ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት
Open in Telegram
በአሰላ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። የቴሌግራም ቻናል:- @Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- @FinoteWongel27 የቲክቶክ ገፅ:- https://www.tiktok.com/@finotewongel27 Youtube:- https://www.youtube.com/@Finote_Wongel ©ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት
Show more669
Subscribers
+124 hours
+27 days
No data30 days
Posts Archive
"አቤቱ የተሰቀልከው ስለ እኔ የሞትከው ስለ እኔ ነውና ይህን ደንዳና ልቤን በፍቅር ችንካር ውጋው ከዓለም ፍቅር ለይተህ ከመስቀልህ ሥር አስጠጋኝ።"
ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ
⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨
የቴሌግራም ቻናል:- T.me/Finote_Wongel
“ድምፀ እገሪሁ ለዝናም ሶበ ይዘንም ዝናም ይትፌስሁ ነድያን፣ ይጸግቡ ርሁባን፡፡
➥የዝናም ድምፅ ተሰማ፤ ዝናም በዘነመ ጊዜ ችግረኞች ይደሰታሉ፤ ረሀብተኞችም ይጠግባሉ፡፡”
ቅዱስ ያሬድ
እንኳን ከዘመነ ጸደይ ወደ ዘመነ ክረምት በሰላም አሸጋገረን።
✨✨✨🌿✨🌿✨🌿✨✨✨
✨ለነፍሳችን ኹለተኛዋ ነፍስ ✨
ወዳጄ ሆይ! እምነት ለነፍስህ ኹለተኛዋ ነፍስ እንደሆነች መርምርና እወቅ፡፡ ሥጋ በነፍስ እንድትቆም የነፍስም በሕይወት መኖር በእምነትህ ላይ የተንጠለጠለ ነው፡፡ እምነትህን ብትክድ ወይም ከራስህ ብታርቃት ነፍስህ ምውት ትሆናለች፡፡
በዚህም መሠረት የሚሞት ሥጋችን በነፍስ ላይ ጥገኛ እንደሆነች ነፍሳችንም በእምነት ላይ ጥገኛ ናት፡፡ እምነትም በእግዚአብሔር አብና በመንፈስ ቅዱስ ሕያዋን ባደረገን በእውነተኛ ልጁ ላይ ጥገኛ ናት፡፡
በዚህም እውነት ሰው ነፍሱን በሰማያት ካሉት ጋር ያገናኛታል፡፡ እንዲህ ዓይነት ሰው በነፍሱ በሕይወት ይኖራል፡፡ በሥጋ ሰውነቱም ያያል ይመለከታል። እንዲሁ እኛም በእምነት በፍቅርና በጥበብ የእግዚአብሔር መልክ ገንዘባችን አድርገን ከመለኮቱ ተካፋይ እንሆናለህ። ስለዚህም በነፍሳችን የሞትን እንዳንሆን ይህን ድንቅ የሆነ ማሰሪያ እንዳንበጥስ ወይም ነፍሳችን ከእምነት ባዶ እንዳናደርጋት እንጠቀቅ፡፡ ጌታችን ይህን አስመልከቶ እንዲህ ብሎ አስተምሮናልና “ሙታናቸውንም እንዲቀብሩ ሙታንን ተዋቸው።” (ማቴ.8፥22) ይህ አየር በእኛ ላይ በንፍሐት እፍ ሳይባልብን ሥጋችንን በሕይወት የሚያቆያት ነው፡፡ የምንተነፍሰው አየር የተቋረጠበት ሰው ሕይወቱ ትቆማለች፤ በሥጋው የሞተ ይሆናል፡፡ እንዲሁ ራሱን ከእውነተኛ ልጁ ከእግዚአብሔር ቃል የለየ ሰውም በነፍሱ የሞተ ይሆናል፡፡ እኔ ሕይወትን የሚሰጠው የእውነተኛ ልጁን ምስክርነት ሳያገኝ ለሞተ ሰው አዝናለሁ፡፡ ልክ እንደ ውቅያኖስ እርሱ የሕይወት ምንጭ ነውና፡፡
✨✨🌿
እርሱ ሰው በመሆን ፈቃዱን እንድናውቀው አደረገን፡፡ ሞትን ድል ለመንሳት ሲል እጅግ መጠማቱ ለእኛ ያለውን ፍቅር አረጋገጠልን። መጽሐፍ ቅዱስ በእምነት ጻድቅ የሆነ እርሱ በሕይወት እንዲኖር አትሞልናል፡፡ እውነት የተባለው እርሱ ራሱን ዋናው ሥር በማድረግ በጎ ምግባራትን ደግሞ በእርሱ ላይ ባለን እምነት ላይ የተንጠለጠሉ ፍሬዎች አደረጋቸው፡፡
እነሆ መልካም ምግባሮቻችን በእውነትኛው ግንድ በእርሱ ቅርንጫፎች ሆነው በዝተው ፍሬን ይሠጣሉ፡፡ እነሆ በሚታይ ምሳሌ የተሰወሩ ምሥጢራት በዓይን እንደሚታዩ ሆነው ተገለጡ። ሥጋ ልክ ትርፉን ለማግኘት እንደጓጓ ነጋዴ ነው እንዲሁ ሕሊናም ከእርሱ ጋር በእምነትን በሕይወት መርከብ ትርፍን እንደሚሰብስብ መርከበኛ ነው፡፡
ሥጋ በነፍስ እንዲቆም ነፍስም ምንም እንኳ ሕያዊት ብትሆን ያለ በጎ ሥራ ሕይወት እንደሌላት፤ ነፍስ በእምነት በሚሠራ የጽድቅ ሥራ በሕይወት እንደምትኖር መጽሐፍ ቅዱስ መስክሮልናል፡፡ በክርስቶስ አምኖ የነበረው አልዓዛር ለዚህ ለምንለው እውነተኛ ምስክር ይሆን ዘንድ ሕያው ሆኖ ተነሣ፡፡
✨✨🌿
እርሱ ከመቃብር በጠራው በጌታችን ቃል ሕይወቱ ጣፍጣ ሕያው ሆነ፡፡ እንዲሁ በአልዓዛር ምሳሌ አህዛብ በሕቡዕ በሚኖረው ሕይወት ሕያዋን ሆኑ፡፡ በተቃራኒው ደግሞ በአይሁድ ሥራ ምሳሌ ወንበዴው ራሱን ሰቀለ እንደ ውርስ አድርጎ ሞቱን ለጸሐፍት ፈሪሳዊያን ተወላቸው፡፡ እግዚአብሔር አምላክ በእርሱ ላይ ባለን እምነት በመንፈስ ቅዱስ ሕያዋን ሆነን እምነታችንን ጠብቀን እንድንኖር ይርዳን፡፡
✨ቅዱስ ኤፍሬም
✨ትርጉም በዲ/ን ሽመልስ መርጊያ)
✨✨✨🌿✨🌿✨🌿✨✨✨
✨️️️️️️✨️️️️️️✨️️️️️️🍃🍃🍃✨️️️️️️✨️️️️️️✨️️️️️️🍃🍃🍃✨️️️️️️✨️️️️️️✨️️️️️️🍃🍃🍃
በትሯን ግያዝ ያዛት
✨🌿
በመጽሐፈ ነገሥት ካልዕ 4፥8 ጀምሮ ስናነብ ሱማናዊቷን ሴት እናገኛለን። በእርግጥ የዚህች ታላቅ ሴት ታሪክ ጥልቅ ምሥጢራት የሚያስተላልፍ እጅግ አስደናቂ ታሪክ ነው። ይህቺ ሴት የእግዚአብሔር ሰው ኤልሳዕን በሱማን ባለፈ ጊዜ ከእርሷ ጋር ተገናኝቶ እንጀራ ይበላ ዘንድ አቁማዋለች። እርሱም ብቻ ሳይኾን ባለሀብት ስለነበረች ለእርሱ ማረፍያ የሚኾን ቤት ሠርታ ሰጥታዋለች። ይህቺ ሴት ባሏ ያረጀ እርሷም መውለድ የማትችል መካን ነበረች። የሆነው ሆኖ በቅዱስ ኤልያስ ጸሎት በእግዚአብሔር ፈቃድ አንድ ልጅ ወለደች። ይህ ልጇ ሞተ ወዲያውኑ ወደ ኤልሳዕ ሄዳ የኾነውን ሁሉ ነገረችው። ኤልሳም ደቀ መዝሙሩ ግያዝን በትሩን ሰጥቶ በሞተው ልጅ ፊት እንዲያደርግ ነገረው፤ ነገር ግን ልጁ ሊነሣ አልቻለም። የዚህችን ሴት አስደናቂ የኾነውን የታሪኳን ምሥጢር እናቆየውና ግያዝ ወደ ያዛት በትር አእምሯችንን እንላከው።
✨🌿
ግያዝ የያዘው በትር የቅዱስ ኤልሳዕ በትር ነው። ጉዳዩን በእርጋታ ስንመረምረው በአእምሯችን ውስጥ አንድ ጥያቄ ሊፈጥር ይችል ይኾናል። የሙሴ በትር ባሕር ከፍሎ አልነበረምን? የኤልያስስ መጎናጸፊያ ይህን አስደናቂ ነገር ፈጽሞ አልነበረምን? እንግዲህ እንዴት የኤልሳዕ በትር ሙት ማሥነሣት አልቻለም? በእርግጥም ይህን ጥያቄ ማንሣት በእጅጉ ተገቢ ነው። በጣም የሚያስገርመው ኤልሳዕ በቅዱስ ኤልያስ በእኔ ላይ ያለው መንፈስ እጥፍ ይሁንብህ የተባለለት ሰው ሲኾን በትሩ ባሕርን ከፍሎ ከማሻገር የሚያንሰውን ሙት ማስነሣት አለመቻሉ ነው!! ይህቺ በትር ተአምር ያላደረገችው የያዛት ግያዝ በስብሐተ ብጡል ወይም በከንቱ ውዳሴ ስለተወጋ ነው። የሞተው ቢነሣ እኔ አስነሣው የሚል ስለኾነ ነበር። ይህን ስናስበው በእኛም ሕይወት ውስጥ በእንዲህ ዓይነት ምክንያት እንዳይፈጸሙ የተከለከሉ ብዙ ነገሮች መኖራቸውን ማሰብ እንችላለን። አገልግሎታችን ፍሬ ሊያፈራ ያልቻለው ስለምን ይመስላቸዋል!? የምናደርገውን የምናደርገው ለራሳችን ክብር ብቻ ከማሰባችንና እኔ እንዲህና እንዲያ አደረግሁ ስለምንል አይደለምን?
✨🌿
ሊቁ አውግስጢኖስ ይህቺን በትር ከእግዚአብሔር በነቢያት በኩል የተላከችው ሕግ ናት ይለናል። በእርግጥም የብሉይ ኪዳኗ ሕግ የሞተውን አዳምን ከሞት የማስነሣት ኃይል የላትም። በሕገ ልቦና የነበሩ አበው የጸለዩት ጸሎት ያቀረቡት መሥዋዕት አዳምን ማዳን አልቻለም። በብሉይ ኪዳን ያለችዋ ቤተ እስራኤልም ከኢሩሳሌም ወደ ኢያሪኮ ማለትም ከጽድቅ ወደ ኃጢአት የወረደውን አዳምን ማዳን ስላልቻለች ደጉ ሳምራዊን ትጠብቀው ነበር። በዘመነ አበው የተደረገው የአበው ጸሎት፣ በዘመነ ካህናት የተደረገው የካህናት ጸሎትና መሥዋዕት፣ በዘመነ ነቢያት የተደረገው የነቢያት ጸሎት የመጀመርያውን ርግማን አጥፍቶ ሰውን ወደ ፍጹም ድኅነት መመለስ አልቻሉም። እንግዲህ ይህቺ በትር ይህን አገልግሎት የምታሳይ ናት። አማናዊው ኤልሳዕ ኢየሱስ ክርስቶስ የሰውን ሥጋና ነፍስ ነሥቶ ፍጹም አምላክ ፍጹም ሰው ኾኖ በሞተ ሥጋ ላይ ሞተ ነፍስ ተፈርዶበት በሲዖል ያለውን አዳምንና ልጆቹን አዳነ!!!
