1 087
Subscribers
No data24 hours
-77 days
-2630 days
Posts Archive
1 086
መሐል አዲስ አበባ ላይ "ነፃ እርምጃ" ተጀምሯል።
ይህ ዛሬ አዲስ አበባ ሽሮ ሜዳ በፖሊስ ተይዞ ከተወሰደ በኃላ እዚያው ፅ/ቤቱ በር ላይ በአራት ጥይት ተመቶ የተገደለው ወጣት ተገኝ ባልቻ በቅፅል ስሙ ኦሮሮ የተባለ የሽሮ ሜዳ ወጣት ነው።
1 086
ልዩ ትንታኔ
ከትንሳኤ ማግስት የተገኘው ታላቅ የምሥራች
በወታደራዊ ሳይንስ የተቃኘው የራያ ኦፕሬሽን
"የጥፋት ጥምረቱ ተሰባበረ፦ የምኒሊክ ዕዝ ድል!"
https://youtu.be/OttFt7xZNbk?si=WuWdFgdzQ4y3EX2_
1 086
በሁሉ እንገፋለን እንጂ አንጨነቅም፤ እናመነታለን እንጂ ተስፋ አንቆርጥም፤ እንሰደዳለን እንጂ አንጣልም፤ እንወድቃለን እንጂ አንጠፋም።" (2ኛ ቆሮንቶስ 4:8-9)
ትንሳኤ ማለት ለወደቁት መነሳት፣ ለታሰሩት መፈታት፣ በጨለማ ላሉትም ብርሃን መውጣት ነው። ዛሬ በፈተና እሳት ውስጥ ላለህው ወገኔ የአማራ ህዝብ፤ እግዚአብሔር የጭንቅህን ቀን አሳጥሮ የትንሳኤውን ሰላም ያሳይህ።
ትግልህ ወደ ድል፣ እንባህ ወደ ሳቅ ይለወጥ።
ይህ በዓል ከሞት በኋላ ህይወት፣ ከመከራ በኋላ ደስታ፣ ከስደት በኋላም መመለስ እንዳለ የምንማርበት ነው። ዛሬ በፈተና እና በትግል ውስጥ ብትሆኑም፣ የትንሳኤው ጌታ የድልን አክሊል እንደሚያቀዳጃችሁ እናምናለን። ፅናታችሁ ለነፃነት፣ መከራችሁ ለክብር እንዲሆን ምኞታችን ነው።
እንኳን ለብርሃነ ትንሳኤው በፅናት አደረሳችሁ።
1 086
በትግል መሃል የመክዳት ፖለቲካ እና የታሪክ ተጠያቂነት!
በትግል ታሪክ ውስጥ ፅናት የድል መሰረት እንደሆነው ሁሉ መክዳትና እጅ መስጠት ደግሞ የውድቀትና የታሪክ ጠባሳ ሆነው ይኖራሉ።
በአሁኑ ወቅት አንዳንድ የፋኖ ታጋዮች ወደ ብልፅግና አገዛዝ እጅ የመስጠታቸው ጉዳይ በሁለት መነፅሮች ይታያሉ በአንድ በኩል የአመራር ክፍተትና ክትትል ድክመት ሲሆን በሌላ በኩል ደግሞ የግለሰቦች የፅናት ማጣት ነው።
ነገር ግን የፈለገ የአመራር ድክመት ቢኖር የህዝብን ነፃነት አንግቦ የወጣ ኃይል እጅ መስጠቱ በምንም መስፈርት ሊጸድቅ የማይችል የታሪክ ስህተት ነው። የአመራር ድክመትም ለእጅ መስጠት ሰበብ ሊሆን አይችልም።
አንድ የትግል ስብስብ ጠንካራ መዋቅር፣ ግልጽ ስትራቴጂ እና የተባበረ አመራር ካጣ በታጋዩ ውስጥ ጥያቄ ሊፈጥር እንደሚችል እሙን ነው።
በዚህ አግባብ ፋኖ ከመጣበት የአደረጃጀት ቅርፅና መዋቅር አኳያ ውጣ ውረድ ቢያስተናግድም ከአደረጃጀት ግንባታና ከሠራዊት ቁመና አኳያ አገዛዙን የሚያስደነግጥ ጥሩ አቅም ላይ ይገኛል። ነገር ግን ዛሬም በአንዳንድ ጉዳዮች ላይ ግልፅ አቅጣጫ የማስቀመጥ የአመራር ክፍተቶች መኖራቸው አይካድም።
ሆኖም ግን ትግል የሚደረገው ለአመራሩ ሳይሆን ለዓላማ ነው። አንድ ታጋይ በረሃ የገባው የአመራሩን ስብዕና ወዶ ሳይሆን የህዝቡን መገፋት ተመልክቶ እስከሆነ ድረስ፣ የአመራር ድክመት ዓላማን ለመተው በቂ ምክንያት ሊሆን አይችልም።
አመራር ሲዳከም አማራጩ አመራሩን ማስተካከል ወይም ለመተካት መስራት፣ በአጀንዳዎች ላይ ጠንካራ አቋም በመያዝ እንጂ፤ ወደ ታገሉት አካል ሄዶ እጅ መስጠት አይደለም።
ህዝብን ነፃ ለማውጣት የወጣ ኃይል እንዴት ህዝቡ ላይ ወረራ ለፈፀመበት አካል፤ እንዴት እጅ ይሰጣል?
