጫኑ ጥያቄው ይጀምራል ። መልካም ዕድል🛎🛎🛎'
🖊 6 questions · ⏱ 30 sec
1 ቀን ብቻ ቀርቶታል
ፈጥነው ይመዝገቡ!
የመጥምቁን ቅዱስ ዮሐንስ በዓለ ልደት በጸበሉ ብዙ ተአምራትን በሚሰራበት በታላቁ ገዳም በሸንኮራ ዮሐንስ ኑ አብረን እናክብር።🗓 ሰኔ 29 ቀን መነሻ 🗓 ሐምሌ 1 በጥዋት መመለሻ 👉በአሰላ ደ/መ/መ/ዓ/ካቴድራል ፎቅ ስር በፍኖተ ወንጌል ሰ/ት/ቤት ንዋያተ ቅድሳት መሸጫ ሱቅ መመዝገብ ይችላሉ። 👉በዚህ ጉዞ ላይ በመሳተፍ በረከትን ያገኙ ዘንድ ‼️ፈጥነው ይመዝገቡ‼️ 🔎 የቴሌግራም ቻናል:- T.me/Finote_Wongel 🔎 የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel27
#በሕይወታችን_የጎደለውን_ኹሉ_የዓለሙ_ቤዛ
#ቸሩ_መድኃኔዓለም_ይሙላልን።
የወደቀ የሚያነሳ የፈጠረውን የማይረሳ የደክመን የሚያበረታ የታመመን የሚፈውስ ያዘነን የሚያጽናና የተከፋን የሚያስደስት የተሰበረን የሚጠግን የዘለዓለም አባት ልዑል እግዚአብሔር ስሙ ለዘለዓለም እስከ ዘለዓለሙ የተመሰገነ ይሁን አሜን።
#በጨነቃቹ_በተከፋችሁ_ጊዜ_ቸሩ_መድኃኔዓለም_አለሁ_ይበላችሁ።
ከታች ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።
▭▭▭▭▭▭▭▭▭ ◎⃝ ◎⃝ ⃟ ◎⃝ ◎⃝ ▭▭▭▭▭▭▭▭▭
ዛሬ ላይ ነገን ለማነጽ የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ድምጽ ልንገነባ ነው። #ሚዲያችንን_ይደግፉ
የአሰላ ደ/መ/መ/ዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት
🔎 የቴሌግራም ቻናል:- T.me/Finote_Wongel
🔎 የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel27
🔎 የቲክቶክ ገጽ:- tiktok.com/@finotewongel27
🔎 Youtube:- youtube.com/@Finote_Wongel
🔎 Instagram:- https://www.instagram.com/finote_wongel
🔎 Facebook:- https://www.facebook.com/profile.php?id=61558615513475
▭▭▭▭▭▭▭▭ T.me/FinoteWongel1 ▭▭▭▭▭▭▭▭
✨✨✨ እንኳን ለ፶፪ኛ ዓመት የምስረታ በዓል በሰላም አደረሳችሁ✨✨✨
በመላው ዓለም የምትገኙት የፍኖተ ወንጌል ሰንበት ትምህርት ቤት አባላት እና ቤተሰቦች እንኳን ለ፶፪ኛ ዓመት የምስረታ በዓላችን አደረሳችሁ እንላለን።
ሰንበት ትምህርት ቤት ዛሬም ትፈልጋችኋለች። ዛሬም ባላችሁበት አገልግሎታችንን እንድንደግፍ ሰንበት ትምህርት ቤታችሁ ትጣራለች።
✨ የሰንበት ትምህርት ቤቴን ውለታ አልረሳም !!
