en
Feedback
Jema Insider

Jema Insider

Open in Telegram
1 086
Subscribers
No data24 hours
-77 days
-2630 days
Posts Archive
አድዋ 130ኛ እንኳን አደረሳችሁ ! የአማራ ሕዝብ ከልሂቅ እስከ ደቂቅ ታጥቆ ከሌሎች ኢትዮጵያውያን ጋር በመሆን የጣልያንን ፋሽስታዊ ኢምፔሪያሊዝም ድባቅ በመምታት በዓለም ታሪክ አንፀባራቂ ድል አስመ
አድዋ 130ኛ እንኳን አደረሳችሁ ! የአማራ ሕዝብ ከልሂቅ እስከ ደቂቅ ታጥቆ ከሌሎች ኢትዮጵያውያን ጋር በመሆን የጣልያንን ፋሽስታዊ ኢምፔሪያሊዝም ድባቅ በመምታት በዓለም ታሪክ አንፀባራቂ ድል አስመዝግቧል፡፡ የአድዋ ድል በኢትዮጵያና በመላው የጥቁር ሕዝቦች ታሪክ ውስጥ ትልቅ ቦታ የሚሰጠው የታሪክ አሻራ ነው። ይህ ድል በአጤ ምኒልክ ፊት አውራሪነትና በእቴጌይቱ አዝማችነት የፋሽስት ኢጣሊያን ወራሪ ኃይል ድል የተመታበት ት ታላቅ ክስተት ነው። የአማራ ህዝብ የአርበኝነትና የጀግንነት እሴት ፣ የአትንኩኝ ባይነት ሥነ-ልቦና ውቅር ፣ ዘመን የማይሽራቸው የህዝባዊ ደህንነት አደረጃጀቶችና መዋቅሮችም በዛሬው ትውልድ እየተደገመ ይገኛል። የዛሬው ትውልድም ሀገር በቀል ፋሽስትን ድባቅ በመምታት የራሱን አድዋ በታሪክ ፊት ይፅፋል።

ዶናልድ ጄ ትራምፕ በኢራን የአገዛዝ ለውጥ እንዲደረግ ጥሪ አቀረቡ። በዩናይትድ ስቴትስ እና በኢራን መካከል ሲካሄድ ከነበረው ያልተሳካ የመጨረሻ ድርድር በኋላ የኢራን መንፈሳዊ መሪ አያቶላህ አሊ ኻሚኒ ተገድለዋል። ለወራት የዘለቀውን ውጥረት እና ያልተሳካ የኑክሌር ድርድር ተከትሎ፣ አሜሪካ እና እስራኤል በኢራን ላይ "ኦፕሬሽን ኤፒክ ፉሪ" የሚል የጋራ ሰፊ ጥቃት ጀምረዋል። ​​ በአሜሪካ እና በእስራኤል የአየር ድብደባ ወቅት የኢራንን አመራር ኢላማ ባደረገው ጥቃት የተገደሉት የኢራን መንፈሳዊ መሪ የአያቶላህ አሊ ካሜኒ ሞትን አሜሪካ በይፋ አረጋግጣለች። ፕሬዝዳንት ማሱድ ፔዜሽኪያንን ጨምሮ ጊዜያዊ ምክር ቤቱ በአሁኑ ጊዜ አገሪቱን ተቆጣጥሯል። ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የጦርነት ኦፕሬሽኖቹ ከተከናወኑ በኋላ በኢራን የአገዛዝ ለውጥ እንዲደረግ ጥሪ አቅርበዋል። የኢራን ህዝቦች "መንግስቱን እንዲቆጣጠሩም" ጠይቀዋል። ባለፉት 24 ሰዓት ኢራን በባህሬን፣ ኩዌት፣ ኳታር፣ የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ እና ዮርዳኖስ ውስጥ በእስራኤል እና በአሜሪካ ወታደራዊ ቤዞች ላይ በርካታ ሚሳኤሎችን እና ድሮኖችን ጥላለች። በአሜሪካና እስራኤል ጥምር ጥቃት በኢራን ውስጥ ከ200 በላይ ሞት እና 700 ጉዳቶችን ሲስተናገድ የአሜሪካ ጦር እስካሁን ድረስ ምንም አይነት ሞት እና በይዞታው ላይ የደረሰ ጉዳት ሪፖርት አላደረገም። ከፍተኛ ቀጠናዊ ቀውስ የፈጠረው የኃያላኑ ቡጢ በመካከለኛው ምስራቅ የሚገኙ በርካታ ሀገራት የአየር ክልላቸውን እንዲዘጉ አስገድዷቸዋል። ሪፖርቶች እንደሚያመለክቱት በውጭ አገር በሚገኙ ኢራናውያን ደስታቸውን እየገለፁ የሚገኙ ሲሆን፤ በአንፃሩ ደግሞ የዩናይትድ ስቴትስና እስራአል ጥምር ጥቃትን የተቃወሙ ኢራናውያን የአሜሪካ የዲፕሎማሲ ሚሲዮኖች ላይ ኃይለኛ ተቃውሞዎችን እያሰሙ ይገኛሉ። ከእነዚህ መካከል በፓኪስታን ካራቺ በሚገኘው የአሜሪካ ቆንስላ ላይ የኢራን ደጋፊዎች የቆንፅላውን ቅጥር ግቢ ጥሰው በመግባት ውድመት መፈፀማቸው ተሰምቷል። ጥቃቱን ለመከለከል የአሜሪካ የባህር ኃይል በወሰዱት እርምጃም 32 የሚጠጉ ሰዎች ሲቆስሉ ዘጠኝ ሰዎች ደግሞ ሞተዋል ተብሏል። የኢራኑ መንፈሳዊ መሪ ወይም የበላይ ጠባቂ አያቶላህ አሊ የካሜኔይ ሞት ከፍተኛ የኃይል ክፍተት ፈጥሯል። ትራምፕ ህዝባዊ አመፅ እንዲነሳ ጥሪ ቢያቀርቡም፣ የኢራን ባለስልጣናት የአገዛዝ ለውጥ "ተልዕኮ የማይቻል" እንደሆነ እየገለፁ ይገኛሉ። ግጭቱ በፋርስ ባሕረ ሰላጤ ውስጥ የነዳጅ ጭነት ዝውውርን አግዷል፣ ጦርነቱ እየተባባሰ ሲሄድ በመቶዎች የሚቆጠሩ መርከቦች መልሕቃቸውን ጥለዋል። አሜሪካ ቁልፍ የኑክሌር ማበልጸጊያ ተቋማትን ኢላማ አድርጋ መምታቷንም ገልጻለች። ቀደም ሲል ሁለቱ ሀገራት በጄኔቫ እና በኦማን ባደረጉት "የሶስት ዙር" የኑክሌር ውይይቶች ላይ የተደረጉ ሙከራዎች ውጤት ሳያስመዘግቡ ወደ ወታደራዊ እርምጃ ተሸጋግረዋል። በቀጠናው ላይ አሜሪካ የበርካታ ወታደራዊ ቤዝ ባለቤት መሆኗን ተከትሎ ኢራን ግዛቷን ለጥቃት እንዲውል የምትፈቅድ ማንኛውም ሀገር ኢላማ እንደምትሆን በማስፈራራት ላይ ትገኛለች። የባህረ ሰላጤ ሀገራት ከአሜሪካ ዘመቻዎች እንዲርቁ ጫና ማደረጓን ቀጥላለች። መንፈሳዊ መሪዋን ጨምሮ ከፍተኛ ወታደራዊ አመራሮቿ የተገደሉባት ቴህራን የአያቶላህ አሊ ኻሚኒ ወንድ ልጅ ሙጅታብ አሊ ኻሚኒ ሀገሪቱን እንዲመራ ሹመት ሰጥታለች። ውጥረቱ አሁንም የዓለም ቀዳሚ አጀንዳ ሆኖ ቀጥሏል።

photo content

- ኤፍራታና ግድም፣ ከአርጡማ ፋርሲና ከጅሌ ጥሙጋ ወረዳዎች ጋር ይዋሰናል፡፡ - አጣዬ ከተማ አስተዳደር ከጅሌ ጥሙጋ ጋር ይዋሰናል፡፡ - ቀወት ወረዳና ሸዋሮቢትም ከጅሌ ጥሙጋ ጋር ይዋሰናሉ፡፡ ከሁሉም ሰፊ ተዋሳኝ የሆነው ጅሌ ጥሙጋ የሚባለው የልዩ ዞኑ ወረዳ ሲሆን ከከተሞችና ከወረዳዎች ጋር በዋና አውራ መንገድና በገጠር ቀበሌዎች ይዋሰናል፡፡ መውጫ:- እዚህ ጋ የምጠቅሰው መረጃ ከወረራው ጀርባ የፌደራል መንግሥቱን ሥልጣን የጨበጡ ቁማርተኞቹ መኖራቸውን የሚያረጋግጥ ነው ፡፡ በተለይ በአማራ ክል በሰሜን ሸዋ ስር ያለችው አጣዬ ከተማና የወረዳው የገጠር ቀበሌዎች በሙሉ በ“ጎግል ማፕ” ላይ በኦሮሞ ልዩ ዞን ጅሌ ጥሙጋ ወረዳ ውስጥ እንዲካተት አድርገውታል፡፡ በ Mulualem G. Medhin ከአራት አመት በፊት የተፃፈ ! ውስን ሀሳቦች የተጨመሩበት !

