1 086
Subscribers
No data24 hours
-77 days
-2630 days
Posts Archive
1 086
የአፋብን ደቡብ አማራ ቀጠና አሳምነው ዕዝ እና ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ የወንድማዊና ጓዳዊ አንድነት ፕሮግራም ሁለተኛው መድረክ በሸዋ ሰማይ ስር ተካሄደ።
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) መመስረቱን ተከትሎ በወረኃ የካቲት መጨረሻ ላይ በሸዋ የሚገኙት ሁለቱ ዕዞች የአንድነት ጉዟችውን ያሳዩበት የመጀመሪያውን የአንድነት መድረክ የአፋብን አሳምነው ዕዝ በሚያስተዳድራቸው ቀጠናዎች በየካኪት 29 ቀን 2018 ዓ.ም የተካሄደ ሲሆን ሁለተኛው መድረክ የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ በሚያስተዳድራቸው ቀጠናዎች የተገኙት የሁለቱም የዕዝ መሪዎችና ልዑካን ቡድን በተገኙበት የአማራው የመጀመሪያ የሸዋ አንድነት በደማቅ ሁኔታ ፕሮግራሙ ተካሒዷል።
የሁለቱ ወንድማማች ዕዞች ሁለተኛው መድረክ መጋቢት 14 ቀን 2018 ዓ.ም "አንድ ሆነን የህዝባችንን የህልውና አደጋ እንቀለብሳለን!" በሚል መሪ ቃል የተከበረ ሲሆን፣ በተዘጋጀው የአንድነት መድረክ ላይ የአፋብን ፖሊት ቢሮ አመራሮች፣ የሁለቱም ዕዝ ከፍተኛ አመራሮች፣ የኮርና የክፍለጦር አመራሮች፣ የፋኖ ሰራዊት አባላት፣ የሀይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የክላስተር አመራሮች፣ የአርበኞች ፋኖ ጦር ሰራዊት አመራሮችና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው የማህበረሰብ ክፍል በተገኙበት በአይነቱ ለየት ያለ የሸዋ ወንድማዊ አንድነት መድረክ ፕሮግራም ተካሂዷል።
የአፋብን ተቀዳሚ ምክትል ሰብሳቢ አርበኛ መከታው ማሞ እና የአንድነት አመቻች ኮሚቴው ሰሞኑን ለተከታታይ ቀናት በየደረጃው ለሚገኙ አመራሮች የሸዋ አንድነቱን ሂደት የማስረዳት ሰፋፊ መድረኮች የተካሔዱ ሲሆን በትላንትናው ዕለትም የተጀመረውን የሸዋ ወንድማዊ አንድነት መድረክ የሚያጠናክር ሁለተኛው መድረክ ተካሂዷል።
አርበኛው በመክፈቻ ንግግሩ ይሕን የሸዋ አንድነት ይመጣ ዘንድ ከሀገር ውጭም ሆነ በሀገር ውስጥ፣ ከጎንደር፣ ከጎጃም፣ ከወሎ ቤተ አምሓራ እና በሸዋ የሚገኙ የትግሉ ደጋፊዎችና ሌሎችም የማህበረሰብ ክፍሎች እንዲሁም ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ ለሸዋ አንድነት በሀሳብም ሆነ በአካል ለተሳተፉ ታላቅ ምስጋና በማቅረብ የህይዎት መስዋዕትነት ተከፍሎበት የመጣውን አንድነት በየደረጃው የሚገኝ አመራርና ሰራዊታችን እንዲሁም የማህበረሰባችን ክፍል አጥብቆ በመያዝ የግል ፍላጎታቸውን ካነገቡ ፀረ አንድነቶችን በጋራ መታገል እንደሚያስፈልግ መልዕክቱን አስተላልፈዋል።