✨ ዛሬም በአገልግሎት እሳተፋለሁ እደግፋለሁ።
እንኳን ለ፶፪ኛ ዓመት የምስረታ በዓል በሰላም አደረሳችሁ።
አድራሻ :- አሰላ ደ/መ/መ/ዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት አዳራሽ
#share
#share
#share
ዛሬ ላይ ነገን ለማነጽ የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ድምጽ ልንገነባ ነው። #ሚዲያችንን_ይደግፉ
▭▭▭▭▭▭▭▭▭ ◎⃝ ◎⃝ ⃟ ◎⃝ ◎⃝ ▭▭▭▭▭▭▭▭▭
የአሰላ ደ/መ/መ/ዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት
🔎 የቴሌግራም ቻናል:- T.me/Finote_Wongel
🔎 የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel27
🔎 የቲክቶክ ገጽ:- tiktok.com/@finotewongel27
🔎 Youtube:- youtube.com/@Finote_Wongel
🔎 Instagram:- https://www.instagram.com/finote_wongel
▭▭▭▭▭▭▭▭ @FinoteWongel1 ▭▭▭▭▭▭▭▭
✨✨✨ እንኳን ለ፶፪ኛ ዓመት የምስረታ በዓል በሰላም አደረሳችሁ✨✨✨
በመላው ዓለም የምትገኙት የፍኖተ ወንጌል ሰንበት ትምህርት ቤት አባላት እና ቤተሰቦች እንኳን ለ፶፪ኛ ዓመት የምስረታ በዓላችን አደረሳችሁ እንላለን።
ሰንበት ትምህርት ቤት ዛሬም ትፈልጋችኋለች። ዛሬም ባላችሁበት አገልግሎታችንን እንድንደግፍ ሰንበት ትምህርት ቤታችሁ ትጣራለች።
✨ የሰንበት ትምህርት ቤቴን ውለታ አልረሳም !!
✨ ዛሬም በአገልግሎት እሳተፋለሁ እደግፋለሁ።
እንኳን ለ፶፪ኛ ዓመት የምስረታ በዓል በሰላም አደረሳችሁ።
አድራሻ :- አሰላ ደ/መ/መ/ዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት አዳራሽ
#share
#share
#share
ዛሬ ላይ ነገን ለማነጽ የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ድምጽ ልንገነባ ነው። #ሚዲያችንን_ይደግፉ
▭▭▭▭▭▭▭▭▭ ◎⃝ ◎⃝ ⃟ ◎⃝ ◎⃝ ▭▭▭▭▭▭▭▭▭
የአሰላ ደ/መ/መ/ዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት
🔎 የቴሌግራም ቻናል:- T.me/Finote_Wongel
🔎 የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel27
🔎 የቲክቶክ ገጽ:- tiktok.com/@finotewongel27
🔎 Youtube:- youtube.com/@Finote_Wongel
🔎 Instagram:- https://www.instagram.com/finote_wongel
▭▭▭▭▭▭▭▭ @FinoteWongel1 ▭▭▭▭▭▭▭▭
52ኛ ዓመት የልደት በዓል
እነሆ የሀገር ባለውለታ የሰንበት ትምህርት ቤቶች ፈርጥ የአሰላ ደ/መ/መ/ዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰ/ት/ቤት የተወለደችበትን 52ኛ ዓመት ሊከበር ጥቂት ቀናት ብቻ ቀርተውታል::
