en
Feedback
ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት

ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት

Open in Telegram

በአሰላ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። የቴሌግራም ቻናል:-  @Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- @FinoteWongel27 የቲክቶክ ገፅ:- https://www.tiktok.com/@finotewongel27 Youtube:- https://www.youtube.com/@Finote_Wongel ©ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት

Show more
669
Subscribers
+124 hours
+27 days
No data30 days
Posts Archive
🌹መምህር ዲ/ን ዘለዓለም ታዬ ተፈተዋል። ❤ ዛሬም በማረሚያ ቤት ያሉ ያለጥፋታቸው የታሰሩ መምህራኖቻችንን እግዚአብሔር አምላክ ያስፈታልን። 🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏 ፍትህ ዛሬም ድረስ ደማቸው እየ
🌹መምህር ዲ/ን ዘለዓለም ታዬ ተፈተዋል። ❤ ዛሬም በማረሚያ ቤት ያሉ ያለጥፋታቸው የታሰሩ መምህራኖቻችንን እግዚአብሔር አምላክ ያስፈታልን። 🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏 ፍትህ ዛሬም ድረስ ደማቸው እየፈሰሰ ላሉ ለአርሲ ምዕመናን🙏

✨✨✨🌱🌱🌱✨✨✨🌱🌱🌱✨✨✨🌱🌱🌱 ✨✨🌱ኃጢአትህን ኹሉ በዲያብሎስ ላይ አታሳብብ✨✨🌱 በንስሐ ተስፋ ከቆረጥክ ዲያብሎስ ይወድሃል፡፡ ግን እርሱ እንዲረካ አታድርግ፡፡ ለድኅነት ቀንም ሁሌም ዝግጁ ሁን፡፡ እነዚህን ኹሉ የተናገርኩት ዲያብሎስን ከነቀፋ ነፃ ለማውጣት ሳይሆን እናንተን ከስንፍና ነፃ ለማውጣት ነው፡፡ ኃጢአታችንን ኹሉ በእርሱ እንዳናሳብብ በእውነት ይስፈልጋል፤ ለሁሉም ክፋታችን ሰይጣንን ተጠያቂ የምናደርግ ከሆነም የራሳችንን ቅጣት እንጨምራለን፤ ጉዳዩን ኹሉ ወደ እርሱ ስላስተላለፍንም ይቅርታ አናገኝም - ልክ ሄዋን ይቅርታን እንዳላገኘች ሁሉ፡፡ ✨✨🌱 ግን ይህን አናድርግ፡፡ እራሳችንን እንወቅ፡፡ ቁስላችንን እንወቅ። ከዚያም መድኃኒቶቹን ተግባራዊ ማድረግ እንችላለን፤ ደዌውን የማያውቅ ሰው፣ ድካሙን አይፈውስምና፡፡ ብዙ ኃጢአት ሠርተናል፤ ይህን በሚገባ አውቃለሁ፡፡ ሁላችንም ቅጣት ይገባናል፡፡ እኛ ግን ያለ ይቅርታ አይደለንም፣ ከንስሐ አንቀርም፤ አሁንም በአደባባይ ቆመናል፤ በንስሐም ተጋድሎ ውስጥ ነን፡ አርጅተኻል እና በመጨረሻው የሕይወት ደረጃ ላይ ነህ? አሁን እንኳን ከንስሐ እንደወደቅክ አታስብ፡፡ በራስህ መዳን ተስፋ አትቁረጥ፤ በመስቀል ላይ ነፃ የወጣውን ዘራፊ አስብ፡፡ እርሱ ዘውድ ከተቀዳጀበት ጊዜ የበለጠ ምን አጭር ነገር አለ? ያም ሆኖ ይህ ለእርሱ መዳን በቂ ነበር፡ ✨✨🌱 ወጣት ነህ? በወጣትነትህ አትተማመን፣ ከፊትህ ረዥም ጊዜም እንዳለ አታስብ “የእግዚአብሔር ቀን እንደ ሌባ በሌሊት ይመጣልና" (፩ኛ ተሰ. ፭፣፪) ለዚህም ነው ፍጻሜያችንን የማይታይ ያደረገው፣ ተግተን እንድንጸና። ማንም ኃጢያተኛ ሊያደርግህ አይችልም ይላል አቡነ ቴዎድሮስ - ዲያብሎስም ቢሆን፡፡ ለኃጢአት የመስማማት ወይም የመቃወም ኃይል ያለው በአንተ ውስጥ ብቻ ነው፡፡ አሁን እግዚአብሔር በቅዱሳኑ ላይ ክፋት እንዲሆን የፈቀደ እንደሆነ አልያም በሌላ ምክንያት እንደሆነ እንመርምር። ✨✨🌱 በስንፍና በልቡም ምኞት ወደ ራሱ ኃጢአትን ከሚያስገባ ሰው በቀር፣ ኃጢአት በማንም ላይ ሊጫን አይችልም፡፡ ፈቃደኛ ባልሆነው እና ኃጢአትን በሚቃወመው ሰው ላይ ዲያብሎስ ኃይል የለውምና፡፡ ዲያብሎስ በኢዮብ ላይ ይህን የኃጢአት ክፋት ለመጫን የክፋት ዘዴውን ኹሉ ከተጠቀመ በኋላ ዓለማዊ ንብረቱን ኹሉ ገፍፎት፣ በሞት ሰባቱን ልጆቹን ነጥቆት፣ ከጭንቅላቱ ፀጉር እስከ እግሩ ጥፍር ድረስ የሚያስፈሩ ቁስሎችን፣ የማያባሩ ስቃዮችን ከሰጠው በኋላ የኃጢአት እድፍ በኢዮብ ላይ እንዲጣበቅ ለማድረግ በከንቱ ሞከረ፤ ኢዮብ በዚህ ኹሉ ጸንቶአልና፤ ከቶ አምላኩን ለመሳደብ ፍቃደኛ አልነበረም። ✨✨🌱 የነፍስ ምግብ ✨ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንዳስተማረው ✨በፍሉይ ዓለም የተተረጎመ ✨✨✨🌱🌱🌱✨✨✨🌱🌱🌱✨✨✨🌱🌱🌱

