1 086
Subscribers
-124 hours
-47 days
-2730 days
Posts Archive
1 086
አገዛዙ በየወረዳው ውስን ቀበሌዎች ላይ ነው የተወሸቀው !
የአፋብን ተቀዳሚ ምክትል ሊቀመንበር ራስ አርበኛ መከታው ማሞ !
ማስታወሻ:- ራስ የሚለው ነባር ወታደራዊ ማዕረግ ስለፀደቀ መጠቀም የምትችሉ መሆኑን በዚሁ አስታውቃለሁ።
1 086
የጥንቃቄ መረጃ
ከቤንሻንጉል ጉምዝ እና ወለጋ የነበሩ የመከላከያ ዕዞች ወደ አማራ ክልል እንዲገቡ ትዕዛዝ ተሰጥቷል።
አንደኛው ወለጋ ደዴሳ የሚባል ቦታ ላይ የነበረ ሠራዊት ተጠርንፎ ጉዞ ጀምሯል።
ሁለተኛው ደግሞ ከጉምዝና ወለጋ መካከል ሶጌ በርካታ ተጠርንፎ ለእንቅስቃሴ ዝግጁ ሆኖ ይገኛል።
የመጀመሪያው ኃይል ወደ ጎጃም ቀጠና የሚሰማራ ሲሆን በወለጋ በአንገር ጉትን አባይ በረሃ አድርጎ ማረፊያው ቡሬ ነው።
ከቤንሻንጉል የሚነሳው ደግሞ በሸዋ ቀጠና የሚሰማራ ሲሆን በወለጋ በአምቦ አዲስ አበባ ተጉዞ መዳረሻውን ደብረብርሃን ያደርጋል።
ግማሹ ትራንስፖርት እየጠበቀ የሚገኝ ሲሆን ግማሹ ተንቀሳቅሷል።
በሁሉም ቀጠናዎች ጥንቃቄ ይደረግ !
1 086
የምርጫ ቦርድ ውሳኔ እና የወልቃይት አቋም!
ሂደቱ በወልቃይት ምርጫ የመካሄድ እድሉን ያጠበበ ሆኗል።
የብልፅግና ፖለቲካ ማስፈፀሚያ ተቋም የሆነው የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ 7ተኛውን ሀገራዊ ምርጫ ለማካሄድ ይፋ ባደረጋቸው የምርጫ ጣቢያዎች ላይ የአማራን ነባርና ታሪካዊ ርስቶች በትግራይ ክልል አካቶ አቅርቧቸዋል።
ይህ ከብልፅግና ጋር ሆነን ወልቃይትን እንጠብቃለን ለሚሉት ትልቅ የማንቂያ ምልክት ነው።
ብልፅግና "ወልቃይት" የአማራም ሆነ የትግሬ ጉዳዩ አይደለም፤ ህወሃትም ቢሆን ወልቃይትና ራያን ከተቆጣጠረ የብልፅግናውን አገዛዝ የመውጋት ፍላጎት የለውም። የህወሃት የመጨረሻ ፍላጎት ወልቃይትና ራያን በመቆጣጠር መደራደርና እነዚህን ታሪካዊ ርስቶች የራሱ ግዛት አካል በማድረግ መገንጠል ነው።
ስለዚህ ከሁለቱም አካል ጋር የሚደረግ ግንኙነት ልክ የማይሆነውም ከዚህ አኳያ ነው።
ፖለቲካዊ ገለልተኛ ተደርጎ የሚቆጠረው ምርጫ ቦርድ ተጠሪነቱ ለተወካዮች ምክር ቤት ቢሆንም ሁለቱንም ተቋማት ለፖለቲካ ማስፈፀሚያነት የሚጠቀምባቸው ግን ፀረ- አማራው ብልፅግና ነው።
አንዳንድ ጊዜም ምርጫ ቦርድ ገለልተኛ መስሎ የሚወስናቸውን ውሳኔዎችም አገዛዙ ተአማኒ ነፃና ፍትሀዊ ምርጫ አድርጌያለው ለማለት በተወካዮች ምክር ቤቱ በኩል የውሳኔ ለውጥ እንዲያደርግ ያደርጋል።
የወልቃይት ጠገዴ የአማራ ማንነትና ወሰን አስመላሽ በበኩሉ ደግሞ ከህዝብ ፍላጎት ውጪ የሚደረግ ማንኛውንም እንቅስቃሴን እንደማይቀበል ዛሬ ባወጣው መግለጫ አሳውቋል።
ወደ ዋናው ነጥብ ስንገባ ብልፅግና በተወካዮች ምክር ቤት በኩል የውሳኔ ለውጥ ካላደረገ በስተቀር፤ ምርጫ ቦርድ ሪፈረንደም ባልተካሄደባቸው አካባቢዎች ላይ በነባሩ የምርጫ ቦርድ ካርታ እንደሚሰራ ገልፆ ወደ ትግበራ መግባቱን የደረሰኝ መረጃ ያመለክታል።
በዚህ ብልፅግናዊ መንገድ ከሆነ ለወልቃይት፣ ጠለምትና ራያ የምርጫ ታዛቢ፣ ፀጥታ ዘርፍና የመሳሰሉት የምርጫ አስፈፃሚዎች ከትግራይ እንደሚመድብ እየነገረን ነው ማለት ነው። (አይሆንም እንጂ አስቂኝም አሳዛኝም ነው 😁)
በጥቅሉ ምርጫ ቦርድ የሰጠው የተሳሳተ ስያሜ ላይ ማሻሻያ ካላደረገ ወይም ብልፅግና ራሱ የትግራይ ሃይል አካባቢውን እንዲቆጣጠር ካልፈቀደ በቀር በዚህ ሂደት በወልቃይት ምርጫ የሚደረግበት ዕድል ያለ አይመስልም።
የህወሃትን የወረራ ዕቅድን በተመለከተ ግን ፌደራል መንግስቱ፣ የአረጋ ከበደው መንግስትና የአገኘሁ ተሻገር ፌደሬሽን ምክር ቤት ዝም ጭጭ ያሉበት ሁኔታ ጠርጥር ከጎንፎ ውስጥ ስንጥር አይጠፋም እንድንል ያደረገ ነው።
ይህ ባለበት ሁኔታ ፋኖ አቋሙን እንዲያሳውቅ የሚጠይቁ ፖለቲከኛ መሳይ ካድሬዎች ቢኖሩም ፋኖ ጊዜውን ጠብቆ በሚያሳልፈው ውሳኔ በአማራ ነባርና ታሪካዊ ርስቶች ላይ ዘላቂ ግብ ላይ ባላተኮረ ፖለቲካዊ ውሳኔ ታሪካዊ ስህተት እንዳይሰራ መጠንቀቅ አለበት።
ህወሃትን ከጌታቸው ረዳ ስምረት ጋር በማነፃፀር በይፋ ፖለቲካ ወዳጅነቴን እወቁልኝ የሚለው የፖለቲካ ስንኩልም ትግሉን ገደል እንዳይከተው መጠንቀቅ ያስፈልጋል።
የብልፅግና እና ህወሃት ፖለቲካዊ ትወና የበዛበት ጦርነት ከጀርባው ያዘላቸው ስጋቶች ቢኖሩትም፤ የወልቃይት ጉዳይ የግለሰቦችና የአስተዳዳሪዎች ወይም የለዘብተኛ ካድሬዎች ጉዳይ ሳይሆን የህዝብና የታሪክ ጉዳይ መሆኑንም መዘንጋት አይገባም።
የመውጫ ጥያቄ:- ጎንደር ላይ የተለጠፈው የግጭት ምሁርና አስከጂ ኮሚቴ ግኔ ከብልፅግና ጋር ሆኖ የምርጫ ቦርድ ውሳኔን ይቀለብሰው ይሆን የምናየው ይሆናል ????
