en
Feedback
ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት

ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት

Open in Telegram

በአሰላ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። የቴሌግራም ቻናል:-  @Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- @FinoteWongel27 የቲክቶክ ገፅ:- https://www.tiktok.com/@finotewongel27 Youtube:- https://www.youtube.com/@Finote_Wongel ©ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት

Show more
668
Subscribers
+124 hours
+27 days
No data30 days
Posts Archive
ዜና ፍኖተ ወንጌል📺 ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ የአሰላ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰ/ት/ቤት ህጻናት እና አዳግያን ክፍል ማህበረ ቂርቆስ የ35ኛ ዓመት ክብረ በዓሉ ከነሐሴ 15
+4
ዜና ፍኖተ ወንጌል📺 ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ የአሰላ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰ/ት/ቤት ህጻናት እና አዳግያን ክፍል ማህበረ ቂርቆስ የ35ኛ ዓመት ክብረ በዓሉ ከነሐሴ 15/2018 ዓ.ም ጀምሮ በድምቀት ሲከበር ቆይቶ በዛሬውም ዕለት የደብራችን አስተዳዳሪ መላከ ፀሀይ አባ ልሳነወርቅ ወርቁ ፣ የደብራችን የአቋቋም መምሕር ርዕሰ ደብር አምደ ብርሃን ፣ የደብራችን የሰበካ ጉባኤ አባላት ፣ የህጻናቱ ወላጆች እና በአሰላ ከተማ የሚገኙ ሰንበት ት/ቤት ጥሪ የተደረገላቸው የህጻናት ክፍል አባላት በተገኙበት በታላቅ ድምቀት በዛሬው ዕለት ተከብሮ ውሏል። ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ ⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨ የቴሌግራም ቻናል:-  T.me/Finote_Wongel

" እግዚአብሔር፥ ቅዱሳንን ስላገለገላችሁ እስከ አሁንም ስለምታገለግሉአቸው፥ ያደረጋችሁትን ሥራ ለስሙም ያሳያችሁትን ፍቅር ይረሳ ዘንድ ዓመፀኛ አይደለምና።" ዕብራውያን 6:10 🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓
+1
" እግዚአብሔር፥ ቅዱሳንን ስላገለገላችሁ እስከ አሁንም ስለምታገለግሉአቸው፥ ያደረጋችሁትን ሥራ ለስሙም ያሳያችሁትን ፍቅር ይረሳ ዘንድ ዓመፀኛ አይደለምና።"             ዕብራውያን 6:10 🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓 🎓🎓🎓 እንኳን ደስ አላችሁ🎓🎓🎓 🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓   በቀን 16/12/2018  ዓ.ም የሰንበት ት/ት ቤታችን እንቁ  አገልጋይ የሆኑት መዘ/ት ልደት ታደሰ እና ዲ/ን በሀይሉ ለገሠ በከተማችን ከሚገኘው ከቀነኒሳ ቴክኒክ እና ሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጅ ተመርቀዋል። ውድ እህታችን እና ወንድማችን እንኳን ደስ አላችሁ መልካም የስራና የአገልግሎት ዘመን እንዲሆንላችሁ  የፍኖተ ወንጌል ሰንበት ትምህርት ቤት አገልጋይ ወንድም እሕቶቻቹ  እንመኝላቹሀለን። ✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨ የቴሌግራም ቻናል:-  T.me/Finote_Wongel

እንኳን ለእመቤታችን ዕርገት በዓል በሰላም አደረሳችሁ! የእመቤታችንን ጣዕሟን በአንደበታችን ፍቅርዋን በልቦናችን ያሳድርብን ከልጅዋ ከወዳጅዋ ከመድኃኔዓለም ከኢየሱስ ክርስቶስ ታማልደን። ✨⚡️✨⚡️✨⚡
እንኳን ለእመቤታችን ዕርገት በዓል በሰላም አደረሳችሁ!    የእመቤታችንን ጣዕሟን በአንደበታችን ፍቅርዋን በልቦናችን ያሳድርብን ከልጅዋ ከወዳጅዋ ከመድኃኔዓለም ከኢየሱስ ክርስቶስ ታማልደን። ✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨ የቴሌግራም ቻናል:-  T.me/Finote_Wongel

