en
Feedback
ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት

ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት

Open in Telegram

በአሰላ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። የቴሌግራም ቻናል:-  @Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- @FinoteWongel27 የቲክቶክ ገፅ:- https://www.tiktok.com/@finotewongel27 Youtube:- https://www.youtube.com/@Finote_Wongel ©ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት

Show more
669
Subscribers
+124 hours
+37 days
-330 days
Posts Archive
“ቅዱስ ጳውሎስን የጠራኸው ጥዑመ ስም ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ፣ እኛንም በሰማያት በሚሆነው ሰርግህ ላይ ጥራን” አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ
“ቅዱስ ጳውሎስን የጠራኸው ጥዑመ ስም ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ፣ እኛንም በሰማያት በሚሆነው ሰርግህ ላይ ጥራን” አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ

"ሰው ሆይ ትላንትና አልፏል ነገም ገና አልመጣም ያለህ ዛሬ ብቻ ናትና በበጎ ሥራ ተጠቀምባት።"    ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ "እንግዲህ በጎ ለማድረግ አውቆ ለማይሠራው ኃጢአት ነው።" ያዕ 4÷17

በረከታቸው ይድረሰን!! 🕯🕯🕯3ኛ ዓመት መታሰቢያ 🕯🕯🕯
በረከታቸው ይድረሰን!! 🕯🕯🕯3ኛ ዓመት መታሰቢያ 🕯🕯🕯

"ሰማዕታት የዚህችን ዓለም ጣዕም በእውነት ናቁ ፤ ደማቸውን ስለ እግዚአብሔር አፈሰሱ ፤ ስለ መንግስተ ሰማያት መራራ ሞትን ታገሱ" ውዳሴ ማርያም ዘሐሙስ ዛሬ ጥር ፳፯ ቀን በሻሸመኔ ከተማ ስለሃይማኖ
"ሰማዕታት የዚህችን ዓለም ጣዕም በእውነት ናቁ ፤ ደማቸውን ስለ እግዚአብሔር አፈሰሱ ፤ ስለ መንግስተ ሰማያት መራራ ሞትን ታገሱ" ውዳሴ ማርያም ዘሐሙስ ዛሬ ጥር ፳፯ ቀን በሻሸመኔ ከተማ ስለሃይማኖታቸው ሰማዕታት የሆኑ ኦርቶዶክሳውያን መታሰቢያቸው ነው። የሰማዕታቱ በረከት አይለየን !

⏳ 2 ቀን ቀረው +++ ዮናስ እና ጳውሎስ +++ ዮናስ ለነነዌ ሕዝብ ንስሐን ስበክ ሲል ወደ እርሱ ለመጣው መለኮታዊ ድምፅ መታዘዝ ስላልፈለገ በባሕር ተሳፍሮ ወደ ጠርሴስ ሊኮበልል ሞከረ፡፡ ይሁንና ወደ መርከብ በገባ ጊዜ ግን እግዚአብሔር በባሕሩ ላይ ታላቅ ነፋስ አመጣ፡፡ ከባድ ማዕበልም ተቀስቅሶ መርከቢቱን ሊሰብራት ደረሰ፡፡ አልታዘዝም ያለው አንዱ ዮናስ ወደ መርከቧ በመግባቱ በዚያ ያሉ ንጹሐን ሁሉ እንዲጠፉ ምክንያት ሊሆን ተቃረበ፡፡(ዮና 1)         የእግዚአብሔርን ፈቃድ በሚያደርገው ታዛዡ ጳውሎስ ምክንያት የሆነውን ግን ተመልከቱ፣ እርሱ በመርከቧ ውስጥ በመኖሩ አብረውት የታሰሩ ወንጀለኞች ሁሉ ሊመጣባቸው ካለው ሞት እና ጥፋት በእርሱ ምክንያት ተረፉ፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ፣ ገጽ 385-386

