ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት
Open in Telegram
በአሰላ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። የቴሌግራም ቻናል:- @Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- @FinoteWongel27 የቲክቶክ ገፅ:- https://www.tiktok.com/@finotewongel27 Youtube:- https://www.youtube.com/@Finote_Wongel ©ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት
Show more669
Subscribers
+124 hours
+27 days
No data30 days
Posts Archive
+6
ፎቶ :- 17/10/2018 ዓ.ም
የጻድቁ አባታችን አቡነ ገሪማ የንግስ ክብረ በዓል በአሰላ ደ/መ/መ/ዓ/ካቴድራል በድምቀት ተከበረ።
⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨
የቴሌግራም ቻናል:- T.me/Finote_Wongel
ይህን ያውቁ ኖሯል?
ጻድቁ አባታችን አቡነ ገሪማ አንድ ቀን ድርሳን እየደረሱ( ወንጌለ ዮሐንስን ሲጽፉ ) ሊመሽ በመሆኑ ፀሐይን አቁመዋታል።
⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨
የቴሌግራም ቻናል:- T.me/Finote_Wongel
ይህን ያውቁ ኖሯል?
ጻድቁ አባታችን አቡነ ገሪማ ጧት የተከሉት ወይን በ9 ሰዓት ያፈራ ነበር።
እንኳን አደረሳችሁ!
⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨
የቴሌግራም ቻናል:- T.me/Finote_Wongel
ሰኔ 17 ሁላችንም በአሰላ ደ/መ/መ/ዓ/ ካቴድራል እንገናኝ።
⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨
የቴሌግራም ቻናል:- T.me/Finote_Wongel
ወአንተሰ ብዕሲ መምህርነ(×2) ወአቡነ ገሪማ(×2) ጸልይ በእንቲአነ(×2)እንኳን አደረሳችሁ! ሰኔ 17 በአሰላ ደ/መ/መ/ዓ/ካቴድራል የአባታችን የአቡነ ገሪማ በዓለ ንግስ ይከበራል። ⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨ የቴሌግራም ቻናል:- T.me/Finote_Wongel
ሞት በሰርግ የተቀየረበት ዕለት
ክፉው ነጋዴ "ግ-ደሉት" የሚል መልእክት አስይዞ ባሕራንን ላከው።
ባሕራን መልእክቱን ይዞ ሄደ።ከቤት ሲደርስ የነጋዴውን አንድያ ልጅ አጋቡት። እልልታው ሞቀ፤ሰርጉ ደመቀ። የባሕራንን መቃብር ሊያይ የተመኘው ሰው ሰርጉን አየ። ሞት በሰርግ ተቀየረ።
ቅዱስ ሚካኤል ይህን ተአምር ያደረገበት ዕለት ነው ዛሬ።
አንድም
ዐባይ ለግብፅ ወንዝ ብቻ አልነበረም፤አምላኳም ነበረ።
በኢትዮጵያ ክረምት መግቢያ ዐባይ ሲሞላ የወንዙን መሙላት አስታከው የሚያመልኩበት ቤተ ጣዖት ነበረ። እለእስክንድሮስ ዐባይ ውኀ እንጂ አምላክ እንዳልሆነ አስተምሮ ቅዱስ ሚካኤልን እንዲያከብሩ እግዚአብሔርን እንዲያመልኩ ያደረገበት ዕለትም ነው።
......
