1 087
Subscribers
No data24 hours
-77 days
-2630 days
Posts Archive
1 087
አቶ ደሳለኝ ጫኔ ከቀጥተኛ የፖለቲካ እንቅስቃሴ ራሳቸውን ማግለላቸውን አስታወቁ
ባለፉት አምስት ዓመታት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል የነበሩት ታዋቂው ተቃዋሚ ፖለቲከኛ አቶ ደሳለኝ ጫኔ፣ የፓርላማ ቆይታቸውን ማጠናቀቃቸውን ተከትሎ ከማንኛውም ቀጥተኛ የፖለቲካ እንቅስቃሴ መውጣታቸውን በይፋ ገለጹ።
በትናንትናው ዕለት የምክር ቤቱ ዘመን ማክተሙን ተከትሎ ውሳኔያቸውን ያሳወቁት አቶ ደሳለኝ፣ ለጊዜው በማንኛውም የፖለቲካ ፓርቲ ውስጥ በአባልነትም ሆነ በደጋፊነት እንደማይሳተፉ አስታውቀዋል።
ቀደም ሲል በዩኒቨርሲቲ መምህርነት እና በሲቪክ ማኅበራት መሪነት ያገለገሉት ምሁር ፣ ባለፉት ስምንት ዓመታት በፖለቲካ አመራርነት እንዲሁም የባሕር ዳር ከተማ መራጮችን በመወከል በፓርላማ በንቁ ተቃዋሚነት አገልግለዋል።
በዚህ ጉዟቸው ወቅትም ለ45 ቀናት መታሰራቸውን ጠቅሰዋል።
ከ10 ዓመታት የፖለቲካ ድካም መልስ ወደ ግሉ ዘርፍ በመግባት በሙያቸው ሀገርን ለማገልገልና ለቤተሰባቸው ጊዜ ለመስጠት መወሰናቸውን አስታውቀዋል።
ከተቃውሞ ፖለቲካው ቢወጡም፣ በሀገራዊ የሰላም እና የብሔራዊ ውይይት ጉዳዮች ላይ በሙያቸው አስተዋጽኦ ማድረጋቸውን እንደሚቀጥሉ ገልፀዋል።
1 087
በተጉለት አውራጃ ደረፎ ክላስተር የገዥው ጥምር ጦር በንጹሃን ላይ ዘረፋ ሲፈፅም፡ አድማ ብተና ሀይሎች ፋኖን ተቀላቅለዋል!!
01/11/2018 ዓ.ም
ከደብረ ብርሃን ተነስቶ ወደ አንኮበር ቀጠና ደረፎ ቀበሌ ያመራውና ራሱን "ጥምር ጦር" ብሎ የሚጠራው የመከላከያና አድማ ብተና ሰራዊት፣ የፋኖ ኃይላችን በሌሉበት የህዝብ ንብረት መዝረፉ ታወቀ።
ሰራዊቱ ሰኔ 29 ቀን 2018 ዓ.ም በየቀበሌው በመግባት አርሶ አደሮች ለክረምት ዝግጅት ያከማቹትን 10 ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ እንዲሁም አቶ ኪዳኔ ከተባለ አርሶ አደር ቤት በመግባት ሥስት(3) ጭነት ባቄላ ዘርፎ መውሰዱ ተረጋግጧል። በዚህ የዘረፋ ተግባር ላይ ለሆዳቸው ያደሩ የአካባቢው ሚሊሻዎችም የተሳተፉበት መሆናቸው ተረጋግጧል።
ድርጊቱ እንደተሰማ የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ፣ መሐመድ ቢሆነኝ ኮር እቴጌ ጣይቱ ክፍለ ጦር በፍጥነት ወደ ስፍራው ቢያመራም፣ የገዥው አካል ጦር የዘረፈውን ንብረት ጭኖ ወደ ደብረ ብርሃን ለመፈርጠጥ ተገዷል።
ይሕ በእንዲሕ እዳለ አገዛዙ በንፁሀን ላይ የሚፈፅመውን ግፍና ዘረፋ የሠሙት የአገዛዙ ደጀን የነበሩት አድማ ብተና ኃይሎች ፋኖን ተቀላቅለዋል። በዚሕም ሁለት የአድማ ብተና አባላት የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ አፄ አምደጽዮን ኮር ራንቦ ክፍለ ጦርን ከነ ሙሉ ትጥቃቸው በቀን 01/11/2018 ዓ.ም ተቀላቅለዋል።
" ክብር ለትግሉ ሠማዕታት!
" ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
1 087
በመንዝ አውራጃ ፤ ጥርጥራ ቀበሌ የደፈጣ ጥቃት፤ የአገዛዙ 104ኛ ኮማንዶ ክፍለ ጦር በፋኖ መብረቃዊ እርምጃ ጉዳት አስተናገደ!!
ሰኔ 30/2018 ዓ.ም
በትጥቅ ትግሉ ስትራቴጂካዊ የደፈጣ ውጊያ መርህ መሰረት፣ የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ አፄ አምደ ፅዮን ኮር ስር የሚንቀሳቀሰው የአፄ ምኒልክ ክፍለጦር (በአባተ ፩ኛ ሻለቃ) በመንዝ ላሎ ክላስተር ጥራጥር ቀበሌ ወታደራዊ የበላይነትን በማድረግ አንጸባራቂ ድል አስመዝግቧል።
ከሰኔ 29 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 9:00 ሰዓት ጀምሮ እስከ ምሽቱ 12:00 ድረስ በተካሄደው የሰዓታት ጠንካራ ውጊያ፣ ከመንዝ ላሎ ወገሬ ከተማ ተነስቶ ወደ ጥርጥራ ቀበሌ ለመንቀሳቀስ የሞከረው የብልፅግናው 104ኛ ኮማንዶ ክፍለ ጦር "ሀያደጋ" በተባለ ልዩ ቦታ ላይ በታቀደ ድንገተኛ የደፈጣ ጥቃት እቅዱ ከሽፏል።
የኮሩ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ክፍል ለዕዙ ባስተላለፈው ግንባር መረጃ መሰረት፣ የፋኖ ስልታዊ ጥቃት የወታደራዊ ግዳጅ አፈጻጸሙን ሙሉ በሙሉ ያሳካ ነበር። በዚህም የአገዛዙ የጥምር ጦር አባላት የነበሩ አንድ የ፶ አለቃ ማዕረግ ያለው የሚሊሻ አመራርን ጨምሮ ከ10 በላይ ወታደሮች የተደመሰሱ ሲሆን፣ በርካቶች ቆስለው በአምቡላንስና በሕዝብ ትራንስፖርት ተሽከርካሪዎች ወደ ሞላሌ ከተማ ሆስፒታል እደላከ ተረጋግጧል።
በሜዳው ፍልሚያ ከፍተኛ የሰው ኃይልና የሞራል ስብራት የገጠመው የአገዛዙ ሰራዊት፣ ሽንፈቱን ለመቀልበስ ከመንዝ ቀያ ዘመሮ ከተማ የኃይል ማዛባት (ማጠናከሪያ ኃይል) ለማንቀሳቀስ ቢሞክርም በምኒልክ ልጆች ፅኑ መከላከል ወደ ኋላ እንዲያፈገፍግ ተገዷል። ሰራዊቱ ወታደራዊ ግዳጁን ማሳካት ሲያቅተው፣ የክፍለ ጦሩ አስተዳደር ኃላፊ የፋኖ ልዑል እሱባለውን ቤተሰቦች መኖሪያ ቤት በር በመስበርና ንብረት በመዝረፍ የተለመደውን የውንብድና ተግባሩን ፈፅሟል።
ይህ በመንዝ ላሎ ቀጠና የተመዘገበው ድል፣ በትጥቅ ትግሉ ሂደት የፋኖን የደፈጣ ውጊያ ብቃት፣ የመረጃ የበላይነት እና የተደራጀ አቅም በተግባር ያሳየ ሲሆን፣ የአገዛዙ ኮማንዶ ክፍለ ጦር መራር ሽንፈት አከናንቦ ወደ መጣበት እንዲፈርጠጥ አድርጎታል።
"ክብር ለትግሉ ሠማዕታት!
"ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!"
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
1 087
ትናንት ለዛሬ ሌሊት በምዕራብ ወሎ ግንባር ቢሊ ታዳጊ ከተማን ሙሉ በሙሉ ነጻ ማድረግ ተችሏል!!
የአፋብን ወሎ ቤተ- አማራ ምኒልክ እዝ 105 ኛ ኮር 29ኛ ክፍለ ጦር በሰራው የሌሊት ኦፕሬሽን ቢሊ ታዳጊ ከተማን ነጻ ማውጣት የቻለ ሲሆን ከአመሻሽ 12 ሰዓት ጀምሮ እስከ እኩለ ሌሊት ድረስ ሞት አይፈሬዎቹ የመካነሰላም አናብስት ጠላትን መፈናፈኛ አሳጥተው የጦር ሰፈራቸውን አስለቅቀዋል::
ኦፕሬሽኑ ላይ የተሳተፉት የ29ኛ ክፍለ ጦር ቃኝ አባላት በተለመደው ፈጣን የውጊያ ስልታቸው ጠላትን አናብዘው ሙት እና ቁስለኛ አስታቅፈውታል:: በሌሊቱ ኦፕሬሽን የተደመሰሱ እና የቆሰሉ የጠላት ኃይል አባላትን ትክክለኛ ቁጥር ለማወቅ የሰአቱ ሁኔታ አስቻይ ባይሆንም የውስጥ ወታደራዊ ምንጮች እንደተናገሩት ጠላት ያላሰበው ሽንፈት ገጥሞት አባላቱን ተነጥቋል::
ከሞት ያድነው ይመስል 3 ዲሽቃና 2 ሞርተር ከበርካታ የቡድን መሳሪያዎች ጋር ይዞ የነበረው ጠላት የ29 ክፍለ ጦር ቃኝን ወደ ሌላ ቀጠና መንቀሳቀስ ተከትሎ ወደ ቢሊ ታዳጊ ከተማ ቢገባም ቃኝይቱ በብርሀን ፍጥነት ተመልሳ ከ3ተኛ ሻለቃ ጋር በመናበብ ስትለበልበው የተማመነበትን የሽፋን እና የቡድን መሳሪያ ሁሉ ነቅሎ እግሬ አውጭኝ ብሎ እንደ ልማዱ ወደመጣበት ሊፈረጥጥ ችሏል::
መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!!
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ሚዲያና ኮሚዩኒኬሽን መምሪያ!!
ሰኔ 30 ቀን 2018 ዓ.ም
1 087
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ - ምኒልክ ዕዝ አስቸኳይ የሚዲያና የዲጂታል ስነ-ምግባር መመሪያ
ለዕዙ አመራሮች፣ አባላት፣ ደጋፊዎች፣ የሚዲያ ባለሙያዎች እና የቲክቶክ ተጠቃሚዎች በሙሉ፤
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ - ምኒልክ ዕዝ የጀመረው የተቀደሰ የትግል ጉዞ በታሪክ እውነታ፣ በፍትህ እና በነፃነት መርሆዎች ላይ የተመሰረተ ነው። ይህ ታላቅ ትግል በሜዳ ላይ የሚደረግ የትጥቅና የአካል ብቃት ፍልሚያ ብቻ ሳይሆን፤ በቃል፣ በፅሁፍ እና በምስል የሚካሄድ የሞራል፣ የሕሊና እና የስትራቴጂክ መረጃ ጦርነት ጭምር መሆኑን ዕዛችን በጥልቀት ይገነዘባል። ስለሆነም የነፃነት ጉዟችን በመረጃ እና በከፍተኛ ስነ-ምግባር የታነፀ የዲጂታል ዲፕሎማሲን አብሮ ማስኬድ ይኖርበታል።