ከሚሴ (?) በኦሮሞ ብሄረሰብ ዞን የተጠመደው ድብቅ ፈንጂ ! የከሚሴ ጉዳይ በሰሜን ምስራቅ ኢትዮጵያ የተጠመደ ድብቅ ቦንብ (Time Bomb) ነው። ጉዳዩ አማራን፣ አፋርን እንዲሁም የከረዩ ኦሮሞን ጨምሮ ከማዕከል ፖለቲካ የትግራይን የጠርዝ ፖለቲካ በአንድነት አጣምሮ የያዘ በጥንቃቄ ሊታይ የሚገባው ጉዳይ ነው። የከሚሴ ፖለቲካ የወለጋ ሰዎች በረጅም እንጨት የሚያማስሉት፤ በፖለቲካው ዕይታ መነፀር የአርሲ እስላሚክ ኦሮሞዎች ጉዳዩን የሚመለከቱት በግብፅ፣ በሳውዲ እና በኳታር መነፀር ነው። የበልግ በጉ ብአዴን ለምለም ሳር ባለበት ፊቱን አዙሮ ጉያው ውስጥ ምን እየተከናወነ እንደሆነ አለመረዳቱ ጉዳዩን የከፋ ያደርገዋል፤ በወቅቱ የአፋር ፖለቲከኞች እየመጣ ያለውን አደጋ ለመቀልበስ ያቀረቡለትን እቅድ ለኦህዴድ ብአዴን አሳልፎ ሰጥቶታል። የድኀረ-ደርጉ የኢትዮጵያ ፌዴራል አወቃቀር የዐማራውን የግዛት ቁጥጥርና የሕዝብ ቁጥር በመቀነስ ላይ የተመሰረተ ነው፡፡ ለዚህ ደግሞ፣ ከጎንደር ወልቃይት ጠገዴና ጠለምት፣ ከወሎ ራያን፣ ከጎጃም መተከልን በመነጠል፤ ሸዋን ከአዲስ አበባ የግንኙነት ማዕከሉ በመቁረጥ ለአገሪቱ መዲና የእሳት ቀለበት አጥልቀዋል፡፡ ነገሩ በዚህ ብቻ አልቆመም፤ በዐማራ ስር የተካለሉ “ልዩ ዞኖች”ንም ፈጥረዋል፡፡ በተለይ “ይፋት እና ጥሙጋ” የሚባለውን አካባቢ ለሁለት ከፍለው “ሰሜን ሸዋ” እና “የኦሮሞ ብሔረሰብ ልዩ ዞን” የተሰኘ የሰዓት ቦንብ ቀብረዋል፡፡ በዚህ አከላለል መለስ ዜናዊ እና ሌንጮ ለታ በአተያይም በተሳትፎም እኩል ድርሻ አላቸው፡፡ የጥያቄውን መልስ እያሰላሰልን፤ የኦሮሞ ብሔረሰብ ልዩ ዞን ለቀውስ አመች ሆኖ መበጀቱንና ከጽንፈኛ የብሔሩ ልሂቃን የግዛት ተስፋፊነት ጋር ያለውን ዝምድና እንመልከት። የኦሮሞ ብሔረሰብ ልዩ ዞን በአምስት ወረዳዎችና በሁለት ከተማ አስተዳደሮች የተዋቀረ ነው፡፡ ከሚሴና ባቲ በከተማ አስተዳደር እየተመሩ፣ የወረዳ መቀመጫዎች ሲሆኑ፤ ዳዋ ጨፋ፣ አርጡማ ፉርሲ፣ ደወይ ሀረዋና ጅሌ ጥሙጋ የተሰኙ ወረዳዎች አሉት፡፡ ከሰሜን ሸዋ፣ ደቡብ ወሎና አፋር ጋርም ይዋሰናል፡፡ የልዩ ዞኑ ዲሞግራፊ፣ በቁጥር የዐማራ ተወላጆች ብልጫ ቢኖረውም፤ የዞኑ የሥራ ቋንቋ ኦሮምኛ ብቻ ይሆን ዘንድ የብአዴን ስጦታ ሆኗል፡፡ የአካባቢው ነባር ነዋሪ የሆኑት ዐማራዎች፣ ከአፍ መፍቻ ቋንቋቸው በተጨማሪ ኦሮምኛ ቋንቋ የሚችሉ ቢሆንም፤ ቢሮክራሲው ከአርሲና ከወለጋ በሚመጡ ሰዎች ቁጥጥር ስር በመውደቁ፣ ከክልሉ ውጪ እንዳለው አማራ ከኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትና ከሥራ-ዕድል ተገፍተዋል፡፡ ከዚህ ቀደም በአካባቢው የነበረው በግጦሽ ሳር፣ በደረሱ ሰብሎች ላይ ከብቶችን መልቀቅ የእንሰሳት ስርቆትና በመሳሰሉት ምክንያቶች ይፈጠሩ የነበሩት ተራ ግጭቶች፣ ከዐቢይ አሕመድ ወደሥልጣን መውጣት በኋላ በብርሃን ፍጥነት የብሔር እና የሃይማኖት መልክ ይዘዋል፡፡ ሪፖርቶች እንደሚያሳዩትም፡- “በኦነግ-ሸኔ አልፎም በኦሮሚያ ክልል ስውር እርዳታ በየጊዜው የሚደረጉ ጥቃቶች መልካቸውን እየቀየሩና መጠናቸውን አሳድገዋል፡፡ ከጊዜ ወደ ጊዜ ያልነበሩ ትርክቶች እየተነሱ በተለይም የወሎ ኦሮሞ በሚል ተስፋፊነት ‹ለግጭቱ መሰረት ጥለውለታል፡፡ ይሄ ካልተሳካ ደግሞ የብሔረሰብ ዞን የሚለውን በማጥፋት ‹ኦሮሞ ዞን› እንዲባል ማድረግን ያለመ እንቅስቃሴ አለ” ሲሉ እውነታውን አትቷል፡፡ ብ/ጀኔራል ከማል ገልቹ መስከረም 2011 ዓ.ም የ “ኦሮሞ አንድነት እና ነፃነት ግንባር (ኦአነግ)›” የተሰኘ ፓርቲ ይዞ ወደ አገር ቤት ከገባ በኋላ፤ ከአርሲ ቀጥሎ የመጀመሪያ ጉዞ ያደረገው ወደ ከሚሴ ነበር፡፡ በከሚሴ የፓርቲውን ቅርንጫፍ ቢሮ ከፍቶ አባላትን መልምሎ እንቅስቃሴ በጀመረ የወራት ልዩነት፣ የኦሮሚያ ክልል ሠላምና ደህንነት ኃላፊ ሆኖ ተሾሟል፡፡ በሥልጣን ላይ በቆየባቸው ስድስት ወራትም ከፓርቲ እንቅስቃሴው አልተለየም ነበር፡፡ ከዚህ ቀደም በወጣ መረጃ የ‹‹ብሄረሰብ ዞኑ›› መዋቅር ውስጥ ለፓርቲው የሚሠሩ ሰዎችን በመመልመል ላይ ስለመሆኑ በስፋት ተገልጾ እንደነበረ አስታውሳለሁ፡፡ ጀኔራሉ በአውራጃ-ተኮር ፍጥጫ ከኃላፊነቱ ከተነሳ በኋላ፣ የፓርቲ ሥራውን የሙሉ ጊዜ አድርጎታል፡፡ የኦሮሞ ኃይሎች የቱንም ያህል ቢበጣጠስም፣ እስከ ራያ ያለውን የዐማራ ግዛት የመውረሩ ፕሮጀከት ላይ ቅንጣት ልዩነት ታይቶባቸው አይታወቅም፡፡ በአካሄድ እንጅ በግብ አንድ ናቸው፡፡ ወሎን በተመለከተ ‹‹ሰሜን ኦሮሚያ›› የሚል ትርክት ፈጥረው የኦነግን የህልም ካርታ ለማጽናት ዘመቻ የከፈቱት አራት ኪሎ የገቡ ዕለት ነው፡፡ በአካባቢው ግጭቶች ከ2010 ጀምሮ በየጊዜ ተደርገዋል፡፡ አስገራሚው ነገር ግጭቶች የየካቲት መጨረሻ የመጋቢትና ሚያዚያ ወርን እየጠበቁ መጠናቸውን እያሰፉ መሄዳቸው ነው፡፡ ሰኔ/2010፣ መጋቢት/2011፣ መስከረም/2012፣ መጋቢት/2013፣ ሚያዚያ/2013፣ መጋቢት 2014፣ መጋቢት 2016 ዓ.ም፣ መጋቢት 2018 እና ሚያዚያ 13/2018) በየዓመቱ በተከታታይ ወራት ጥቃቶች ተፈጽመዋል፡፡ ሁሉም ጥቃቶች የሰ/ሸዋ አዋሳኝ ወረዳዎች ዒላማዎች ነበሩ፡፡ ከእዚህ ውስጥ አጣዬ ከተማ በከፍተኛ ሁኔታ ዒላማ ሆናለች፡፡ በመጨረሻው ጥቃት ወድማለች፡፡ አንጾኪያ፣ ማጀቴ፣ አላላ፣ ካራ ቆሬ፣ ቀወትና ሸዋ ሮቢት… በውድመቱ ተጋላጭነት ተመዝግበዋል፡፡ መስከረም 2012 ዓ.ም ላይ ‹‹ከሚሴን ወደ እናት ኦሮሚያ እንመልሳት›› የሚል ኮሚቴ በይፋ እስከማቋቋም ደፍረዋል፡፡ ይሄ ‹‹ኮሚቴ›› በሥራ-አጥ ወጣቶች የተሞላ ቢሆንም፤ ከመነሻው ከውጭና ከውስጥ (ከዞኑ አመራር) ፖለቲካዊ አቅጣጫ እንዲቀበል፣ በእነ ጃዋር መሐመድ አስተናባሪነት የሚዲያ ፕሮፖጋንዳ እንዲኖረው ተመቻችተውለት ነበር፡፡ ዓላማውን ከግብ ለማድረስ የሚሰሩት ደግሞ የዞኑ አመራሮች ናቸው፡፡ እነዚህ ኃይሎች ተጠሪነታቸው ለነሽመልስ ነው፡፡ እነዚህ አመራሮች በ2011ዱ ግጭት እጃቸው እንዳለበት መረጃ ተገኝቶ የተከሰሱ ቢሆንም፣ በነ ዐቢይ አህመድ ጣልቃ-ገብነት ክስቻው ተቋርጦ ወደ ሥልጣናቸው ተመልሰዋል፡፡ “በኤፍራታና ግድም ወረዳ ነጌሶ ቀበሌ ሰው ሲገድሉ፣ ሲያቃጥሉ ንብረት ሲዘርፉ እጅ ከፍንጅ የተያዙ ግለሰቦች- የኦነግን ባንዲራ ግንባራቸው ላይ የጠመጠሙ፣ ስካርቭ ያደረጉ፣ በስልካቸው ስክሪን ላይ የኦነግን ባንዲራ ያስቀመጡ፣ የታጠቁት ትጥቅ ላይም ባንዲራው የታተመበት ነበር፡፡” የብልፅግና ወደ ስልጣን የመጣ ሰሞን አካባቢው ለኦነግ ጎጆ መውጫነት የተሰጠ ቢመስልም፤ ዛሬ ላይ የዐቢይ አህመድ አገዛዝ ሀሳቡን ገዝቶ ቀጣናውን የቀውስ ማዕከል አድርጎታል። የዞኑ መጠሪያ ‹የኦሮሞ ብሔረሰብ ዞን› የሚል ቢሆንም፤ አሁን በጉልበት ‹ኦሮሚያ ልዩ ዞን› የሚል ዕውቅና የሌለው ስያሜ ተሰጥቶታል፡፡ ልዩ ዞኑን በሳተላይት ሲመሩ የነበሩት የጨፌ-ሸኔ ጽንፈኞች፣ ከሳተላይት ወደ ግዛት ጥቅለላ ተሸጋግረዋል፡፡ የልዩ ዞኑ አመራሮች ከበጀት በቀር፤ ሙሉ በሙል ከዐማራ ክልል አፈንግጠዋል፡፡ ቀድሞውንም ... ‹‹ከሚሴን ወደ እናት ኦሮሚያ እንመልሳት›› ባይ ‹‹ኮሚቴ›› አሁንም ጥቃት ላይ ነው። የአሁንና የመካከለኛ ጊዜ ዓላማቸው የምስራቅ ዐማራን ግዛት ትርጉም አልባ ለማድረግ ያለመ ነው፡፡ መልከዐ-ምድራዊ አቀማመጥ ... የሁለቱ ዞኖች መልከዐ-ምድራዊ አቀማመጥን በተመለከተ ሰሜን ሸዋ ዞን፣ ከኦሮሞ ብሔረሰብ ዞን ጋር በሦስት ወረዳዎችና በሁለት ከተማ አስተዳደሮች ይዋሰናል፡፡ - አንፆኪያ ገምዛ ወረዳ ከአርጡማ ፋርሲ ወረዳ፣ ከኬሚሴ ከተማ አስተዳደርና ከዳዋ ጨፋ ጋር ይዋሰናል፡፡