ወልቃይት፣ ጠለምት፣ ራያ፣ አዲስ አበባ፣ ደራ ፣መተከል 💪💪💪
1 086
!!!!
የአማራ ፋኖ ራሱን ችሎ መቆሙን ከሚያረጋግጥባቸው ዋነኛ መንገዶች አንዱ፤ በአማራ ህዝብ ነባርና ታሪካዊ ርስቶች ላይ በሚይዘውና በሚወስደው አቋም ነው።
ነገር ግን አገዛዙ ለአማራ ህዝብ አስመስሎ በሚያዘጋጃቸው አቦ ሰጥ የወጥመድ አጀንዳዎች ሁሉ ከብልፅግና ሚሊሻ እየተንጋጋ የሚሰለፍ አርበኛ ሠራዊት የለም።
ይልቁንም ፋኖ የአማራ ታሪካዊና ነባር ርስቶችን በተመለከተ፤ ወቅታዊ የአሰላለፍ ሁኔታና የጠላትን የፍላጎት ደረጃ በመመዘን፤ በራሱ መንገድ ያስከብራል፤ አቋም ይይዛል። ይህ እንዲሆን እኛም ውስጠ ድርጅታዊ ትግል እናደርጋለን።
በአንድ በኩል አጀንዳው ወልቃይትን ከማስጠበቅ ባሻገር የአማራ ፋኖ ድርጅታዊ አንድነትን ማፍረስ ኢላማ ያደረገ ብልፅግናዊ ተልዕኮ ነው .... ( ይህ ቀሽሙ ሙከራ ነው)
በሌላ በኩል ደግሞ ከወያኔ ተፈጥሯዊ ባህሪ የተነሳ የሚነሳ ተገቢ ሰጋት እና አፍቅሮተ-ወያኔ የተጠናወታቸው፤ አማራዊ ስነ-ልቦናቸው የተገፈፈ የባህር ማዶ ሻርኮች በትግሉ ውስጥ የፈጠሩት የፍላጎት ተቃርኖ ጫና ነው።
ይህን የከሸፈ የጠላት አጀንዳ አፋብን እንደ ድርጅት አስቸኳይ ግምገማና ጥናት በማድረግ የውስጥ ውሳኔ ወይም ይፋዊ ውሳኔ ሊያሳልፍበት የሚገባው ጉዳይ መሆኑን ግን አፅንኦት ለመስጠት እንወዳለን።
ከዚህ ውጪ የብአዴን ቤተኛ ባይተዋሮችን ጩኸት ተፈርቶ የሚሰጥ ምላሽ የለም፤ !!
አማራ ያሸንፋል ...
✍️ ያሬድ ሙሉነህ
1 086
ሃገራችን ጎንደር ወንዛችን ተከዜ !
መቅድም ....
የአማራ ህዝብ ከግማሽ ክፍለ ዘመን የተሻገሩ ግልፅና ተጨባጭ አደጋዎች ገጥመውት የነበረ ቢሆንም በተለየ ሁኔታ ከ1983 ወዲህ ግን በወያኔና በኦህዴድ በማንነቱ የደረሰበት የዘር ማፅዳት ወንጀል በሁኔታዎች መለዋወጥ የሚታለፍ ጉዳይ አይደለም።
አማራዊ ማንነትን ወንጀል ያደረገው ህወሃት ስልጣን በተቆናጠጠ ማግስት አማራን ከማዕከላዊ መንግስቱ መግፋትን ጨምሮ መዋቅራዊ ጥቃት ፈፅሟል፤ ታሪካዊና ነባር ርሰቶቸን ያለ ፖለተካ ይሁንታ ወስዷል፤ አማራዊ ማንነትን ለማጥፋት ስውርና ግልፅ በሆነ መንገድ ሥርዓታዊ ጥቃቶችና በደሎችን ፈፅሟል።
ይህንን ህወሃታዊ እሳቤ በሪፎርም ስም እንዲረከብ የተደረገው ኦህዴድ ብልፅግና ደግሞ ከቀደመው ጥፋት በከፋ መልኩ በአማራ ህዝብ ላይ ግልፅ ጦርነት ከፍቶ ከፍተኛ ውድመት እያደረሰ ይገኛል።
ለዚህም ነው ኦህዴድም ሆነ ህወሀት የአማራን የአገር ባለቤትነት የማሳጣት የጥፋት ፕሮጀክቶች በሕግና በመዋቅር ደረጃ ሲፈፅሙና ሲያስፈፅሙ የኖሩ ልዩነት የሌላቸው ቡድኖች ናቸው የምንለው።