የህዝብን ነፃነት እንደ ትልቅ አደራ የተሸከመ ኃይል እጅ ሲሰጥ የሚያጣው የግል ነፃነቱን ብቻ ሳይሆን ህዝብ ጥሎበት የነበረውን የመታመን ተስፋ ጭምር ነው።
እጅ መስጠት ማለት፦ ለተሰውት ጓዶች መስዋዕትነት እውቅና መንፈግ፤ ትግሉ የተነሳለትን በደል አምኖ መቀበል፤ እና የጠላትን የበላይነት ማረጋገጥ ማለት ነው።
አንድ ታጋይ መሣሪያውን ይዞ ለጠላት እጅ ሲሰጥ ለራሱ ጊዜያዊ ሰላምን ሊያገኝ ይችላል፤ ነገር ግን እታገልልሀለሁ ሲለው ለነበረው ህዝብ ጠላት በመሆን ዳግም ውርደትን ይከናነባል።
በተለይ የአመራር ድክመት ስላለ እጅ ሰጠሁ የሚለው ሰበብ በሌሎች አማራጮች ሊመከት የሚችል ነው።
ቀዳሚው ውስጣዊ ተሃድሶ ማድረግ ሲሆን በትግሉ ውስጥ ያሉ ስህተቶችን በውስጠ ድርጅታዊ ትግል በማስተካከል የሚፈታ ነው፣ ሌላኛው ቀጠና መቀየር ሲሆን አስፈላጊ ተደርጎ ባይወሰድም፤ የፈለገ መራር ሁኔታ ቢፈጠር እንኳን የትግል ሚስጥርን ይዞና መሣሪያን ሳያስረክቡ ለጊዜው ከእንቅስቃሴ መራቅ እጅ ሰጥቶ የትግል ባንዳ ከመሆን እጅግ የላቀ ክብር አለው።
ትግልን መክዳት ከወቅታዊ ፖለቲካ ባለፈ የታሪክ ተጠያቂነትን ያስከትላል። ታሪክ መዝጋቢ እንጂ መሃሪ አይደለም። ዛሬ እጅ የሰጡ አመራሮችና ታጋዮች ነገ በሚገነባው አዲስ ስርዓት ውስጥ "ትግሉን የሸጡ" ባንዳ ተብለው ከመፈረጅ አይድኑም።
የአንድ ትግል ውጤት ባልታወቀበትና ህዝቡ አሁንም በመከራ ውስጥ ባለበት ወቅት፣ መሣሪያን ለጠላት ማስረከብ በታሪክ ፊት "ከዳተኝነት" ተብሎ ይጻፋል።
ትውልድም የሚዘክረው በፅናት የቆሙትን እንጂ በፈተና ወቅት የህዝብን አደራ ጥለው የሄዱትን አይደለም።
የአመራር ድክመት የትግል ፈተና እንጂ የክህደት ምክንያት ሊሆን አይገባም። ለህዝብ ነፃነት የቆመ ታጋይ አማራጩ ፅናት ወይም ክብር ያለው መስዋዕትነት እንጂ ለጠላት እጅ መስጠት አይደለም።
እጅ መስጠት ከታሪክ ተጠያቂነት አያድንም፤ ይልቁንም ለዘላለም የሚከተል የህሊና ቁስልና የታሪክ ጠባሳ ሆኖ ይቀራል።
ዛሬ እጅ የሰጡ አመራሮችና ታጋዮችም ነገ በሚገነባው አዲስ ስርዓት ውስጥ "ትግሉን የሸጡ" ባንዳዎች ተብለው ከመፈረጅ አይድኑም!