የአፋብን ደቡብ አማራ ቀጠና አሳምነው ዕዝ ሳብሳቢ አርበኛ ኢንጅነር ደሳለኝ ሲያስብ ሸዋ በተዘጋጀው መድረክ ላይ ባደረገው የመክፈቻ ንግግር "ከመቅረት ማረፈድ ይሻላልና" እኛ የሸዋ ወንድማማቾች በተለያዩ ጎራ በተሰለፍንበት ወቅት ለመደበኛ ጠላታችን ሰፊ ክፍተት በመፍጠራችን የበደልነውን ህዝብ ለመካስ በርካታ ስራዎችን በጋራ ሰርተን እንድናሳይ ሲል ለመላው የአማራ ፋኖ አባላትና ለመድረኩ ታዳሚዎች መልዕክቱን አስተላልፏል።
በመድረኩ ላይ በየደረጃው የሚገኙ አመራሮች የሸዋ ወንድማዊ አንድነትን በማስመልከት መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን፣ የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ ኀላፊ አርበኛ አበበ ሙላቱ መድረኩን በተሳካ ሁኔታ የመራው ሲሆን የዕዙ ወታደራዊ ኪነት ቡድን የመድረኩ ድምቀት በመሆን የተለያዩ ትምህርት አዘል መልዕክቶችን የአባቶቻችንን ጥበብ ተላብሰው ለታዳሚው አስተላልፈዋል።
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ ህዝብ ግንኙነት ክፍል!
1 086
+3
📌የፋኖ ድሮን ቴክኖሎጂና የትንሳኤው ምዕራፍ
በአማራ ፋኖ ትግል ታሪክ ውስጥ የአየር ኃይል ክፍል መመሥረቱ የተሰማው ብስራት፣ ለወዳጅ የድል ተስፋን ለጠላት ደግሞ የድንጋጤ መርዶን ይዞ መጥቷል። ሆኖም አንዳንድ ወገኖች የቴክኖሎጂውን አቅም ካለመረዳት ወይም የትግሉን ስልታዊ ዕድገት ዝቅ አድርጎ በመመልከት ሰሞኑን ይፋ የተደረገውን ሲያቃልሉ ይታያሉ።
ለእነዚህ ወገኖች ምላሹ የሚገኘው ከወቅታዊው የዓለም የጦርነት ቀመርና በምድር ላይ ካለው እውነታ ነው።
ዛሬ በዓለም ላይ የጦርነትን መልክ የቀየረው የዩክሬንና የሩሲያ ጦርነት ትልቁ ትምህርት፤ ድል የሚገኘው በሰራዊት ብዛት ወይም በታንክ ክምችት ሳይሆን በቴክኖሎጂ የበላይነት መሆኑን ነው። ዩክሬን በዓለም ግዙፍ የተባለውን የሩሲያን መካናይዝድ ሰራዊት የገታችውና ወደ ኋላ የመለሰችው በቢሊዮን ዶላር በሚገዙ ጄቶች ብቻ ሳይሆን፣ "ካሚካዚ" በተባሉና በራሷ መሐንዲሶች በለወጠቻቸው ትናንሽ ድሮኖች ነው።
በአነስተኛ ዋጋ የሚመረቱ ድሮኖች በሚሊዮን ዶላር የሚቆጠሩ ዘመናዊ ታንኮችንና የጦር መርከቦችን ሲያወድሙ አይተናል። ይህ የሚያሳየው ቴክኖሎጂ የኃይል ሚዛንን ያስተካክላል የሚለውን እውነት ነው። ፋኖ ሰሞኑን ይፋ ያደረገው ይህ ቴክኖሎጂ፣ አገዛዙ በቢሊዮን የሚቆጠር የሕዝብ ሀብት አፍስሶ የገዛቸውን ከባድ መሣሪያዎች ዋጋ አልባ የሚያደርግ ስትራቴጂካዊ ዱላ ነው።
ፋኖ፣ የአየር ኃይል ክፍል ማቋቋሙ ለፋኖ እግረኛ ሰራዊት ሦስት መሠረታዊ ጥቅሞችን ይሰጣል፦