** ዝርዝር ጉዳይ ...
በወልቃይት ጉዳይ የአማራ ወጣት ተሰፍሮ የማያልቅ ዋጋ ከፍሏል። ሐምሌ 5 የተቀሰቀሰው የትግል ችቦ ተከትሎ በአራቱም የአማራ አፅመ ርስቶች ለነፃነት የወጡ እልፍ ወጣቶችን የህይወት ዋጋ አሳጥቷል።
ጎንደር፣ ጎጃም፣ ወሎና ሸዋ ስለ ወልቃይት ብለው ደምተዋል።
በባህርዳር ከተማ ነሀሴ 1/2008 ዓ.ም በተካሄደው ሰላማዊ ሰልፍ ላይም አበበ ገረመውን ጨምሮ ከ90-100 የሚገመቱ ታዳጊ ወጣቶች ወልቃይት ብረሳሽ ቀኜ ትርሰኝ ብለው በአንድ ቀን በህወሃት ኢህአዴግ አፈሙዝ ጎዳና ላይ ለወልቃይት ሲሉ ወድቀዋል። ( የወልቃይትን ጉዳይ ድህረ መንደሬነትን የተቀላቀለው ኃይል በብቸኛ ጠበቃነት እንደሚያስጮኸው የማይሆነውም ለዚሁ ነው)።
ለወልቃይትና ለአማራነት ከትናንት አስከዛሬ ሁሉም አማራ ዋጋ ከፍሏል።
በዚህ መሠል መስዋዕትነትና በአማራ ህዝብ ተጋድሎ ህወሃት ቢወገድም ግን የህዝብን ተጋድሎ የራሳቸው አጀንዳ አድርገው ብቅ ያሉት ኦህዴድና ብአዴን በሪፎርም ስም ብልፅግና የሚል ስርዓት ሲወልዱ የበልግ በጉ ብአዴን ደግሞ ድልዳሉን ከህወሃት ወደ ኦህዴድ ተጋላቢነት ቀይሮ አማራን ማስጨፍጨፉን ቀጥሏል።
የአማራ ፋኖ ትግል በመሰረታዊነት የብሄርተኝነት ስርፀትና የጠራ የመታገያ ሰነድ መፍጠር ባለመቻሉ ለትርጉም ተጋላጭነትና ለጠላት ፍረጃ ምቹ እድሎችን ፈጥሯል። ይህንን በዘላቂነት ለመቋጨት ፋኖ የርስትና የማንነትን ጨምሮ ሌሎች ጉዳዮች ላይ ግልፅና የጠራ የትግል ሰነድ ይፋ በማድረግ ወይም ማብራሪያ በመስጠት የጠላትን አጀንዳ ሊያከሽፈው ይገባል።
የአማራ ፋኖ በወልቃይት ጉዳይ ያለውን ተጨባጭ የህዝብ ድጋፍ እንዳያጣና አጀንዳው የጠላት ፍላጎት ማስፈፀሚያ እንዳይሆን ጥንቃቄ ማድረግ ያስፈልጋል ስንልም ''ወልቃይት'' አሁን በአማራ ፋኖ ትግል ውስጥ ያለው ኃይል በራሱ ዋጋ የከፈለበት ጭምር በመሆኑ ነው።
ትግሉ ያለበት ውስብስብ ጫናና የጠላት ፍላጎት በግልፅ የሚታይ በሆነበት በዚህ ጊዜ፤ ህወሃት ወደ ወልቃይት አይደለም ባሩድ Ballon እንዲያፈነዳ የሚፈቅድ አማራ የለም።
ይህ ሲባል ወልቃይት ላይ ብልፅግና ሌላው አካባቢ የሚሰራው አይነት ፖለቲካዊ ሸፍጥ ሳይኖር ቀርቶ ሳይሆን ወልቃይት ያለበትንና የነበረበትን ፖለቲካዊ ጫናና ዋጋ መረዳት ተገቢ በመሆኑ ነው።
ወልቃይትን ከብልፅግና መዳፍ ፈልቅቆ መልሶ የአማራ ማድረግ የሚችል ሀይል ካለ ሌሎች የአማራ ዞኖች ላይ ከሚደረገው ትግል የተለየ ላያደርገው ይችላል። (መሠረታዊው ጥያቄ ወልቃይት የአማራ ሆኖ መቀጠሉ ላይ ነው። )
ነገር ግን ያንን ለማድረግም አሳማኝና አስተማማኝ የሆነ ለማሳያ የሚቀርቡ የወገን ኃይል ነፃ ያወጣቸው የዞን ከተሞችን በዘላቂነት ተቆጣጥሮ በማስተዳደር ማስመስከር ያስፈልጋል። ቢሆን እንኳን? ለማለት ትግሉ ሊመልሳቸውና ሊያስቀድማቸው የሚገቡ ጉዳዮች አሉ!። ("ቢሆን እንኳን ??!!!!"")
ይህንን ሂደት በዚህ ጊዜ መደገፍ ልክ የማይሆነውም ህወሀት በአቡነ ሰላማ ፀሎትና በተደጋጋሚ የወረራ ዕቅድ ያላገኘውን ለም የአማራ መሬት በችሮታ እንደመስጠት ስለሚቆጠር ነው። ቀድሞ ነገር ህወሃት ወልቃይትንም ሆነ ራያን ሙሉ ለሙሉ የመቆጣጠር ዕድሉን ካገኘ ከአብይ አህመድ አገዛዝ ጋር የሚዋጋበት መሠረታዊ ምክንያት የለውም/ አይኖረውም።
በተለይ ለዚህ ትግል ወልቃይትን የዚህ ትግል አካል ማድረግ ያለው ስትራቴጂካዊና ፖለቲካዊ ጠቀሜታ ሳይታለም የተፈታ ቢሆንም፤ ህወሃት እንዲተኩስ መፍቀድ ግን የተለየ ሂሳብ ማወቅ የማይጠይቅ አክሳሪ መንገድ ነው። ( የአማራን ለአማራ ..)
** ወልቃይትን ላይ ያፈጠጠው ብአዴናዊ አጀንዳና ጎንደር ላይ የተለጠፈው የግጭት ምሁር ሲፈተሽ ..
ወልቃይት ላይ የተለጠፈው ብአዴንና ተረፈ ብአዴን ወልቃይትን ለመተረፊያው መቀስቀሻና ፤ የማያውቀው የህዝብ ልብ ሊሸሸግባት ሙከራ ማድረግ ከጀመረ ሰነባብቷል።
ወልቃይትን ሸራርፎ በነሲብ ሊቸረችረው ሲል በአማራ ህዝብ እጅ ከፍንጅ ተይዞ የከሸፈበት ብአዴን በወልቃይት ጉዳይ ላይ ተለጣፊ ሊሆን ካልሆነ በቀር ዛሬም ነገም ባለቤትነት የለውም።
ወልቃይት የተመለሰው በህዝባዊ ትግል እንጂ በብአዴናዊ የፖለቲካ ስሪት ወይም ጥበብ አይደለም። ወልቃይትን ላይ ውጫዊ ኃይል ጣልቃ እንዲገባ የማንፈቅደውም ለዚሁ ነው።
ነገር ግን ጎንደር ክልል አደርጋለሁ፤ ለወልቃይት የተለየ ጠበቃ ነኝ የሚል ቅዠት የተሸከመው የቀበሌና የግጭት ምሁር ስብስብ፤ ከብአዴናዊ የጥቅም ትስስርና እሳቤ ጋር ገጥሞ አሳሳች አጀንዳዎችን እየፈጠረ በጣት የሚቆጠሩ ለትግሉ የወጡ አርበኞችን የብልፅግና አሮጌ ሚሊሻዎች አድርጓቸዋል።
ይህ የጎንደር አማራ ስነልቦናን ተሸናፊ የማድረግ ብአዴናዊ መንገድ የአማራ ፋኖ ትግልን በተልዕኮ ሲያውኩ የነበሩትን ከማጥራቱ በተጨማሪ በተባዮች ሲፈተን የከረመው የጎንደርን ውስጣዊ አንድነት ግን ከአለት የጠነከረ እንዲሆን አድርጎታል።
የብአዴን የውስጥ ፀብ አስፈፃሚ የሚል ተቀጥላ ሹመት ያለው ይህ ስብስብ ወልቃይትን አጀንዳ አድርጎ የአማራ ፋኖን ገፅታ ለማበላሸት፣ ታጋዮችን ከትግል ለማስከዳት የሚያደርገው ሙከራም የገብርዬና ቴዎድሮስን የመንፈስ አደራ በተከተሉ ሀቀኛ አርበኞች ከሽፏል።
ለወልቃይት ስንቆም የምንቆመው ለአማራነት ነው።
የወልቃይት ጉዳይ የማንም ጉዳይ ሳይሆን የአማራ ጉዳይ ነው!