ስለሆነም የሰንበት ት/ቤታችን የልደት በዓል ባማረና በደመቀ መልኩ እንዲከበር ከወራት ሐምሌን ከዕለታት ቅዳሜና እሁድ ከቀናት 13 እና 14 ተመርጠው በደማቅ ሁኔታ ለማክበር ዝግጅቱ ተጀምሯል።
ስለዚህ እርስዎም በዕለቱ ቅዳሜ ሐምሌ 13 ከቀኑ 6:00 ጀምሮ እሑድ ሐምሌ 14/2016 ዓ.ም ከቅዳሴ በኋላ ከጠዋቱ 3:00 ሰዓት ጀምሮ በደመቀ ሁኔታ ስለሚከበር እርስዎም በእለቱ በመርሐ ግብሩ ላይ ተገኝቸው የደስታችን ተካፋይ እንዲሆኑ በአክብሮት ተጋብዘዋል::
በእለቱም የሰንበት ትምህርት ቤቱ ክፍላት እና ሰ/ት/ቤቱ ያፈራቸው አገልጋዮች 30፣ 60፣ 100 ፍሬ የምናፈራበትን ልዩ ልዩ መረሐ ግብሮች ይዘው ይቀርባሉ::
ባለውለታዬ ማንነቴ ዛሬ ላለሁበት መሠረቴ ሰንበት ትምህርት ቤቴ አንቺ ጠርተሽኝማ አልቀርም ልደትሽ ልደቴ ደስታሽ ደስታዬ ነው።
እናቴ መልካም ልደት ይሁንልሽ አሁንም ማህጸንሽ ይለምልም።
ዛሬ ላይ ነገን ለማነጽ የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ድምጽ ልንገነባ ነው። #ሚዲያችንን_ይደግፉ
▭▭▭▭▭▭▭▭▭ ◎⃝ ◎⃝ ⃟ ◎⃝ ◎⃝ ▭▭▭▭▭▭▭▭▭
የአሰላ ደ/መ/መ/ዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት
🔎 የቴሌግራም ቻናል:- T.me/Finote_Wongel
🔎 የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel27
🔎 የቲክቶክ ገጽ:- tiktok.com/@finotewongel27
🔎 Youtube:- youtube.com/@Finote_Wongel
🔎 Instagram:- https://www.instagram.com/finote_wongel
▭▭▭▭▭▭▭▭ @FinoteWongel1 ▭▭▭▭▭▭▭▭
#ሰኔ_25
አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
ሰኔ ሃያ አምስት በዚች ቀን ከሰባ ሁለቱ አርድእት አንዱ የፀራቢው ዮሴፍ ልጅ #ሐዋርያው_ይሁዳ በሰማዕትነት ሞተ፣ የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት #ቅዱስ_አባ_ጴጥሮስ አረፈ፣ ሰማዕቱ #መስፍኑ_ጲላጦስ መታሰቢያው ነው፡፡
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#ቅዱስ_ይሁዳ_ሐዋርያ (ከ72ቱ አርድእት)
ሰኔ ሃያ አምስት በዚህች ቀን ከሰባ ሁለቱ አርድእት አንዱ የፀራቢው ዮሴፍ ልጅ ሐዋርያው ይሁዳ በሰማዕትነት ሞተ። ይህም ሐዋርያ በብዙ አገሮች ሰበከ ወደ አንዲት ደሴትም ገብቶ በውስጧም ሰበከ ሰዎቿንም በጌታ አሳመናቸው ቤተ ክርስቲያንም ሠራላቸው በቀናች ሃይማኖትም አጸናቸው።
ከዚያም ወደ ሮሃ ሀገር ሒዶ የሮሃ ንጉሥ አውጋንዮስን ከደዌው ፈወሰው የክርስትና ጥምቀትንም አጠመቀው ከዚያም ደግሞ ሐራፒ ወደሚባል አገር ሒዶ በውስጧ ሰበከ ከሰዎቿ ብዙዎቹን አጠመቃቸው ቤተ ክርስቲያንም ሠራላቸው።
