ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት
Open in Telegram
በአሰላ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። የቴሌግራም ቻናል:- @Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- @FinoteWongel27 የቲክቶክ ገፅ:- https://www.tiktok.com/@finotewongel27 Youtube:- https://www.youtube.com/@Finote_Wongel ©ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት
Show more668
Subscribers
+124 hours
+27 days
No data30 days
Posts Archive
"ሐዘን ያለበት ርህራሄ ምልክቱ የበደሉትን ሁሉ ይቅር ማለቱ ነው። የጠማማ ምልክቱ ጸብ ክርክር ነው።"
ማር ይሳሐቅ
⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨
የቴሌግራም ቻናል:- T.me/Finote_Wongel
ጌታ የልብህን ጸሎት ሁሉ ይመልስልሃል ። መልካም በሮችንም ይከፍትልሃል ደስታን ፣በረከትን ፣ፈውስንና ማለቂያ የሌለው መጽናናትን ይሰጥሃል !
አቡነ ቄርሎስ
⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨
የቴሌግራም ቻናል:- T.me/Finote_Wongel
"የድሀውን ጩኸት እንዳይሰማ ጆሮውን የሚደፍን ሰው፥ እርሱ ራሱ ይጮኻል አይሰማለትምም።"
ምሳ 21÷13
⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨
የቴሌግራም ቻናል:- T.me/Finote_Wongel
✨✨🌱️️️️️️✨🌱️️️️️️✨✨🌱️️️️️️✨🌱️️️️️️✨✨🌱️️️️️️✨🌱️️️️️️
✨✨🌱️️️️️️ ከእግዚአብሔር መማር✨✨🌱️️️️️️
ዕውቀትን ፈጽሞ መቀበል የማይችሉ አንዳንድ አላዋቂ ሰዎች አሉ፡፡ ሌሎች ደግሞ ከሰዎች የሚማሩ አሉ። እነዚህኛዎቹ የበለጠ አላዋቂዎች ናቸው፡፡ በትክክል ተምረዋል ወይም አዋቂዎች ናቸው የሚባሉት ግን በቀጥታ ከእግዚአብሔር የተማሩት ናቸው፡፡
እግዚአብሔር ሰውን ሲፈጥረው ብዙ ዓይነት ዕውቀቶችን ሰጥቶት ነው:: ከዚያ የበለጠ ዕውቀትን በፈለገ ጊዜም እግዚአብሔር ይጨምርለት ነበር። ሰው በዚህኛው መንገዱ ቢገፋበት ኖሮ ፍጹም አዋቂ ስለሚሆን ከሕይወት ዛፍ: በመብላት ለዘላለም ሞትን ሳያይ ይኖር ነበር፡፡ ነገር ግን ሰው እግዚአብሔርን ትቶ ከሌላ መማር በጀመረ ጊዜ አላዋቂ መሆንን ጀመረ፡፡ መጀመሪያ ከእባቢቱ ተማረና መልካሙንና ክፉውን ከምታሳውቀው ዛፍ በላ፡፡ በዚህ ጊዜም አላዋቂ ሆነ፡፡ ከዚህ በኋላም ሰው ከእግዚአብሔር ሌላ ዕውቀትን በመፈለጉ በአላዋቂነት ላይ አላዋቂነትን እየጨመረ መጣ፡፡
✨✨🌱️️️️️️
ሰው የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ስለሆነ የእግዚአብሔር መንፈስ በእርሱ ውስጥ ያድራል፡፡ ስለዚህ የእግዚአብሔር መንፈስም ኢየሱስ ክርስቶስ እንዲህ በማለት ተናግሯል፡፡“ እርሱ የእውነት መንፈስ በመጣ ጊዜ ወደ እውነት ሁሉ ይመራችኋል፡፡” ዮሐ 16፥13። ቅዱስ ጳውሎስም ስለዚሁ ስለ እግዚአብሔር መንፈስ እንዲህ ብሏል፡፡ “መንፈስም የእግዚአብሔርን ጥልቅ ነገር ስንኳ ሳይቀር ሁሉን ይመረምራልና።'' 1ኛ ቆሮ 2፥10። ይሁን እንጂ ሰው ከታላቅ ደካማነቱና አላዋቂነቱ የተነሳ የተነሳ ዕውቀትን የሚፈልገው በእርሱ ውስጥ ከሚኖረው ከእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ሳይሆን ከውጪ ነው፡፡ ከሰዎችና ሕይወትን ይሰጡኛል ብሎ ከሚገምታቸው ከዓለማዊ መጻሕፍት፡፡
ስለሆነም ምንም እንኳ የዚህ ዓለም ጥበብ በእግዚአብሔር ፊት ሞኝነት ቢሆንም ዛሬ በዓለማችን ብዙ የተማሩና አዋቂ ሰዎች ይገኛሉ፡፡ ቅዱስ አውግስጢን በዚህኛው መንገድ ለረዥም ጊዜ ከተጓዘና እግዚአብሔርን በውጪ ሲፈልገው ቆይቶ ካጣው በኋላ በመጨረሻ እርሱ በወደደ ሲገለጥለት ይህን ዘላለማዊ ቅኔ ተቀኝቶለታል፡፡
✨✨🌱️️️️️️
“የወደድኩህ በጣም ዘግይቼ ነው፡፡ ቀዳማዊ ብትሆንም ምንጊዜም አዲስ ነህ፡፡ የወደድኩህ በጣም ዘግይቼ ነው ኣንተ በእኔ ውስጥ እያለህ እኔ በውጪ ሆኜ እፈልግህ ነበር። አንተ በፈጠርከውና ባሳመርከው ውስጥ ሁሉ ያለማስተዋል እባዝን ነበር፡፡ በዚህ ሁሉ ጊዜ ግን አንተ ከእኔ ጋር ነበርህ እኔ ግን ከአንተ ጋር አልነበርሁም።”
ከዚህ በኋላ ቅዱስ አውግስጢን እግዚአብሔርን በውስጡ ሲያገኘው ከጻድቃን ወገን ሆነ፡፡ ውድ ወንድሜ ሆይ! አንተም ብትሆን እግዚአብሔርን ከአንተ ውጪ ብትፈልገው መንገዱ ይጠፋብሃል። ስለዚህ በአንድ ሥፍራ ተቀመጥና በተመስጦ አስተውል! ወደ አንተነትህና ወደ ውስጥህ ጠልቀህ ግባና እግዚአብሔርን ፈልገው፡፡ በዚያ በጥልቁ ባለው ውሳጣዊ ማንነትህ ውስጥ ታገኘዋለህ፡፡ በዚያ ምንጩ የማይነጥፍና የማይደርቅ የፍቅር ውኃ ሆኖ ፊት ለፊት ታየዋለህ፡፡ ያኔ ነው እጅግ በመደነቅ በዝምታ በልቅሶና የደስታ ሲቃ ተውጠህ “እግዚአብሔርን አየሁት” ማለት የምትችለው፡፡
✨✨🌱️️️️️️