ሰላም ለሁላችሁ ይሁን በመታሰሬ ለተጨነቃችሁ በሙሉ ዛሬ ተፈትቻለሁ፡፡ በተለያዩ የሚዲያ አማራጮች ድምፅ የሆናችሁኝ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን፣ ውሉደ ብርሃን ምእመናን ሁላችሁም እግዚአብሔር ያክብርልኝ፡፡
ሰላም ለሁላችሁ ይሁን በመታሰሬ ለተጨነቃችሁ በሙሉ ዛሬ ተፈትቻለሁ፡፡ በተለያዩ የሚዲያ አማራጮች ድምፅ የሆናችሁኝ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን፣ ውሉደ ብርሃን ምእመናን ሁላችሁም እግዚአብሔር ያክብርልኝ፡፡ በአካል መጥታችሁ ለጠየቃችሁኝ የማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት አመራሮች፣ የማዕከላዊ ጎንደር ማኅበረ ቅዱሳን አመራሮች፣ የማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት የሰንበት ትምህርት ቤቶች አመራሮች፣ የጎንደር የመጻሕፍት ትርጓሜ ቤትና የአቋቋም የምስክር መምህራንና ደቀመዛሙርት፣ የጎንደር ዩንቨርሲቲ መምህራን፣ የደብረ ኀይል ወደብረ ጥበብ በአታ ለማርያም ማኅበረ ካህናትና የሰንበት ትምህርት ቤት አባላት፣ በጠቅላላው የጎንደር ከተማ ወጣቶች ሁሉ እግዚአብሔር መልካሙን ሁሉ ያድርግላችሁ፡፡

የቀድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ደቀመዛሙርት በምስራቅ አርሲ በኦርቶዶክሳዊያን ላይ ለተፈፀመው ጥቃት ሐዘናቸውን በመግለፅ ለብፁእ ሥራ አስኪያጅና ለብፁአን አባቶች ጥያቄያቸውን አቀረቡ። ሰኔ 3/2018 ዓ.
የቀድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ደቀመዛሙርት በምስራቅ አርሲ በኦርቶዶክሳዊያን ላይ ለተፈፀመው ጥቃት ሐዘናቸውን በመግለፅ ለብፁእ ሥራ አስኪያጅና ለብፁአን አባቶች ጥያቄያቸውን አቀረቡ። ሰኔ 3/2018 ዓ.ም