የዚያችም አገር ገዥ ይዞ ጽኑዕ ሥቃይ አሠቃየው ችንካር ያለው ጫማ በእግሮቹ ውስጥ አድርጎ አንድ ምዕራፍ ያህል አስሮጠው ከዚህም በኋላ ሰቅሎ በፍላፃ ነደፈው ክብር ይግባውና በጌታችን እጅ ነፍሱን ሰጠ።
ከመከራውም አስቀድሞ ለምእመናን መልእክትን ጽፎ ላከ እርሷም ከሐዋርያት መልእክቶች ሰባተኛ የሆነች ምሥጢርን የተመላች ናት በእርሷም ብዙዎች አረማውያንን ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ወደ ማመን አስገባቸው።
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#አባ_ጴጥሮስ_ሊቀ_ጳጳሳት
ዳግመኛም በዚህች ቀን ለአባቶች ሊቃነ ጳጰሳት አርባ አራተኛ የሆነ የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት ቅዱስ አባ ጴጥሮስ አረፈ። ይህም አባት ከመሾሙ በፊት የማርቆስ መንበር ያለ ሊቀ ጳጳሳት ለብዙ ዘመናት ኖረ የእስላሞች ንጉሥና መኳንንቶቹ አልፈቀዱላቸውም ነበርና።
ከዚህም በኋላ ሃይማኖቱ የቀና ደግ መኰንን በእስክንድርያ ከተማ ላይ ተሾመ ያንጊዜም የአገር ሽማግሌዎች ወደ ርሱ ተሰብስበው ሊቀ ጳጳሳት እንደ ሌላቸው ኀዘናቸውን ነገሩት። እርሱም ደብረ ማሕው ወደሚባለው ወደ ደብረ ዝጋግ ወጥተው እንዲጸልዩ ለራሳቸውም ሊቀ ጳጳሳት እንዲሾሙ አዘዛቸው። በዚህም ነገር ደስ ብሏቸው ቀሲስ አባ ጴጥሮስን ወስደው ሊቀ ጵጵስና ሾሙት በእርሱም ደስ አላቸው።
በዚያም ወራት የአንጾኪያ ሊቀ ጳጳሳት አባ ሳዊሮስ ሞተ የአንጾኪያ አገርም ያለ ሊቀ ጳጳሳት ትኖር ነበር የአንጾኪያ ምእመናንም ለእስክንድርያ ከተማ አባ ጴጥሮስ እንደ ተሾመ በስሙ ጊዜ እነርሱም የተማረ ደግ ሰው ለአንጾኪያ ሾሙ ስሙም ታውፋንዮስ ይባል ነበር ። እርሱም ከአባ ጴጥሮስ ጋራ ተስማማ እነርሱም ስለ ቀናች ሃይማኖት በመልእክቶቻቸው ይገናኙ ነበር።
ከእነርሱም እያንዳንዱ በባልንጀራው ምክር በጸሎትና በቅዳሴ ጊዜ ይሰብክ ነበር ወደ አገራቸውም መግባት አልተቻላቸውም ነበርና አባ ጴጥሮስም በግብጽ ደቡብ በአንባንያ ገዳምና በዝጋግ ገዳም ይኖር ነበር አባ ታውፋንዮስም ከአንጾኪያ ከተማ ውጭ በአፍቆንያስ ገዳም ይኖር ነበር።
በዚያም ወራት ከእስክንድርያ ከተማ ውጭ ሰባት መቶ ገዳማትና ሃይማኖታቸው የቀና ምእመናንም ያሉባቸው ሠላሳ ሁለት መንደሮች ነበሩ በግብጽ አውራጃ ሁሉና በላይኛው ግብጽ በአስቄጥስ ገዳማት የሚኖሩ መነኰሳት እንዲሁም ኖባና ኢትዮጵያ በዚህ በአባ ጴጥሮስ ስልጣን ሥር ነበሩ። እኒህ ሁሉ ሃይማኖታቸው የቀና ነበር። በትእዛዙም ጸንተው ይኖሩ ነበር። እርሱም በቀናች ሃይማኖት ይጸኑ ዘንድ ወደእርሳቸው መልእክቶችን መጻፍ አያቋርጥም ነበር። የእስክንድርያን ገዳማት ሁሉና መንደሮችንም እየዞረ ያስተምራቸውና ይመክራቸው ያጽናናቸውም ነበር።