የቀደሙት ቅዱሳን አባቶቻችን በዚህ መንገድ ተጠቅመዋል፡፡ ይህን ዓለም ከነ ሁካታው ግርግሩና ጫጫታው ትተውት ወጥተዋል፡፡ ሁሉን ትተው በውስጣቸው : ያለውን እግዚአብሔር በማያቋርጥ ምሥጋናና ስለፈለጉት ሊያዩትም ሆነ ሊያገኙት በቅተዋል፡፡ በሌላ መልኩ ሃሳባውያን፡ ፈላስፎች፡ ተመራማሪዎችና ሳይንቲስቶች እግዚአብሔርን በመጻሕፍትና በሰዎች ስለሆነ አላዋቂነትን ምሥጢር የሆነ ነገርንና መታከትን ገንዘባቸው አድርገዋል።
ይህን በምናገርበት ጊዜ ግን ስለ እነርሱ ህመም ይሰማኛል። ለእነርሱ ብቻ ሳይሆን ዓለሙን ትተው ወደ ምድረ በዳ ከገቡ በኋላ እግዚአብሔርን በመጻሕፍት በኘሮጀክቶችና በአገልግሎት ውስጥ ለሚፈልጉት አንዳንድ አባቶችም ጭምር ነው፡፡ በእርግጥ እግዚአብሔር በልቦናቸው ውስጥ ሆኖ እነዚህን ሁሉ ትተው ከእርሱ ጋር እንዲቀመጡ ይፈልጋል፡፡ በዚህም ማንም ያላወቃቸውን ምሥጢራት ሊገልጥላቸውና የሌሎች ዓይኖች ያላዩትን ሊያሳያቸው ይወዳል። ይህም ለመነኮሳት አባቶች ብቻ ሳይሆን ለሌሎችም ይሆናል። ውድ ወንድሜ ሆይ! መንፈሳዊውን ዕውቀት ለመገብየት ትክክለኛው መንገድ የቱ ይመስልሃል? በእርግጥ ለሰው የምታስተምረው ምንም አዲስ ነገር የለህም፡፡ ምክንያቱም ሁሉን ስለሚያውቅና በእርሱ ውስጥ የሚያድረው የእግዚአብሔር መንፈስ አንተ ልታስተምረው ከምትችለው በላይ ስለሚያወቅ ነው፡፡ ስለዚህ ትክከለኛው የማሰተማርያ መንገድ ሰውን ከሚያውቀው የተሳሳተ ዕውቀት ነፃ ማውጣት ነው፡፡ ከዓለምና ከሰዎች ካገኘው ማንኛውም ዓይነት የተሳሳተ ዕውቀት፡፡
✨✨🌱️️️️️️
ሕፃን ሲወለድ በህሊናው በልቦናውና በአሳቡ ሁሉ ስለ እግዚአብሔር ድንቅ እውቀትን ይዞ ነው የሚወለደው፡፡ ከዚህ በኋላ ነው ማህበረሰቡ ለዚህ ምስኪን ሕፃን እርሱ ስለ እግዚአብሔር ከሚያውቀው የተለየ እውቀትን የሚያቀርብለት፡፡ በዚህም ስለ እግዚአብሔርም ሆነ ስለ ቅዱሳኑ ሁሉ ጥቂቱንና ሕሊናው ሊያውቀው ከሚችለው በታች የሆነውን ገድበው ይሰጡታል፡፡ ከዚህ በኋላ ያ ሕፃን ስለ እግዚአብሔርም ሆነ ስለ ቅድስና ያለው ዕውቀት ልማዳዊ በሆኑና በሰዎች ሁሉ ዘንድ ክፉና መልካም ተብለው በሚታወቁ ነገሮች ይተካል። በዚህ ጊዜም ያ ሕፃን አዳምና ሔዋን አስቀድመው ከበሉትና መልካሙንና ክፉውን ከሚያሳውቀው ከዕውቀት ዛፍ ስለሚበላ እንደ እነርሱ አላዋቂ ይሆናል፡፡ እዚህ ጋር ነው ታዲያ የዚያ የመንፈሳዊ መሪ ሚና የሚመጣው፡፡ በዚህ ሕፃን ላይ ተጨማሪ ዕውቀትን ከመጨመር ይልቅ በሃይማኖት ሰበብ የገቡትን አላስፈላጊ ወይም የተሳሳቱ አመለካከቶች በማስወጣት ላይ ማተኮር የሚገባው፡፡ መንፈሱ ከእነዚህ ሁሉ ስትላቀቅ እውነተኛው ዕውቀት እግዚአብሔር መሆኑን ያውቃል። እግዚአብሔር ከእርሱ ሳይርቅ በእርሱ አድሮ ይኖራልና።