photo content

ፋኖነት + ሰብዓዊነት ! አፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት ዕዝ 206ኛ ከፉያለው ደሴ ኮር ጀኔራል ኃይሌ ዘ ውባንተ ክፍለ ጦር እጅ የሰጡና የተማረኩ የሚሊሻ እና የፖሊስ አካላትን አካላት ጋር ውይይት ማድረጉን ገልጿል ። በስማዳ ወረዳ ሸረፍ ጎዲ ላይ በነበረ ውጊያን ራሳቸውን ለማትረፍ እጅ የሰጡ በርካታ የሚሊሻ፣የፖሊስ እና የብልጽግና አመራሮች ከተቀላቀሉ በኋላም በአለም አቀፍ ሰብዓዊ አያያዝ ማዕቀፍ ውስጥ እንዲያልፉ በማድረግ በክፍለ ጦሩና በአፋብን ከፍተኛ የፖለቲካ ዘርፍ አመራሮች የፖለቲካ ግንዛቤ ተፈጥሮላቸዋል። እነዚህ የሚሊሻ፣የፖሊስና የብልፅግና መዋቅር አባል የነበሩ አካላት ተጨማሪ ስልጠናዎችን ወስደው የፈለጉትን አማራጮች እንደሚወስዱም ኮሩ ገልጿል።

''ወይ ፍንክች አጅሬ አይበገሬ'' የሆኑት የመከታው ወንድሞች ደግሞ በጠንካራ ተቋማዊ መሠረትና ዲስፕሊን የታነፀው የተቋሙን ሠራዊት እየመሩና ወታደራዊ ቁመናቸውን እያዘመኑ ሀሰተኛ ዘመቻ የማይበግረው፤ የብልፅግናን አየር ወለድ ኮማንዶ እርቃኑን ማስቀረት የቻሉ ስብስቦች ያሉበት ግዙፍ ተቋም ለመመስረት በቅተዋል። እኛም በጥላቻ ያበዱ የመርዘኛው መረጃ ቴቪ እብድ ውሾች የሚያደርጉት ሐሰተኛ ስም ማጥፋቶችን እየተመለከትን ዝም የምንለው የአደባባይ ነውራቸውና በጨረጨሰ አዕምሯቸው የሚሰሩት ብልግና ጠፍቶን ሳይሆን ልብ ገዝተው ከድንቁርና በሽታችሁ ይመለሱ እንደሆነ ብለን ነበር። ካላችሁ ግን ... 🤷🤷🤷 ምን ይደረጋል ... እስከ ተላላኪው ስም እየጠራን ምንጠራ እንጀምራለን። በሸዋ ያለው እውነታና የሻንቅላው ግርማ ካሳ የሽንፈት እብደቶች ይቀጥላል .... ዝምታ ሰብረናል ... @ገ