ከእርሱ በኋላ ሊቀ ጳጳሳት የሆነ ቅዱስና ዐዋቂ የሆነ ደቀ መዝሙር ነበረው እርሱም በሊቀ ጵጵስናው ሥራ ሁሉ ይራዳው ነበረ። ይህም አባት ጴጥሮስ አንዳንድ ጊዜ ወደ እስክንድርያ ከተማ ይገባ ነበር የሰዎቿንም ሥራቸውን ተመልክቶ ያስተምራቸውና በሃይማኖት ያጸናቸው ነበር።
በዐሥራ ሁለቱ ዓመት የሹመቱ ዘመን እንደ ሐዋርያት መንጋዎቹን እየጠበቀ እንዲህ በሹመቱ ኑሮ በሰላም አረፈ።
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#ሰማዕቱ_ጲላጦስ_መስፍን
ዳግመኛም በዚህች ዕለት ሰማዕቱ ጲላጦስ እና የሚስቱ ቅደስት አብሮቅላም መታሰቢያ ነው፡፡ ብዙዎቻችን መስፍኑን ዺላጦስ መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ጌታችን እንዳይሰቀል ከአይሁድ ጋር ሲከራከር እናውቀዋለን። የጌታችን ሞቱ በፈቃዱ ነበርና አይሁድ እንቢ ሲሉት የክርስቶስን ንጽሕና መስክሮ: እጁንም ታጥቦ ሰጥቷቸዋል። የዺላጦስ ታሪክ ግን እዚህ ላይ አያበቃም።
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሞትን ድል አድርጐ ከተነሳ በሁዋላ ትንሳኤውን በራዕይ ገልጦለት አይሁድን ተከራክሯቸዋል። ውሸታም ወታደሮችንም ቀጥቷል። በመጨረሻ ግን በሮም ቄሳር ተጠርቶ ከእሥራኤል እስከ ሮም ድረስ ሰብኮ በሮም አደባባይ አንገቱ ተሠይፏል።
ቅድስት እናታችን አብሮቅላም የዺላጦስ ሚስት ስትሆን ቁጥሯ ከ36ቱ ቅዱሳት አንስት ነው። ጌታችንን ተከትላ ቤቷን ለሐዋርያት አስረክባ ቤተ ክርስቲያንንም በዘመኗ አገልግላ ዐርፋለች። ዛሬ ሁለቱም ቅዱሳን ይታሠባሉ።
ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
(#ስንክሳር_ዘወርኀ_ሰኔ እና #ዲያቆን_ዮርዳኖስ_አበበ)
52ኛ ዓመት የልደት በዓል
እነሆ የሀገር ባለውለታ የሰንበት ትምህርት ቤቶች ፈርጥ የአሰላ ደ/መ/መ/ዓ/ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰ/ት/ቤት የተወለደችበትን 52ኛ ዓመት ሊከበር ጥቂት ቀናት ብቻ ቀርተውታል::
ስለሆነም የሰ/ት/ቤታችን የልደት በዓል ባማረና በደመቀ መልኩ እንዲከበር ከወራት ሐምሌን ከእለታት ቅዳሜና እሁድ ከቀናት 13 እና 14 ተመርጠው ሐምሌ 13እና14/2016 ዓ.ም በደማቅ ሁኔታ ለማክበር ዝግጅቱ ተጀምሯል።
ስለዚህ እርስዎም በዕለቱ ቅዳሜ ሐምሌ 13 ከቀኑ 6:00 ጀምሮ እሑድ ሐምሌ 14/2016 ዓ.ም ከቅዳሴ በሗላ ከጠዋቱ 3:00 ሰዓት ጀምሮ በደመቀ ሁኔታ ስለሚከበር እርስዎም በእለቱ በመርሐ ግብሩ ላይ ተገኝቸው የደስታችን ተካፋይ እንዲሆኑ በአክብሮት ተጋብዘዋል::
በእለቱም የሰንበት ትምህርት ቤቱ ክፍላት እና ሰ/ት/ቤቱ ያፈራቸው አገልጋዮች 30 60 100 ፍሬ የምናፈራበትን ልዩ ልዩ መረሐ ግብሮች ይዘው ይቀርባሉ::
ባለውለታዬ ማንነቴ ዛሬ ላለሁበት መሠረቴ ሰንበት ትምህርት ቤቴ አንቺ ጠርተሽኝማ አልቀርም ልደትሽ ልደቴ ደስታሽ ደስታዬ ነው።
እናቴ መልካም ልደት ይሁንልሽ አሁንም ማህጸንሽ ይለምልም።
ፈጥነው ይመዝገቡ!