"እግዚአብሔርን ደጅ ጥና፥ መንገዱንም ጠብቅ፥ ምድርንም ትወርስ ዘንድ ከፍ ከፍ ያደርግሃል፤ ኃጢአተኞችም ሲጠፉ ታያለህ።"    መዝ 37÷34

+ ቅዳሴ የማይችሉት ካህን + ታሪኩ የኾነው በግብጽ ሀገር ነው። የተወሰኑ ምዕመናን ተሰብስበው ቀሲስ ዳንኤል ዮሐና የተሰኙትን ካህን ለሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ከሰሷቸው። የክሱ ጭብጥ "ካህኑ የቅዳሴውን ጸሎት በቅብጥ ቋንቋ ለማለት ተቸግረዋል፤ በአግባቡ በቃላቸው ማድረስ አይችሉበትም" የሚል ነበር። መቼም "ቅዳሴ መቀደስ አይችልም" የሚል ክስ በካህን ላይ ሲመጣ ከባድ ነውና፤ የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ብጹዕ አቡነ ቶማስ  ጉዳዩን እንደሰሙ ካህኑ በአስቸኳይ እንዲመጡ መልእክት ላኩባቸው።  ቀሲስ ዳንኤል ዮሐናም ጥሪው በደረሳቸው በማግስቱ ለጉዞው መዘጋጀት ጀመሩ። አህያቸውን እየጫኑ እያለም ባለቤታቸው በመንገድ ላይ ረሃብ ከጸናባቸው እንዲበሉት በሚል የጋገረችላቸውን ኅብስት በመሀረብ ጠቅልላ ሰጠቻቸው። ካህኑ ቀሲስ ዮሐናም ኅብስቱን ተቀብለው የሀገረ ስብከቱ መቀመጫ ወደ ሆነው አል-ሚኒያ ጉዞ ጀመሩ። በመንገድ ላይ እየሄዱ ሳለም ሊቀ ጳጳሱ ሊጠይቁኝ ይችላሉ ብለው ያሰቧቸውን የቅዳሴ ክፍሎች በቅብጥ ቋንቋ እያዜሙ መለማመድ ጀመሩ፤ በዚህ ሁኔታ ተጉዘውም ወደ አል-ሚኒያ ደረሱ። ቀሲስ ዳንኤል ዮሐና ወደ ሊቀ-ጳጳሱ ብጹዕ አቡነ ቶማስ ቢሮ ሲገቡ ግን ሊቀ-ጳጳሱ ባዩት ሁኔታ ተደናገጡ። ቀሲስ ዳንኤል በእጃቸው በመሃረብ የተጠቀለለ እና በደም የራሰ ኅብስት ይዘዋል። ሊቀ ጳጳሱም በመንገዳቸው ምን እንዳጋጠማቸው ቀሲስ ዳንኤልን ጠየቁ። ቀሲስ ዳንኤልም በትህትና መንፈስ ኾነው "በዚህ መሀረብ የተጠቀለለው ኅብስት ነው። በመንገድ እየመጣሁ እያለሁ ቅዳሴውን በቅብጥ ቋንቋ እየተለማመድኩ ነበር" ብለው መለሱ። ብጹዕ አቡነ ቶማስ በሁኔታው ተደነቁ። ለካስ በካህኑ ጸሎት ኅብስቱ የጌታችንን አማናዊ ቅዱስ ሥጋ ሆኖ ነበር። ሊቀ ጳጳሱ የጌታችንን አማናዊ ቅዱስ ሥጋ በቦታው ለነበሩት ሰዎች ካቀበሉ በኋላ ወደ ቀሲስ ዳንኤል ዮሐና በመዞር "በሉ ወደመጡበት ቤተክርስቲያን ይመለሱ፤ ከዚህ ቀደም ሲያደርጉ እንደነበረው አገልግሎትዎን ይቀጥሉ" ብለው አሰናበቷቸው። እርሳቸውን ለመፈተን ተሰብስቦ የነበረውም ጉባዔ ተበተነ። ምንጭ፦ “Mallawy’s Blessed Priest: The Late Hegumen Daniel Youhanna Maqa" by Fr. Youannis Kamal ✒️  Fresenbet G.Y Adhanom ----------