አማራ ያሸንፋል 💪💪💪💪
1 086
+3
የኢትዮጵያ አየር መንገድ መስራች ንጉሠ ነገስት አፄ ኃይለ ሥላሴ !
በአፄ ሀይለሥላሴ ዘመን የነበሩ የተቋም ግንባታዎች አብዛኃኞቹ ትውልድ እንደ ሀገር የሚኮራባቸው ናቸው። አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ፣ ንግድ ባንክና አየር መንገድን ጨምሮ መሰል ተቋማት የተመሰረቱት በንጉሠ ነገሥት አፄ ኃይለ ስላሴ የንግስና ዘመን ነው።
ገጣሚው ሸዋ "ሰው ይሰራል" እንደ አግዜር አፍርሶ ሲል የተቀኘው ለእርሳቸው ይመስለኛል።
ሸዋ የዘመናዊት ኢትዮጵያ መሀንዲስና ሀገሪቱ ያሏት ተቋሞች ባለ አሻራ ጭምር ነው።
የብልፅግና አገዛዝ በህዝብ ላይ የሚፈፅመውን በደል ለማውገዝ 90 አመት ወደኋላ ተመልሶ ከታሪክ መጣላት የቀደመውን ክብር አያደበዝዘውም። የማይርሱበትን ለመንካት መንጠራራት የሚሆነውም ለዚሁ ነው።
የአባቱን ቢሰጡት ህይወቱ የአባቱን ቢነሱት ሞቱ እንደተባለው' ልክ እንደዛው ነው።
አብይ አህመድን ስርዓተ መንግስት መቃወምና የአማራ ህዝብ ታሪካዊ አሻራ ያረፈባቸው ተቋሞችን መካድ ለየቅል ናቸው።
በድስት መቀቀያ ሲፎክር የነበረ ሁሉ በዘመን መለዋወጥና በስርዓት መቀያየር የማይነኩ መስመሮችን እና ተቋማትን ሲነካ በዝምታ አናልፍም።
ለማስታወስ ያክል :- የአማራን ህዝብ የሚጨፈጭፈው ተቋሙ ሳይሆን ተቋሙን የሚመሩት የኦህዴድ ተረኞች ናቸው።
አስበህ ተራመድ !!!'
1 086
60 የሚሊሻ አባላት 2ብሬንና 45 ክላሽ በመያዝ ፋኖን ተቀላቀሉ።
አንድነቱ በተበሰረ ማግስት በርካታ የአገዛዙ ሰራዊት አባላት እየፈራረሱ ወደ ፋኖ እየተቀላቀሉ እንደሚገኙ ይታወቃል።
ይህ ብቻ ሳይሆን በተለያዩ ቀጠናዎች #ብልፅግና ሲያሳድዳቸዉ የነበሩ ኃይሎች ታጥቀዉ ራሳቸውን ከአረመኔዉ መንግስት ጥቃት ሲከላከሉ የቆዩ፣ በመተከል አዉራጃ ዳንጉር ወረዳ በሻለቃ #ሲሳይ ገነት ሲመሩ የነበሩ 60 የአገዉ ተወላጅ ወንድሞቻችን አባላትና መሪዉ ሻለቃ ሲሳይ ገነት በቀን 14/05/2018 ዓ.ም #2 ብሬን እና ከ45 በላይ ክላሽንኮቭ በመያዝ የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ቴዎድሮስ ዕዝ 105ኛ ኮር 66ኛ ክ/ጦርን በመቀላቀል አረመኔዉን የአብይ አህመድ መንግስት ስርዓት በማዉገዝ እስከመጨረሻው ለማስወገድ ቃል መግባታቸውንም አስታዉቀዋል።
በተመሳሳይ
1ኛ. ከድር አብዲ
2ኛ.ገመቹ ገመዳ
3ኛ. ሀይሉ ሙንየ እንግዳ
4ኛ. ምኒችል ቡችል ፀጋ ከ601ኛ ኮር 52ኛ ክፍለ ጦር እና 6ኛ ዕዝ 605 ኮር 14ኛ ክፍለ በመክዳት ቴዎድሮስ ዕዝ 102ኛ ኮርን ተቀላቅሉ ሲሆን
5ኛ.ጌታው መሌ
6ኛ ታደሰ ደሴ የሚባሉ ምሊሻዎች ደግሞ ከሸበል በረንታ በመውጣት 201ኛ ኮርን ተቀላቅለዋል።
ጋንታመሪዎች የፋኖን አንድነት ሲሰሙ በዛሬው ዕለት እየተቀላቀሉን ይገኛሉ።
፲ አለቃ ደርብ ምስጌ፣ ፲ አለቃ አትርሳው መዝገቡ ፣ ፲ አለቃ ሸጋየ ተሸገር፣ ፲ አለቃ መኳንት አዱኛ የምዕራብ ዕዝ 401ኛ ኮር ቃኝና መሐንዲስ ጋንታ አዛዦች የአማራ ፋኖ አንድነት ምስረታ በፈጠረባቸው ደስታ ከኦሮሚያ ክልል በመነሳት ቀናትን የወሰደ ጉዞ ተጉዘው 206ኛ ኮር 34ኛ ክ/ጦር አብራጅት ሻለቃን ተቀላቅለዋል።
ብልፅግና ካንፕ ያለው ሙሉ በሙሉ እየፈራረሰ ይገኛል። ቀሪዎችም በቡድን ፋኖን ለመቀላቀል ምቹ ሁኔታ እየጠበቁ መሆኑን ማረጋገጥ ተችሏል። በብልፅግና ቤትም ፍፁም መተማመን በመጥፋቱ እየተረበሸ ይገኛል።
አዲስ ትውልድ፣ አዲስ አስተሳሰብ ፣አዲስ ተስፋ!