የነፍስ አርነት
📝አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ
📝አያሌው ዘኢየሱስ እንደተረጎመው
✨✨🌱️️️️️️✨🌱️️️️️️✨✨🌱️️️️️️✨🌱️️️️️️✨✨🌱️️️️️️✨🌱️️️️️️
+3
" እግዚአብሔር፥ ቅዱሳንን ስላገለገላችሁ እስከ አሁንም ስለምታገለግሉአቸው፥ ያደረጋችሁትን ሥራ ለስሙም ያሳያችሁትን ፍቅር ይረሳ ዘንድ ዓመፀኛ አይደለምና።"
ዕብራውያን 6:10
🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓
🎓🎓🎓 እንኳን ደስ አላችሁ🎓🎓🎓
🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓
በቀን 11/11/2018 ዓ.ም የሰንበት ት/ት ቤታችን እንቁ አገልጋይ የሆኑት መዘ/ት ናርዶስ ያሬድ፣ መዘ/ት ራኬብ ግርማ ፣ ዘማሪት ትዕግስት በቀለ እና መዘ/ት ሄለን ደቻሳ ከሮሆቦት ሀርሜ ኮሌጅ ተመርቀዋል። ውድ እህቶቻችን እንኳን ደስ አላችሁ መልካም የስራና የአገልግሎት ዘመን እንዲሆንላችሁ የፍኖተ ወንጌል ሰንበት ትምህርት ቤት አገልጋይ ወንድም እሕቶቻቹ እንመኝላቹሀለን።
✨✨🌿✨
ሐዋርያው ቅዱስ ናትናኤል ከጌታችን እግር ሥር ምሥጢረ መንግስተ ሰማያትን ተምሮ: በጸጋ መንፈስ ቅዱስም ሰክሮ: ብዙ አሕዛብን ከጨለማ (ጣኦት አምልኮ) ወደ ብርሃን (አሚነ ክርስቶስ) መልሷል:: እጅግ ብዙ መከራንም ተቀብሏል::
የጌታችን ወንድም የተባለ ቅዱስ ያዕቆብ በአይሁድ ከተገደለ በኋላም ቅዱስ ናትናኤል የኢየሩሳሌም ሁለተኛ ኤጲስ ቆጶስ ሆኖ አገልግሏል:: ከአይሁድም ዘንድ ብዙ መከራ ደርሶበታል:: በመጨረሻም በዚህች ዕለት በሰማዕትነት አልፏል:: በገድለ ሐዋርያት ላይ እንደተጠቀሰው ቅዱሱ ሰማዕት የሆነው በመቶ ሃምሳ ዓመቱ ነው:: ያ ማለት ደግሞ ከሐዋርያት አባቶች በመጨረሻ ያረፈው እርሱ ነው ያሰኛል::
"ጌታ ኢየሱስ ናትናኤልን ወደ እርሱ ሲመጣ አይቶ ስለ እርሱ 'ተንኰል የሌለበት በእውነት የእሥራኤል ሰው እነሆ' አለ:: ናትናኤልም 'ከወዴት ታውቀኛለህ?' አለው:: ጌታ ኢየሱስም መልሶ 'ፊልጶስ ሳይጠራህ ከበለስ በታች ሳለህ አየሁህ' አለው:: ናትናኤልም መልሶ 'መምሕር ሆይ አንተ የእግዚአብሔር ልጅ ነህ:: አንተ የእሥራኤል ንጉሥ ነህ' አለው::" ዮሐ. ፩፥፵፰-፶፩ወስብሐት ለእግዚአብሔር ✨✨🌿✨🌿✨✨🌿✨🌿✨✨🌿✨🌿 ⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨ የቴሌግራም ቻናል:- T.me/Finote_Wongel
✨✨🌿✨🌿✨✨🌿✨🌿✨✨🌿✨🌿