"ጌታዬ አምላኬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ የውስጤን የሚረዳልኝ እንዳንተ ያለ ማንንም አላገኝም፤ ከአንተ ጋር ስሆን ብቻ ደህንነት ስለሚሰማኝ ለአንተ ለአምላኬ ልቤን ከፍቼ ምስጢሬን አዋይሃለሁ። ቃልህን የ
"ጌታዬ አምላኬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ የውስጤን የሚረዳልኝ እንዳንተ ያለ ማንንም አላገኝም፤ ከአንተ ጋር ስሆን ብቻ ደህንነት ስለሚሰማኝ ለአንተ ለአምላኬ ልቤን ከፍቼ ምስጢሬን አዋይሃለሁ። ቃልህን የምሰማ ነገር ግን የማላስተውል ደካማ ነኝና፣ ናፍቆቴን ቢገልፅልኝ እንባዬን በፊትህ አፈሰዋለሁ።ልቤን ከሚያጸናውና በሃይሉ ከሚደግፈኝ ጋር እንደሆንኩ አውቃለሁና ከአንተ ጋር ብቻ ስሆን ብቸኝነት አይሰማኝም። ያለ አንተ ግን ባዶነቴ ያስጨንቀኛል። ከእኔ ጋር የሆንክ አማኑኤል አምላኬ ሆይ ነፍሴ ከአለምና በአለም ካሉት ከቁሳዊ ነገሮች ይልቅ የአንተን ሁሉን ቻይነት ትናፍቃለች። ውስጤ የማትወሰን አንተን ተጠምቷል። ከአንተም በቀር ይህን የሚረዳኝልኝ ከቶ የለም።" (ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ሽኖዳ) እንኳን ለአባታችን ለመድኃኔዓለም ወርሐዊ መታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሳችሁ!!!

"እመኑኝ እግዚአብሔር የተጋለጥንባቸውን እና በእርሱ የተጠበቅንባቸውን አደጋዎች ሁሉ ቢገልጥልን ሕይወታችን ሁሉ እርሱን ለማመስገን አይበቃም  ነበር።"     አቡነ ሺኖዳ የቴሌግራም ቻናል:-  T.me/Finote_Wongel 

ጥምቀት ጥምቀት ከጌታ ሞትና ትንሣኤ ጋር የምንተባበርባት ሞተን ተቀብረን ሞትን አሸንፈን የምነሣባት በር ከፋች ናት ብለናል። የብሉይ ኪዳኑ ምሳሌ አንዱ ነቢዩ ዮናስ ነው። “እግዚአብሔርም ዮናስን የሚ
ጥምቀት  ጥምቀት ከጌታ ሞትና ትንሣኤ ጋር የምንተባበርባት ሞተን ተቀብረን ሞትን አሸንፈን የምነሣባት በር ከፋች ናት ብለናል። የብሉይ ኪዳኑ ምሳሌ አንዱ ነቢዩ ዮናስ ነው።  “እግዚአብሔርም ዮናስን የሚውጥ ታላቅ ዓሣ አሰናዳ፤ ዮናስም ሦስት ቀንና ሦስት ሌሊት በዓሣው ሆድ ውስጥ ነበረ።” ዮና.2:1  ዮናስ ወደ ባሕር ተጣለ ታላቅ አሳ ዋጠው። ወደ ባሕር መጣሉ የጥምቀት አምሳያዋ ነበር። በአሳ መዋጡ መቃብሩ ነው። ጌታ ሞትና ትንሣኤውን በዮናስ መመሰሉን ይነግረናል።  “ዮናስ በዓሣ አንባሪ ሆድ ሦስት ቀንና ሦስት ሌሊት እንደ ነበረ፥ እንዲሁ የሰው ልጅ በምድር ልብ ሦስት ቀንና ሦስት ሌሊት ይኖራል።” ማቴ.12:40 ከሰማይ ምልክትን የጠየቁ ፈሪሳውያን ከምድሩ ምልክት ጠቀሰላቸው። የዮናስ ወደ ባሕር መጣሉ አሳ ሆድ ውስጥ ሳይሞት መቆየቱ፣ የጥምቀት የሞትና ትንሣኤ አምሳል መኾኑን አስረዳ። 

       እንኳን ለጾመ ነነዌ በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ! እግዚአብሔር አምላካችን ምሕረቱን ይቅርታውንና ሰላሙን ለሀገራችንና ለቤተክርስቲያናችን  ይስጠን እንደ ነነዌ ህዝብ ምህላችንንም ይቀበልልን።