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን !
አፋብን| ቴወድሮስ ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
ጥር 14/2018 ዓ.ም
1 086
"በሕልውና ትግላችን ውስጥ በባለፉት ጊዜያቶች በነበሩ ችግሮች ዙሪያ የነበሩ መጠላላቶች በይቅር መባባል ሂደት አስተካክለናል። ዲያስፖራውም፣ የሚድያ ደጋፊውም በተመሳሳይ ይቅር ተባብሎ አንድ ግንባር መፍጠር አለበት"
አርበኛ መከታው ማሞ
(የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ተቀዳሚ ምክትል ሊቀመንበር!)
የቴሌግራም ገፃችን👉https://t.me/MerebMedia24
1 086
ብዙዎች የወደቁለትን በርካቶች የሚሰቃዩበትን ትግል እንጠብቀው!
የአማራ ህዝብ ትግል የሚለካው በሚያስመዘግባቸው ወታደራዊና ስትራቴጂክ ድሎች እንጂ በተለመደው የጩኸት መንገድ ወይም ውድቀትን በሌላ ውድቀት በማነፃፀር አይደለም።
በተለይ በሚዲያው መስክ ያለው ድንቁርና አሁንም አልታከመም። ሚዲያው ላይ ላለው የጥፋት ኃይል ደግሞ በከፊል የልብ ልብ የሚሰጠው መሬት ላይ ያለው አመራር ጭምር ነው። ለዚህም ነው ከሀላፊነት ውጪ ሆነው አንዳንዶች በአቅጣጫ የሚበጠብጡት፤ በዚሁ የሚቀጥል ከሆነም ሰጪውንም ተቀባዩንም ስለምናውቀው ወደፊት በድፍረት የምንጋፈጠው ጉዳይ ይሆናል።
ከዚህ አኳያ የአፋብን ህዝብ ግንኙነት መምሪያ ከሚዲያ መረጣ ጀምሮ ትግሉን ሊጎዳ የሚችል የልዩነት አቋም በሚያራምዱ ሚዲያዎች ላይ ቁጥጥር ሊያደርግ ውሳኔ ሊሰጥ ይገባል። ትግል የሚከፋፍሉ ሚዲያዎችን የአማራ ፋኖ ብሄራዊ ንቅናቄ አጋር አድርጎ ያስቀጥላል/አያስቀጥልም የሚለውን አብረን የምናየው ይሆናል።
ቢቻል የድጋፍና የተቃውሞ ጎራ ሸፍኖት ከከረመው ውድቀት ለመማር መሞከር ብልህነት ነው ! እንደ ድርጅትም ጓዳዊ መቀራረብና ተቋማዊ ልምምድን ማዳበር፣ ሀላፊነትን በአግባቡ መወጣት፣ መተማመንን መፍጠር፣ የለየለት መንደሬነትን ማስወገድ ቀጣዩ የቤት ስራ ማድረግ ይገባል።
የዲያስፖራው ያልተማከለ ፍላጎትና መስመር ያለፈ ጣልቃ ገብነትም በተቋማዊነት መገራት አለበት። ትግሉን የሚያስተባብሩ በሁሉም ዘንድ የታመኑ ሀላፊነት የመወጣት ብቃት ያላቸው ውስን ልሂቃንን በጋራ መወከል ይገባል። ትግሉን መሰብሰብና የሚና ክፍፍል መፍጠር ካልተቻለ ተቋም መመስረቱ ብቻ እምብዛም ጥቅም የለውም፤ ተቋም ተቋማዊ ባህሪን መላበስ ይኖርበታል።
ትግሉን ጨርሶ ቀድሞ 4 ኪሎ የገባውን ፣ መሬት ላይ ያለውን ትግል በተጨባጭ የማያውቀውንና የማይረዳውን፣ በራስህ ምድጃ ላይ የሚጥድህን የዘወትር ድንቁርና የተጠናወተው የባህር ማዶ ሻርክ እየሰማህ እንዳትሰምጥ! ሻርክ ሻርክ ነው ይበላሀል እያልኩህ ነው !
አንድነቱ እንዲፈጠር ካለን ቀና ፍላጎት የተነሳ ዝም እንዳልነው ሁሉ ፍፃሜውም ሆነ የቀሩ የቤት ስራዎች እንዲጠናቀቁ በጎ አስተዋፅኦ እያደረግን እንቀጥላለን። ያ ማለት ግን አጀንዳ ለመፍጠር የሚጋጋጡ በተቋም የተከለሉ እባቦችን ዝም እንላለን ማለት አይደለም።
አላማህን ተከተል !
✍️ ያሬድ ሙሉነህ
1 086
በአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ የአፄ አምደ ፂዮን ኮር አመራሮች አንድነቱንና በዓሉን አስመልክቶ ያስተላለፉት መልዕክት:-
#የከተራ_በዓል_አከባበር_ከአፄ_አምደ_ፂዮን_ኮር_ጀግናው_ራንቦ_ክፍለጦር_ጋር🥇🥇
#ድርብ ድርብርብ_በዓል🙏
#እንኳን_ደስ_አላችሁ🥇
1 086
ባንዳነትን የመረጠው ታማኝ የተባለው ኮሎኔል!