እንኳን ለሐዋርያው ቅዱስ ናትናኤል ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን።
በቤተ ክርስቲያን ትውፊት መሠረት ከቅዱሳን ሐዋርያት መካከል ዘግይቶ ሰማዕትነትን የተቀበለ ይህ ቅዱስ ሐዋርያ ነው::
ቅዱሱ ሐዋርያ የተወለደው ከእሥራኤላውያን ወላጆቹ ጌታችን በተወለደበት ዘመን አካባቢ ነው:: ይህ በምን ይታወቃል ቢሉ እርሱ ሕፃን እያለ ሔሮድስ 144,000 ሕፃናትን ሲፈጅ እርሱ ግን በእግዚአብሔር ጥበብ ተርፏል:: እናቱ በቅርጫት ውስጥ አድርጋ የበለስ ዛፍ ላይ አስቀምጣው ተደብቃ ታጠባው ነበር::
✨✨🌿✨
ለሐዋርያው ወላጆቹ ያወጡለት ስም ስምዖን ሲሆን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ደግሞ ናትናኤል ብሎታል:: በባልንጀሮቹ ሐዋርያት ደግሞ የቃናው ስምዖን (ገሊላ ቃና አካባቢ ስላደገ) አንዳንዴም ቀናተኛው ስምዖን ይሉት ነበር::
ምሑረ ኦሪት ነበርና ዘወትር ለሕግ ይቀና ነበር:: በገሊላ ቃና ሰርግ የደገሰው ዶኪማስ የቅዱስ ናትናኤል የአጎት ልጅ ነው:: ጌታና ደቀ መዛሙርቱን ዶኪማስ የጠራበት አንዱ ምክንያትም ይሔው ነው::
✨✨🌿✨
ቅዱስ ናትናኤል ኦሪትን ከገማልያል ተምሮ: ከበለስ ቁጭ ብሎ ይተክዝ ነበር:: "መሲሕ ምነው ቀረህ?" እያለም ይተክዝ ነበር:: ማዕምረ ኅቡዓት አምላካችን ክርስቶስ ይህንን አውቆ በፊልጶስ አማካኝነት ጠርቶታል::
ናትናኤል ለጊዜው ተከራክሮ ነበር:: በኋላ ግን የጌታችንን ማንነት በደቂቃዎች ተረድቶ አምኗል:: ጌታችንም "ክዳት ሽንገላ በልቡ ውስጥ የሌለበት ንጹሕ እሥራኤላዊ" ሲል አመስግኖታል::
"ከመስጠት መልካም ቃል ይበልጣል ደገኛ ሰው ግን ሁሉንም አጠቃሎ ይይዛቸዋል ።"
ቅዱስ ቀለሜንጦስ
⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨
የቴሌግራም ቻናል:- T.me/Finote_Wongel
🌿⚜🌿⚜🌿⚜🌿⚜🌿
እንኳን ለክቡራንና ዐበይት አባቶቻችን ሐዋርያት ቅዱስ ጴጥሮስ እና ቅዱስ ጳውሎስ የሰማዕትነት መታሰቢያ በዓላቸው አደረሳችሁ
🌿⚜🌿⚜🌿⚜🌿⚜🌿
‹‹ጴጥሮስ ኰኵሐ ሃይማኖት ወጳውሎስ ልሳነ ዕፍረት፥ በበዓልክሙ እምርት ንሥኡነ ዐሥራተ ምሕረት፥ ሰላም ለክላሌክሙ በዛቲ ዕለት።
ትርጉም:-
ቅዱስ ጴጥሮስ የሃይማኖት ዐለት ነው፤ ቅዱስ ጳውሎስ ልሳነ እፍረት ነው፤ (የተመረጠ ዕቃ)
በታወቀችው በዓላችሁ የምሕረት ዐሥራታችሁን ያዙ፤ በዚች ዕለት ለተሰየፈችው አንገታችሁ ሰላም ይሁን።››
✨ባሕረ ጥበባት ቅዱስ ያሬድ✨
ከቅዱስ ጴጥሮስና ከቅዱስ ጳውሎሰ ረድኤትና በረከት ያድለን!