"ጻድቅም በጭንቅ የሚድን ከሆነ ዓመፀኛውና ኃጢአተኛው ወዴት ይታይ ዘንድ አለው?" 1ኛ ጴጥ 4÷18

ኑ የልጆችዎን ፍሬ ይመልከቱ! ✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨ የቴሌግራም ቻናል:- T.me/Finote_Wongel
ኑ የልጆችዎን ፍሬ ይመልከቱ! ✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨ የቴሌግራም ቻናል:-  T.me/Finote_Wongel

✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ ታላቅ እና ልዩ አመታዊ የምስረታ ክብረ በዓል 🌼ከነሐሴ 15 እስከ 16/2018 ዓ/ም 🌼 በአሰላ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ትምህት ቤት ማ
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ ታላቅ እና ልዩ አመታዊ የምስረታ ክብረ በዓል 🌼ከነሐሴ 15 እስከ 16/2018 ዓ/ም 🌼 በአሰላ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ትምህት ቤት ማህበር ቂርቆስ ህጻናት እና አዳጊያን ክፍል  የተመሰረተበትን 35ኛ አመት ክብረ በዓል ያከብራል። 👉 በ15 ከቀኑ 11 ሰዓት በ አውደምህረት 👉በ16 ከቀኑ 10:30  በ አውደምህረት 👉በ17 ከቀኑ 6:30 ጀምሮ  በቅፅር ጊቢ ውስጥ በተዘጋጀ ድንኳን መርሃ ግብሮቹን አዘጋጅቶ ይጠብቆታል ። እርሶ እንዲገኙ ፍኖተ ወንጌል ሰ/ት/ቤት ማሕበረ ቂርቆስ ህጻናት እና አዳግያን ክፍል ጥሪውን ያስተላልፋል። ✨✨✨✨✨✨✨✨✨
ኑ ልጆቻችሁ ያፈሩትን ፍሬ ተመልከቱ።
✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨ የቴሌግራም ቻናል:-  T.me/Finote_Wongel

ታቦር አበራ ታቦር አበራ ምድርን ከደናት ያደመና እንቅልፍ የለንም ታላቅ ነጎድጕድ ሆኗልና አነቃን ለምስጋና
አዝ       
ሙሴም የቀደመው ሰዉ  ኤልያስ ኃይለኛው ተገኝተዋል በታቦር ምስክርህ ሆነው እኛም ከገናናው ክብር ያባቱን ቃል ሰምተናል በረዶ ሆኗል ልብሱ እፁብ እፁብ ብለናል
አዝ
 
ቃል ገብተህልኝ ነበር ልታሳየኝ ክብርህን ንገስ ከሞት ገስግሰህ አይቸሃለሁ አሁን የሳት ፈረሶች አሉህ ታዋጊው የኔ ጌታ አርሙኒየም ደስ አለው ስሳራን ስለመታ
አዝ
እጠብቅሃለሁኝ በምታልፍበት ቆሜ መብራቶቼን አብርቼ ነጩን ልብስ ተሸልሜ የዳዊት ልጆይ ግባ ኢየሱስ ወደቤቴ ብልኤል እልሀለሁ ድናለች ሰውነቴ
አዝ     
ሁሉንም ብታከብር ሁሉንም ብትምረው ማነው ቸርነትህን የሚከለክለው ጠዋትም የተጠራ አምሽቶ የገባው ሆነዋል ባለዋጋ ከበዛው ስጦታው
አዝ     
የረዳኸው ይናገራል ያሰበከው በሕይወቱ አቤነዘር እያለ ይዘምር ባንደበቱ በደስታየም ቀን አለህ አይሃለሁ ከጎኔ ከነጋር አልቅሰሃ አሳዝኖህ ሀዘኔ ዘማሪት ምርትነሽ ጥላሁን ✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨ የቴሌግራም ቻናል:-  T.me/Finote_Wonge