ማስታወሻ:- "አመራር" የሚለው ቃል በቀጥታ ግለሰቦችን የሚመለከት ሳይሆን ጥቅል ድርጅታዊ አቅጣጫዎችን የሚወክሉ "የአመራር" አካሄዶችን የሚወክል ነው።
ያሬድ ሙሉነህ !
@highlight
1 086
የብልፅግና አገዛዝ የውድቀት ማሳያዎች !
በዛሬው ዕለት በመላው የአማራ ክልል ከተሞች "ገዳዮቻችንን አናነግስም" በሚል የተካሄደው የተቃውሞ ሰልፍ፤ የብልፅግናው አገዛዝ በአማራ ክልል የገጠመውን የመጨረሻ ምዕራፍ የፖለቲካ ውድቀት በግልጽ ያሳየ ክስተት ሆኖ ተመዝግቧል።
1. የሞራል እና የሕጋዊነት (Legitimacy) መሸርሸር
"ገዳዮቻችንን አንመርጥም" የሚለው የህዝብ መሪ ቃል፣ በሕዝቡና በአገዛዙ መካከል ያለውን ግንኙነት ሙሉ በሙሉ መቋረጡን ያሳያል።
ሕዝቡ አገዛዙን እንደ "ገዳይ" መፈረጁ፣ ሥርዓቱ በሕዝብ ዘንድ ያለውን ማንኛውንም ዓይነት የሞራል ተቀባይነት ማጣቱን ያረጋግጣል።
2. የምርጫ ካርዱ ዋጋ ማጣት
ብልፅግና የገጠመውን የፖለቲካ ቀውስ በምርጫ ስም ለማደስና ዓለም አቀፍ ድጋፍ ለማግኘት አቅዶ የነበረ ቢሆንም፣ ሕዝቡ ምርጫው ገና ሳይካሄድ "የሞራልና የሕጋዊነት መሰረት የሌለው" በማለት ውድቅ ማድረጉ አገዛዙ የያዘው የመጨረሻው የፖለቲካ መውጫ ቀዳዳ መዘጋቱን ያሳያል።
ይህም ምርጫው የሕዝብን ውክልና ሳይሆን የአገዛዙን ዕድሜ ለማራዘም የሚደረግ "የአየር ላይ ድራማ" መሆኑን ሕዝቡ መረዳቱን ያመላክታል።
3. የአስተዳደራዊ መዋቅሩ መፈራረስ
ተቃውሞው በክልሉ ዋና ዋና ከተሞችና በበርካታ አካባቢዎች በአንድ ጊዜ መቀስቀሱ፣ የብልፅግና መዋቅር በመሬት ላይ ያለውን ቁጥጥር ማጣቱን ያረጋግጣል።
ብልፅግናዊ መዋቅሩ ከሕዝብ እምቢተኝነት ጋር መጋፈጡ፣ የአገዛዙን የትዕዛዝ ሰንሰለትና መበጣጠሱንና መዋቅራዊ ፍርሰቱን ያሳያል።
4. የኃይል ሚዛኑ መቀየር
ይህ መጠነ ሰፊ ሕዝባዊ እምቢተኝነት፣ ሕዝቡ የታመቀ ቁጭቱን ይዞ ወደ አደባባይ መውጣቱን ያሳያል። አገዛዙ በኃይልና በጭቆና ሰልፎችን ለማፈን ቢሞክርም፣ የሕዝቡ ቁጣ ግን አቅጣጫውን ወደ "ፍጹም እምቢተኝነት" ቀይሮታል።
ይህ የኃይል ሚዛኑ ከብልፅግና ቁጥጥር ውጪ መሆኑንና ስርዓቱ ድጋሚ ሊጠገን የማይችል የተቀባይነት ቀውስ ውስጥ መግባቱን የገለፀ ትልቅ የውድቀት ምልክት ነው።
5. የፕሮፓጋንዳው መክሸፍ