የደም ማህበርተኞች ስብስቡ መርዘኛው መረጃ ቲቬ! በዚህ ጉዳይ ዝርዝር መፃፍ ባልፈልግም በግርማ ካሳ ግብዣ ዶሴውን ለመፈተሽ መጥቻለሁ። የመርዘኛው መረጃ ቲቬ አማካሪ የሆነው ሻንቅላው ግርማ ካሳን የቤት ውሻ (Salon dog) አድርገው ፍርፋሪ የሚወረውሩለት የመረጃ ቴቪ ባለቤቶች በአማራ ፋኖ አንድነት ተበሳጭተው መረጃ ቴቬ የተባለውን የስድብና የነውር ማሰልጠኛ ሳተላይት ቴሌቭዥን ጠርቅመው ከጠፉ 1 ወር ሞልቷቸዋል። የዘጉበት ምክንያትም እነዚህ ገንዘብ እንጂ አንጎል ያልፈጠረባቸው አዛውንቶች ትግሉን ካልዘወርን በሚል ብቸኛ ምክንያት ነው። በእነርሱ ቤት ብቸኛ ሳተላይት ስለሆንን አፋብን ይለምነናል ብለው ነው የዘጉት ደግነቱ አስፈላጊ ከሆነ አፋብን ያለውን የህብረተሰብ ድጋፍ ተጠቅሞ የራሱን የትግል ሳተላይት ቴሌቭዥን ይዞ ሊከሰት ይችላል እንጂ ላንቃቸው ከትናጋቸው እየተጣበቀ የሚያስቸግራቸውና የትግል መረዳት የሌላቸው የድንጋይ ዘመን ስብስብ አዛውንቶችን የሚለምንበት ምክንያት አይኖረውም። ካለም ወደፊት እኛም የራሳችንን ግልፅ አቋም እንወስዳለን። የማይካድ አንድ እውነታ ቢኖር መረጃ ቴቪ ከምስረታው ጀምሮ ለነበሩ ተከታታይ 6 አመታት በተጨባጭ የአማራ ህዝብ አይንና ጆሮ፣ ለንፁሃንና ለተገፉት እንዲሁም መዋቅራዊ በደል ለተፈፀመባቸው ዜጎች ድምፅ ሆኖ ሲያገለግል ነበር ቢባል ስህተት የለውም። ነገር ግን ከአማራ ፋኖ ይፋዊ የትጥቅ ትግል እንቅስቃሴ ማግስት ወይም ከሰኔ 2016 ዓ.ም ጀምሮ የግርማ ካሳና ኤልያስ ... መፀዳጃ ነበር ቢባል ይቀላል። በተለይ የሚዲያው የጀርባ አጥንት እንደሆኑ የሚነገርላቸው ሁለቱ ጥንዶች አቶ ሰለሞንና ወ/ሮ መሠረት በእርጅናና በምንኩስና ዘመናቸው ለምን እንዲህ ያለ የብሽሽቅና የውርደት ካባና ቅሌት መከናነብ እንደፈለጉ ለእኔ ግልፅ አይደለም። አብዛኻኞች ሳተላይቱን በበላይነት የሚመሩት ግለሰቦች በእድሜ የበሰሉ ቢመስሉም ተግባራቸው ከተራ ዱርዬ ያለፈ አይደለም። ክብር ይፈልጋሉ ነገር ግን ሊያስከብር የሚችል የተግባርም የሞራልም እንቅስቃሴ የላቸውም። ክብርን የማውቅ ሀላፊነት የሚሰማኝ በጨዋነት ያደኩ መሆኔ ጠቀመኝ እንጂ ከግርማ ካሳ ጀርባ ያሉት እነዚህ በደም የተቦካ እንጀራ መብላት የማይሰለቻቸው አዛውንቶች የቅሌት ድምፅ እጄ ላይ አለ። ግን አላደርገውም። ከዛሬ ነገ ይሻሻላሉ። ተመልሰው ለሸዋም ሆነ ለአማራ የሚረባ ቁምነገር ይሰራሉ ብለን በተስፋ ብንጠብቃቸውም ዛሬም በፋኖ ሠራዊት መካከል ሌላ መገዳደል እንዲፈጠር አበክረው መስራታቸውን አላቆሙም። መከታውና እስክንድር ነጋን ማስገደል የዘወትር ህልማቸው ነው። ከዚህ ቀደም በርካታ ሚሊዮን ብሮችን ከፍለው የቀጠሩት ነፍሰ ገዳይ ገንዘቡን ከሰጡት በኋላ የት እንዳለ እነርሱም የሚያውቁ አይመስለኝም። አሁንም በሸዋ ለማካሄድ የምታስቡትን ደም መፋሰስ አቁሙ! በጥቅሉ የመረጃ ቴቪ ባለቤቶች በወንጀል ሊጠየቁ የሚገባቸው በአራቱም ግዛቶች ለተፈጠሩ ደም መፋሰሶች ከፍተኛ ሚና የነበራቸው የሰው ገፅታ የተላበሱ አውሬዎች ናቸው። እነዚህ በወንድማማቾች መገዳደል ሰይጣናዊ ፍትወታቸውን የሚፈፅሙ የዱር አራዊቶች ናቸው እንግዲህ አርበኞችን መክሰስ የሚያምራቸው። አፋብን ከሚዲያ አኳያ ትግሉን ጤናማ በሆነ መንገድ ለመምራት ካሰበ ከእነዚህ የሰይጣን ማህበርተኞች ጋር ግንኙነት ላለማድረግ ከፍተኛ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርበታል። ይህ ቡድን እስክንድር ነጋን ከአፋብን ምስረታ ውጪ ለማድረግ በገንዘብ ከማማለል ጀምሮ ፣ ሎቢ ለማድረግ ያልሞከረው ፋኖ የለም። ከዘመነ ካሴ እስከ ምሬ ወዳጆ ከደሳለኝ ሲያስብ ሸዋ እስክንድርን ከአፋብን አስወጡ ተብለው ከቅድመ ድርጅት ምስረታ በፊት በእነዚህ ሰዎች ተለምነዋል። በተለይ አሳምነው ዕዝ ውስጥ ያሉ ውስን ግለሰቦችና ከተቋም እውቅና ውጪ በግላቸው ፍርፋሪ የሚወረውሩላቸውን የቀበሌ ሚሊሻ የነበሩ ቅርንቡሶችን ለማሳመፅና ጥያቄ እንዲያነሱ ለማድረግ ሞክረዋል። ከጎንደር በጊዜ ተጠልዘው ስለወጡ ፊት የሚሰጣቸው አላገኙም። (ይህን ጉዳይ የማነሳው የግለሰቦቹን የሴራ እንቅስቃሴ ለማጋለጥ እንጂ የየትኛውም አደረጃጀት መሪዎችና ድርጅት ለመንካት አይደለም። እናንተም ስለምታውቁት የተደበቀ ጉዳይ አይደለም።) ይህ እስክንድርን የማሳደድ የድንቁርናና የበቀል ጩኸታቸው ባይሳካም ጥያቄውን ለማስፈፀም ግን ሲሯሯጡ የነበሩ ቅጥረኞች የመኖራቸውን ያክል አንዳንድ አስተዋይ አመራሮች ድጋሚ እንዳይደርሱ አድርገው አባረዋቸዋል። የመርዘኛው መረጃ ቴቪ ባለቤቶች እስክንድር ነጋ ከኃላፊነት ራሱን አግልሎ እንኳን እንዲገደልና እንዲሞት የሚፈልጉ አርዮስ ስብስብ ናቸው። (ለዚህም ግርማ ካሳና መሠል የመረጃ ቴቪ ቦርድ አባላት ስለእስክንድር በተለያየ መድረኮችና ለአርበኞች የዘባረቁት የቅርሻት ድምፅ ቅጂ እጄ ላይ አለ ጊዜና ታሪክ ይገልጠዋል። የምንተዋቸው ለክብራቸው ብለን ነበር። ግን አይከበሩም ወራዶች ናቸው። መከታውን የእያንዳንዱ ሀሰተኛ ዘመቻ አካል ማድረግ የተፈለገውም ለእስክንድር ነጋ በሰጠው ከለላ አማካኝነት ነው። ሸዋን እንኳን እስክስንድር ነጋ ነገደ አማራ ሁሉ ይሸሸግበት፤ ቢፈልግ ይጠለልበት ብናደርግ ማን ይከለክለናል። ወፍ ዘራሹንና በሸዋ ስም የሚምለውን ሹምባሽ የከለከልነው ይሄንን ኢ-ሰብዓዊ ድርጊቱን ነው። ከእስክንድር ነጋ ጋር የማልጋራቸውአንዳንድ ጉዳዮች አሉ። ነገር ግን እየከፈለ ላለው ዋጋ ግን ትልቅ ክብር አለኝ። እስክንድርን የዘመቻ ሰለባ ያደረጉት በዙሪያው ተኮልኩለው የነበሩ ወያላዎችና የዶላር ሻርኮች ናቸው። ለበርካታ ችግሮች መፍትሄ መስጠት እየቻለ ዙሪያውን የከበቡት ሾተላዮች ከሌላው አማራ ሲነጥሉት በዝምታ ማለፉ ራሱን እስክንድርን ዋጋ አስከፍሎታል። በርካቶች የሚያነሱለት ጠንካራ ጎኖች ቢኖሩም አመራር ከመስጠትና ለችግሮች መፍትሄ ከመስጠት አኳያ ግን ደካማ የሚባል መገለጫ ቢሰጠው ሐሜት አይሆንም። እንዲያም ሆኖ የተከፈቱበት አብዛኻኞቹ ሐሰተኛ ዘመቻዎች ልክ አልነበሩም። በእስክንድር ላይ ከራሱ ውስን ድክመቶች ባሻገር በርካታ መዘዞች ያመጡበት በውጭ የወከላቸው የዱር አራዊቶችና እንደ ጌጥዬ ያለው ያሉ የችጋር/የመቀንጨር ምልክቶችን ከነችግራቸው ተሸክሞ መዝለቁ ነው። መከታውና ሠራዊቱን አይነት ጀግኖች አርበኞችና አርቆ አሳቢዎች ከጎኑ ባይኖሩ በመንጋው የድንቁርና ዘመቻና በአምሳሉ አስናቀ እና የሀብታሙ አያሌው የወያላ ባህሪ ከእስካሁኑ የበለጠ ያልተገባ ዋጋ በከፈለ ነበር። (እስክንድር ችግሮች አሉበት ቢባል እንኳን በሀገረ አሜሪካ ተቀምው በረሃ ለበረሃ የሚንከራተትን ታጋይ እንዲገደል ማሳደድ ምን ይሉታል ?? የመረጃ ቲቬ ባለቤቶች የሚታገሉለት እውነት ይሄ ነው) ደግሞስ የትኛው የፋኖ አመራር ከችግርና ከጥፋት ነፃ ሆኖ አንዱ ተከሳሽ ሌላው ተወዳሽ ሆኖ የሚቀርበው ??። ደም መጣጭ ወደ ሆኑት የመረጃ ቴቪ ባለቤቶችና ወደ ሻንቅላው ግርማ ካሳ ስንመለስ በሸዋ ያለውን ፖለቲካዊ የትጥቅ ትግል እንቅስቃሴ በሀሰተኛ ስም ማጥፋት መቀየር የሚቻል እየመሰላቸው አማራ የሚኮራበትን ድርጅት በምክትል ተቀዳሚ ሊቀመንበርነት የሚመራው ራስ አርበኛ መከታው ማሞ ላይ ሀሰተኛ ዘመቻዎችን በተለያየ መንገድ 2 አመት ሙሉ ተንደፋድፈዋል። ነገም ይንደፋደፋሉ። ግን የሚለውጡት አንዳች ነገር የለም። 😂😂😂

photo content

የብልፅግና ሠራዊት ፍርሰት በሸዋ ግንባር ቀጥሏል። አፋብን የሰጠውን የምህረት አዋጅ ተከትሎ በርካታ የአገዛዙ ሠራዊት በአራቱም ግንባር እየፈረሰ ፋኖን መቀላቀሉን ተያይዞታል። ለ15 ተከታታይ ቀናት የ
+1
የብልፅግና ሠራዊት ፍርሰት በሸዋ ግንባር ቀጥሏል። አፋብን የሰጠውን የምህረት አዋጅ ተከትሎ በርካታ የአገዛዙ ሠራዊት በአራቱም ግንባር እየፈረሰ ፋኖን መቀላቀሉን ተያይዞታል። ለ15 ተከታታይ ቀናት የታወጀው የምህረት አዋጅ 7 ቀን ቀርቶታል። ድል ለፋኖ 💪