የመርከበኞቹ ተግባር
የመርከቢቱ ሰዎች አማኞችን ይወክላሉ፡፡ሰዎቹ ወደ አምላካቸው ጮሁ፡፡የነሱ የመጀመሪያ የመፍትሔ ስራ ጸሎት ነበር፡፡ ትልቁን ተግባር ጀመሩ:: ሁለተኛ ተግባራቸው መርከብ ማቅለል ነበር፡፡ የዛሬ ችግራችንም እቃ ሳይሆን ሰው ነው፡፡ አልታዘዝ ያለ አገልጋይ፡፡እነዚህ ሰዎች የሚያንገላታቸው በማይመለከታቸው ነው፡፡ ባለ ጉዳዩ ሌላ ነው፡፡እቃ የጣሉት  የራሳቸውን እንጂ የዮናስ እቃ የለበትም፡፡ ሶስተኛ የምንማረው የተኛውን መቀስቀሳቸው ነው:: “የመርከቡም አለቃ ወደ እርሱ ቀርቦ፦ ምነው ተኝተሃል? እንዳንጠፋ እግዚአብሔር ያስበን እንደ ሆነ ተነሥተህ አምላክህን ጥራ አለው” የመርከቡ አለቃ ዮናስን ቀሰቀሰው፡፡ የተኛውን ቀሰቀሱ፡፡  ከዮናስ የተሻሉ ነበር፡፡እግዚአብሔር ጉዳዩ ካልገባቸው ሰዎች ወደ ባለ ጉዳዩ መጣ :: መርከበኞቹ አራተኛ ተግባራቸወ እጣ መጣጣል ነው፡፡ አልፈረዱበትም በማእበል ላይ እያሉ ነው ይህንን ያደረጉት “እርስ በእርሳቸውም፦ ይህ ክፉ ነገር በማን ምክንያት እንዳገኘን እናውቅ ዘንድ ኑ፥ ዕጣ እንጣጣል ተባባሉ። ዕጣም ተጣጣሉ፥ ዕጣውም በዮናስ ላይ ወደቀ። እጣ መጣጣል ነው፡፡ አልፈረዱበትም በማእበል ላይ እያሉ ነው ይህንን ያደረጉት፡፡ እቃ ያታሉ የራሳቸውን እንጂ የዮናስ እቃ የለበትም፡፡ “ እርስ በእርሳቸውም፦ ይህ ክፉ ነገር በማን ምክንያት እንዳገኘን እናውቅ ዘንድ ኑ፥ ዕጣ እንጣጣል ተባባሉ። ዕጣም ተጣጣሉ፥ ዕጣውም በዮናስ ላይ ወደቀ።እጣ ሲወጣበት እንኳ ዝርዝር ጠየቁት አልጣሉትም፡፡ ልበ ሰፊ ነበሩ “የዚያን ጊዜም፦ ይህ ክፉ ነገር በማን ምክንያት እንዳገኘን እባክህ ንገረን፤ ሥራህ ምንድር ነው? ከወዴትስ መጣህ? አገርህስ ወዴት ነው? ወይስ ከማን ወገን ነህ? አሉት” ምን እንደሚያድርጉበት እንኳ ያስወሰኑት ራሱን ነው፡፡ “ባሕሩንም ሞገዱ አጥብቆ ያናውጠው ነበርና፦ ባሕሩ ከእኛ ዘንድ ጸጥ እንዲል ምን እናድርግብህ? አሉት” ራሳቸው ልፈረዱበትም፡፡ ጥፋተኛ መሆኑን እንኳ አውቀው ነበር፡፡ የዮናስ ደግነትና የዋህነት ጥፋቱን አምኖ በራሱ መፍረዱ ነው፡፡  “እርሱም፦ ይህ ታላቅ ማዕበል በእኔ ምክንያት እንዳገኛችሁ አውቃለሁና አንሥታችሁ ወደ ባሕር ጣሉኝ፥ ባሕሩም ጸጥ ይልላችኋል አላቸው” ሁላችንም በሌላው መፍርድ እንጂ ችግሩ የኛ ነው አንልም፡፡ ወደ ማእበሉ እንዲጥሉት መብት ቢኖራቸውም አላደረጉበትም፡፡ ምርጫ ሰጡት፡፡ሊያተርፉት መጣራቸው ነው፡፡  “ሰዎቹ ግን ወደ ምድሩ ሊመለሱ አጥብቀው ቀዘፉ፤ ዳሩ ግን ባሕሩ እጅግ አብዝቶ ይናወጥባቸው ነበርና አልቻሉም” ለዮናስ ጸለዩለት “ስለዚህ ወደ እግዚአብሔር ጮኸው፦ አቤቱ፥ እንደ ወደድህ አድርገሃልና እንለምንሃለን፤ አቤቱ፥ ስለዚህ ሰው ነፍስ እንዳንጠፋ ንጹሕም ደም በእኛ ላይ እንዳታደርግ እንለምንሃለን አሉ።”