✨🌿
ይህቺ በትር የቃል ኪዳኑን ታቦት የምታሳይ መኾኗን ቅዱስ ያዕቆብ ዘሥሩግ ይግለጣል። የቃል ኪዳኗ ታቦት እስራኤል ዘሥጋን ብዙ ጊዜ የታደገች የእግዚአብሔር ክብር መገለጫ መኾኗ አጠያያቂ ባይኾንም፥ የሚይዛት ሰው ግን በእጅጉ ወሳኝ ነው። ይህን ለማጠየቅ ነው የእግዚአብሔርን ታቦት የያዙ እስራኤላዊያን በኃጢአታቸው ሲከፉ በፍልስጥኤማዊያን እጅ እንዲወድቁ የኾነው ለዚህ ነው። ሊቁ እንዳለው ግያዝ የእግዚአብሔር ጸጋ የሌለው ነው። የማዳን ኃይል ያለውን በትር ይዞ ማዳን ያልቻለው በትሩን የያዘው እርሱ ውስጡ ባዶ ስለኾነና የቅድስና ፍሬ የሌለው መኾኑ ይታወቀው ዘንድ ነው። በትሩ ሳይኾን ኃይል የሌለው በትሩን የያዘው ግያዝ ነበር! በእርግጥ ይህን የግያዝን የመሰለ ጠባይ አንድ ወቅት ላይ የጌታችን ደቀ መዛሙርትም አሳይተው ነበር። በእምነታቸው ጉድለት ምክንያት ማዳን አቅቷቸው ጌታችንን ለምንድነው ማዳን ያልቻልነው ሲሉ የእምነታቸውን ጉድለት ነግሮ ገስጿቸዋልና። በእምነታችን ጉድለት ብዙ ኃይል ያላቸውን ነገሮች ኃይላቸው እንዳይገለጥ እንዳደረግን ብናውቅ ወደ ልባችን ተመልሰን ለመስተካከል ይጠቅመን ነበር። ብዙ ጊዜ እንዲህ ዓይነት ነገሮች የሚደረጉት እኛ ራሳችንን ራሳችን በያዝነው በኩል እንድንረዳ ለማድረግ ነው። ጉድለትን ማወቅ ወደ ቀናው መንገድ ለመምጣት በጣም አስፈላጊ ነው።
✨🌿
ብዙዎቻችን በአንገታችን ላይ ያለውን መስቀል የተባለውን የኤልሳዕ በትር ኃይሉን እንዳይገልጥ አድርገነዋል። ኃጢአታችንን የማያስወግድ ኾኖ አይደለም፤ ከዚህ ይልቅ በኃጢአት ላይ ኃጢአት በማብዛት በእኛ እንዳይሠራ፤ የሞተ አሳባችንን አጥፍቶ የአሳብ ልዕልና እንዳይሰጠን አድርገነዋል። በእርግጥ ሰዓታቱን፣ ማኅሌቱን፣ ቅዳሴውን ይዘነዋል ኾኖም ከሞታችን መነሣት አልቻልንም። ምክንያቱም የማይገባን ሰዎች ይህን መልአካዊ አገልግሎት ይዘን በክፉ ድርጊታችን ምክንያት በእኛ ላይ እንዳይሠራ አደረግነው። በእርግጥም ከክርስትና የበለጠ በትር ምን ነበር!? ክርስትና በክርስትና ራስ በኢየሱስ ክርስቶስ መሪነት እየተመሩ የሚኖሩት የጽድቅ ሕይወት ነበር፤ እኛ ግን ገለበጥነውና ለመጠላላት፣ ለመነቃቀፍ፣ ለመለያየት፣ ለመቀናናት፣ ለመሰዳደብ አደረግነው!!! የያዝናቸው ታላላቅ በትሮችን በሕሊናችን ፈጽሞ ካድናቸው፤ ከእነርሱም ይልቅ በጣም ተራ የኾኑ ነገሮችን ተማመንን። ብዙ ሙታን ሲነሱ ያየንበትን ጠበል የተባለውን በትር እኛ ያዝነውና የእኛን ሙት አስተሳሰብ ማስነሣት አቃተን! ሩቅ መሄድ አያስፈልገንም፥ እኛው ጋ ያሉት የእግዚአብሔር በትሮች እንዴት ኃይላቸው መገለጥ እስኪያቆም ድረስ ግያዝን እንደኾን ታስተውላላችሁን? እንግዲያውስ ከምንም አስቀድመን በትራችንን በበጎ ሥራዎቻችን ይዘን እንደ ዮሐንስ ሐፂር እናለምልማት። እርግጥ ነው 19.2 Km እንደ ቅዱስ ዮሐንስ ሐፂር ተጉዘን ውኃ እየቀዳን በትርነታችንን ፍሬ እስኪያፈራ ልንተጋ ያስፈልገናል። ያም ሆኖ ሦስት ዓመት መታገስንም ሊጠይቀን ይችላልና ከቀቢጸ ተስፋ ፈጽሞ መራቅና መልካም ሥራችንን ሠርተን በትር ሃይማኖታችንን፣ መስቀላችንን፣ ክርስትናችንን አብቦ እንዲታይ ማድረግ አለብን። እግዚአብሔር በቸርነቱ ይርዳን አሜን!!