በዚህ ትግል ውስጥ ባልተገባ ተቃርኖ ውስጥ ሆነን በታጋይ ስም የማይገባቸውን ቦታና ክብር የሰጠናቸው ሰዎች ቁጥራቸው ቀላል አይደለም።
በዛው ልክ በሁሉም ዘንድ የሚታመኑና በብዙሀኑ የሚወደዱ አርበኞችም አሉ። ከእነዚህ መካከል አንደኛው ኮሎኔል ፈንታሁን ሙሀቤ ሲሆን ያንን የህዝብ ድጋፍና የመታመን አደራ ግን በክህደት ቀርጥፎ በልቶታል።
በእርግጥ ኮሎኔል እጅ ሊሰጥ የነበረው ባንዳው ማስረሻ ሰጤ እጅ ሊሰጥ የነበረ ጊዜ መሆኑን ሁኔታዎች ቢገልፁም ሳይሳካለት በመቅረቱ ለጊዜው ማስረሻን አሳሳች አድርጎ በማቅረብ ሊተርፍ ችሎ ነበር። በቂ ምልክቶች እየታዩ ኮሎኔሉን አፋህድ በቁጥጥር ስር ያላዋለበት ምክንያትም ግልፅ አይደለም። ለነገሩ አማራነት ባፍጢሙ ተደፍቶ አካባቢያዊ ጥብቅና መቆም ትግል በሆነበት በዚህ ጊዜ እንዲህ ያለ ውሳኔ ማሳለፍ ቀላል ላይሆን ይችላል።
ድርጅቱ ኮሎኔሉን ጨክኖ ሊያስረው ሲገባ የተለመደ ጩኸት ፈርቶ ጉዳዩን ማለዘቡም ልክ አልነበረም። የመስፍን ከፈለኝና ማስረሻ ሰጤ ምልክቶች ሲታዩበት የነበረው ኮሎኔሉ በክትትል ላይ መሆኑንም ሲያውቅ ሰሞኑን ወሎ ላይ በነበረው የግንባር ተጋድሎ ከፊት ሆኖ ውጊያ በመምራት እጅ የማይሰጥ ለማስመሰል ሊያሳስታቸው ሞክሯል። አሳስቷቸዋልም።
ስንት ወጣት ከጎኑ የረገፈበትን ትግል የሸጠው ኮሎኔል በእርስ በእርስ ግጭት መርጦ ላይ ለእውነተኛ ትግል የወጡ ታጋዮችን ዋጋ ከሚያስከፍል እርሱ ተደምስሶ ቢሆን እኛንም እውነተኛ ታጋይ መስሎ አያሳስተንም ነበር።
በሌላ በኩል ደጀን እንሁነው አባታችን ነው ብለው ከስንት ወጥመድ አልፈው ጋሻ ከለላ የሆኑትን ኮራ ደርብና ደምስ ይመርን የመሰሉ እንቁ ወጣቶችን አስጨርሶ በእርጅና ዘመኑ ለየትኛው ነፍሱ የውርደት ካባ መልበስ እንደፈለገ ግራ አጋቢ ነው።
ጣልያንም በወረራ ዘመኗ ባንዳ ለመመልመል አልተቸገረችም ነበር። ዳሩ ግን የወረራ ዘመኗ አብቅቶ ስትመለስ ባንዳዎች መግቢያ አልነበራቸውም።
የሚገርመው ባንዳው ማስረሻ ሰጤም ኮሎኔል ሙሀባም አስከትለው የገቡት የለበሱትን ካኪ ብቻ ነው። ለሁሉም ከሌሊቱ 9 ሰዓት ከሠራዊት ተደብቀህ በጠላት ፓትሮል የህዝብ ትግል ክደህ መኮበለልህን ታሪክ ይመዘግብልሀል።
በጥቅሉ አፋህድ ውስጥ ከመነሻው ጀምሮ እስካሁን ያለው ችግር የእስክንድር የአመራር አቅም ማነስና ቸልተኝነት በድርጅቱ ላይ የፈጠረው ቀውስ ውጤት ነው።
ቀጣዩ እጅ ሰጪ እስክንድር ነጋ ወይም ሀቅአለው ፀጋ ሊሆን ይችላል እርሱ የእኛ ጉዳይ አይደለም። የእኛ ቀዳሚ ሀላፊነት ለሀቀኛ ትግል ከወጡ ወንድሞቻችን ጎን መሰለፍ ነው። ሌሎችም እጅ ሰጪ ባንዳዎች ካላችሁ በጊዜ ግቡና ሀቀኞቹ ለህዝብ ይታገሉበት።
ይህንን ስንፅፍ ጉዳዩን የአፋብኃና አፋህድ የሚያደርገው ጅል መንጋ እንደሚኖር እገምታለሁ። በንፅፅር ቢሰላ በዚህ ወር ከአፋብኃም በርካታ ቁጥር ያለው የፋኖ ሠራዊት በተለያየ መንገድ ለአገዛዙ እጅ ሰጥቷል።
በተለይ ባለፉት ሁለት አመት ትግሉ ያለበትን ደረጃ ገምግሞ የመፍትሄ አቅጣጫ ከማስቀመጥ ይልቅ የታለፈበት የብሽሽቅ ዘመን ዋጋ አስከፍሏል። ነገር ግን ዛሬም ይህንን የሚረዳው ጥቂቱ ነው። የትግል ብተና እየገጠመው በቴሌግራም ሰበር ዜና የሚጎፈላው ሀይል ብዙ ነው።
ዛሬ የሚፈጠሩ ክስተቶችንም ለመሰል ጉዳይ ማዋል ትግሉን ከመጉዳት ባለፈ የሚያመጣው ለውጥ አይኖርም። በአፋህድም ሆነ አፋብኃ ውስጥ ምቹ ሁኔታ የሚጠብቅ ባንዳ ሞልቷል።
እነዚህን ተስፈኛ የትግል ሾተላዮችና አይጠቅሜዎች ለአገዛዙ ፕሮፖጋንዳ መጠቀሚያና የህዝብን የትግል ስነልቦና መጉጃ መሳሪያ ከመሆናቸው በፊት በአፋህድም ሆነ አፋብኃ ውስጥ ያሉ አኮብኳቢዎችን ቀድሞ በቁጥጥር ስር ማዋል ያስፈልጋል።
አሳፋሪው ኮሎኔል ሙሀባ መስፈን ከፈለኝና ማስረሻ ሰጤ የተባሉትን ባንዳዎች ሁለት አመት ተሸክሞ የካደን ሳያንስ ዛሬ ዋነኛ ተባባሪነቱን አረጋግጦ የአማራን ህዝብ በክህደት ተሰናብቶታል።
ነገም የሚከዳ ይኖራል የፀና ግን ያሸንፋል!
ሁሌም ከወጣንለት ዓላማ ጎን ነን።
1 086
የአማራ ፋኖ ትግል መዳኛው አንድነት ብቻ ነው!