1. ጠላት የት እንዳለ፣ ወዴት እየተንቀሳቀሰ እንደሆነና የት እንደመሸገ ከሰማይ ሆኖ ማየት መቻል፣ ወታደራዊ ኦፕሬሽኖች በትንሽ መስዋዕትነትና በትክክለኛ ኢላማ እንዲከናወኑ ያደርጋል።
2. የፋኖ ታጋዮች ደረት ለደረት ሳይጋጠሙ፣ የጠላትን ስንቅና ትጥቅ ማከማቻ፣ የመገናኛ ማማዎችንና የከባድ መሣሪያ ምሽጎችን ከራቀ ቦታ ሆኖ መምታት ያስችላል።
3. ጠላት በተኛበት፣ በበላበትና በቆመበት ቦታ ሁሉ ከሰማይ ምን ሊወርድብኝ ይችላል? የሚል ስጋት እንዲያድርበት ማድረጉ፣ የሰራዊቱን የመዋጋት ሞራል ሙሉ በሙሉ የሚሰብር መሳሪያ ነው።
ባለፉት ሦስት ዓመታት በምስጢር ተይዞ ቆይቶ ሰሞኑን ይፋ የሆነው ይህ ቴክኖሎጂ፣ ወደፊት ለሚመዘገቡት ድሎች ፋና ወጊ ነው። የፋኖ ትግል ዛሬ በነፍጥ ብቻ ሳይሆን በዕውቀትና በምህንድስና የታጀበ መሆኑን ዓለም እንዲረዳም ማሳያ ሁኖ መቅረብ ይችላል።
በቀጣይ የአየር ኃይል ክፍሉ አቅሙን እያሳደገ ሲሄድ፣ ጠላት የሚመካባቸው ካምፖችና መከላከያ ምሽጎች መሸሸጊያ መሆናቸው ያበቃል። የእግረኛው ፋኖ ሰራዊትም በምድር ላይ በሚያደርገው ተጋድሎ የአየር ሽፋን እያገኘ ወደ ዋና ዋና ከተሞችና ስልታዊ ቦታዎች የሚያደርገው ጉዞ የተፋጠነ ይሆናል።
ስለዚህ፣ ይህንን ስኬት የሚያቃልሉ ኃይሎች ነገ በምድር ላይ የሚታየው እውነት አንደበት ሊሆናቸው ይገባል። የአማራ ፋኖ በራሱ ልጆች ዕውቀትና ጥበብ የሰማዩን በር መቆለፍ መጀመሩ፣ የአገዛዙ የመጨረሻ ምዕራፍ መቃረቡን የሚያበስር ታሪካዊ ክስተት ነው።
ድል ለአማራ!
1 086
ምኒልክ ዕዝ 101ኛ ኮር ወልድያ ዙሪያ ከባድ ተጋድሎ በማድረግ ድል አስመዘገበ::
ምኒልክ ዕዝ 101ኛ ኮር አሃዶች የሆኑት 11ኛ ክፍለ ጦር እና 35ኛ ክፍለ ጦር በጋራ በመሆን መጋቢት 9/2018 ዓ.ም ንጋት ጀምሮ ከወልድያ እና ከመርሳ ተነስቶ በበርካታ እግረኛ እና መካናይዝድ እንዲሁም ድሮን ታጅቦ ወደ መርጦ ማጥቃት ያደረገ የጠላት ሃይል ጋር ብርቱ ትንቅንቅና ተጋድሎ በማድረግ ድል አስመዝግበዋል::
በተጋድሎው በርካታ የጠላት ሃይል በኮሩ መካናይዝድ በታገዘ ውጊያ ከባድ ሰብዓዊ ኪሳራ የደረሰበት ሲሆን ቁጥሩ ቀላል የማይባል እግረኛ ሰራዊት ተደምስሷል በርካታ ቁስለኛም ወደ ወልድያ እና መርሳ ሆስፒታል አስገብቷል::
በዚህ ከባድ ውጊያ ጠላት ከወልድያ ስታዲየምና ከተለያዩ ቦታዎች ከባድ መሳሪያ ወደ ተለያዩ የገጠር ታዳጊ ከተሞች እያስወነጨፈ የዋለ ሲሆን በሰው ህይወት በቤት ንብረትና እንስሳቶች ላይ ከባድ ጉዳት አድርሷል:: ይህ የፋሽስቱ አገዛዝ ተግባርም የተለመደና ዛሬ ስንት ሰው ገደለ ስንት እንስሳት መታ ስንት ቤትና ንብረት አወደመ በሚል ጥያቄ እየተለመደ መምጣቱ ጭፍጨፋውን እንዲለመድና አሳሳቢ አድርጎታል::
©በአፋብን ምኒልክ ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ!