🍁🍁🍁✨🍁✨🍁✨🍁🍁🍁 ✨ደብረ ታቦር✨
ነሐሴ ዐሥራ ሦስት በዚች ቀን ክብር ይግባውና የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ታላቅና ክቡር በዓል ነው።
በዚች ቀን መድኃኒታችን ሦስቱን ደቀ መዛሙርቶቹን ጴጥሮስን፣ ያዕቆብንና ዮሐንስን ይዞ ወደ ታቦር ተራራ ላይ አወጣቸው። መልኩም በፊታቸው ተለወጠ ልብሱም እንደ በረዶ ነጭ ሆነ። ስለ እነርሱም ጌታችን የሰው ልጅ በጌትነቱ ሲመጣ እስከሚያዩት ድረስ በዚህ ከቆሙት መካከል ሞትን የማይቀምሱት አሉ አለ። ሰዎች ሁሉ እርሱ ለሙሴ ጌታውና ከሞት ያስነሣው እንደሆነ ለኤልያስም ፈጣሪው እንደሆነና ካሳረገበትም ያወረደው እርሱ እንደሆነ ያውቁ ዘንድ እነሆ ከጌታ ከኢየሱስ ጋራ እየተነጋገሩ ሙሴና ኤልያስ ወደርሱ መጡ። ስለዚህም ጴጥሮስ ጌታችንን እንዲህ አለው አቤቱ በዚህ ትኖር ዘንድ ትወዳለህን ሦስት ሰቀላዎችንም አንድ ላንተ፣ አንድ ለሙሴ፣ አንድ ለኤልያስ እንሠራ ዘንድ። 🍁✨🍁✨ በዚህም ቃል የደካማነትና የትሕትና ምልክት አለበት። ደካማነት የተባለ ጴጥሮስ ጌታችን ከሰማይ የወረደበትን ሥራ ትቶ በተራራ ላይ ይኖር ዘንድና ራሱን የሚሠውርበትን ቤት ይሠራለት ዘንድ የተናገረው ነው። ትሕትና ያልነውም ጴጥሮስ ለራሱና ለባልንጀሮቹ ሐዋርያት ቤት ይሠራ ዘንድ ስለ አላሰበ ነው። ራሱንና ባልንጀሮቹ ሐዋርያትን እንደ ባሮች ነቢያትን ደግሞ እንደ ጌቶች አድርጎ አስቧልና። ሰለ ሐዋርያትም የእውቀት ማነስ አታድንቅ በዚያን ጊዜ ፍጹማን አልሆኑምና። እንዲህም በሚልበት ጊዜ ጌታችን በሰው እጅ የተሠራ ማደሪያን የማይሻ መሆኑን ለጴጥሮስ ያሳየው ዘንድ እነሆ ደመና ጋረዳቸው። የጌታችንን ጌትነቱን የሚገልጽ በሐዋርያትም ልቡና እምነትን የሚያጸና እንዲህ የሚል ቃል ከደመና ውስጥ መጣ። ይህ የምወደው በእርሱ ደስ የሚለኝ ልጄ ይህ ነው እርሱንም ስሙት። ሙሴና ኤልያስም ከእርሱ ጋራ ሲነጋገሩ ተሰሙ ስለ ርሱ መምጣት የተናገሩትን ትንቢታቸውንም በቸርነቱ አረጋገጠ። ወደ ተራራ ላይ በመውጣቱም ነቢያትና ሐዋርያት ደስ አላቸው። 