የድርጅታችንም ሆነ የዕዛችን ስም፣ አርማ እና ዓላማ ለግል ጥቅም፣ ለስሜታዊነት መተንፈሻ ወይም ለጠላት የፕሮፓጋንዳ ማጥቂያ እንዲሆኑ መፍቀድ ትግሉን ማዳከም ብቻ ሳይሆን የውስጥ አንድነታችንንም አደጋ ላይ ይጥላል። ዕዛችን እስካሁን ባለው የሚዲያ አጠቃቀም ረገድ የተሻለ ስም አስከብሮ የቆየ ቢሆንም፣ ይህንን ስኬት ወደ ላቀ እና ስልታዊ ደረጃ ለማሸጋገር ከዛሬ ጀምሮ የሚከተለው የሚዲያ ስነ-ምግባር እና የድርጅታዊ ተጠያቂነት አስገዳጅ መመሪያ ወጥቶ ስራ ላይ ውሏል።
1. የኦፊሴላዊ መረጃ መስመሮች (Official Channels)
ማንኛውም የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ - ምኒልክ ዕዝን ስም፣ አርማ ወይም ወታደራዊ እንቅስቃሴ የሚመለከት መረጃ መተላለፍ ያለበት በይፋ በታወቁት የዕዛችን የቴሌግራም፣ የፌስቡክ ገጾች እና እውቅና በተሰጣቸው ሀቀኛ አጋር ሚዲያዎች ላይ ብቻ ነው። ከእነዚህ ውጪ በግልም ሆነ በቡድን ስም የሚለቀቁ ማናቸውም መረጃዎች ዕዙን የማይወክሉ እና የእኛን አቋም የማይገልጹ መሆኑን እናሳውቃለን።
2. የዲጂታል ስነ-ምግባር (ለሚዲያ ባለሙያዎች እና ቲክቶከሮች)
በዕዛችን ስም የሚንቀሳቀሱ እና ድጋፍ የሚሰጡ ማናቸውም የሚዲያ አካላት ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ድንጋጌዎችን፣ የጦርነት ህግጋትን (Rules of Engagement) እና የዲጂታል ደህንነት መርሆዎችን የማክበር ግዴታ አለባቸው። በተለይም ከሌሎች ህዝቦች ጋር ቅራኔን የሚፈጥሩ የጥላቻ ንግግሮችን፣ የዘር ቅስቀሳዎችን ወይም ዕዛችንን ከዓለም አቀፍ ህግጋት ጋር የሚያጋጩ ይዘቶችን ማሰራጨት በጥብቅ የተከለከለ ነው።
3. ድርጅታዊ ዲሲፕሊን እና የውስጥ አንድነት
የዕዛችንን መዋቅር እና ስም ሽፋን በማድረግ የውስጥ አንድነትን የሚያናጉ፣ በየደረጃው ያሉ አመራሮችን ያለአግባብ ስም የሚያጠፉ እና የሚሳደቡ፣ ወይም የድርጅቱን ስልታዊ ምስጢር የሚያባክኑ ግለሰቦች ላይ ጥብቅ ድርጅታዊ እርምጃ ይወሰዳል። የእውነተኛ አርበኛ ዋነኛ መገለጫው ዲሲፕሊን ነው። የዕዙን ስም ለግል ታዋቂነት (የፎሎወር ማብዛት) ወይም ለቡድን ፍላጎት ማሟያ ማድረግ ትግሉን ማቀጨጭ በመሆኑ፣ ዕዛችን በዚህ ላይ ከፍተኛ ቁጥጥር እና ተጠያቂነት ያሰፍናል።
4. የይዘት ቁጥጥር እና ዓለም አቀፍ ህግጋት
ምኒልክ ዕዝ በዓለም አቀፍ ህግ የተከለከሉ እና እንደ ጦር ወንጀል ሊያስቆጥሩ የሚችሉ ምስሎችን፣ ቪዲዮዎችን ወይም መመሪያዎችን ማሰራጨትን ፈጽሞ አይቀበልም። የሰብአዊ መብት ጥሰት የሚታይባቸውን ምስሎች ማጋራት የትግሉን ገጽታ ከማበላሸቱም በላይ፣ ነገ ለምናደርገው ህጋዊና ፖለቲካዊ ትግል ትልቅ እንቅፋት ነው። በመሆኑም መሰል ይዘቶችን የሚለቅ ማንኛውም አካል በህግና በድርጅት ፊት ሙሉ ኃላፊነቱን ይወስዳል።
5. አስመሳይነትንና የሃሰት ወሬዎችን ስለመከላከል
በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ ሀገር ሆናችሁ በቲክቶክ፣ በዩቲዩብ እና በሌሎች የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በቀጥታ ስርጭት (Live) በመግባት፣ ከዕዙ ጋር ግንኙነት እንዳላችሁ በማስመሰል የራስን አጀንዳ የሚያራምዱ ግለሰቦች ከምኒልክ ዕዝ ጋር ምንም ዓይነት ትስስር የሌላቸው መሆኑን በይፋ እንገልጻለን። ከዚህ ማሳሰቢያ በኋላ ሕዝብን በሚያደናግር መልኩ ዕዙን አስመስሎ የሚንቀሳቀስ ማንኛውም የሚዲያ ተጠቃሚ ላይ ዕዙ ህጋዊና ድርጅታዊ እርምጃ ይወስዳል።
6. ክትትልና ተጠያቂነት
ከዚህ መመሪያ ውጭ የሚንቀሳቀሱ፣ ወሬ የሚያናፍሱ እና ዲሲፕሊን የጎደላቸው ግለሰቦች ጉዳይ በየደረጃው በሚገኙ የዕዛችን የደህንነት እና የህግ መምሪያዎች በጥብቅ የሚመረመር ሲሆን፣ እንደ ጥፋቱ ክብደት ፅኑ ድርጅታዊ ቅጣት ይጠብቃቸዋል።
ማጠቃለያ ማሳሰቢያ፦
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ - ምኒልክ ዕዝ ስም ለተቀደሰና ለታላቅ ዓላማ የቆመ እንጂ ለግል ምኞት መጫወቻ አይደለም። ይህንን መመሪያ ጥሰው በሚገኙ አካላት ላይ ዕዙ ግንኙነቱን ሙሉ በሙሉ የሚያቋርጥ ሲሆን፣ አስገዳጅ ሆኖ ሲገኝም ጉዳያቸው ለሕዝብ ይፋ ይደረጋል።
መላው የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ አባላት እና ደጋፊዎች ይህንን መመሪያ በንቃት በመተግበር የትግላችንን ስም፣ ክብር እና ድል እንድታስጠብቁ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።
ማሳሰቢያ ለደገፊ ሚዲያዎች፦ የተከበራችሁና የተወደዳችሁ የትግላችን ደጋፊ ሚዲያዎች በሙሉ፤ ከዕዙ ሕዝብ ግንኙነት እንዲሁም ሚዲያና ኮሚኒኬሽን የሚወጡ ይፋዊ መግለጫዎችን ሳይጨመርና ሳይቀነስ (ባሉበት ይዘት) ለሕዝብ ማድረስ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።
ህልዉናችን በተባበረ ክንዳችን!
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ - ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ የህዝብ ግንኙነት መምሪያ
1 087
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ እና የአፋብን ምኒልክ ዕዝ ወቅታዊ የጋራ የውይይትና ህዝባዊ መድረኮችን አካሄደ!!