5 ቀን ብቻ ቀርቶታል።
የመጥምቁን ቅዱስ ዮሐንስ በዓለ ልደት በጸበሉ ብዙ ተአምራትን በሚሰራበት በታላቁ ገዳም በሸንኮራ ዮሐንስ ኑ አብረን እናክብር።🗓 ሰኔ 29 ቀን መነሻ 🗓 ሐምሌ 1 በጥዋት መመለሻ 👉በአሰላ ደ/መ/መ/ዓ/ካቴድራል ፎቅ ስር በፍኖተ ወንጌል ሰ/ት/ቤት ንዋያተ ቅድሳት መሸጫ ሱቅ መመዝገብ ይችላሉ። 👉በዚህ ጉዞ ላይ በመሳተፍ በረከትን ያገኙ ዘንድ ‼️ፈጥነው ይመዝገቡ‼️ 🔎 የቴሌግራም ቻናል:- T.me/Finote_Wongel 🔎 የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel27
#ሰኔ_24
#ቅዱስ_ሙሴ_ጸሊም_ኢትዮጵያዊው
አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
ሰኔ ሃያ አራት በዚች ቀን አባ ሙሴ ጸሊም በሰማዕትነት ሞተ። ሰዎች ከገድሉ የተነሣ ይህን ቅዱስ ያደንቁታል እርሱ አስቀድሞ መንግሥተ ሰማያትን ገፍቷት ነበረና እርሱ በሥጋው ጠንካራ በሥራውም ኃይለኛ ነበር ይበላና ይጠጣ ይቀማና ያመነዝር ነበር ይገድልም ነበር ማንም ሊቋቋመው አይችልም ነበር።
አንድ በግ በአንድ ጊዜ ጨርሶ እንደሚበላና አንድ ፊቀን ወይን ጠጅ እንደሚጠጣ ስለ እርሱ ተነግሮአል። እርሱም ፀሐይን ለሚያመልኩ ሰዎች አገልጋይ ነበረ ብዙ ጊዜም ወደ ፀሐይ እያንጋጠጠ ፀሐይ ሆይ አንተ አምላክ ከሆንክ አነጋግረኝ ይል ነበር ደግሞም በልቡ የማላውቅህ ሆይ ራስህን አሳውቀኝ ይል ነበር።
ከዚህም በኋላ በአስቄጥስ ገዳም ያሉ መነኰሳት እግዚአብሔርን ያውቁታል ያዩታልም እያሉ ሲነጋገሩ ሰዎችን ሰማቸው። ያን ጊዜም ተነሣ ሰይፉንም ታጥቆ ወደ አስቄጥስ ገዳም ሔደ በደረሰም ጊዜ አባ ኤስድሮስን አገኘው። አባ ኤስድሮስም ፈራው ሙሴ ጸሊምም እውነተኛውን አምላክ ታሳውቁኝና ታስረዱኝ ዘንድ ወደ እናንተ መጣሁ አለው። አባ ኤስድሮስም ወደ አባ መቃርስ ወስዶ አገናኘው።
እርሱም ተቀብሎ ሃይማኖትን አስተማረው እንዲህም አለው ታግሠህ የማስተምርህን ከጠበቅህ እግዚአብሔርን ታየዋለህ። ከዚህም በኋላ የክርስትና ጥምቀትን አጥምቆ አመነኰሰው ከብዙዎች ገድለኞች ቅዱሳን ይልቅ ብዙና ጽኑዕ ገድልን መጋደል ጀመረ።
ሰይጣንም ቀድሞ ሲሠራው በነበረ በመብሉና በመጠጡ በዝሙቱም ይዋጋው ነበረ እርሱም በራሱ ላይ የሚደርስበትን ሁሉ ለአባ ኤስድሮስ ይነግረው ነበር እርሱም አጽናንቶ ሊሠራው የሚገባውን ያስተምረው ነበር።
ከገድሉ ብዛትም የተነሣ አረጋውያን መነኰሳት በሚተኙ ጊዜ ቤቶቻቸውን በመዞር ውኃ መቅጃዎችን ወስዶ ውኃ መልቶ በየቤታቸው ደጃፍ ያኖር ነበር። ውኃው ከእነርሱ ሩቅ ነበረና እንዲህም እያደረገ በመጋደል ለብዙ ዘመናት ኖረ።