ተርሲስ
ተርሴስ ትልቅ ከተማ ናት የወርቅ፣ የብር፣ የዝሆን ጥርስ ይሸጥባት ነበር፡፡ ዮናስ የእግዚአብሔርን ሳይሆን የራሱን ኃሳብ ተከትሎ አለመታዘዝ መረጠ፡፡ የአገልግሎት መነሻ መታዘዝ ነው::ዮናስ ከእግዚአብሔር ሸሽቶ ሰላም መሆን ፈለገ “ዮናስ ግን ከእግዚአብሔር ፊት ወደ ተርሴስ ይኰበልል ዘንድ ተነሣ፤ ወደ ኢዮጴም ወረደ፥ ወደ ተርሴስም የምታልፍ መርከብ አገኘ፤ ከእግዚአብሔርም ፊት ኰብልሎ ከእነርሱ ጋር ወደ ተርሴስ ይሄድ ዘንድ ዋጋ ሰጥቶ ወደ እርስዋ ገባ” ጌታ ያለ ዋጋ ከፍሎ ወደደን እኛ ለኃጢአት ግን ዋጋ እንከፍላለን፡፡ ሰው ከእግዚአብሔር መሸሽ አይችልም፡፡ ዮናስ ሲሸሽ ከየብስ ወደ ባሕር ገባ፡፡ ታሪኩ ከግለሰብ ወደ ሕዝብ ጉዳይ(ታሪክ) ተቀየረ:: በወቅቱ እግዚአብሔር በባሕሩ ላይ የለም አልያ ባሕሩን አይገዛም የሚል እምነት ነበራቸው ምናልባትም ዮናስ ይህንን አስቦም ይሆናል፡፡ዮናስ በእምነት ወደማይመስሉት ሰዎች ተቀላቀለ፡፡ በሸሸ ቁጥር ወደሚማርበት ቦታ ሄደ፡፡ እግዚአብሒር ሌላ ማስተማሪያ አነሳ፡፡” እግዚአብሔርም በባሕሩ ላይ ታላቅ ነፋስን አመጣ፥ በባሕርም ላይ ታላቅ ማዕበል ሆነ፥ መርከቢቱም ልትሰበር ቀረበች።” ዮናስ ካደረገው ስህተት መካከል ሁለተኛው መተኛቱ ነው፡፡ “መርከበኞቹም ፈሩ፥ እያንዳንዱም ወደ አምላኩ ጮኸ፤ መርከቢቱም እንድትቀልልላቸው በውስጥዋ የነበረውን ዕቃ ወደ ባሕር ጣሉት፤ ዮናስ ግን ወደ መርከቡ ውስጠኛው ክፍል ወርዶ ነበር፥ በከባድ እንቅልፍም ተኝቶ ነበር” ሰዎቹ ለምን መርከቢቱ መናውጥ ምክንቱን አላወቁም ነበር፡፡ ሀገርም ቤተክርስቲያንም የሚታወከው በተኙ አገልጋዮች ጭምር ነው፡፡“መርከበኞቹም ፈሩ፥ እያንዳንዱም ወደ አምላኩ ጮኸ”