የቴሌግራም ገፃችን👉https://t.me/MerebMedia24
1 086
አርበኛ መከታው ማሞና የሸዋ ጦር "የአባዱላ ፋኖ፣ የብልፅግና ተላላኪ፣ የመንግስት ተቀላቢ፣ መሳሪያ ከመከላከያ የሚቀበል" ኧረ ምን ያልተባለ አለ ? እ ? ምን ያልተባለ አለ ? 🤔 ?
በዝምታ ውስጥ ሆነህ ስራህን ሰራው። ስራህም አፍ አውጥቶ መሰከረ 💪
በቃ 💪
አማራ 💪
1 086
“ለአማራ ፋኖ ታጋዮችና ደጋፊዎች አዲስ ብስራት ይዘን መጥተናል።” የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ አየር ሃይል ክፍል !
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛ ዕዝ አየር ሀይል ክፍል ላለፉት ሶስት አመታት በተሰማራባቸው ቀጠናዎች በሙሉ በጠላት መካናይዝድ ጦር፣ አየር ወለድ ኮማንዶ ፣ እግረኛ ሠራዊት፣ የአገዛዙ ካምፕ እና ሎጀስቲክ ማከማቻ ላይ በተጠና መልኩ ስኬታማ ጥቃቶችን ፈፅሟል!!
የሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ ከትግሉ መታወጅ ማግስት ጀምሮ የጠላት ኃይልን ለመምታት የተጠቀመበት እና በአማራ ፋኖ ትግል ውስጥ የመጀመሪያው የሆነው ድሮን ቴክኖሎጂ በመታጠቅ በርካታ ድሎችን ሲያስመዘግብ የቆየ ቢሆንም የአገዛዙን የትኩረት አቅጣጫ ለማሳት እና የወገን ጦር ተገማችነትን ለማራቅ በሚል በሚስጥር ተይዞ ቆይቷል።
በመሆኑም የአማራ ፋኖ ትግል ይፋዊ አንድነት መታወጅና ወጥ ድርጅታዊ መዋቅሮች ከመፈጠራቸው ባሻገር በድርጅታችን አፋብን ቴክኖሎጂና ምህንድስና መምሪያ ክፍል ዘርፍ መኖሩን ታሳቢ በማድረግ ለመላው ህዝባችን እንዲሁም ደጋፊዎቻችን ይፋ ማድረግ አስፈላጊ ሆኗል።
የጦር ጠበብቶችን፣ መሀንዲሶችን፣ መምህራኖችን፣ ጋዜጠኞችን፣ ዶክተሮችን፣ ተመራማሪዎችንና ታላላቅ ምሁራኖችን አቅፎ የአማራን ትግል በፊታውራሪነት እየታገለና እያታገለ የሚገኘው በራስ መከታው ማሞ የሚመራው የሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ በአማራ ጠሉ ኦህዴድ መራሹ የብልፅግና ስርዓት ላይ በጀግና የፖለቲካ ልሂቆቹና፣ በጠንካራ ወታደራዊ ክንፉ በኩል በሚያሳርፈው ጠንካራ ምት ስርዓቱን በማፍረስ ረገድ ትልቅ ታሪካዊ አሻራውን ተወጥቷል፤ እየተወጣም ይገኛል።