✨️️️️️️️✨️️️️️️️✨️️️️️️️🍂🍂🍂✨️️️️️️️✨️️️️️️️✨️️️️️️️🍂🍂🍂✨️️️️️️️✨️️️️️️️✨️️️️️️️🍂🍂🍂
“አቤቱ አድነኝ፤ ደግ ሰው አልቆአልና” (መዝ.11፡1)።
✨️️️️️️️✨️️️️️️️🍂 በሃይማኖት መጽናት፣ በጎ ሥራን መሥራት በራሱ ከባድ ነው:: አርአያ ሊኾኑ የሚችሉ የሚያጽናኑ ደጋግ ሰዎች ሳይኖሩ ሲቀሩ ደግሞ ይበልጥ ጭንቅ ነው፡፡ አንድ መንገድ የሚጓዝ ሰው እንዲሁ በመጓዙ ብቻ የሚያገኘው ፈተና ብዙ ከኾነ፡ ተጓዡ ብቻውን ሲኾንና ከእርሱ ጋር አብሮት የሚጓዝ ሰው ከሌለ ደግሞ የበለጠ ፈታኝ ነው፡፡ በመንፈሳዊ ሕይወትም እንደዚህ ነው፡፡ በሌላ አነጋገር የባልንጀራና የወንድም እኅት ማጽናኛ አይዞህ ባይነት እንደ ቀላል የሚታዩ ነገሮች አይደሉም፡፡ እንዲህ በመኾኑም ቅዱስ ጳውሎስ፡-
“ለፍቅርና ለመልካምም ሥራ እንድንነቃቃ እርስ በእርሳችን እንተያይ” አለ (ዕብ.10፡24)፡፡
በዘመነ ብሉይ የነበሩት ቅዱሳን ይበልጥ ንዑዳን ክቡራን እንዲሰኙ ያደረጋቸው ዋናው ምክንያት ይህ ነው ስለ ሠሩት ደግ ምግባር [ብቻ] ሳይኾን ደግ ምግባርና ይህን የሚያደርግ ሰው ባልነበረበት ዘመን ኖረው ይህን በማድረጋቸው! መጽሐፍ ቅዱስ ይህን አስመልክቶ ሲናገር፡-
“ኖኅም በትውልዱ ጻድቅ ፍጹምም ሰው ነበረ
” ማለቱም ስለዚህ ምክንያት ነው (ዘፍ.6፡9)፡፡ ስለዚሁ ምክንያት አብርሃምን እናመሰግነዋለን፡፡ ✨️️️️️️️✨️️️️️️️🍂 ስለዚሁ ምክንያት ሎጥን ከፍ ከፍ እናደርገዋለን፡፡ ስለዚሁ ምክንያት ሙሴን እናከብረዋለን፡፡ በዚያ በድቅድቅ ጨለማ ውስጥ እንደ ከዋክብት አብርተዋልና፡፡ በእሾኽ መካከል ኾነው ሳይታነቁ አድገዋልና፡፡ ቍጥር በሌላቸው ተኩላዎች መካከል በጎች ኾነዋልና፡፡ የሌላውን ሰው ኹሉ  ተቃራኒ መንገድ ተጉዘዋልና፤ ከጉዞአቸውም አላቋረጡምና እነዚህን ቅዱሳን ንዑዳን ክቡራን እንላቸዋለን፡፡ ተመልከቱ! በአንድነት ኾነው መኼድ በራሱ ጉዞው አድካሚ ከኾነ፡ በቍጥር እጅግ ብዙ ከኾኑ ሰዎች ተለይቶ ለብቻ መጓዝ፣ ለብቻ ኾኖ ብዙ ሰው ከሚጓዝበት መንገድ በተቃራኒው መጓዝ ደግሞ አንድ ሰው ብዙ ተግዳረቶች ይገጥሙታል፡፡ ማዕበል ሲኖር ለአንዲት መርከብ ወደ ፊት መጓዝ ከባድ ከኾነ፡ ምግባር ሃይማኖት ሲኾን ደግሞ የበለጠ ከባድ ነው፡፡ ✨️️️️️️️✨️️️️️️️🍂 ስለዚሁ ዋና ምክንያት ይህ ጻድቅ ሰውም (ዳዊትም)፥ በጊዜው በምግባር በሃይማኖት የጸናው እርሱ ብቻውን ስለ ነበረ፣ ሰው ኹሉ በተቃራኒው መንገድ የሚኼድ ስለ ነበረ፥ “አቤቱ አድነኝ” በማለት መጠጊያውን ረድኤተ እግዚአብሔር አደረገ፡፡ ስለዚህ ሌላ ምንም ሳይኾን እንዲህ ማለቱ ነው፡- የረድኤት እጅህን እሻለሁ፤ ሰማያዊ ጸጋህን እፈልጋለሁ፤ ትረዳኝ ዘንድ እለምናለሁ፡፡ ከሰው ኹሉ ተቃራኒ መንገድ እየተጓዝኩ ስለ ኾነ እጅግ ትረዳኝ ዘንድ እማፀንሃለሁ፡፡ “ቅዱስ ነኝና" አድነኝ አይደለም ያለው፤ “ደግ ሰው አልቆአልና” እንጂ፡፡ ይኸውም ደጋግ የተባሉ ሰዎች ጠፍተው እንደ ነበርና ክፋት ዓመፃ ገንኖ እንደ ነበረ እንደዚሁም ይህ ብዙ ሰዎችን በክሎዋቸው እንደ ነበረ ሲገልፅ ነው። ✨️️️️️️️✨️️️️️️️🍂 📚የክርስቲያን መከራ እና ሌሎች ✍ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ✨️️️️️️️✨️️️️️️️✨️️️️️️️🍂🍂🍂✨️️️️️️️✨️️️️️️️✨️️️️️️️🍂🍂🍂✨️️️️️️️✨️️️️️️️✨️️️️️️️🍂🍂🍂