📝ዲያቆን ዮሐንስ ጌታቸው
✨️️️️️️✨️️️️️️✨️️️️️️🍃🍃🍃✨️️️️️️✨️️️️️️✨️️️️️️🍃🍃🍃✨️️️️️️✨️️️️️️✨️️️️️️🍃🍃🍃
"እግዚአብሔር ዓለቴ፥ አምባዬ፥ መድኃኒቴ፥ አምላኬ፥ በእርሱም የምተማመንበት ረዳቴ፥ መታመኛዬና የደኅንነቴ ቀንድ መጠጊያዬም ነው።"
መዝ 18÷2
🔱⚜🔱⚜🔱⚜🔱⚜🔱⚜🔱⚜🔱⚜
እንኳን ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ዓመታዊ ሕንፀተ ቤታ (ሕንፀታ) በሰላም አደረሳችኹ
ሰኔ ፳፩ (ሕንፀታ ወቅዳሴ ቤታ ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን) ከእመቤታችን ፴፫ቱ በዓላት አንዱ ነው፡፡
ጌታችንም ከእመቤታችን እና ከቅዱሳን መላእክት ጋር ከሰማየ ሰማያት ወርዶ እመቤታችንን ታቦት፣ ሐዋርያትን ልዑካን አድርጎ፣ እርሱ ሠራዒ ካህን ኾኖ ቀድሶ ካቈረባቸው በኋላ ‹‹እምይእዜሰ አንትሙኒ ከመዝ ግበሩ፤ ከዛሬ ጀምሮ እናንተም እንደዚህ አድርጉ›› ብሎ አዝዟቸው በክብር በምስጋና ወደ ሰማይ ዐርጓል፡፡ ከዚህ በኋላ ሐዋርያት ከጌታ እንዳዩት በዓለም ዞረው ቤተክርስቲያንን አንፀዋል።
እግዚአብሔር አምላክ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ፍቅር፥ ረድኤት፥ ጸጋ - የቡሩካን ሐዋርያቱን በረከት ያሳድርብን! አሜን🙏
⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨
የቴሌግራም ቻናል:- T.me/Finote_Wongel
" እግዚአብሔር፥ ቅዱሳንን ስላገለገላችሁ እስከ አሁንም ስለምታገለግሉአቸው፥ ያደረጋችሁትን ሥራ ለስሙም ያሳያችሁትን ፍቅር ይረሳ ዘንድ ዓመፀኛ አይደለምና።"
ዕብራውያን 6:10
🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓
🎓🎓🎓 እንኳን ደስ አላችሁ🎓🎓🎓
🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓
በቀን 20/10/2018 ዓ.ም የሰንበት ት/ት ቤታችን እንቁ አገልጋይ የሆነው መዘ/ር የግል ከ Addis abeba science and technology University ተመርቋዋል። ውድ ወንድማችን እንኳን ደስ አለህ መልካም የስራና የአገልግሎት ዘመን እንዲሆንልህ የፍኖተ ወንጌል ሰንበት ትምህርት ቤት አገልጋይ ወንድም እሕቶችህ እንመኝልሀለን።
ሰላም ለኪ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን
👉"ሰኔ 20 ቀንም ሐዋርያት የተሰበሰቡበት ልጅዋም ቤቷን ለመሥራት የወረደበት ነው" መቅድመ ተአምረ ማርያም ቁጥር 29
👉“እርሱም፦ ቤቴ የጸሎት ቤት ይሆናል ተብሎ ተጽፎአል፤ እናንተ ግን የወንበዴዎች ዋሻ አደረጋችሁት አላቸው።”
— ሉቃስ 19፥46
"ሰላም ለኪ ቅድስት ቤተክርስቲያን
አምሳለ ኢየሩሳሌም ሰማያዊት
ማኅደረ መለኮት
ምስአል ወምስጋድ ወመስተስርየ ኃጢያት"
⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨
የቴሌግራም ቻናል:- T.me/Finote_Wongel
“ሕይወታችን ብሩህ ቢሆን ኖሮ
በድርጊታችን ከመሰከርን
ቃላት ባላስፈለገም ነበር፣
እውነተኛ ክርስቲያኖች ብንሆን
አረማውያን አይኖሩም ነበር።’’
✍️ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨
የቴሌግራም ቻናል:- T.me/Finote_Wongel
“ጊዜ ስላላችሁ ወደ እግዚአብሔር በንስሐ ተመለሱ በሲኦል ኃጢአትን መናዘዝና ንስሐ መግባት የሚችል ማንም የለም።’’ በንስሐ ወደ ቤተ ክርስቲያን አንድነት ለመግባት ከፈለጉ
እንደ ኢየሱስ ክርስቶስ ቃል ሊኖሩ ይገባል።
✍️ቅዱስ አግናጥዮስ
" እግዚአብሔር፥ ቅዱሳንን ስላገለገላችሁ እስከ አሁንም ስለምታገለግሉአቸው፥ ያደረጋችሁትን ሥራ ለስሙም ያሳያችሁትን ፍቅር ይረሳ ዘንድ ዓመፀኛ አይደለምና።"
ዕብራውያን 6:10
🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓
🎓🎓🎓 እንኳን ደስ አላችሁ🎓🎓🎓
🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓
በቀን 16/10/2018 ዓ.ም የሰንበት ት/ት ቤታችን እንቁ አገልጋይ የሆነው ዲ/ን ዳዊት ትርፌ ከደብረ ታቦር University ተመርቋዋል። ውድ ወንድማችን እንኳን ደስ አለህ መልካም የስራና የአገልግሎት ዘመን እንዲሆንልህ የፍኖተ ወንጌል ሰንበት ትምህርት ቤት አገልጋይ ወንድም እሕቶችህ እንመኝልሀለን።
" እግዚአብሔር፥ ቅዱሳንን ስላገለገላችሁ እስከ አሁንም ስለምታገለግሉአቸው፥ ያደረጋችሁትን ሥራ ለስሙም ያሳያችሁትን ፍቅር ይረሳ ዘንድ ዓመፀኛ አይደለምና።"
ዕብራውያን 6:10
🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓
🎓🎓🎓 እንኳን ደስ አላችሁ🎓🎓🎓
🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓
በቀን 16/10/2018 ዓ.ም የሰንበት ት/ት ቤታችን እንቁ አገልጋይ የሆነው ዲ/ን ነብዩ ዳንኤል ከArsi University ተመርቋዋል። ውድ ወንድማችን እንኳን ደስ አለህ መልካም የስራና የአገልግሎት ዘመን እንዲሆንልህ የፍኖተ ወንጌል ሰንበት ትምህርት ቤት አገልጋይ ወንድም እሕቶችህ እንመኝልሀለን።
+9
ፎቶ :- 17/10/2018 ዓ.ም
የጻድቁ አባታችን አቡነ ገሪማ የንግስ ክብረ በዓል በአሰላ ደ/መ/መ/ዓ/ካቴድራል በድምቀት ተከበረ።
⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨
የቴሌግራም ቻናል:- T.me/Finote_Wongel
+7
ፎቶ :- 17/10/2018 ዓ.ም
የጻድቁ አባታችን አቡነ ገሪማ የንግስ ክብረ በዓል በአሰላ ደ/መ/መ/ዓ/ካቴድራል በድምቀት ተከበረ።
⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨
የቴሌግራም ቻናል:- T.me/Finote_Wongel