ተቋሙን ስኬታማ ካደረጉት የትግል መስመሮች መካከል አንደኛው ጠንካራው ወታደራዊ ክንፉ ሲሆን በዚህም በተቋሙ ውስጥ የተሰባሰቡ ተመራማሪዎችና የጦር ጠበብቶች የአየር ሀይል ክፍል በማቋቋምና ስርዓቱ የሚመካባቸውን ካሚካዚ ድሮኖችን ጨምሮ ሌሎች የአየር ትጥቆችን ጭምር በመታጠቅ የጀግናውን እግረኛ የፋኖ ሰራዊት መስዋዕትነት ከመቀነስ አንፃር የአየር ሀይል ክፍሉ ከተቋቋመ ከህዳር 3 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ ላለፋት ሶስት አመታቶች በጠላት የብልፅግና ስርአት ወንበር አስጠባቂ ሀይል ላይ በተሳካ ሁኔታ ወታደራዊ ኢላማዎችን በመምረጥ ጥቃቶችን ሲያደርስ ቆይቷል።
የአየር ሀይል ክፍላችን ከተቋቋመ ጀምሮ የፈፀማቸዉ ተጋድሎዎች በትንሹ፦
👉የካቲት 23/2016 ዓ.ም በጠላት ላይ በተፈፀመ የመጀመሪያ ጥቃት የጠላት መካናይዝድ መሳሪያዎችን ከጥቅም ውጭ ማድረግ ተችሏል።
አየር ሀይል ክፍሉ በተጠና የጠላት ሀይል ላይ ባደረሰው ጥቃት አገዛዙ በንፁሀን አማራዎች ላይ፣ በተቋማት ላይ ያደርስ የነበረውን የከባድ መሳሪያ ጉዳት መከላከል የተቻለ ሲሆን ለዚህም የፎቶና የቪዲዮ ማስረጃዎች ተሰንደው ተይዘዋል።
የሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ ዋና አዛዥና የአፋብን ተቀዳሚ ምክትል ሊቀመንበር ራስ መከታው ማሞ የሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ አየር ሀይል ክፍሉን የጎበኘና መልዕክት ያስተላለፈ ሲሆን በመልዕክቱም ካለፉት 50 አመታቶች ወዲህ አማራ በተለዬ መልኩ የገጠመውን የህልውና አደጋ ለመቀልበስ ጀግና የቁርጥ ቀን የአማራ ልጆች ዋጋ እየከፈሉ ይገኛሉ፣ እናንተም ጀግና ሳይንቲስት ፋኖዎች ያለማንም የሀገራት ድጋፍ በራሳችን ኢኮኖሚ፣ በራሳችን እውቀትና የፈጠራ ጥበብ ተጠቅማችሁ የአየር ሀይል ክፍል እንዲቋቋምና ለእግረኛ ፋኖ ሰራዊት የአየር ሽፋን በመስጠት ትልቅ ድጋፍ በማድረጋችሁ የከበረ ምስጋናዬን አቀርባለሁ፣ ነገ የተሻለ አቅም እንዲኖራችሁ እንደ ድርጅት እገዛ እናደርጋለን ሲል በጉብኝቱ መልዕክቱን አስተላልፏል።
ክብርና ሞገስ ለትግሉ ሰማዕታት!!
ድል ለአፋብን!!
ድል ለአማራ ህዝብ!!
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!
ስር-ነቀል ለውጥ በተባበረ ክንዳችን!!
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ የህዝብ ግንኙነት መምሪያ
መጋቢት 9 ቀን 2018 ዓ.ም
1 086
የክፍለጦሩ መስራች አርበኛ አበበ ሙላቱን ጨምሮ የዕዙ መሪና የአፋብን ከፍተኛ አመራር ራስ መከታው ማሞ በተገኙበት ክፍለጦሩ ደማቅ የተሀድሶ ፕሮግራም አደረገ!!