🌿💫🌿💫🌿💫🌿💫🌿💫🌿💫🌿💫
አመ አመ ሰበክሙ
አመ አመ ሰበክሙ(፪)
ቅዱሳን ሐዋርያት
ቅዱሳን ሐዋርያት - - - ሐዋርያት
የዓለም ብርሃን ናችሁ - - - ሐዋርያት
መጀመሪያ ጴጥሮስ - - - ሐዋርያት
አለና ጳውሎስ - - - ሐዋርያት
አዝብርሃናተ ዓለም - - - ሐዋርያት ጴጥሮስ ወጳውሎስ- - - ሐዋርያት በእውነት ተሰየፉ - - - ሐዋርያት ስለ ክርስቶስ - - - ሐዋርያት
አዝሐዋርያት ፈርተው - - - ሐዋርያት ሲለቅሙ በሻማ - - - ሐዋርያት ሰዎች አትለዩ - - -ሐዋርያት ከወንጌል አውድማ - - - ሐዋርያት
አዝየዘላለም ሕይወት - - - ሐዋርያት ማደስ ካማራችሁ - - - ሐዋርያት የሐዋርያት ሥራ - - - ሐዋርያት ይሁን አላማችሁ - - - ሐዋርያት
አዝውኆች ቀለም ሆነው - - - ሐዋርያት እንጨቶች ብዕር - - - ሐዋርያት ቢፅፉት አያልቅም - - - ሐዋርያት የሐዋርያት ክብር - - - ሐዋርያት
አዝሐምሌ አምስት ቀን - - - ሐዋርያት ማኅበራችን - - - ሐዋርያት በክርስቶስ መስቀል - - - ሐዋርያት ተባረከልን - - - ሐዋርያት መዝሙር በጴጥሮስ ወ ጳውሎስ ቤ/ክ ሰ/ት/ቤት ዘማርያን 📖"ስለ አንተ ቀኑን ሁሉ እንገደላለን እንደሚታረዱ በጎች ተቆጠርን" ሮሜ ፰ ፥ ፴፮ ⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨ የቴሌግራም ቻናል:- T.me/Finote_Wongel
"የዮና ልጅ ስምዖን ሆይ፥ ከእነዚህ ይልቅ ትወደኛለህን?
አለው። አዎን ጌታ ሆይ፥ እንድወድህ አንተ ታውቃለህ አለው። ግልገሎቼን አሰማራ አለው። ደግሞ ሁለተኛ። የዮና ልጅ ስምዖን ሆይ፥ ትወደኛለህን? አለው። አዎን ጌታ ሆይ፥ እንድወድህ አንተ ታውቃለህ አለው።ጠቦቶቼን ጠብቅ አለው። ሦስተኛ ጊዜ። ልጅ ስምዖን ሆይ፥ ትወደኛለህን? አለው። ሦስተኛ። ትወደኛለህን? ስላለው ጴጥሮስ አዘነና። ጌታ ሆይ፥ አንተ ሁሉን ታውቃለህ፤ እንድወድህ አንተ ታውቃለህ አለው። ኢየሱስም። በጎቼን አሰማራ።"
ዮሐ 21÷15-17
⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨
የቴሌግራም ቻናል:- T.me/Finote_Wongel
✨🌿
በኋላም ቅዱስ ቴዎፍሎስ እንዳረፈ ይህንን ደገኛ ሊቅ በርሱ ፈንታ ሊቀ ጳጳስ አደረጉት። በርሱም ዘመን የቊስጥንጥንያው ሊቀ ጳጳስ የነበረው ንስጥሮስ ክልኤ ባህርይ ክልኤ ፍና የምትል ክፉ ትምህርትን አመጣና በዚህ ምክንያት ቅዱስ ቄርሎስ አፈ ጉባኤ የነበረበት የኤፌሶን ጉባኤ በንጉሡ ቴዎዶስዮስ ዘመነ መንግስት ተካኤደ። በዚህም ዘመን በተካሄደው ጉባኤ ኹከት መቶ ሊቃውንት የተገኙ ሲኾን ንስጥሮስን ክህደቱ ከመረመሩ በኋላ ተዋሕዶን አጽንተው ፈጸሙ። በኋላም ባለ ዐሥራ ሁለት አንቀፅ ቃለ ግዘትን አርቅቆ ጻፈ። እሊህም ቃለ ግዘታት መሃከል አንደኛው የሚከተለውን ይይዛል። "አማኑኤልን እርሱው ራሱ እግዚአብሔር እንደኾነ ካልመሰከረና ከቅድስቲቱ ድንግል ሥጋን ነስቶ ሰው የኾነውን የእግዚአብሔርን ቃል በመውለዷ (እርሷንም) የእግዚአብሔር እናቱ ታዶኮስ እንደኾነች የማይመሠክር ማንም ቢኖር የተለየ የተወገዘ ይሁን"።ከዚህም በኋላ ብዙ ድርሳናትንና ተግሣጻትን ደረሰ። መጻሕፍትንም ተረጎመ፣ ከነዚህም የተወሰኑት ቢጠቀሱ፦