ቀን 29/10/2018 ዓ.ም
በቀነ 28/10/2018 ዓ.ም በአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ፣ አፄ ዘረያዕቆብ ፩ኛ ኮር በአፄ ይኩኖ አምላክ ክፍለ ጦር ስር ብርጌዶች በተገኙበት በወቅታዊ የጠላት አሰላለፍ ዙሪያ ሰፊ ውይይት ተካሂዷል። በመድረኩ ላይ የክፍለ ጦሩ ዋና ሰብሳቢ ፋኖ አቡሽ ጌታሁን ሰራዊቱን የሚያነቃቃና የሞራል ዝግጁነት እንዲኖረው የሚያደርግ ንግግር ያደረጉ ሲሆን፣ ሌሎች የክፍለ ጦር አመራሮችም በተመሳሳይ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።
በዕለቱ የተገኙት የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ዘመቻ መሪ ፋኖ አሳልፍ ደስታ (ቀጭን) አባት አርበኛው የሰራዊቱ የኋላ ደጀን በመሆን ትግሉን መደገፍና ማታገል እንዳለበት ገልጿል፣ ለዚህም ከወትሮው በተለየ ሁኔታ መዘጋጀት እንደሚገባ አሳስበዋል። የዕለቱ የክብር እንግዳ የነበሩው የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ዋና መሪ እንጅነር ደሳለኝ ሲያስብ ሸዋ በበኩላቸው በድርጅታዊ አንድነቱ መፈጠር የተሰማውን ደስታ ገልፆ፣ እኛ የአባቶቻችን ልጆች ነን" ካሉ በኋላ ጠላትን የማያዳግም እርምጃ ለመውሰድ ሞትን መፍራት እንደማይገባና ሞትን የማይፈራ ሰራዊት ሁልጊዜም እንደሚያሸንፍ ገልጿል ለዚህም ሁሉም ዝግጁ እንዲሆን ጥሪ አቅርቧል። አባት አርበኞቹም በበኩላቸው በተደረገው የማነቃቃትና ጠላትን በጋራ የመመከት ውይይት እንዲሁም በታየው የወትሮ ዝግጁነት ፕሮግራም እጅግ መደሰታቸውን አስታውቀዋል።
በሌላ ዜና ከቀን 27-28/10/2018 ለተከታታይ ሁለት ቀን በግሼ ራቤል ወረዳ በጎልታ መዘራዝር ቀበሌ ከሁለቱም እዞች (ከአፋብን ምኒልክ እዝ እና ከአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው እዝ) የተወጣጡ አመራሮች የተገኙበት ህዝባዊ መድረክ ተካሂዷል። ከ700 በላይ የህዝብ ቁጥር የተገኘበትና ከእስልምናም ከክርስትናም የሃይማኖት አባቶች የተሳተፉበት ይህ ስብሰባ በጸሎት ተጀምሮ በጸሎት ተጠናቋል። በመድረኩ ማጠቃለያ ላይም ከማህበረሰቡና ከአመራሩ የተገኙ ጥንካሬዎችን በማስቀጠልና ያሉትን ክፍተቶች በመሙላት ከዚህ በላይ በጋራ ለመስራት ስምምነት ላይ ተደርሶ ስብሰባው በሰላም ተጠናቋል።
የአፋብን ሽዋ ጠቅላይ ግዛት ዓሳምነው ዕዝ ህዝብ ግኑኝነት መምሪያ
1 087
የራስ አበበ አረጋይ ክፍለ ጦር ልዩ የወታደራዊና ፖለቲካዊ አቅም ግንባታ ተሃድሶ መርሃ ግብር አከናወነ!!