መጋቢት 04 / 2018 ዓ.ም
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ መሀመድ ቢሆነኝ ኮር ግዙፉ አስቴጎማ ተራራ ክፍለ ጦር በቀጠናው ላይ የተሰጠውን ወታደራዊ ግዳጅ ካጠናቀቀ በኋላ ያሉትን ጠንካራ ሻለቆች ወደ አንድ ማዕከል በማሰባሰብ እረገድ የአፋብን ተቀዳሚ ምክትል ሊቀመንበር አርበኛ መከታው ማሞ እና የሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ ዋና አዛዥ፣ የአፋብን ልዩ ዘመቻ መሪ አርበኛ ድርሳን ብርሃኔ፣ ሌሎች የአፋብን ከፍተኛ አመራሮች፣ የክፍለጦሩ መስራች አርበኛ አበበ ሙላቱና የሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ ከፍተኛ አመራሮች እንዲሁም የኮሩ ከፍተኛ መሪዎች በተገኙበት የክፍለጦሩ ሰራዊትና የአመራር የግዳጅ አፈፃፀም ሁኔታ ከገመገመ በኋላ ለክፍለ ጦሩ ሙሉ ተሀድሶ ፕሮግራም ተደርጓል።
አስቴጎማ ተራራ ክፍለጦር ከውስጥና ከውጭ በሚገጥሙት ችግሮች በርካታ ፈተናዎች ቢደርሱበትም፣ ትግሉን እየመሩ ያሉ ጠንካራ የክፍለጦሩ አመራሮች ባሳዩት ብልሀት የተሞላበት አመራርና ጀግናው የህዝብ ልጅ ሰራዊቱ ለትግሉ ባለው ቁርጠኛ አቋም ፈተናዎችን ተቋቁሞ ዕዙ በቀጠናው ላይ የሰጠውን ግዳጅ በታማኝነት ሲወጣ የቆየ ጠንካራ ክፍለጦር ነው።
"ላለፉት ከ50 አመታቶች በላይ እንደ አማራ የደረሱብን ችግሮች ብዙ ናቸው፣ ከነዚህም አንደኛው ማነቆ ሆኖ የነበረው አማራ እንዳይተማመንና እንዲገፋፋ ተደርጎ ሲሰሩ የነበሩ የጠላቶቻችንን ሴራዎች ሰብረን ዛሬ ላይ በወንድማማችነት መንፈስ አማራ የራሱ አንድ አታጋይ ድርጅት እንዲኖረው ማድረግ ችለናል።
እንደሸዋም የነበረንን ልዩነት ፈተን አንድነቱን አጠናቀናል" እንኳን ደስ አላችሁ፤ ከአሁን በኋላ አንድ ሆነናል፣ የጠመንጃችንን አፈሙዝ ወደ ጠላታችን ብቻ በማድረግ አማራ ጠሉን የብልፅግና ስርዓት ጥለን ለተበደለው ህዝባችን ነፃነቱን ማወጅ ይኖርብናል። ለዚህም እናንተ ጀግና ተዋጊዎች ድርጅታችሁ የሚሰጣችሁን የተኛውንም ግዳጅ ለመወጣት ዝግጁ ሁኑ ሲል በተሀድሶው ላይ የተገኘው የዕዙ መሪና የአፋብን ከፍተኛ አመራር ራስ መከታው ማሞ መልዕክቱን አስተላልፏል።
እንዲሁም የመሀመድ ቢሆነኝ ኮር ዋና ጦር አዛዥ አርበኛ 100 አለቃ ኤርሚያስ ግጨው በመድረኩ መልዕክቱን እንዳስተላለፈው በድርጅቱ አማካኝነት ዕዙ የሚሰጠንን ማንኛውም ግዳጅ ለመፈፀም ኮሩ ዝግጁ ሆኖ እየተጠባበቀ መሆኑን ገልጿል።
በመጨረሻም በጦር ግንባር ጀብድ ለፈፀሙና አርአያ ለሆኑ የክፍለጦሩ ጀግኖች የማበረታቻ የሞራል ድጋፍና ሽልማት በማበርከት ክፍለጦሩ በተዋረድ ለሚሰጠው አማራዊ ግዳጅ ዝግጁ እንዲሆን የስምሪት አቅጣጫ በማስቀመጥ ፕሮግራሙ ተቋጭቷል።
ክብርና ሞገስ ለትግሉ ሰማዕታት!!