የአማራ ሕዝብ እንደ ሕዝብ ግልፅና ተጨባጭ የህልውና አደጋ አጋጥሞታል፡፡ አስከፊ የዘር ማጥፋት አደጋ አለበት፡፡ ሰብዓዊ ክብሩ ተገፎና ተዋርዶ እንዲጠፋ አበክረው የሚሰሩ ጠላቶች ዙሪያውን ከበውታል፡፡ በአማራ ግዛቶች የተከፈተው ጦርነትም የዘር ማጥፋት ዓላማ ያለው ጦርነት ነው፡፡፡
በመሆኑም የፋኖ የትግል መስመር አማራ እንደ ሕዝብ የጋጠመውን የህልውና አደጋ በመቀበልስ በቀጣይ ዳግም የሕልውና አደጋ እንዳያጋጥመው የሚያስችል አዲስ ሥርዓት በሕብረት መፍጠር ነው፡፡
ፋኖ የአማራ ሕዝብን የሕልውና አደጋ ለመቀልበስ እና እሱን ቀልብሶ ጠንካራና የሚከበር ኅብረተሰብ ለመፍጠር ደግሞ የትግል መስመሩን አጥርቶ አንድ ሆኖ መቀጠል አለበት፡፡ አንድ በደንብ መታወቅ ያለበት ነገር ፋኖ እንደጥንት አያት ቅድመ አያቶቹ የፀረ-ወረራ ተጋድሎ ብቻ አያደርግም፤ ይህንን የህልውና ትግል በአሸናፊነት በመወጣትና የአማራ ሕዝብ ዘላቂ ጥቅሞቹ እንዲከበሩ በማድረግ ፋኖ/አማራ የሥልጣን ባለቤት ይሆናል።
ትግሉ ፖለቲካዊ የትጥቅ ትግል ቅርጽ የያዘ ነው፡፡ አማራ ሕልውናውን ማስከበር የሚችለው፤ ድሉን ዘላቂ የሚያደርግለት፤ ዳግም ለሕልውና አደጋ የማይዳርገውና ሕልውናው የሚረጋገጥበት አስተማማኝ አዲስ ሥርዓት ሲፈጠር ብቻ ነው፡፡ ትግሉ የሚቋጨውም በዚሁ አግባብ ሊሆን ይገባል፡፡
የአማራ ሕዝብ ሕልውና የሚረጋገጠው ጥቅሞቹ በዘላቂነት ሊከበሩ የሚችሉት እውነተኛ ወኪሎቹ ሥልጣን ላይ ሲወጡ ነው፡፡ በዚህ ሰዓት እውነተኛ ወኪሎቹ ደግሞ የትግል ሜዳው ላይ ይገኛሉ፡፡
ስለሆነም አማራ የገባበት የሕልውና ጦርነት በድል ይቋጭ ዘንድ የትግሉ ፊት አውራሪ ፋኖ ከወታደራዊ ሳይንስና ከአማራ ሕዝብ ነባር እሴቶች ጋር የሚዋሃድ የትግል መስመር መከተል ይጠበቅበታል፡፡
በተለይ ይፋዊ የትጥቅ ትግሉ ከጀመረበት አንስቶ በአጭር ጊዜ ተዓምር ተሰርቷል፡፡ እነዚህን ወታደራዊ ድሎችም በፖለቲካው መስክ መድገም ግን አልቻለም። በዚህ አግባብ አንድ ወጥ ኃይል በመሆን የዘላቂ ድሉ መረጋገጫ መስመሩን ከወዲሁ እየጠረገ ሊጓዝ ይገባል፡፡ በአማራ ፋኖ ትግል ውስጥ የሚስተዋሉ የትኞቹም ሳንካዎችንም ከስር ከስር እያረመ ወደፊት መጓዝ የግድ ይለዋል፡፡
ከዚህ በኋላ የአማራ ፋኖ ትግል በራሱ ውስንነቶች ምክንያት ድሉን ወደኋላ ይጎትተው ይሆናል እንጂ በፋሽስቱ አገዛዝ ጥንካሬ የሚቀለበስ የአማራ ትግል የለም፡፡ ትግሉ ብዙ ርቀት ተጉዟል፡፡ ከፋሽስቱ ብልጽግና አቅም በላይ ሆኗል፡፡ ስለሆነም ፋኖ ከውስጡ የሚስተዋሉ ውስንነቶቹን በፍጥነት እያረመ ወደዘላቂ ድሉ መገስገስ ይጠበቅበታል፡፡ ( ትግሉን አደጋ ውስጥ የሚከቱ በወጉ ያልነጠሩ ሀሳቦችን የንትርክና የልዩነት ማዕከል ማድረግም ማቆም ይጠበቅበታል)
በተለይም የዚህ ትግል ባለቤት የሆነው ታላቁ የአማራ ሕዝብ ልጆቹ ‘ሰልፍ’ ጥለው ‘ሰይፍ’ ካነሱበት ጊዜ ጀምሮ የማይተካ ዋጋ በመክፈል የአርበኝነት ታሪኩን እያደሰ ቀጥሏል። ይህንን ህዝባዊ ድጋፍ በአግባቡ መጠቀምና ወቅቱን የዋጀ የሁኔታ ግምገማ በማድረግ ለህዝብ ጥያቄ ምላሽ መስጠትም ያስፈልጋል።
ከዚህ አኳያ ስድብና ፍረጃን መታገያ መሳሪያ ያደረጉ የአንድነት ጠንቅ የሆኑ ጥቂት ኃይሎችንም በአማራዊ ባህል በመገሰጥና በማረም ካልሆነም በማግለል፤ የህዝብ ትግል ለማደናቀፍ የሚሞክሩ አካላቶችንም ለማስቆም የጋራ አቋም ሊያዝ ይገባል፡፡
በፋኖ በኩል የትግል መስመሩን ጠብቆ፣ የትግል ዓላማውን ለማሳካት ታክቲካልና ስትራቴጂካዊ ስልቶችን ነድፎ ከጎንዮሽ ትግል ወጥቶ ''አንድ ልብ መካሪ አንድ ቃል ተናጋሪ'' በመሆን ዋናው ጠላቱ ላይ ትኩረት አድርጎ መታገል ከቻለ አሸናፊነቱን ጥያቄ ውስጥ አያስገባም፡፡
የአማራ ህዝብም የሚፈልገው የትግሉን ተስፋ የሚያለመልሙ የጠላትን ቅስም የሚሰብሩ የአንድነት እንቅስቃሴዎችን እንጂ ከፋፋይ ሀሳቦችን አይደለም፡፡ የአማራ ፋኖ የትግል መስመር የሚጠበቀውም በአንድነት መንገድ ነው።
ይህን በማድረግ ትግሉ በአሸናፊነት እንዲቋጭ ፋኖ በጠላት ላይ እየወሰደ ያለውን የድል የበላይነት እና የመሪነት ሚውን አጠናክሮ እንዲቀጥል ወሳኝ ሚና ይጫወታል፡፡
ትግሉ ከድርጅቶች በላይ ነው። !
አንድ አማራ 💪
1 086
143. Mr. T/brehan Zewdu
144. Mr. Abreham Abeje
145. Mr. Chane Demeke
146. Mr. Cherent Eshetu
147. Mr. Setegn Beyeno
148. Mr. Tesema Melese
149. Mr. Asemamaw Melak
150. Mr. Dachew Getu
151. Mr. Bekure Mulate
152. Mr. Desalegn Jenbere
153. Mr. Nigusu Tilahun
154. Mr. Adisu Derebew
155. Mr. Mola Bazezew
156. Mr. Belay Sisay
157. Mr. Yonatan Girma
158. Mr. Yimer Mohamed
159. Mr. Niguse Yilekal
160. Mr. Habtamu Dagnew
161. Mr. Tadele Melkamu
162. Mr. Samuel Mengistu.
163. Mrs. Hiwot Alemayehu እና ሌሎችም...
ሁላችንም ኃላፊነታችንን እንወጣ! የህሊና እስረኞችን መደገፍ የአማራን ህዝብ የህልውና ትግል ማገዝ ብሎም ''ወገናችን ከጎናችን ነው'' ብለው በፅናት የሚታገሉ ጀግኖችን መፍጠር ጭምር ነው!