ነነዌ ማናት
በጤግሮስ ወንዝ ዳርቻ ናምሩድ በተባለው ሰው ተመሰረተች፡፡ ለአሶራውያን መናገሻ ከተማ ነበረች፡፡ ሰፊና ውብ ከተማ ሆና የተገነባች ናት። ዘፍ 10፤1 አሶር ከእስራኤላውያን ጋር ጠላት ሆነው በተቀናቃኝነት የኖሩ መንግስታት ናቸው፡፡ዮናስ የተላከው ተቀናቃኝ ወደ ሆኑት ሕዝቦች ነው፡፡ ከተማዋ ውብና ብዙ ሕንጻዎች ነበሩባት የከተማዋ ቅጽር  ርዝመት 12 ኪ.ሜ  እንደ ነበር በውስጧ ብዙ ሕንጻዎቸ ተሰርተወባት ነበር፡፡ የባቢሎን መንግሰት ከከርስቶስ ልደት በፊት ከተማዋን  አፈረሳት ዮና4.1 ሕንጻዎቿን የሰራቸው ሰናክሬም ሲሆን በስተመጨረሻ የባቢሎን መንግስት አፍርሷታል በ621 ዓ.ዓ:: ነነዌ ዛሬ የኢራቅ ከተማ ሞሱል ናት በኩሽ ልጅ ናምሩድ በ1800 ዓ.ዓተቆረቆረች፡፡ ሽታር ወይም አስታሮትን ያመልኩ ነበር፡፡በተደጋጋሚ የመሬት መንቀጥቀጥ ገጥሟታል፡፡የመጽሐፉ ይዘት ታሪክ ነው፡፡ታሪኩን የጻፈው ራሱ ነው፡፡ ዮናሰ የራሱን ስህተቱን መጻፉ ታላቅ ያደርገዋል፡፡ዮናስ ብዙ ሰዎችን (አገልጋዮችን) ይወክላል፡፡“የእግዚአብሔርም ቃል ወደ አማቴ ልጅ ወደ ዮናስ እንዲህ ሲል መጣ፦ተነሥተህ ወደዚያች ወደ ታላቂቱ ከተማ ወደ ነነዌ ሂድ፥ ክፉታቸውም ወደ ፊቴ ወጥቶአልና በእርስዋ ላይ ስበክ” አለው::ወደ አሶራውያን ተለከ ፡፡ ዮናስ ግን ኮበበለለ።

ዮናሰ ማነው
አባቱ አማቴ እናቱ ሶና ትባላላች፡፡ኤልሳዕ ያዳነላት  የሰራጵታዋ ሴት ልጅ ነው የሚሉ የመጽሐፍ ቅዱስ ምሑራን  አሉ፡፡ስለ ቤተሰቡ ዝርዘር የተጻፈ ነገር የለም፡፡ በተጨማሪም  ዮናስ  በዳግማዊ ኢዮርብአም የኖረ ነቢይ ሲሆን ከታላላቆቹ ከነ አሞጽ፣ኢሳይያስ፣ ጋር በተመሳሳይ ጊዜ ኖሯል 786_ 746 ዓ.ዓ  መሆኑን ከመጽሐፉ መረዳት ይቻላል፡፡ ነቢይነቱን የጀመረው ለነነዌ ከመስበኩ በፊት ነው፡፡ዮናስ የጋትሔፌር ሰው ነው፡፡ጋትሔፌር ገሊላ ከተማ አካባቢ የነበረ ከተማ ነው፡፡ ትንቢቱን የጀመረው አስራኤል ሲሆን ያጠናቀቀው ነነዌ ነው ዮና.1፤1  2 ነገ.14፡25

ጾመ ነነዌ ትንቢተ ዮናሰ
ዮናስ  በእብራይስጥ ቋንቋ ርግብ የሚልው ተረጉም ይገልጸዋል፡፡ቁጥሩ ከደቂቀ ነቢያት መካከል ነው፡፡  የመጽሐፉ  ይዘት የትንቢት ይዘት የለውም “ ነነዌ እስከ ሶስት ቀን ድረስ ትገለበጣለች ”የሚል ብቻ ነው፡፡ መጽሐፉ የተጻፈው በራሱ ነው፡፡መጽሐፉ አራት ምእራፍ አለው፡፡ታሪኩ ልብ ሰቃይ ነው፡፡ዮናስ ከእግዚአብሔር መኮበለል አሰቦ   ወደ ተርሴስ በሚያደርገውን ሸሽት ይጀምራል፡፡ ታሪኩ በየብስ ጀምሮ ወደ ባሕር ይዘልቃል፡፡ ካንድ ሰው ታሪክ ወደ ብዙ ተሳፋሪዎች  ይቀየራል፡፡ 

"ደካሞችን አትናቁ ምክንያቱም የእነርሱ አባት እግዚአብሔር በእነርሱ ላይ ለሚደርሰው በደል ፈራጅ ነው።"    ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ

"እግዚአብሔር በተነሣ ጊዜ ምን አደርጋለሁ ? በጎበኘኝ ጊዜ ምን እመልስለታለሁ ?"   ኢዮብ 31÷14

"ኃይልን በሚሰጠኝ በክርስቶስ ሁሉን እችላለሁ።"         ፊል 4÷13

ሰንበት ተማሪ ሰንበት_ተማሪነት ዛሬ ሰንበት ተማሪ መሆን ስድብ ሊያደርጉት የሚቃጡ አንዳንድ አጉል ሰዎች አሉ ነገር ግን። ሰንበት ተማሪ መሆን መስዋዕትነት ነው መስዋዕቱም ጊዜ ነው ሁሉም ሰንበት ተማሪ አብዛኛው ከተማ ላይ ያለው ከአካዳሚ ትምህርት መልስ ወጣቶች ደግሞ ከሥራ መልስ ጎልማሶች ደግሞ ከቤተሰብ ላይ ጊዜያቸውን ነጥቀው ነው የሚሰጡት። እንደ ሰንበት ትምህርት ቤት እሳቤ አንድ ሰንበት ተማሪ የሚያስቀድስ የሚቆርብ እና በመንፈሳዊ ህይወቱ እንደ ዐለት የጠነከር ይሆን ዘንድ ግዴታው ነው፡፡ ይህንን ሳያደርግ የቀረ ሁሉ ግን በግሉ ይወቀሳል እንጂ ድሮስ ሰንበት ተማሪ ተብሎ አይሰደብም ነውር ነው። የሰንበት ትምህርት ቤት የውስጥ ፈተናዎች፦ በዚህ ዘመን ቤተክርስቲያንን ከሰንበት ት/ቤት አብነቱን ከሰንበት ት/ቤት ለይተው የሚያዩ ሰዎች አላዋቂ ናቸው አዋቂ ነን ቢሉ እንኳን አላዋቂ ናቸው፡፡ ምሳሌ ከመምህሮቼ ታሪክ ልውሰድ ፦ በገጠሪቱ ክፍል አንድ ሰው በጥሩ ሁኔታ የሚማር እና ቀለማ አካቶ የሚይዝ ከሆነ አዋቂ ከሚመስሉ ነገር ግን ብዙም የተሳካ እውቀት ከሌላቸው ቀሳውስት እና ከቅናተኛ የቦታው መምህር ዘንድ እንዳይማር ከፍተኛ ጥረት ይደረጋል ቅስሙ እንዲሰበር እና ትምህርቱን እንዲተውው፡፡ አሁንም ሰንበት ትምህርት ቤትን ሁለት አካላት ይዋጓታል:- 1. እንዳልተማሩ ቀሳውስት ያልተማሩ እና እዚህ ግባ የማይባል እውቀት የያዙ ነገር ግን ነገ በአገልግሎት እንዳይበለጡ የሚሰጉ አካላት ምን ሰንበት ተማሪ ከበሮ አንጠልጥሎ መዞር ነው የምትል ቅስም ሰባሪ ቃል ይወረውራሉ ሰሚ ካገኙ። 2. እንደ ቦታው መምህር ነገ ይሄ ልጅ ተምሮ አውቆ በእውቀት ይበልጠኝ ይሆን የምትል ክፉ ቅናት እንደምታድርበት... በአድባራት ያሉ አንዳንድ አስተዳዳሪዎች አለማወቀቸውን እንዳይገለጥ እና ሰንበት ተማሪ የሚመጣው ጥቅም ፈልጎ ለደሞዝ ሳይሆን ለማገልገል ስለሆነ ጥፋቴን ያጋልጥብኛል ገንዘብ መመዝበሬን ሙስና መብላቴን ያጋልጥብኛል ኪሴ ሳይሞላ ደረቴ ሳይቀላ በፊት ይነቅለኛል የሚል ፍራቻ ስላለው ግብረ አበር ሰብስቦ በደረሰበት ሰንበት ተማሪ ያሳድዳል። ልዩ_አስተያየት፦ ሰንበት ት/ቤት ሆናችሁ ግን የእኛ ሰንበት ት/ቤት አባላት ጎበዝ ናቸው ምንም አይናገሩም እኮ ከተባላችሁ በቃ ተበልታችኋል አስተያየት ስጡ ለምን ይሄ ሆነ በሉ ደብሩ የአንድ አለቃ እና የተወሰኑ አካላት አይደለም የአንተ አባት እና እናት በዋጋ የሰሩት ነው። በዚህ ዘመን ሰንበት ተማሪ ባይኖር:- -የቤተክርስቲያን ውበት ይደበዝዝ ነበር ማኅሌቱን ሊቃውንቱ ቢቆሙት ከበሮ የሚቆረቁር አይገኝም በአዲስ አበባ ካሉ ዲያቆናት ሁሉም በሚያስብል ደረጃ የመጀመሪያ አገልግሎታቸው ሰንበት ት/ቤት ነው፡፡ - ልጆች በስነምግባር አያድጉም ነበር። የፊቱ ቆዳ እስኪለወጥ በማግስቱ ፊቱ እስኪላጥ ድረስ ጉሮሮው እስኪዘጋ ድምጹ እስኪጎረንን ድረስ ጉልበቱ እየተብረከረከ ራሱን ስቶ እየወደቀ በውኃ ጥም እየተቃጠለ ታቦት የሚሸኝ ከቶ አይኖርም ነበር። በብዙ አድባራት እንደ ልባቸው የሚፈነጩ የአድባራት አስተዳዳሪዎችን ማን ልክ ያስገባልን ነበር። ከሰንበት ትምህርት ቤት ችግሩ ! - ከሊቃውንቱ ጋር መከባበር ቢኖር አክብሮ መከበር ልዩ ጸጋ ነው የተለያዩ የግእዝ ቃላትን በመዝሙር በስብከት በጽሑፍ በምናገኝበት ጊዜ ብትጠይቁ የሚላለው ሲጠብቅ የሚጠብቀው ሲላላ ትርጉም አልባ ይሆናል አንዳንዱ ደግሞ ትርጉም ይቀይራል ስለዚህ ኩራትን አስወግዶ መጠየቅ። በመዝሙር ጥናት ጊዜ አዳራሹ ሞልቶ በተለይ ጥር ላይ በትምህርት ወቅት አዳራሹ ባዶ ሲሆን ይስተዋላል ቢስተካከል። ሰንበት ት/ቤቶች አባላት ሲጠፉ ለምን ጠፉ ብሎ ቢፈልግ ብዙዎቹ ኃይማኖት ከለወጡ ሰዎች ጀምሮ ሁሉም እኔ እኮ ሰንበት ተማሪ ነበርኩ የሚል ቃል ከአንደበታቸው ይገኛል። አንዳንድ ሰንበት ት/ቤቶች ወጣቶችን ከመምከር ይልቅ ውጡልን በሚመስል መልኩ ተግሳጽ፣ከአገልግሎት እገዳ ይደረጋል በዚያው ወጥተው ይቀራሉ ይሄ ቢቀነስ እና ዘመኑን ብንመስል። -ሰንበት ተማሪዎች እርስ በራሳቸው መጋባት ይችላሉ ነገር ግን በግቢ ውስጥ እና ሰንበት ት/ቤት ልሄድ ነው ብሎ እንዲያ እንዲያ ማለት አይቻልም። ማጠቃለያ ቤተ ክርስቲያን ለአንዳንዶች የሥልጣን ተዋረድና የአስተዳደር መዋቅር ያላት ድርጅት ስትኾን ለሌሎች ደግሞ የማትታይ የማትጨበጥ መንፈሳውያን በመንፈስ የሚያመልኩባት ተቋም ናት ዳሩ ግን ጌታችን መድኅኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አንድ ጊዜ ከድንግል ማርያም በነሣው ሥጋ ለዘለዓለም ሥግው ቃል ሆኖ እንደሚኖር፣ አካሉ የኾነች ቤተ ክርስቲያንም ሥግው ባሕርያት አሏት። ይኸውም ክርስቶስ ፍጹም ሰው ኾኖ በመካከላችን ተገልጦ እንደ ተመላለስ፣ እንደ በላና እንደ ጠጣ እንደ ተዳስስ፣ እንዲሁም ቤተ ክርስቲያን የምትታይየምትጨበጥ አስተዳደራዊ መዋቅርና የራስዋ ተጠሪ ያላት፤ በራስዋ ሕግ የምትተዳደር የምእመናን ማኅበር ናት። መ/ር ነቢዩ ኤልያስ