ለምሳሌ ድርሣነ ቄርሎስ፣ ተረፈ ቄርሎስ፣ ስለመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አንድ አካል አንድ ባህርይነት፣ እሊህንም የመሰሉ ሌሎችን ደረሰ። ከሠለስቱ ምዕት ዐሠርቱ ወሰመንቱ ርቱዓነ ሃይማኖት የወጡትን መናፍቃን ኹሉ አወገዛቸው። በወንጌላዊ ማርቆስም መንበር ሃያ አራተኛ ሊቀ ጳጳሳት ኹኖ ለሠላሳ ኹለት ዓመታት ቆይቶ በሰላም ዐረፈ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን፣ እኛንም በዚህ አባት ጸሎት ይማረን ለዘላለሙ አሜን።
✨✨🍂✨🍂✨✨🍂✨🍂✨✨🍂✨🍂✨✨🍂✨🍂
⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨
የቴሌግራም ቻናል:- T.me/Finote_Wongel
‛‛የእግዚአብሔር ምሕረቱ እንጂ
ቁጣው እንዳያገኛችሁ በበጎነት እራሳችሁን አስጊጡ።’’
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨
የቴሌግራም ቻናል:- T.me/Finote_Wongel
‛‛የእግዚአብሔር ምሕረቱ እንጂ
ቁጣው እንዳያገኛችሁ በበጎነት እራሳችሁን አስጊጡ።’’
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨
የቴሌግራም ቻናል:- T.me/Finote_Wongel
✨🕯✨🕯✨🕯✨
ሃሌ ሉያ ሰምዑ አዝማዲሃ ወሰብአ ቤታ። እስመ አዕበየ እግዚአብሔር ሣህሎ ላዕሌሃ። ወተፈሥሁ ፍሥሃ ፈድፋደ። ወፈቀዱ ይስምይዎ በስመ አቡሁ ዘካርያስ። ወትቤ እሙ ዮሐንስሃ ይሰመይእግዚአብሔር ይቅርታውን በእርሷ ላይ አብዝቷልና ቤተሰቦቿ ና ዘመዶቿ ሰሙ ተደሰቱም በአባቱም ስም ዘካርያስ በለው ይጠሩት ዘንድ ወደዱ እናቱ ግን ዮሐንስ ይባል አለች። ✨ ሊቁ ቅዱስ ያሬድ በድጓው ላይ። ✨🕯✨🕯✨🕯✨🕯✨
“● ትላንት ስለ ዛሬ ያወቀ የለም
● ዛሬም ስለ ነገ የሚያውቅ የለም
ሁሉን አዋቂ የሆነው እግዚአብሔር
መጨረሻህን ያሳምርልህ።’’
✍️አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ
+5
ቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ዛሬ ሰኔ 27 ቀን 2018 ዓ.ም ዕጩ ደቀ መዛሙርቱን አስመረቀ።
በመርሐ ግብሩ ላይ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ፣ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ፣ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ተገኝተው ለተመራቂዎች አባታዊ ቡራኬ ሰተዋል።