ከ72ሺ በላይ የነበረው የጋዜጠኛ ሙሉጌታ አንበርብር የቲውተር (X) አካውንቱ ስለተዘጋ በአዲስ አካውንት ተመልሷል፣ ቤተሰብ እንሁነው እንወዳጅ! 👇 https://x.com/mulugetaanberbr?s
ከ72ሺ በላይ የነበረው የጋዜጠኛ ሙሉጌታ አንበርብር የቲውተር (X) አካውንቱ ስለተዘጋ በአዲስ አካውንት ተመልሷል፣ ቤተሰብ እንሁነው እንወዳጅ! 👇 https://x.com/mulugetaanberbr?s=21 https://x.com/mulugetaanberbr?s=21

photo content
+3

የውስጥ ሰርጎ ገቡን ሴራም የውጭ ጠላትን ሁሉን አቀፍ የብረት አጥር ሰባብሮ አንድ ተቋም መውለድ የትውልዱ ታሪካዊ ግዴታ ነበር እና በድል ተወጥተነዋል። ሐ) ከድርጅት ምስረታው ማግስት የተዘጋጀ የጥፋት ድግስየድርጅቱ መወለድ ከፍተኛ ድንጋጤ ውስጥ የከተተው አገዛዝ አለኝ የሚለውን የጦር መሳሪያና የማጥቃት ስልት ተጠቅሞ ዘመቻዎችን በማድረግ በዋናነትም ከፍተኛ አመራሮች ላይ ጥቃት በማድረስ የድርጅት ምስረታ ሂደቱን ማደብዘዝ እና የፕሮፖጋንዳ እና የስነ ልቦና የበላይነት ለመያዝ ተፍጨርጭሯል። በተለይም በሸዋ፣ በወሎ እና በጎጃም ቀጠናዎች ኔትወርኮችን በማጥፋት የተጀመረው ዘመቻ በሁሉም ቀጠና ባለው ሰራዊት የተጠናከረ መከላከል ተደርጎበታል። አልፎ አልፎም በመልሶ ማጥቃት ድሎችን መጎናፀፍ ተችሏል። በተለይ በሸዋ የተሰማራው የአገዛዙ ኤሊት ኃይል ያሰበውን ሳያሳካ በሚገባ ተመክቷል። በእነዚህ አካባቢዎች በተፈፀመ ቀጥተኛ የንፁሃን ጥቃት በመቶዎች የሚቆጠሩ ንፁሃን ከመረሸናቸውም ባሻገር መንደሮች በከባድ መሳሪያ ወድመዋል፤ የቤት እንስሳት ተጨፍጭፈዋል። ይህም የአገዛዙን አረማኔያዊ ባህሪ በግልፅ ያሳዬ ሆኗል። መ) የአገዛዙ የበቀል እርምጃ በደብረ ታቦር እና አካባቢው:- ይህ የሽብር እና የቀውስ አገዛዝ ብዙ መቶ ኪሎ ሜትሮችን በሸፈነው የጎንደሩ ተጋድሎ የደረሰበትን ከባድ ውርደት በጦር ሜዳ ውሎ ማካካስ ስላልቻለ ሆን ተብሎ በታቀደ ሁኔታ ከውጊያው ጋር ግንኙነት የሌላቸውን ንፁሐን በመጨፍጨፍ በሽብር መንገድ ወታደራዊ ሽንፈቱን ለመቀልበስ ሰፊ ጥረት አድርጓል። በተለይም የደብረ-ታቦር ከተማ እና አካባቢው ህዝብ እና የህዝብ ተቋማት ላይ የአለማቀፍ ሕግን በመጣስ ተከታታይ የድሮን ድብደባዎችን አድርጓል። በዚህም ደብረ-ታቦር ከተማ ላይ ብቻ ሃያ አራት ሰዓት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ከአስራ ስድስት ጊዜ በላይ ስትራቴጅክ ድሮኖችን ያለምህረት በመጠቀም የአረመኔነት ባህሪውን አሳይቷል። በዚህ ጥቃት የፋርጣ ወረዳ ፖሊስ ጣቢያ፣ የገብርየ ክ/ከተማ ፖሊስ ጣቢያ፣ የዞን ጤና መምሪያ፣ የዞን ሲቪል ሰርቪስ እና ፋይናንስ ቢሮ፣ የቴዎድሮስ ክ/ከተማ ፖሊስ ጣቢያን ጨምሮ ማህበራዊ ተቋማትን እና ሌሎች የህዝብ አገልግሎት የሚሰጥባቸውን ተቋማት አውድሟል። በመደበኛ እንቅስቃሴ ላይ እና በየቤታቸው የነበሩ የከተማ ነዋሪወችንም በድሮን ጨፍጭፏል። ይህ አሳፋሪ ተግባር በሰራዊታችን ላይ ያደረሰው ተጨባጭ ጉዳት ካለመኖሩም በተጨማሪ የውጊያውን ውጤት በመለወጥ ደረጃም ሆነ ሰራዊታችን ደብረ ታቦርን ጨምሮ በሁሉም አካባቢወች የተደረገለትን ህዝባዊ እና ደማቅ አቀባበል ማደብዘዝ እንኳን አልቻለም። የድሮን ቦንቦች ጥቃት ያልበገረው የድርጅቱ ሰራዊት የከተማው እምብርት ድረስ በመግባት የሚፈልጋቸውን ወታደራዊ ኦፕሬሽኖች በሚገባ በማከናወን አይበገሬነቱን እና ጀግንነቱን አሳይቷል። ሠ) በጎንደሩ የወንድማማቾች ድል የተገመደው አፋብን በሸዋ፣ በጎጃም እና በወሎ ኔትወርክ በማጥፋት የጀመረው የአገዛዙ ጥቃት ሸዋ ላይ በአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት እዝ እና በአሳምነው እዝ ሰራዊት በቅንጅት፤ በደቡብ እና ምዕራብ ወሎም በምኒልክ እዝ ብርቱ ተጋድሎ ተመክቷል። ጎንደር ላይ መሀል አርማጭሆን እና ሁለቱን በለሳወች ባካለለው ማእከላዊ የጎንደር ክፍል፤ ከስማዳ እስከ ደብረ ታቦር፤ ከደራ ሀሙሲት እስከ እብናት፤ ከጋይንት እስከ አለምበር ድረስ በሸፈነው ደቡባዊ የጎንደር ክፍል የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ የበላይ ዘለቀ እዝ እና የጎንደር ጠቅላይ ግዛት እዝ በጋራ በፈፀሙት ልዩ ተጋድሎ ከደቡብ እና ማእከላዊ ጎንደር በርካታ ወረዳወች የአገዛዙን ሰራዊት በመጠራረግ የድርጅታችን አንድነት በድል እንዲታጀብ አድርገውታል። ከ2540 በላይ የጠላት ኃይል ምርኮኛ ሲሆን በርካቶችም እጅ ለመስጠት በመዘግየታቸው ምክንያት ተደምስሰዋል፡፡ በዚያው ልክም የአፋብን ሰራዊት ከነፍስወከፍ እስከ ድሽቃ ድረስ ለማስታጠቅ ተችሏል፡፡ የሎጅስቲክ እጥረቱንም እንደተለመደው ከጠላት በመረከብ ተንበሽብሷሻል፡፡ በዚህ የጠላት አቅም እና አቋም ልፍስፍስነት ገሃድ በወጣበት ወታደራዊ ኦፕሬሽን የአገዛዙ የፕሮፖጋንዳ ቋንቋ ሲደበላለቅ ታይቷል። የአገዛዙ ባሪያ የሆነው ካድሬ በሚያሰማራቸው አክቲቪስቶቹ በኩል እርስ በእርሱ መካሰስ አልበቃ ብሎት ለህዝብ የሚያስብ በመምሰል ፋኖ ከተማ ላይ ውጊያ ማድረግ እንደሌለበት ለመምከርም ሞክሯል። የእምነት ተቋማትን ምሽግ አድርጎ የሚዋጋን ጨፍጫፊ ሰራዊት የፕሮፖጋንዳ ድጋፍ የሚሰጥ ስብስብ እንደ ጨዋ ለመጫወት መሞከሩ በመጨረሻዋ ሰዓት ላይ የበግ ለምድ የለበሱ ተኩላዎችን ግልጽ አድርጎ አሳይቶናል። ህሊናቸውን እና ህዝባቸውን በሆዳቸው ይሸጡ የነባሩ ብአዴናዊ በሽታ ተጠቂዎችን ማደናገሪያ በመረማመድ የልዩነቱን ሸለቆ የደፈነው ባለማተብ ትውልድ መራር መስዋዕትነት በከፈለበት የጎንደሩ ተጋድሎ መላው የአማራ ህዝብ እና የድርጅታችን አመራር ከፍተኛ ኩራት ተሰምቶታል። በተመሳሳይ ጊዜ ምዕራቡን የጎንደር ክፍል ሊያካልል በጃዊ እና መተከል የዘለቀውን የጠላት ኃይል ላይ ከባድ ምት በማሳረፍ የቡድን እና የነፍስ ወከፍ መሳሪያችን የማረከው የቴወድሮስ ዕዝ ለጎንደሩ ድል ሌላ ድምቀት ጨምሮለታል። የድላችን የምስጢር ቁልፍ አንድነታችን ላይ መሆኑ በተግባር በተተረጎመበት የጎንደሩ ተጋድሎ ለማረክነው የጠላት ሰራዊት ርህራሔን፣ ሰብአዊነትን እና ወገናዊነትን በማሳዬት እጅ ሊሰጥ ያልፈቀደውን ደግሞ እስከ መጨረሻው በመዋጋት የአማራን ህዝብ የሞራል ልዕልና ያሳዬንበትም ሁኔታ ነበር። የጠላትን ስስ ብልት በተደጋጋሚ በመምታት ትግሉን በፅኑ አለት ላይ ያቆሙት የጎንደር ቀጠና የሰራዊቱ አባላት በራስ በቅነት አመራር እና ስምሪት በመስጠት ኩራት የሆኑትን ወታደራዊ አመራሮች ለበለጠ ድል የሚያነሳሳ ሞራል ጭምር ኖኗል። በመጨረሻም ሰራዊታችን በየደረሰበት ሁሉ ተባባሪ በመሆን እና ፍቅር በመስጠት ከጎናችን ለቆመው የጎንደር ህዝብ ልዩ ምስጋና እያቀረብን የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ነፃ በወጡ አካባቢዎች የህዝብ አስተዳደር መዋቅሮችን በመዘርጋት፣ ጠላትን ደግሞ በፅናት በመፋለም ለአማራ ህዝብ ነፃነት ማንኛውንም መስዋዕትነት ለመክፈል የወትሮ ዝግጁነትን ባነገበ አመራር እና ሰራዊት የታነፀ መሆኑን እናረጋግጣለን። የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ

አንድነታችን ሸዋ፣ ወሎ እና ጎጃም ላይ የተከፈተብንን ጥቃት በመመከት ጎንደር ላይ ባገኘነው የድል ማህተም ታትሟል። የካቲት 07 ቀን 2018 ዓ.ም የጎንደሩን ድል አስመልክቶ ከአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ የተሰጠ መግለጫሀ) መግቢያ የጨፍጫፊው ብልፅግና አገዛዝ የሰሞኑ አዲስ ቀጠናዊ ጦርነት ድግስ ምስጢር አማራን የማጥፋት ፕሮጀክት ነው። በሁለት ቀን ትጥቅ አስፈትቸ አማራውን በባርነት እገዛለሁ ርስቶቹንም መደራደሪያ አደርጋለሁ በሚል እብሪት በህዝባችን ላይ ጦርነት ያወጀው አገዛዝ ቅስሙ የተሰበረው ገና ጦርነቱን በለኮሰው የመጀመሪያ ሳምንት ላይ ነበር። የመጀመሪያውን ኮሎኔል ባህርዳር ከተማ ላይ የማረክነው ጠላት በጎጃም፣ በጎንደር፣ በሸዋ፣ በወሎ እና በወለጋ ቀጠናወች በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ የቡድን እና የነፍስ ወከፍ መሳሪያወችን፣ ሚሊዮን ተተኳሾችን፣ ታንክና ዙ-23 ን ጨምሮ ከባድ መሳሪያወችን ማርከነዋል። በርካታ አሃዶችን በተለይም በክፍለ ጦር እና በሬጅመንት ደረጃ ያሉትን ከእነ አመራሮቹ በተደጋጋሚ ደምስሰናል። በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ ምርኮኞወችን ወደ ቤተሰባቸው ልከናል ከፊሉንም ለቀይ መስቀል አስረክበናል። የክልሉን ዋና ከተማ ጨምሮ በሁሉም ከተሞች ጠላት ላይ ከባድ ምቶችን አሳርፈናል። በዚህ የትውልዱ አስደናቂ ተጋድሎ ነባሩን የብአዴን መዋቅር በማፈራረስ አገዛዙን አየር ላይ የተንሳፈፈ ፊኛ ማድረጋችንን መሬት ያለው ህዝብ ብቻ ሳይሆን ዓለም አቀፍ ማህበረሰቡም በገሃድ የመሰከረው ሐቅ ነው። በዚህም ምክንያት አገዛዙ በውጊያ እንደማያሸንፈን ሲያውቅ ሌሎች የጥፋት እና የማደናገሪያ ስልቶችን ሲጠቀም ቆይቷል። ከእነዚህ የጥፋት ፕሮጀክቶቹ መካከልም:- 1) ንፁሃን ላይ ያነጣጠረ ጥቃት የአማራን ህዝብ ማንበርከክ የአገዛዙ የጦርነት ተልዕኮ መሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ በህዝቡ ላክ በድሮን፣ በጀትና በሌሎችም ከባድ መሳሪያዎች ድብደባ በማድረግ የኃይል የበላይነትን ማሳዬት እና የወገን ኃይል ላይ የስነ ልቦና ጫና መፍጠርን እንደ ስልት ለመጠቀም ሞክሯል። በዚህም የንፁሃን መኖሪያ መንደሮችን፣ ትምህርት ቤቶችን፣ ቤተ-እምነቶችንና ጤና ተቋማትን ጨምሮ ኃላፊነት በማይሰማው መልኩ ጭፍጨፋዎችን ፈጽሟል፡፡ በዚም ምክንያት በርካታ ሴቶች፣ ህፃናት እና አረጋዉያንን ጨምሮ ሲቪሊያንን በገፍ ጨፍጭፏል። ይሁን እንጅ የአገዛዙ ጭካኔ ህዝባዊ መሰረታችንን ከማጠንከር እና አረመኔነቱን ከማረጋገጥ ያለፈ ፋይዳ አላመጣለትም። 2) ብሔራዊ አጀንዳወችን እንደ ማደናገሪያ ስልት በራሱ ህዝብ ላይ ጨካኝ አረመኔ ተግባራትን የሚፈፅም አገዛዝ ለሀገር ክብር እና ብሔራዊ አጀንዳወች ትኩረት ሊሰጥ አይችልም። በተለይም ግጭት ጠማቂው የብልጽግና አገዛዝ የሀገርን ሉዓላዊነት አሳልፎ ለመስጠት የማያመነታ ስለመሆኑ ባለፉት ሰባት ዓመታት ሀገር ውስጥ አንዱን በአንዱ ላይ በማስነሳት ግጭትን በመለኮስ በፍቅር የሚኖሩትን ማህበረሰቦች ሳይቀር ለራሱ ፕሮጀክት በሚመቸው መልኩ ስውር ጦር በማስገባት ሲወጋና ሲያስወጋ ቆይቷል፡፡ ከዚህም ባሻገር ለዘመናት በመከባበርና በፍቅር የኖሩ አጎራባች ሀገራት ድረስ በመዝለቅ እርስ በእርስ እንዲከፋፈሉ አለማቀፍ የሉአላዊነት ህግን በመጣስ ታጣቂዎችን በማሰልጠንና በማሰመራት ለጎረቤቶቻችን ጠንቅ እየተከለ ይገኛል፡፡ አብይ አህመድ የቀጠናው የሰላም ፀርና አተራማሽ ስለመሆኑ በየጊዜው ያደረጋቸው መርህ አልባ ስምምነቶች፣ የአደባባይ መግለጫዎች እና መሃላዎች በቂ አመላካች ናቸው። ከምንም በላይ የቱርክ፣ የዩናይትድ አረብ ኤምሬት፣ የቻይና፣ የአዘርባጃን ድሮኖች እና ሌሎች ዘመናዊ የጦር መሳሪያወችን በአማራ ህዝብ ላይ በመሞከር የሀገሪቱን ህዝብ የአዳዲስ የጦር መሳሪያ መሞከሪያ ያደረገው አገዛዝ የኢትዮጵያን ክብር እና ሉዓላዊነት ተራ ሸቀጥ እንዳደረገው ሌላኛው ማሳያ ነው። እውነታው ይህ ሆኖ ሳለ አንድ ጊዜ በባህር በር ጉዳይ፣ ሌላ ጊዜ በሉዓላዊነት እና የወደብ ጉዳይን አጀንዳ በማድረግ የህልውና ተጋድሎ ውስጥ የገባን ህዝብ ለማዘናጋትና በሌላ ትኩረት ተጠምዶ ዋናውን አጀንዳውን ቸል እንዲለው እና የትግላችንን ማህበራዊ መሰረት ለመናድ ጥረት አድርጓል። በእርሻ ማሳው፣ በንግድ ቦታው፣ በአምልኮ ቦታወች እና በመኖሪያ ቤቱም ጭምር እያለ የሚጨፈጭፈውን ህዝብ በዚህ መልኩ ለማታለል ያደረገው ሙከራም አገዛዙ በፖለቲካ መቀንጨር መጠቃቱን ያረጋገጠ እና የከሸፈ ጉዳይ ነው። 3) የስሁት ትርክቶች ግንባታ ሙከራ የፋኖ ኃይል ከአብይ አህመድ ሰራዊት ጋር ጦርነት በጀመረበት ወቅት አገዛዙ ከሌሎች ኃይሎች ጋር አፍላ ፍቅር ላይ ነበር። በተለይም ከአገዛዙ ሰራዊት የመጀመሪያዎቹን በርከት ያሉ የቡድን መሳሪያወች በመማረክ ኃይላችንን ባጠናከርንበት ወቅት አገዛዙ ከትግራይ ኃይልም ጋር ሆነ ከሌሎች የቀጠናው ኃይሎች ጋር ግጭት ውስጥ አልገባም ነበር። ፋኖ በራሱ አቅም ወራሪውን ሰራዊት በመመከት ወደ መልሶ ማጥቃት ይሸጋገራል ብሎ ማሰብ የተሳነው የብልፅግና ቡድን ተከታታይ ባዳ እና ባንዳ የሚሉ መሰረተ ቢስ ፍረጃወችንም ሊያለማምድ ሞክሯል። የማጥቃት ዘመቻወችን በራሱ የእብሪት እቅድ ጀምሮ በሂደት መቋቋም ያልቻለውን ኃይል በስም ማጥፋት እና በሀሰት ትርክት ዘመቻ ለማዳከም ሞክሯል። አንድ አይሆንም በትነነዋል የተባለው ፋኖ በረቀቀ የአመራር ጥበብ እንደ አለት የጠነከረ ድርጅት ሲፈጥር "በሌሎች ኃይሎች ትዕዛዝ" ነው፤ "የጠላት ድጋፍ" ነው፤"አንደኛው ወደዚህ ሌላኛው ግን ወደዚያ" ነው በሚል መቀባጠር ጀመረ። ይህም አልበቃ ብሎት ሎጅስቲክ፣ ፕሮፖጋንዳ፣ እና ፖለቲካ የሚሰፍርልን ሐይል እንዳለ አድርጎ ያለማቋረጥ በመለፈፍ ላይ ይገኛል። ከገባበት የእብሪት ጦርነት መውጫ ያጣው አገዛዝ ለአማራ ህዝብ አጀንዳዎች በመታመን፣ በብሔራዊ ጀግንነትም ሆነ በራስ በቅነት በመታገል የፋኖን ሰራዊት እና አመራር የሚቀድም እንደሌለ ጠንቅቆ ያውቃል። 4)የጦርነቱን ገፅታ ቀጠናዊ የማድረግ ግብግብ ኢትዮዮጵያ በዓለም የዲፕሎማሲ መድረክ የምትታወቅባቸውን የውጭ ግንኙነት መርሆወችን በመጣስ በሶማሊያ፣ በሱዳን እና ኤርትራን ጨምሮ የዲፕሎማሲ ሀ ሁን በጣሰ መንገድ የትንኮሳ ተግባራትን ፈፅሟል። ደቡብ አፍሪካ፣ ናሚቢያ እና ዚምባቡዌን ጨምሮ ለአፍሪካ አገሮች ነፃነት የቀዳሚነት ሚና የተጫወተችው ኢትዮጵያን ገፅታ እና ታሪክ በማይመጥን ሁኔታ በሌሎች ሀገራት ላይ ወታደራዊ ጣልቃ ገብነቶችን ጭምር አድርጓል። በዚህም ከአማራ ህዝብ ጋር የገባበትን የዘር ማጥፋት ጦርነት ቀጠናዊ እና ዓለማቀፋዊ መልክ እንዲኖረው ሞክሯል። የአማራን ህዝብ የተጋድሎ ትርክት በቀጠናዊ ጦርነት ውስጥ እንዲዋጥ በማድረግ በስኬት ላይ ያለውን የህልውና የተጋድሎ በአርቴፊሻል ብሔራዊ ጀብደኝነት ለማደብዘዝ ጥረት አድርጓል። ይህም እንደሌሎች ማደናገሪያዎች ከጅምሩ የከሸፈ ነው። ለ) የድርጅታችን ውልደት አገዛዙ ቢሊዮን በጀት መድቦ ብዙ የደከመበት ጉዳይ የፋኖ ኃይል አንድ ወጥ ድርጅት እንዳይኖረው ድርጅት ከተፈጠረም እንዳይፀና ማድረግ ነበር። ገና የአንድነቱ ውይይት መስመር መያዝ ሲጀምር የቆዩ የጠላት ተላላኪዎች ሮጠው ጠላት ጉያ በመሸሸግ የአሉባልታ ናዳ የሚያወርዱት የድርጅቱ መፈጠር የተልዕኳቸውን ክሽፈት ስለሚያንፀባርቅባቸው ነበር። ፋኖ መስለው በመተወን ከመወለድ ያላስቀሩትን ተቋም በሐሜት ሊያፈርሱ መሞከራቸው ከንቱ ድካም ሆኖባቸው ህዝብም ታሪክም እየሳቀባቸው ይገኛል።