አገዛዙ 8ኛ አመት የጭፍጨፋ በዓለ ሲመቱን በሚያከብርበት ዕለት "ሀገርን ከመፈራረስ አድነናል በሚል የውድቀት ትርክት ላይ ቢጠመድም፣ በተግባር ግን ሕዝቡ በአደባባይ "ገዳዮቻችን" እያለ መጮሁ፣ የአገዛዙ የሚዲያና የፕሮፓጋንዳ ሥራዎች በመሬት ላይ ካለው እውነታ ጋር ፍጹም ተቃራኒ መሆናቸውንና ውጤት አልባ መሆናቸውን ያረጋግጣል።
አብይ አህመድ ስልጣን ሲቆናጠጥ ለሽንገላ ቃል የገባው የሀሰት ዲሞክራሲን በጠመንጃ አፈሙዝ፣ የሰበከውን የይስሙላ ሰላም ደግሞ በማያልቅ ጦርነት ተክቶ ሀገሪቱን በታሪኳ አይታው የማታውቀው የውድቀት አዘቅት ውስጥ ከቷታል ሲል ህዝቡ በአደባባይ የስርዓት ለውጥ እንዲመጣ ጠይቋል።
በዛሬው ዕለት መጋቢት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የታየው ሕዝባዊ ቁጣ፣ ብልፅግና በአማራ ክልል ብቻ ሳይሆን በመላው ሀገሪቱ የገጠመው ጥልቅ የፖለቲካ ኪሳራ ማሳያ ነው።
አገዛዙ በምርጫ ስም ራሱን ለመቀባት የሚያደርገው ጥረት፣ በሕዝቡ "ገዳዮቻችንን አንመርጥም" በሚል ጠንካራ የታቃውሞ አቋም ጋር መጋጨቱም ሥርዓቱ ወደ መጨረሻው የመውደቂያ ምዕራፍ መሸጋገሩን አመላካች ነው።
ይህንን ህዝባዊ በትር በኑሮ ውድነትና በመዋቅራዊ በደል የተማረረው የመሀል ሀገሩ ዜጋ በከተማ አመፅ ቢቀላቀለው ደግሞ ተዓምራዊ ለውጥ በአጭር ጊዜ ይመዘገባል።
ድል ለፋኖ 💪💪💪
1 086
+3
ዛሬ መጋቢት 24 ቀን 2018 ዓ.ም "ገዳዮቻችንን በምርጫ ካርድ አናነግስም" በሚል መሪ ቃል በመላው አማራ ክልል ምርጫውን የሚቃወም የህዝብ ድምፅ እየተስተጋባ ነው።
ይህ ምስራቅ ጎጃም ዞን-ዲማ ከተማ እየተካሄደ ያለ ትዕይንተ ህዝብ ነው።
1 086
+3
ዛሬ መጋቢት 24 ቀን 2018 ዓ.ም "ገዳዮቻችንን በምርጫ ካርድ አናነግስም" በሚል መሪ ቃል በመላው አማራ ክልል ምርጫውን የሚቃወም የህዝብ ድምፅ እየተስተጋባ ነው።
"ህዝብን እየገደሉ ምረጡኝ ማለት የህልም ቅዠት ነው"
ይህ የጃዊ-ፊልፊል እና አካባቢው ማህበረሰብ እያካሄደ ያለው ትዕይንተ ህዝብ ነው።
1 086
+2
ዛሬ መጋቢት 24 ቀን 2018 ዓ.ም "ገዳዮቻችንን በምርጫ ካርድ አናነግስም" በሚል መሪ ቃል በመላው አማራ ክልል ምርጫውን የሚቃወም የህዝብ ድምፅ እየተስተጋባ ነው።
ይህ ሸዋ መዘዞ ከተማ እየተካሄደ ያለ ትዕይንተ ህዝብ ነው።
1 086
+1
ዛሬ መጋቢት 24 ቀን 2018 ዓ.ም "ገዳዮቻችንን በምርጫ ካርድ አናነግስም" በሚል መሪ ቃል በመላው አማራ ክልል ምርጫውን የሚቃወም የህዝብ ድምፅ እየተስተጋባ ነው።
ይህ ደቡብ ጎንደር ስማዳ ወረዳ የኳሳ ከተማ እየተካሄደ ያለ ትዕይንተ ህዝብ ነው።