ድል ለአፋብን!!
ድል ለአማራ ህዝብ!!
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!
ስር-ነቀል ለውጥ በተባበረ ክንዳችን!!
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ የህዝብ ግንኙነት መምሪያ
መጋቢት 04 / 2018 ዓ.ም
https://t.me/shewafa
1 086
አምሓራው የዘር ፍጅት ሰለባ ሆኖ ቀጥሏል‼️
ያ ከአፈር ጋር ታርቆ፣ ከጎረቤት ጋር ተዋዶ፣ አምላኩን ፈርቶ የሚኖረው የአማራ ሕዝብ በወለጋ ምድር በምታዩት መልኩ ደሙ እንደ ጎርፍ እየፈሰሰ ነው።
ይህ አከባቢ የሰው ልጅ የመጨከን ጥግ የሚለካበት መለኪያ ነው፡ የሰብአዊነትና የእዝነት እርካሽነት የሚመዘንበት ስፍራ ሆኗል።
የአማራው ደም እየፈሰሰ የፍትሕ ሚዛን ዝምታን የመረጠችበት አንዳች አስፈሪ ጥላ የሰፈነበት...ወለጋ።
ምድርን የሚያንቀጠቅጥ ሰሚ አልባ የፍጥረታትት"የድረሱልን" ጩኸት እዚህ አለ።
የወለጋ አፈር በገፍ የተጨፈጨፈውን የአማራን ደም ዋጋ ይናገራል። እዚህ አከባቢ የሚነፍሰው ንፋስ የአማራን የሲቃ ድምፅ ያስተጋባል።
ይህ የምትመለከቱት የእልቂት ምስል፡ 2018 ዓ/ም መጀመሪያዎቹ ወራት ላይ በሆሮጉድሩ ወለጋ ዞን ስር በሚገኙ አከባቢዎች በአሰቃቂ ሁኔታ የተጨፈጨፉ የአማራ ተወላጆ ምስል ነው።
ያለቀው አልቆ ቀሪው ሕይወቱን ለማዳን መንደሩን ለቆ ተሰድዶ ነበር። የወደቀውን አስከሬንና ቁስለኛ የሚያነሳ የቅርብ ቤተሰብ በመጥፋቱ በአከባቢው የሚኖሩ አንዳንድ ደጋግ የኦሮሞ ተወላጅ አርሶ አደሮች እያነሱ ሲቀብሩ የሚያሳይ ነው።
አሁን ደግሞ➞
በሆሮጉድሩ ወለጋ ዞን አቤ ደንጎሮ ወረዳን ጨምሮ በጉዳያቢላ፣ በአሙሩ ወረዳና በሌሎች የዞኑ አከባቢዎች እንዲሁም በምስራቅ ወለጋ ዞን በጊዳ አያና ወረዳ፡ በሊሙ ገሊላ እንዲሁም በሌሎች የዞኑ አከባቢዎች በአሁን ሰዓት ተመሳሳይ ጭፍጨፋ ተከፍቶ በርካታ ንፁኋኖች እያለቁ ነው።
ጭፍጨፋውና የንብረት ዘረፋው እንዲሁም ከመኖሪያ ቤት ጀምሮ ንብረትና መንደር የማውደሙ ድርጊት የሚመራው በክልሉ መንግስት ፀጥታ ኃይል ነው።
ጭፍጨፋው እንደ አዲስ የተጀመረው እየተገባደደ ባለው በዚህ የካቲት ወር አጋማሽ ጀምሮ ነው።
ምንጭ፦ መረብ ሚዲያ
የካቲት 28/2018 ዓ.ም