ሰኔ 29/2018 ዓ.ም
ተሃድሶ ለወታደር ዘርፈ ብዙ የስኬታማ ወታደራዊ ግንባታ ስራዎች የሚከናወኑበት የወታደራዊ ሳይንስ ክፍል አካል ሲሆን፣ ወታደራዊ ግዳጆችን በመገምገም፣ የአመርና የሰራዊቱን ወቅታዊ የፖለቲካ ግንዛቤ በማሳደግ ህዝባዊነትን የተላበሰ የፋኖ ሰራዊት መገንባትን ራዕይ ያደረገ ለየትኛውም ግዳጅ ብቁ እና በከፍተኛ የሞራል ስንቅ የተሞላ አማራዊ ስነልቦና የተላበሰ ዘመናዊ የአማራ ፋኖ ሰራዊት የማደራጀት ዓላማ አንግቦ የፖለቲካዊና የወታደራዊ ሳይንስ ትምህርቶች በጥምረት በአንድ መድረክ ላይ የሚሰጡበት ዘመናዊ የማታገያ ጥበብ ነው።
የአፋበን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የአፄ አምደ ፅዮን ኮር አካል የሆነው ለራስ አበበ አረጋይ ክፍለጦር ከሰኔ 24/2018 ዓ.ም ጀምሮ ለተከታታይ አምሥት(5) ቀናት ልዩ የተሃድሶ መርሀ ግብር ለክፍለጦሩ አመራርና አባላት ሰፊ ፖለቲካዊና ወታደራዊ ግንባታ በመስጠት የተሳካ የግንባታ መድረክ ማካሄዱን የአፄ አምደ ፅዮን ኮር ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ክፍል ለዕዙ ዜና ክፍል በላከው የግንባር መረጃ አስታውቋል።
በዚሁ የግምገማና የግንባታ መድረክ ላይ በየደረጃው የሚገኙ የድርጅትና የዕዝ አመራሮች በአካል ተገኝተው ለክፍለ ጦሩ አባላት ውጤታማ ስልጠናውን የሰጡ ሲሆን፣ የአፋብን ዘመቻ መምሪያ ኃላፊ ፊትአውራሪ ባዩ አለባቸው እና የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የህዝብ ግንኙነት መምሪያ ኃላፊ ፋኖ አከበር ስመኘው እንዲሁም ሌሎች ከፍተኛ የአሳምነው ዕዝ አመራሮች በተዘጋጀው የተሃድሶ መርሀ ግብር ላይ በአካል ተገኝተው ለራስ አበበ አረጋይ ክፍለጦር አባላትና አመራሮች በቂ ግንዛቤ መስጠታቸውን ኮሩ አክሎ ገልጿል።
በመድረኩም ስለ ትግሉ አሁናዊ ሁኔታ፣ ስለ ማህበረሰብ አያያዝ እንዲሁም ስለ ውስጣዊ አንድነት ሰፊና ጥልቅ ውይይት በማድረግ በተለዬ አቀባበል ዓላማና ግብ ተኮር መግባባቶች የተፈጠሩበት የተሳካ መድረክ ሲከናወን ሰንብቷል።
ይህንን ድርጅታዊ የሆነ ፖለቲካዊና ወታደራዊ ግንባታ ተከትሎ፣ የሰራዊቱን ሞራል ይበልጥ ከፍ ያደረገ ደማቅ የተሃድሶ መርሀ ግብር ሲከናወን፣ ይህን የተግባር ተኮር ስልጠና እስከ ግንባር ምሽጎች ድረስ በመዝለቅ የሰራዊቱ የሞራል ማማ በመሆን የሚታወቁት የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የአፄ ዘረያዕቆብ ፩ኛ ኮር የናደው ክፍለ ጦር የባህል ቡድን አባላት የፕሮግራሙ ድምቀት ሆነው የተሳተፉበት መርሀ ግብር የተካሔደ ሲሆን፣ በዕለቱም የአማራን ማንነትና ባህል የሚገልጹ ልዩ ልዩ የባህል ጭውውቶችና ክዋኔዎች ቀርበው ለሰራዊቱ አባላት ከማነቃቃት አልፎ ለሰራዊቱ የሞራል ስንቅ በመሆን የተሳካ መድረክ ተከናውኗል።