1 086
+4
🔜አገዛዙ ኢሊት ፎርስ ብሎ የሚጠራቸው ኮማንዶዎች በፋኖ ተ-ደ-መ-ሰ-ሱ!!
ትናንት ታህሳስ 23/04/2018 ዓ.ም ከአዲስ አበባ በ180 ኪ.ሜ ርቀት ላይ በምትገኘው ''ደብረሲና''ከተማ ውስጥ በተደረገ ው-ጊ-ያ አገዛዙ "ኤሊት ፎርስ" ሲል የሚጠራቸው በርካታ ኮማንዶዎች በፋኖ መ-ገ-ደ-ላ-ቸ-ው ተሰምቷል::
በከተማዋ ''ቦርቸሌ'' ተብሎ በሚጠራው አከባቢ የሚገኘው ትልቁ የአየር ወለድ ኮማንዶ ካምፕ የተሰበረ ሲሆን ''ፋኖዎቹ'' ከምሽግ ምሽግ እየተወረወሩ "የባለምጡቅ አዕምሮ ባለቤቶች" ሲል አገዛዙ የሚያሞካሻቸው ህፃን ደፋሪ፡ ሀብት ንብረት አውዳሚ ፀረ አማራ ኮማንዶዎችን ባፈሙዝ ሲያናግሯቸው ውለዋል ነው የተባለው።
1 086
ሰበር የድል ዜና - ፋኖ ደብረሲና ከተማን ተቆጣጠረ ‼️
የንፁሀን ወገኖቻችን ደም ሳይውል ሳያድር በጀግናው የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ ሰራዊት ተመልሷል ‼️
አፋሕድ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ
ታህሳስ 23 / 2018ዓ.ም
የአፋሕድ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ የመሀመድ ቢሆነኝ ኮር ከአፄ አምደ ፂዮን ኮር ከተወጣጡ የክፍለጦር ውስን ሻለቆች የብልፅግናውን አየር ወለድ ኮማንዶ ክፍለጦር እንዲሁም ሪፐብሊካን ወደሚገኝበት ጣርማበር ፣ደበረሲና እና በአርማኒያ ከተሞች ዘልቀው በመግባት የተቀናጀ ጥቃት ሲፈፅሙ፣ ደብረሲና ከተማ የገባው ጀግናው ሰራዊታችን በቦርቸሌ ካምፕ ላይ የመሸገውን የጠላት አየር ወለድ ኮማንዶ ክፍለጦርን ሙሉ በሙሉ ተደምሷል !!
ጠላት በቀጠናው ያሰማራው ተጨማሪ የ105ኛ ኢሊት ፎርስ አየር ወለድ ክፍለጦር ላይ ታላቅ ኪሳራ ማድረስ ተችሏል።
አናብስቶቹ ደብረሲና ከተማን ተቆጣጥረው የአገዛዙን ጦር ከደመሰሱ በኋላ የማረኩትን ማርከው ከስትራጂክ ጠቀሜታ አንፃር ከተማውን ለቀው ጀግኖቹ በክብር ወደምሽጋቸው ተመልሰዋል ።
በዛሬው ልዩ የተቀናጀ ኦፕሬሽን የአባገነኑ ስርዓት ዙፋን አስጠባቂ ኢሊት ፎርስ አከርካሪውን የተመታ ሲሆን በእግረኛ ሰራዊት የተሸነፈው ብልፅግና ሰሞኑን የራሱን ምርኮኞች ጨምሮ በንፁሀን ወገኖቻችን ላይ በፈፀመው የድሮን ጥቃት በግፍ የተጨፈጨፉትን የወገኖቻችንን ደም ሳይውል ሳያድር ጠላት ባለበት የሸዋ ሶስት (3) ከተሞች ዘልቆ የገባው በጀግናው ሰራዊታችን ተመልሷል።
ወገቡ ተመቶ፣ እራሱ እንደ እባብ ተቀጥቅጦ በሸዋ ተራሮች ላይ የአሞራ ቀለብ የሆነው የአገዛዙ ሰራዊት ምላሱ ብቻ በቀረው የብልፅግናው ተከፋይ የሚዲያ ሚሊሾቹ አማካኝነት ሰሞኑን ፋኖን እያፀዳሁ እየደመሰስኩ ነው ቢልም በዛሬው እለት ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ በወሰደው መልሶ ማጥቃትና ቆረጣ በተገኘው ድል መላው ሰራዊታችን እና ሰሞኑን በግፍ በተገደሉ ንፁሀን ወገኖች ምክነያት ከፍተኛ ሀዘን ውስጥ የገባው ህዝባችን ከዚህ በላይ ተከታታይ ስራዎች ሰርተን የምናሳይ መሆኑን እየገለፅን ህዝባችን እስከዛሬ ሲያደርገው እደነበረው ከልጆቹ ጋር ተሰልፎ የስረዓቱን እድሜ እዲያሳጥር መልዕክት እናስተላልፋለን !!
ክብርና ሞገስ ለትግሉ ሰማዕታ !!
ድል ለአማራ ፋኖ !!
ድል ለአማራ ህዝብ !!
የአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት (አፋሕድ) ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ !!!.
1 086
በሸዋ ጠቅላይ ግዛት በይፋትና ጥሙጋ አውራጃ በራሳ ቀጠና ኩሬበረት/እንቧይ ባድ -ቀበሌ የብልፅግና አገዛዝ የፈፀመው አሰቃቂ የድሮን ጥቃት !!
ከፊል ከልዩ ዞን የተሰበሰቡ ጨካኝ ታጣቂዎችን ያሰማራው የአብይ አህመድ አገዛዝ ብዙ ንፁሃኖችን ሲረሸኑ በራሳ አባያጥር ፣ሂዲ፣ግልጥበረት፣ጠድቻ ፣አሻል፣ሰፊበረትና በርበሬ በሚባሉ ቀበሌዎች በየማሳቸው የትህሳስ አዝመራን የሚያዘምሩ ንፁህ ገበሬዎችን ጨፍጭፏል !!
ነፍስ ይማር !!
#መረጃዎቻችን ለሁሉም ተደራሽ ይሆን ዘንድ ሸር በማድረግ፣ የሞዐ ሚዲያ የቴሌግራም እና ፌስቡክ ቻናላን በመቀላቀል የበኩልዎን አስተዎፆ ያድርጉ።
ታህሳስ 21/2018 ዓ.ም
ሞዐ ሚዲያ
አዲስ አበባ
ኢትዮጵያ
⚖🗣
https://www.facebook.com/share/16GvytdZSY/
https://t.me/Moamediamoresh