ሰይጣንም በእርሱ ቀንቶ በእግሩ ውስጥ አስጨናቂ የሆነ አመታትን መታው ተኝቶም እየተጨነቀ ብዙ ቀን ታመመ። ከዚህም በኋላ የመታውና የሚፈታተነው ሰይጣን እንደሆነ ዐውቆ ሥጋው በእሳት ተለብልቦ እንደ ደረቀ ዕንጨት እስቲሆን ድረስ ተጋድሎውንና አገልግሎቱን አበዛ። እግዚአብሔርም ትዕግስቱን አይቶ ከደዌው ፈወሰው የሰይጣንንም ጦር ከእርሱ አራቀለት የመንፈስ ቅዱስም ጸጋ አደረበት ወደርሱም አምስት መቶ ወንድሞች መነኰሳት ተሰበሰቡ በእነርሱም ላይ አበ ምኔት ሆነ።
ከዚህ በኋላ ቅስና ሊሾሙት መረጡት በቤተ መቅደስም በሊቀ ጳጳሳቱ ዘንድ በአቆሙት ጊዜ ሊቀ ጳጳሳቱም አልፈቀደም ነበር አረጋውያኑንም ይህን ጠቋራ ለምን አመጣችሁት ከዚህ አውጡት አላቸው እርሱም መልክህ የከፋ ጠቋራ ሆይ መልካም አደረጉብህ በማለት ራሱን እየገሠጸ ወጣ ከዚህ በኋላ ዳግመኛ ሊቀ ጳጳሳቱ ጠራውና እጁን በላዩ ጭኖ ቅስና ሾመው እንዲህም አለው ሙሴ ሆይ እነሆ በውስጥም በውጭም ሁለመናህ ነጭ ሆነ።
በአንዲትም ዕለት ቅዱሳን አረጋውያን ወደርሱ መጡ በእርሱም ዘንድ ውኃ አልነበረም እርሱም ከበዓቱ ብዙ ጊዜ ወጣ ገባ ይል ነበር ከዚህ በኋላም ብዙ ዝናም ዘንሞ ጕድጓዶችን ሁሉ ሞላ። አረጋውያንም ለምን ብዙ ጊዜ ወጣ ገባ ትል ነበር ብለው ጠየቁት እርሱም እግዚአብሔርን ውኃ ካልሰጠኸኝ ቅዱሳን አገልጋዮችህን ምን አጠጣቸዋለሁ እለው ነበር በቸርነቱም ዝናምን ልኮልን ውኃን አገኘን አላቸው።
በአንዲትም ዕለት አባ ሙሴ ከአረጋውያን ጋራ ወደ አባ መቃርስ ሔደ አባ መቃርስም የሰማዕትነት አክሊል ያለው ከእናንተ ውስጥ አንዱን እነሆ አያለሁ አላቸው አባ ሙሴም አባቴ ሆይ ምናልባት እኔ እሆናለሁ በሰይፍ የገደለ በሰይፍ ይገደል ዘንድ አለው የሚል ጽሑፍ አለና ብሎ መለሰ።
ከዚህም በኋላ የበርበር ሰዎች መጡ አባ ሙሴም ከእርሱ ጋራ ያሉትን መነኰሳት እነሆ የበርበር ሰዎች ደረሱ መሸሽ የሚፈልግ ይሽሽ አላቸው እነርሱም አባታችን አንተስ አትሸሽምን አሉት እርሱም በሰይፍ የገደለ በሰይፍ ይገደላል ስለሚለው የእግዚአብሔር ቃል እነሆ ያቺን ቀን ለብዙ ዘመናት ስጠብቃት ኖሬአለሁ አላቸው።
ወዲያውኑም የበርበር ሰዎች ገብተው በሰይፍ ገደሉት መሸሽ ስለ አልፈለጉ ከእርሱ ጋራ ሰባት መነኰሳትም ተገደሉ አንዱ ግን ከምንጣፍ ውስጥ ተሠወረ የእግዚአብሔርንም መልአክ አየ በእጁም አክሊል ነበር እርሱም ቆሞ ይጠብቅ ነበር። ይህንንም በአየ ጊዜ ከተሠወረበት ወጣ የበርበር ሰዎችም ገደሉት የሰማዕትነትንም አክሊል ተቀበለ።
ወንድሞች ሆይ ከሀዲና ነፍሰ ገዳይ ቀማኛና ዘማዊ የነበረውን ለውጣ ደግ አባት መምህርና የሚያጽናና ለመነኰሳትም ሥርዓትን የሠራ ካህን እንዳደረገችው በሁሉም አብያተ ክርስቲያን ስሙ እንዲጠራ እንዳደረገችው የንስሐን ኃይሏን ተመልከቱ። ሥጋውም በአስቄጥስ ገዳም ደርምስ በተባለ ቦታ ለዘላለም ይኖራል ከእርሱም ብዙዎች ድንቆችና ተአምራት ይታያሉ።
ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
(#ስንክሳር_ዘወርኀ_ሰኔ)
8 ቀን ቀረው
ፈጥነው ይመዝገቡ!