ወደ ቤተ ክርስቲያን የምትሄደው ፍጹም ሆነህ አይደለም፤ ፍጹም ለመሆን ትፈልጋለህ እንጂ። ደጁን የምትረግጠው በራስህ ማንነት ወይም በሥራህ አይደለም፤ ይልቁንም የፈጠረህ አምላክ "ኑ ወደ እኔ" ብሎ የሰጠህን ጥሪ ስለምትቀበል ነው። ​ስለዚህ፣ አትፍራ፤ የኃጢአትህ ብዛት ወደ ቤተ ክርስቲያን ከመሄድ እንዲያግድህ አትፍቀድ። ይልቁንም፣ ያ ኃጢአትህ ይበልጥ ወደ ደጁ እንዲያቀርብህ አድርገው። ምክንያቱም ወደዚያ የምትሄደው ለራስህ መመጻደቅ ሳይሆን፣ አምላክን ለይቅርታውና ለቸርነቱ ለማመስገን ነው። የቴሌግራም ቻናል:-  T.me/Finote_Wongel

"አንድም ብልት ቢሣቀይ ብልቶች ሁሉ ከእርሱ ጋር ይሣቀያሉ፤ አንድ ብልትም ቢከበር ብልቶች ሁሉ ከእርሱ ጋር ደስ ይላቸዋል" በማለት እንደተናገረ በየትኛውም ሥፍራ የሚፈጸም ግድያ የቅድስት ቤተ ክርስቲያን ሁሉ ኀዘን ነው:: 1 ቆሮንቶስ 12:26

"አሕዛብ፦ አምላካቸው ወዴት ነው? ለምን ይላሉ? የፈሰሰውን የባሪያዎችህን ደም በቀል ዓይኖቻችን እያዩ አሕዛብ ይወቁት።" መዝሙር 79:10