፭) የዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብቶች ድንጋጌወችን እና መርሆወችን እንዲሁም ዓለም አቀፍ የጦር ህግጋትን የተከተለ አሰራር ይተገበራል። ፮) ይህንን አዋጅ ጥሶ የተገኘ ማንኛውም የድርጅቱ አመራር እና አባል ወይም ሌላ አካል ከባድ ቅጣት ይጠብቀዋል። ረ) የሕዝቡ፣ የሀገር ሽማግሌወች እና የኃይማኖት አባቶች ሚና በየቀጠናው ያለው ህዝብ፣ የሀገር ሽማግሌወች፣ የኃይማኖት አባቶች፣ ምሁራን እና ሌሎች ተሰሚነት ያላቸው ግለሰቦች በጠላት  የፀጥታ እና የፖለቲካ መዋቅር ውስጥ ያሉ ግለሰቦች በዚህ አዋጅ መሰረት አፈሙዛቸውን ወደ ዋናው ጠላት እንዲያዞሩ ካልሆነም ሰላማዊ ኑሯቸውን እንዲኖሩ እና የአማራው ኃይል ፍፁም ህብረት እንዲኖር የበኩላቸውን ገንቢ ሚና እንዲጫወቱ ይጠበቃል። በመጨረሻም የአማራ ልጆች በጋራ ተባብረን ህዝባችንን ሊያጠፋ የተነሳውን ጠላት እናስወግድ ዘንድ አንድነት እና ህብረት ያስፈልገናል እና ወደ አማራ የምንተኩሰው ጥይት እንዳይኖር እና አንድ ጠላት ላይ ብቻ አነጣጥረን እናሸንፍ ዘንድ ኑ እንላለን። የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ የቴሌግራም ገፃችን👉https://t.me/MerebMedia24