🍁✨🍁✨ ሁለተኛም የአብን ቃል በሰሙ ጊዜ ከእነርሱ ሥውር የነበረ የወልድ ዋሕድን በእውነት ሰው መሆን በዚያን ጊዜ ተረዱ ያን ጊዜ የጌትነቱ ክብር ተገልጦአልና። ሐዋርያትም ፍጹም አምላክ ፍጹም ሰው የሆነ እርሱ ሙሴን ከመቃብር ያስነሣው ኤልያስንም ያሳረገው አውርዶም ያመጣው እርሱ እንደሆነ አወቁ። ከእርሱ በቀር ማንም ማን የሙሴን መቃብር የሚያውቅ የለምና ከዐሳረገው ከእርሱ በቀር ማንም ማን ኤልያስ ያለበትን የሚያውቅ የለምና። በሰማይና በምድር ሥልጣን ካለው ከሁሉ ጌታ በቀር ሙታንን አድኖ ሊአስነሣቸው ማንም አይችልም። ደብረ ታቦርም የቤተ ክርስቲያን አምሳል ሆነች ከብሉይና ከሐዲስ በውስጧ ሰብስባለችና። የአብንም ቃል በሰሙ ጊዜ በግምባራቸው ፍግም ብለው በምድር ላይ ወደቁ እንደ ሙታንም ሆኑ። ከዓለም አስቀድሞ ከእርሱ ጋራ በህልውና እንዳለ ለልጁ አብ ምስክርን ሆነ ወዲያውኑ ሙሴ ወደ መቃብሩ ኤልያስም ወደ ቦታው ተመለሱ።
ሐዋርያትንም በአነቃቸው ጊዜ ከብቻው ጌታችን በቀር ማንንም አላገኙም። ከባሕርያችን የተዋሐደና ሥጋችንን የለበሰ ፍጹም አምላክ እንደሆነ በዚህ ሐዋርያት አስተማሩ።
🍁✨🍁✨ እንግዲህ እናስተውል ሰው ካልሆነ ቅዱስ ገብርኤል እመቤታቸንን ድንግል ማርያምን በአበሠራት ጊዜ እግዚአብሔር ከአንቺ ጋራ ነው እንዴት አላት። አምላክ ካልሆነስ ለመንግሥቱ ፍጻሜ የለውም እንዴት አላት። ሰው ካልሆነ በበረት እንዴት አስተኙት። አምላክስ ካልሆነ መላእክት ከሰማይ ወርደው ለእግዚአብሔር በሰማያት ምስጋና በምድርም ሰላም ለሰውም ግዕዛኑ ሊሰጠው እያሉ እንዴት አመሰገኑ። ሰው ካልሆነ ዮሐንስ በውኃ እንዴት አጠመቀው አምላክስ ካልሆነ አልዓዛርን ከመቃብር እንዴት ሊያስነሣው ቻለ። ይህ ተቀዳሚ ተከታይ የሌለው እንድ ልጅ አካላዊ ቃል እግዚአብሔር እርሱ ያለ መለወጥ ያለ መለየት አንድ አካል አንድ ባሕርይ በመሆን ፍጹም አምላክ ፍጹም ሰው እንደሆነ እናምንበታለን። እርሱም ከአብ ከመንፈስ ቅዱስ ጋራ ሁል ጊዜ አንድ ህላዌ ነው ዛሬም ዘወትርም ለዘላለሙ አሜን። 📚ስንክሳር ዘወርኀ ነሐሴ 13 🍁🍁🍁✨🍁✨🍁✨🍁🍁🍁 ⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨ የቴሌግራም ቻናል:-  T.me/Finote_Wonge