ኑ! አብረን ተጉዘን አብረን ከመጥምቁ በረከት እንሳተፍ።
🚌 የንግስ በዓል ጉዞ 🚎
ወደ ሸንኮራ ቅዱስ ዮሐንስ
⏱ መነሻ፡- ሰኔ 29
መመለሻ፡- ሐምሌ 1
የመመዝገቢያ ቦታ
- በሰንበት ት/ቤቱ ጽ\ቤት
- በሰንበት ት/ቤቱ ቤተ መጽሐፍት
- በሰንበት ት/ቤቱ ንዋየ ቅድሳት መሸጫ
ለበለጠ መረጃ
📞 09 55 25 20 34
📞 09 40 23 05 15
📞 07 13 83 09 96
አዘጋጅ፡- የአሰላ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ትምህርት ቤት ጉዞ ክፍል
ከታች ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።
▭▭▭▭▭▭▭▭▭ ◎⃝ ◎⃝ ⃟ ◎⃝ ◎⃝ ▭▭▭▭▭▭▭▭▭
ዛሬ ላይ ነገን ለማነጽ የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ድምጽ ልንገነባ ነው። #ሚዲያችንን_ይደግፉ
የአሰላ ደ/መ/መ/ዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት
🔎 የቴሌግራም ቻናል:- T.me/Finote_Wongel
🔎 የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel27
🔎 የቲክቶክ ገጽ:- tiktok.com/@finotewongel27
🔎 Youtube:- youtube.com/@Finote_Wongel
🔎 Instagram:- https://www.instagram.com/finote_wongel
🔎 Facebook:- https://www.facebook.com/profile.php?id=61558615513475
▭▭▭▭▭▭▭▭ T.me/FinoteWongel1 ▭▭▭▭▭▭▭▭
+1
ሰኔ 212016 ዓ.ም የነበረን የጥያቄና መልስ መርሐ ግብር ውጤት ይህን ይመስላል። የተሳተፋቹ ሁላችሁንም መድኃኔዓለም ያክብርልን።
እስከ ሣምንት መልካም ሣምንት!
🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹
የአሰላ ደ/መ/መ/ዓ/ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
የቴሌግራም ቻናል:- T.me/Finote_Wongel
የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel27
የቲክቶክ ገጽ:- tiktok.com/@finotewongel27
Youtube:- youtube.com/@Finote_Wongel
Instagram:- https://www.instagram.com/finote_wongel
Facebook:- https://www.facebook.com/profile.php?id=61558615513475
+1
ሰኔ 212016 ዓ.ም የነበረን የጥያቄና መልስ መርሐ ግብር ውጤት ይህን ይመስላል። የተሳተፋቹ ሁላችሁንም መድኃኔዓለም ያክብርልን።
እስከ ሣምንት መልካም ሣምንት!
🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹
የአሰላ ደ/መ/መ/ዓ/ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
የቴሌግራም ቻናል:- T.me/Finote_Wongel
የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel27
የቲክቶክ ገጽ:- tiktok.com/@finotewongel27
Youtube:- youtube.com/@Finote_Wongel
Instagram:- https://www.instagram.com/finote_wongel
Facebook:- https://www.facebook.com/profile.php?id=61558615513475
🎲 Quiz 'Qophii Gaafii fii Deebii Daandii Wangeelaa. Carra Gaarii🛎🛎🛎'
🖊 7 questions · ⏱ 30 sec
🎲 Quiz 'ፍኖተ ወንጌል ልዩ የጥያቄና መልስ ውድድር "start the quiz "የሚለውን ሲጫኑ"i am ready"ሲጫኑ ጥያቄው ይጀምራል። መልካም ዕድል🛎🛎🛎'
🖊 7 questions · ⏱ 30 sec