( በሊቀ ሊቃውንት ሥሙር አላምረው )
----------------------------
"ክብረ ሚካኤል ናሁ ተዐውቀ በትሕትናሁ ዐብየ ወልሕቀ ዲበ አእላፍ ዘተሰምየ ሊቀ ዘይትዐፀፍ መብረቀ ይተነብል ጽድቀ"። ትርጉም፦ የሚካኤል ክብር እነሆ አኹን ታወቀ፤ በትሕናውም ፈጽሞ ላቀ ከፍ ከፍ አለ፤ በአእላፍ ነገደ መላእክት ላይ አለቃን የተባለ መብረቅን የሚጐናፀፍ ርሱ ጽድቅን ይለምናል። ቅዱስ ያሬድ በድጓው ላይ⚡️እንኳን ንዑድ ክቡር ለሆነ ለከበረ ለመላእክት አለቃ ለቅዱስ ሚካኤል በነገዱ ውስጥ በመላእክት ሁሉ ላይ በብዙ ክብር ለተሾመበት፣ ⚡️የባሕራንን የሞት ደብዳቤ ቀዶ እርሱን ለታላቅ ክብር ላበቃበት፣ ⚡️ቅድስት አፎምያን ከሰይጣን ተንኮል ለታደገበትና የእረፍቷ መታሰቢያ በዓል፣ ⚡️ቅዱስ እለእስክንድሮስ አንድን ቤተ ጣዖት አፍርሶ ከቦታው ላይ ቤተ ክርስቲያን ሠርቶ ታቦተ ቅዱስ ሚካኤልን አግብቶ በዓሉን በደስታ በሐሴት ላከበሩበት ዕለት፣ ⚡️ዳግመኛም በዚህች ዕለት የተባረከና የተመሰገነ በሰማያት ያለ ምሥጢርን ያየ የኢትዮጵያ ንጉሥ ላሊበላ ለዕረፍቱ መታሰቢያ በዓል፣ እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን አደረሳችኹ።🙏 ⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨ የቴሌግራም ቻናል:- T.me/Finote_Wongel
"ዲያብሎስ በሚኖርባት ምድር እንዴት ሰው ይከለከላል?"
"የሆነ ነገር ተቃጥሎ ካለፈ በኋላ አመዱ አጠገብ ቆሞ ስለ እሳቱ ታሪክ ማውራት እንዴት ቀላል ነው! በእሳቱ ታሪክ ውስጥ ማለፍ ግን አስቸጋሪ ነው።የአባቶቻችንን ዘመን ስንተርክ ኖርን እኛው ውስጥ እሳቱ ሲነድ ግን ማለፍ እያቃተን ነው።ይኽ በነሱ ዘመን የሆነው ነው።አንድን ሰው ሀገር ማሳጣት፣ ሀገር መንሳት፤ እግዚአብሔር ሰይጣንን እንኳን እንዲኖር በፈቀደለት ምድር ሰው እንዳይኖር ማድረግ፤ እግዚአብሔር ሰይጣንን በምድር እንዲኖር ፈቅዶለታል።ከሰይጣን የበለጠ ክፉ የለም።የእግዚአብሔርን አምልኮ የሚገዳደር፤ መቅደሱን ለማርከስ የሚሮጥ፤ ሰዎችን ከሰማይ ጉዟቸው አሰነካክሎ የሚደፋ ክፉና አመፀኛ ወንበዴ የእግዚአብሔር ጠላት ነው።ዲያብሎስ በሚኖርበት ምድር እንዴት ሰው ይከለከላል?"
ርዕሰ ሊቃውንት አባ ገብረኪዳን ግርማ!
በፍቅር ተመላለሱ
"እንግዲህ እንደ ተወደዱ ልጆች እግዚአብሔርን የምትከተሉ ሁኑ፥ ክርስቶስም ደግሞ እንደ ወደዳችሁ ለእግዚአብሔርም የመዓዛ ሽታ የሚሆንን መባንና መሥዋዕትን አድርጎ ስለ እናንተ ራሱን አሳልፎ እንደ ሰጠ በፍቅር ተመላለሱ።
ኤፌሶን 5:1
“ጌታ እውነተኛ ወዳጅ ነው
ጓደኞችህ ወንድሞችህ ሲረሱህ
እርሱ አይረሳህም አይለይህም ካንተ ጋር ነው።’’
✍️ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ
"አቤቱ፥ ወደ አንተ የጮኽሁትን ቃሌን ስማኝ። ማረኝና አድምጠኝ። አንተ ፊቴን እሹት ባልህ ጊዜ፡— አቤቱ፥ ፊትህን እሻለሁ ልቤ አንተን አለ። ፊትህን ከእኔ አትሰውር፥ ተቈጥተህ ከባሪያህ ፈቀቅ አትበል፤ ረዳት ሁነኝ፥ አትጣለኝም፥ የመድኃኒቴም አምላክ ሆይ፥ አትተውኝ።"
መዝ 27÷7-9