" በመከራችን ሁሉ እግዚአብሔር የትዕግስት ፍፃሜ ይሰጠን ዘንድ ስለነፍሳችን ትዕግስት እንማልዳለን። "                በእንተ ቅድሳት

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! ❤️ ነሐሴ (7) ቀን ❤️ እንኳን ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም የፅንሰት በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላም አደረሰን!                 ✝️ ✝️ ✝️ 📖 የእመቤታችን የፅንሰት አጭር ታሪክ ጻድቁ ኢያቄም እና ቅድስት ሐና በ እግዚአብሔር ፊት በቅንነትና በደግነት የሚኖሩ እውነተኛ አማኞች ነበሩ። ነገር ግን በጋብቻ ዘመናቸው ልጅ ባለመውለዳቸው ምክንያት እጅግ ያዝኑ ነበር። በወቅቱ የነበሩ የእስራኤል ልጆችም “ልጅ ያልወለደ ከእግዚአብሔር በረከትን ያጣ ነው” እያሉ ያቃልሏቸውና ይነቅፏቸው ነበር። ቅዱሳኑ ግን በሰው ነቀፌታ ተስፋ ሳይቆርጡ፣ “የአባቶቻችን የእስራኤል አምላክ ሆይ! ለአይናችን ማረፊያ፣ ለልባችን ተስፋ የሚሆን ፍሬ ስጠን” እያሉ ዘወትር በጾምና በጸሎት ወደ አምላክ ይለምኑ ነበር። ከዕለታት አንድ ቀን ቅድስት ሐና በቤቷ አትክልት ስፍራ ሳለች፣ አንዲት ርግብ ከልጆቿ ጋር ስትጫወት ተመለከተች። በዚያን ጊዜ ልቧ ተነክቶ፦ “አቤቱ ጌታዬ! ለዚች ግእዛን ለሌላት እንስሳ ልጅ የሰጠህ አምላክ፣ ምነው ለኔ ልጅ ነሳኸኝ?” ብላ ምርር ብላ አለቀሰች። ከዚህ በኋላ ቅዱስ ኢያቄምና ቅድስት ሐና ወደ ሊቀ ካህናቱ ዘካርያስ ዘንድ በመሄድ ታላቅ ስዕለት ተሳሉ፦ “ወንድ ልጅ ብንወልድ ተምሮ ቤተ እግዚአብሔርን እንዲያገለግል፤ ሴት ልጅም ብንወልድ ውኃ ቀድታ፣ መሶበ ወርቅ ሰፍታ፣ መጋረጃ ፈትላ ካህናትን አገልግላ እንድትኖር ለእግዚአብሔር ቤት አገልጋይ እናደርጋለን” አሉ፤ ሊቀ ካህናቱ ዘካርያስም ጸሎታቸውን አሳርጎ ባረካቸው።
ሐምሌ 30 ቀን ቅዱሳኑ አስደናቂ ራእይ አዩ፦ ጻድቁ ኢያቄም፦ “ሰባት ሰማያት እንደ መጋረጃ ተገልጠው፣ ከላይኛው ሰማይ ነጭ ወፍ ወርዶ በራሴ ላይ ሲቀመጥ አየሁ” አለ። ቅድስት ሐና፦ “እኔም ነጭ ርግብ መጥታ በራሴ ላይ ወርዳ፣ በጆሮዬ ገብታ በማኅፀኔ ስትተኛ አየሁ” አለችው። ይህንን ራእይ ካዩ በኋላ “ፈቃደ እግዚአብሔር ይሁን” ብለው ዕለቱን አልጋና ምንጣፍ ለይተው ለሰባት ቀን ያህል በጸሎት ተለይተው ሰነበቱ።
በሰባተኛው ቀን የእግዚአብሔር መልአክ ቅዱስ ገብርኤል ለጻድቁ ኢያቄም በተራራ ላይ ሲጸልይ በተገለጸለት ጊዜ፦ “ሚስትህ ሐና ትፀንሳለች፤ ዓለሙ ሁሉ ደስ የሚሰኝባትን፣ ለብዙዎች የሕይወት ብርሃንና ድኅነት የምትሆን ሴት ልጅ ትወልድልሃለች” ሲል አበሰረው። መልአኩ ለቅድስት ሐናም ተገልጦ የጌታን ፈቃድ ነገራት። በብስራተ መልአክና በፈቃደ እግዚአብሔር፣ እሁድ ዕለት በነሐሴ 7 ቀን ከሰው ሁሉ የበለጠች፣ ከመላእክትም የከበረች፣ የዓለም ሁሉ መመኪያ የሆነችው አምላክን የምትወልደው እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በማኅፀነ ሐና ተፀነሰች።                      ✝️ ✝️ ✝️ የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም አማላጅነትና በረከት፣ የቅዱስ ኢያቄምና የቅድስት ሐና ጸሎት አይለየን።🙏 ⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨ የቴሌግራም ቻናል:-  T.me/Finote_Wonge

አሁንም የእግዚአብሔር የጸጋ ልጆችና የቅድስት ቤተ ክርስቲያን ማኅበሮች ሆይ ይኽቺን የተባረከችና የተመረጠች ሙሽራ የወለዱልንን ኢያቄምንና ሐናን እናመስግናቸው የማትነቀፍ የእስራኤል ድንግልን የተባረከ
አሁንም የእግዚአብሔር የጸጋ ልጆችና የቅድስት ቤተ ክርስቲያን ማኅበሮች ሆይ ይኽቺን የተባረከችና የተመረጠች ሙሽራ የወለዱልንን ኢያቄምንና ሐናን እናመስግናቸው የማትነቀፍ የእስራኤል ድንግልን የተባረከችዋን ፍሬ ያፈራችበትን ንጽሕት የምትኾን የሩካቤያቸው ዕለት እንደምን ያለች ዕለት ናት ከይሁዳ ወገን ለኾነችው ንጽሕት ርግብ መፀነስ በእግዚአብሔር ፈቃድ የተደረገ የጾታዊ ተዋሕዷቸው ቀን ይኽቺ እንዴት ያለች የተመረጠች ቀን ናት፤ ለንጉሥ ማደሪያ አዳራሽ መመሥረት የተደረገባት (የኾነባት) የደስታ ቀን እንዴት ያላት ቀን ናት። (አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ አርጋኖን ዘረቡዕ)