ኑ ጠላትን በጋራ ታግለን የአማራን ህዝብ ሕልውና እናረጋግጥ! የካቲት 05 ቀን 2018 ዓ.ም ከአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ የተላለፈ የምህረት አዋጅ ሀ) መግቢያ: አረመኔው የብልፅግና አገዛዝ የአማራን ህዝብ ህልውና አደጋ ላይ ለመጣል የጀመረውን ጦርነት ለማሳካት ይችል ዘንድ በርካታ አረመኔያዊ ተግባራትን ሲፈፅም መቆየቱ ይታወቃል። የአማራን ህዝብ ያለ ልዩነት ለመፍጀት አቅሙ የፈቀደውን ሁሉ እየተጠቀመ ያለው አገዛዝ የመካከለኛው ምስራቅ ሀገራት ጂኦ ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ፍላጎቶችን በማገልገል በፈጠረው የማውደም አቅም ተማምኖ በከፈተው ጦርነት ራሱ እየተለበለበበት ይገኛል። የአማራን ህዝብ ለማጥፋት ከሚጠቀምባቸው ስልቶች መካከል ነባሩን የብአዴን መዋቅር በመጠቀም ባሰባሰበው የምሊሻ እና የአድማ ብተና ኃይል ከፋኖ ጋር እንዲዋጋ እና ህዝባችን በሁለት ጎራ ተሰልፎ እንዲጠፋፋ የሞከረበት መንገድ አንደኛው ነው። በአንድ ህዝብ መካከል እና በኢትዮጵያዊያን መካከል እንዲሁም ቀጠናዊ ጦርነቶችን በማስነሳት ለአፍሪካ ቀንድ የቀውስ ዘበኛ የሆነውን አገዛዝ በወንድማማችነት እና በጥበብ በማስወገድ የጋራ መንግስት መመስረት እንደሚገባን በተደጋጋሚ ጥሪወች ስናስተላልፍ የቆዬን መሆኑ ይታወቃል። በተለይም ከሰሞኑ ደግሞ ጠላት በአንድ በኩል የህዝብ መገናኛ መስመሮችን በመዝጋት ንፁሃን ላይ ጭፍጨፋ እያደረገ በሌላ በኩል ደግሞ ብሔራዊ አጀንዳ ያለው እና ለሀገር ብሔራዊ ተልዕኮ የተሰለፈ በመምሰል የሚያደርገውን የማደናገሪያ ስልት በንቃት በመከታተል የፋኖ ሰራዊት በወሰዳቸው እርምጃወች ወራሪው የብልፅግና ኃይል ከፍተኛ ትርምስ ውስጥ ገብቷል። የድርጅታችን የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ መወለድ ያስገኘው የአንድነት መንፈስ ለተገኙ ወታደራዊ ድሎች ቁልፍ ሚና ተጫውቷል። የድላችን ምስጢር ያለው አንድነታችን ላይ መሆኑም በተግባር ተረጋግጧል። ድርጅታዊ አንድነታችንን በጠበቀ መልኩ ከኢትዮጵያዊያን እና ከቀጠናው ኃይሎች ጋር የሚደረግ ትብብር አገዛዙን ሙሉ በሙሉ ለማስወገድ ወሳኝ ሂደት መሆኑ ግልፅ ነው። ህዝባዊ ዓላማችንን የተጋራን ጋር በመርህ የምናደርገው ትብብር እና አንድነት የአረመኔውን አገዛዝ እድሜ ለማሳጠር ትልቅ ፋይዳ ያለው ጉዳይ ነው። ይህንን ተከትሎ ባቀረብነው ወገናዊ ጥሪ በርካታ የአገዛዙ አገልጋይ የነበረ ምሊሻ፣ አድማ ብተና እና የመከላከያ ኃይል የወገንን ኃይል እየተቀላቀለ ይገኛል። ስለሆነም ዛሬም አገዛዙን በማገልገል ላይ ለምትገኙ የምሊሻ፣ የአድማ ብተና፣ የመደበኛ ፖሊስ፣ መከላከያ እና በሌሎች የአገዛዙ ታጣቂ አደረጃጀቶች ውስጥ ላላችሁ ተመሳሳይ ጥሪወችን እናስተላልፋለን። ይህንን  ጥሪ ያስተላለፈው የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ስራ አመራር በጉዳዩ ላይ በዝርዝር ተወያይቶ ጥሪዉን በመቀበል ወገናቸውን ለመካስ ለሚፈልጉ የአገዛዙ ሰራዊት አባላት እና የካድሬ መዋቅር የምህረት አዋጅ አውጇል። ለ) የምህረት አዋጁ የተላለፈላቸው የአገዛዙ መዋቅር አካላት:- ፩) በየደረጃው የሚገኙ የብልፅግና አመራር አባላት ፪) ምሊሻ፣ ሰላም አስከባሪ እና በሌላም ስያሜ ብልፅግና ያደራጃቸው ታጣቂወች ፫) የክልል አድማ ብተና እና መደበኛ ፖሊስ አባላት ፬) በሀገር መከላከያ ሰራዊት ስም በየቀጠናው የተሰማሩ እግረኞች እና የአገዛዙ መኮንኖች ሐ) የምህረት አዋጁን ማውጣት ያስፈለገበት ምክንያት ሶስት ዓመታትን ሊደፍን ጥቂት ጊዜ በቀረው የጦርነት ሂደት በግልፅ መገንዘብ እንደሚቻለው የብልፅግና መዋቅር በአማራ ህዝብ ማህበራዊ እና ፖለቲካዊ ድቀት ላይ ስልጣኑን ከማራዘም ያለፈ ለአማራ ህዝብ የሚጠቅም አንድም አጀንዳ የሌለው በመሆኑ የአማራ ህዝብ እንደ ህዝብ በተለያዬ ጎራ የተሰለፍን የአማራ ልጆችም እንደ የአንድ እናት ልጆች በመቀናጀት የህዝባችንን ህልዉና ማስጠበቅ ከእኛ የሚጠበቅ ተግባር ነው።  በመሆኑም:- ፩) ለአማራ ህዝብ ሁለንተናዊ መብት እና ነፃነት እንጅ ለአብይ አህመድ ወንበር መፅናት የሚወድቅ የአማራ ወጣት መኖር ስለሌለበት፤ ፪) ህዝባችንን በጅምላ ለሚጨፈጭፍ አገዛዝ በማገልገል የዘቀጠ ታሪክ ውስጥ ራስን ከማግኘት ይልቅ ለነፃነቱ የሚዋደቅን ኃይል በመቀላቀል ደማቅ ታሪክ መፃፍ ታሪክ የጣለብን ግዴታ በመሆኑ፤ ፫) ህዝብን ታግሎ ያሸነፈ አገዛዝ እንደሌለው ሁሉ አብይ አህመድም የአማራን ህዝብ ማሸነፍ ስለማይችል እና በተሸናፊነት ለሚያጠናቅቀው ብልፅግና በመላላክ እና በራስ ወገን ላይ በመተኮስ የታሪክ፣ የህሊና እና የፍትህ ተጠያቂነትን ከማስተናገድ ለመዳን ሲባል፤ ፬) አገዛዙን በጋራ ታግለን በማሸነፍ ለህዝባችን ሰላም ማምጣት የትውልዱ ግዴታ በመሆኑ፤ ፭) እንዲሁም የምንታገለው ለአማራ ህዝብ ህልውናና መዳን እንደመሆኑ መጠን የፋኖ ትግልም የአማራ ህዝብ ትግል ስለሆነ በሁሉም ጎራ ላሉ አማራዊ ወንድሞች ጥሪ ማድረግ እና ማታገል የድርጅታችን ተልዕኮ በመሆኑ፤ ይህንን የምህረት አዋጅ በአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ስራ አመራር ውሳኔ መሰረት ለህዝብ ይፋ ማድረግ አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል። መ) የምህረት አዋጁ አተገባበር ፩) የምህረት አዋጁ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ካላይ በተራ ቁጥር "ለ" ስር የተዘረዘሩት የምሊሻ፣ አድማ ብተና፣ መከላከያ እና ሌሎች የታጠቁ የብልፅግና ኃይሎች እንዲሁም በየደረጃው ያሉ አመራሮች በየአካባቢያቸው ላለው የድርጅታችን መዋቅር እና ለዚህ ጉዳይ በተቋቋመው ግዜያዊ ግብረ ኃይል በአካል ቀርበው ሪፖርት ያደርጋሉ። ፪) ምህረት ጠይቀው ወገናቸውን ለመካስ የሚመጡ ግለሰቦች የአካል ደህንነት ዋስትና ይሰጣቸዋል። በተዘጋጀላቸው ማረፊያ የተሃድሶ ስልጠና እንዲወስዱ ይደረጋል። ፫) ለትግል አገልግሎት ከሚዉል የጦር መሳሪያን ጨምሮ ማንኛውም የምህረት ጠያቂወች ንብረት በባለቤቶች እጅ ይቆያል። ፬) ምህረት የተደረገላቸው ግለሰቦች ድርጅቱ ባዘጋጀው ፎርም መሠረት ለአማራ ህዝብ ነፃነት ሊሰሩ ካልተቻለም ከጠላት ወገን ላይሰለፉ ቃለ-መሃላ ይፈፅማሉ። ፭) አቅሙ እና ፍላጎቱ ያላቸው የምህረት ተጠቃሚወች የወገንን ወታደራዊ እና ፖለቲካዊ መዋቅር ተቀላቅለው ለህልዉና ተጋድሎው የበኩላቸውን ድርሻ ይወጡ ዘንድ በሌላ ማናቸውም ለህዝብ ጠቃሚ በሚሆኑ ተልዕኮወች ላይ ይሰማሩ ዘንድ ድርጅቱ ሁኔታወችን ያመቻቻል። ፮) ይህ የምህረት አዋጅ ከዛሬ የካቲት 04 ቀ 2018 ዓ.ም ላሉት ተከታታይ 15(አስራ አምስት ቀናት) ብቻ ተፈፃሚ ይሆናል። ሠ) የምህረት አዋጁን በማስፈፀም የሰራዊታችን እና የድርጅታችን አመራር ግዴታ ፩) የምህረት አዋጁን አፈፃፀም ለመከታተል በማዕከል የተቋቋመው ግብረ ኃይል የመመሪያዉን አተገባበር ይከታተላል፤ መረጃወችን ይሰጣል፤ መፍትሔ ያስቀምጣል። ፪) የድርጅቱ መዋቅር አመራር እና ሰራዊቱ ለምህረት ጠያቂወቹ የአካል ዋስትና መስጠትን ጨምሮ በእንክብካቤ በማስተናገድ በፍፁም ጨዋነት አዋጁን ይተገብራል። ፫)በአፈፃፀም ሂደት የሚያጋጥሙ ችግሮችን ወዲያውኑ ለግብረኃይይሉ ያሳውቃል፣ የተሰጠዉን የመፍትሔ አቅጣጫ ይተገብራል። ፬ በግል ቂም ቁርሾ ወይም በሌላ ግላዊ እና ቡድናዊ ፍላጎቶች ምክንያት ከዚህ አዋጅ በተቃረነ መንገድ በማንኛውም ምህረት ጠያቂ ላይ አካላዊ እና ስነ ልቦናዊ ጉዳት ማድረስ ወይም ንብረት መቀማት ፍፁም የተከለከለ ተግባር ነው።

photo content
+2