ቋሚ ሲኖዶስ በምሥራቅ አርሲ ተገኝተው የተጎዱ ወገኖችን የሚያጽናኑ በፁዐን አባቶችን መደበ። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት ተገኝተው ጉዳት የደ
ቋሚ ሲኖዶስ በምሥራቅ አርሲ ተገኝተው የተጎዱ ወገኖችን የሚያጽናኑ በፁዐን አባቶችን መደበ። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ  በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት ተገኝተው ጉዳት የደረሰባቸውን ኦርቶዶክሳዊያን የሚያጽናኑ ብፁዓን አባቶችን መደበ። የቋሚ ሲኖዶስ አባላት በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት በአሰኮ፣ በሺርካ፣ በሆንቆሎ ዋቤ ወረዳዎች በኦርቶዶክሳውያን ወገኖቻችን ላይ የደረሰውን ጥቃት ተከትሎ በዛሬው ዕለት ባካሔደው መደበኛ ስብሰባው  በችግሩ ምክንያት ለተፈናቀሉ ወገኖች ድጋፍ እንዲደረግ፣በብፁዓን አባቶች የሚመራ የቤተ ክርስቲያናችን ልዑካን ቡድን ችግሩ ወደ ተፈጠረበት ቦታ በመሄድ ተጎጂዎችን እንዲጎበኝ፣ እንዲያጽናና እና አስፈላጊውን ጊዜያዊ ድጋፍ አንዲያደርግ ወስኗል። ቋሚ ሲኖዶስ በጠቅላይ ቤተክህነት በኩል በሚቋቋም ኮሚቴ አስተባባሪነትም  በተፈጠረው ችግር ምከንያት የመቃጠል አደጋ የደረሰበት ጥንታዊው የጠላታ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያንን እንዲያሰራ፣ከቀያቸው የተፈናቀሉ ወገኖች በቋሚነት ወደ መኖሪያቸው እንዲመለሱ የሚዲያደርግ፣ በሀገረ ስብከቱ  ዳግመኛ መሰል ችግሮች እንዳይፈጠርሩ ጥናት አካሒዶ ከመፍትሔ ሐሳብ ጭምር የሚያቀርብ ዐቢይ ኮሚቴ ተሰይሞ በአስቸኳይ ወደ ሥራ እንዲገባ ወስኗል። በትላንትናው ዕለት በምሥራቅ አርሲ አንዳንድ ወረዳዎች የተከሰተውን ችግር ተከትሎ ፦ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ ብፁ አቡነ ዲዮስቆሮስ ብፁዕ አቡነ ጎርጎሬዎስ ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ ብፁዕ አቡነ ማርቆስ ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ ብፁዕ አቡነ ፊሊጶስ ብፁዕ አቡነ ገብርኤል ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ ከፌዴራል ሰላም ሚኒስቴርና ከኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ጋር  በተከሰተው ችግር ዙሪያ ውይይት ማድረጋቸው ይታወሳል።