"እግዚአብሔር በተነሣ ጊዜ ምን አደርጋለሁ ? በጎበኘኝ ጊዜ ምን እመልስለታለሁ ?" ኢዮብ 31÷14 ⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨ የቴሌግራም ቻናል:- T.me/Finote_Wonge
"እግዚአብሔር በተነሣ ጊዜ ምን አደርጋለሁ ? በጎበኘኝ ጊዜ ምን እመልስለታለሁ ?"   ኢዮብ 31÷14 ⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨ የቴሌግራም ቻናል:-  T.me/Finote_Wonge

የምስራች የምስራች የምስራች ዜና ዘማሪት ሃና ኃይለ መስቀል ለቅኖች ምስጋና ይገባል ከሁሉ አስቀድሞ ሁሉን ላደረገ ሲሰጥ የማይሰስት ሰጥቶ የማይነጥፍበት ሁሉ በርሱ ለእርሱ የሆነለት አምላካችን ቅዱስ እግዚአብሔር ስላደረገልን መልካም ነገር ሁሉ ስሙ ለዘለአለሙ የተመሰገነና ከፍ ከፍ  ያለ ይሁንልን!!! ከሐምሌ 19/2018 ዓ/ም ጀምሮ  በአሰላ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ትምህርት ልዩ ልዩ ሚዲያዎችና በቅን እህት በወንድሞቻችን የግል ማህበራዊ ሚዲያ ላይ በቅዱስ ገብርኤል አመታዊ የንግስ ክብረ በዓልና በተለያዩ በአሰላ ከተማ አድባራት አውደምህረቶች ላይ በዚህ በምስሉ ላይ የምትመለከቷት የሰንበት ትምህርት ቤታችን አገልጋይ የሆነችው እህታችን ዘማሪት ሰርክአዲስ( ሃና )ኃይለ መስቀል በመተንፈሻ አካሏ በደረሰባት የጤና እክል ምክንያት ጥቁር አንበሳ እስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ባደረገችው ምርመራ የልብ ቀዶ ጥገና ማድረግ እንዳለባት ስለተነገራት ህክምናውን በታዝማ ሆስፒታል ለመፈጸም ደግሞ 1,300,000.00 (አንድ ሚሊየን ሶስት መቶ ሺህ ብር) መጠየቋን ጠቅሰን መላ ኢትዮጵያውያን ለእህታችን ማሳከሚያ የሚሆን እጅ እንድትዘረጉልን ጠይቀን እናንተም ደግ ኢትዮጵያዊያን ከጉለታችሁም ላይ ቢሆን የምትችሉትን ሁሉ እንዳደረጋችሁልን ይታወቃል ለዚህም ላቅ ያለ ምስጋናችንን እናቀርባለን መድኃኔዓለም ከክፉ ነገር ሁሉ እንዲጠብቃችሁ ጸሎታችን ነው። ስለሆነም እግዚአብሔር አምላካችን የእናንተን ጸሎት ተቀብሎ እስካሁን በሰበሰብነው ብር ላይ ሞልቶ የሚያሳክም ወዳጅ ዘመድ ስለተገኘ አሁን በዚህ ሳምንት ውስጥ ወደ ህክምና ለመሄድ ዝግጅቷን ስለጨረሰች ሁላችሁም ህክምናው በተሰካ ሁኔታ ተሰርቶላት በሙሉ ጤናዋ ጠብቆ ፍጻሜዋን እንዲያሳምርላት በጸሎት እንድታስቧት ስንል በአክብሮት እናሳስባለን። የአሰላ ደ/መ/ መ/ዓ/ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ትምህርት ቤት ⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨⚡️✨ የቴሌግራም ቻናል:-  T.me/Finote_Wonge