mahtot.m4a5.35 MB

“​​​​​​​​​​​​​​​​​​በልቤ ውስጥ ያለውን መናገር አልችልም። ዝምታየን እግዚአብሔር ይሰማዋል።’’                 ✍️አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በአርሲ ሀገረ ስብከት በቤተ ክርስቲያናችን እና በኦርቶዶክሳውያን ላይ የደረሰውን ጥቃት በማስመልከት  አባታዊ መልእክት አስተላለፉ። ግንቦት 26  ቀን 2018 ዓ.ም. አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ ቅዱስነታቸው  ያስተላለፉት አባታዊ የኀዘን  መልእክት እንደሚከተለው  ነው፦ መልእክተ ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡ ‹‹ወረሰዩ አብድንቲሆሙ ለአግብርቲከ መብልዐ ለአዕዋፈ ሰማይ፣ ወሥጋሆሙኒ ለጻድቃኒከ ለአራዊተ ገዳም፦ የአገልጋዮችህንም በድኖች ለሰማይ ወፎች መብል አደረጉ፥ የቅዱሳንህንም ሥጋ ለምድር አራዊት።›› (መዝሙረ ዳዊት ፸፰፥፪) በአርሲ ሀገረ ስብከት በአሰኮ፣ በሽርካ፣ በሆንቆሎ፣ በዋቤ እና በሙኔሳ ወረዳዎች በመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችንና በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ላይ ስለደረሰው አሰቃቂ ጥቃት የሰማነው በተሰበረ ልብ ነው። የእምነት ነፃነት ተደፍሮ መቶ ዓመታት ያስቆጠረው የጠላታ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን በተቃጠለበት፣ እንዲሁም የካራ ኩፍቴና መድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን በተዘረፈበት በዚህ ክፉ ቀን፤ በርካታ ምእመናን በግፍ መሰዋታቸውና በመቶዎች የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ከቀዬአቸው መፈናቀላቸው ቤተ ክርስቲያናችንን በእጅጉ ያሳዘነ ክስተት ነው። የሰላም፣ የፍቅርና የታሪክ ማህደር የሆነችው ቤተ ክርስቲያን በምድራዊ መከራ ውስጥ ያሉትን ምእመናን በምታጽናናበት በዚህ ወቅት ራሷ በፈተና ውስጥ ሆና ከመቸገሯም በላይ በአርሲ ምድር በተደጋጋሚ የሚስተዋለው በደልና ግፍ በሁላችንም ልቡና ውስጥ "እስከ መቼ?" የሚል የቁጭት እና የኀዘን ጥያቄን ፈጥሯል። በመሆኑም ይህ መከራ እያበቃ ሳይሆን እየሰፋ በመምጣቱ የዜጎችን ደኅንነት የመጠበቅና ሰላምን የማስፈን አደራ የተጣለባችሁ የጸጥታ አካላትና በየመዋቅሩ ያላችሁ ሓላፊዎች ከምንም በላይ ታሪክ የሚጠይቃችሁ በሥልጣን ዘመናችሁ ለዜጎች ደኅንነት በምትከፍሉት ዋጋ ነውና ይህንን የጥቃት ሰንሰለት በማስቆምና ወንጀለኞችን ለሕግ በማቅረብ ከታሪክ ባለዕዳነት ትድኑ ዘንድ በቤተ ክርስቲያናችን ስም አበክረን እናሳስባለን። በየአካባቢው የምትገኙ ምእመናንና መላው ኢትዮጵያውያንም በወንድማማችነት መንፈስ ተጋግዛችሁ፣ የተፈናቀሉ ወገኖችን በመደገፍና በጸሎት ከቤተክርስቲያናችን ጎን እንድትሆኑ ጥሪያችንን እናቀርባለን። በመጨረሻም ቤተ ክርስቲያናችን ለሰላም፣ ለይቅርታና ለሰው ልጆች ክብር ሁል ጊዜ የምትቆም መሆኑን በመግለጽ ይህንን የኀዘን ሰዓት አምላካችን በምሕረቱ ያሳልፍልን፣ የሞቱትን ነፍሶቻቸውን በመንግሥቱ ይቀበልልን፣ የተጎዱትንም በቸርነቱ ያጽናናልን በማለት አባታዊ የኀዘን መልእክታችንን በእግዚአብሔር ስም እናስተላልፋለን። እግዚአብሔር አምላክ ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ!! ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!! አሜን።  አባ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ም. አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ © የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽሕፈት ቤት

ሐናም ስትጸልይ እንዲህ አለች፡— ልቤ በእግዚአብሔር ጸና፥ ቀንዴ በእግዚአብሔር ከፍ ከፍ አለ፤ አፌ በጠላቶቼ ላይ ተከፈተ፤ በማዳንህ ደስ ብሎኛል።   1ኛ ሳሙ 2÷1

✨✨✨በዓለ ጰራቅሊጦስ✨✨ ✨✨የቤተክርስቲያን የልደት ቀን✨✨ "አቤቱ አምላካችን እግዚአብሔር ሆይ ከአንተ ዘንድ ከሰማይ የሚገኝ ሰላምን ሁሉ በሁላችን ልቡና አሳድርብን። በእርስዋም የሕይወትን ሰላም ስ
✨✨✨በዓለ ጰራቅሊጦስ✨✨ ✨✨የቤተክርስቲያን የልደት ቀን✨✨ "አቤቱ አምላካችን እግዚአብሔር ሆይ ከአንተ ዘንድ ከሰማይ የሚገኝ ሰላምን ሁሉ በሁላችን ልቡና አሳድርብን። በእርስዋም የሕይወትን ሰላም ስጠን።ለሀገራችን ኢትዮጵያም ሰላሟን አጽናላት።"           ሥርዓተ_ቅዳሴ ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
"ነገ እግዚአብሔር በመካከላችሁ ድንቅ ነገር ያደርጋልና ተቀደሱ"       መጽ ኢያሱ 3÷5
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