የስልጠናው ተሳታፊ ከሆኑት የራስ አበበ አረጋይ ክፍለጦር ሰራዊትና አመራሮች በሰጡት አስተያየት፣ ይህ ዓይነቱ ድርጅታዊ ስራና የግንባታ መርሃ ግብር ቀደም ሲል የነበሩ በርካታ ብዥታዎችን ያጠራ መሆኑን በመግለፅ፣ አያይዘውም ይህ መድረክ ቀጣይ ለምናደርገው የተቀናጀ ፖለቲካዊ የትጥቅ ትግል ምቹ ሁኔታ የፈጠረ ነው፤ ትግላችንም ከተናጠል ወደ ህብረት የተሸጋገረበት በመሆኑ፣ በማንኛውም ሁኔታና ሰዓት ለህልውና ትግሉ የምንከፍለውን መስዋዕትነት በደስታና በሙሉ ልብ እንድንወጣ ያደርገናል ብለዋል።
ራስ አበበ አረጋይ ክፍለ ጦር የተሰየመበት የጀግናው የራስ አበበ አረጋይ ስም ተራ ስያሜ ብቻ እንዳልሆነ የገለጹት አመራሮቹና አባላቱ፣ የህዝብ ፍቅርንና በፅናት ለዓላማ የሚደረግ ተጋድሎን ከክፍለ ጦሩ የአሁናዊ ህልውና ትግል ጋር በማቆራኘት የስልጠና ቆይታቸውን ከታሪክ ጋር አነፃፅረው ሀሳባቸውን ገልፀዋል።
የራስ አበበ አረጋይ ክፍለ ጦርም ከትንሽ የሰው ሃይልና ትጥቅ በመነሳት በከፍተኛ ፍጥነት አሁን ግዙፍ ከሚባሉ ክፍለ ጦሮች ተርታ እንድትሰለፍ ያስቻላት የአመራሮቿ እና ሰራዊቱ የአርበኛው ራስ አበበ አረጋይ የፅናት ፈለግን በመላበስ ሌት ከቀን ተግተው በመስራታቸው መሆኑንም በመድረኩ አስታውሰዋል። ታዋቂው አርበኛ ራስ አበበ አረጋይ በፋሺስት ጣሊያን ወረራ ወቅት የሸዋ አርበኞችን በማስተባበርና በመምራት፣ ለሀገር ሉዓላዊነትና ለህዝብ ነፃነት ያደረጉት ተጋድሎ ዛሬም ለክፍለ ጦሩ አባላት ታላቅ የፅናት ምንጭ መሆኑም ተነስቷል።
በመሆኑም የክፍለ ጦሩ አባላት ትናንት በታሪክ እንደተደረገው ሁሉ፣ ዛሬም ሆነ ነገ ይህንን ታሪካዊ ስም በተግባርና በልዩ ልዩ የጦር ሜዳ ጀብዱዎች እንደሚያስጠሩት በጋራ ቃል በመግባት ለተከታታይ ቀናት ሲሰጥ የነበረው የተሃዲሶ መርሀ ግብር በስኬት ተጠናቋል ሲል የኮሩ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ክፍል ገልጿል።
በመጨረሻም የክፍለ ጦሩ አመራሮችና ሰራዊት ስለ ህዝብና ዓላማ፣ ስለ አማራ ታሪክና ፋኖነት እንዲሁም ስለ ድርጅትና ድርጅታዊነት ያላቸውን ግንዛቤ ይበልጥ በማሳደግ፣ ቀጣይ መርህን የተላበሱ አሰራሮችን በማስተካከል ተግተው በመስራት ድርጅቱ ካስቀመጠው ግብ ላይ ለመድረስ ዝግጁ መሆናቸውን በቁርጠኝነት አረጋግጠዋል ሲል ኮሩ በግንባር መረጃው አረጋግጧል።
" ክብር ለትግሉ ሰማዕታት !
"ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ
1 087
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ - ምኒልክ ዕዝ አስቸኳይ የሚዲያና የዲጂታል ስነ-ምግባር መመሪያ
ለዕዙ አመራሮች፣ አባላት፣ ደጋፊዎች፣ የሚዲያ ባለሙያዎች እና የቲክቶክ ተጠቃሚዎች በሙሉ፤
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ - ምኒልክ ዕዝ የጀመረው የተቀደሰ የትግል ጉዞ በታሪክ እውነታ፣ በፍትህ እና በነፃነት መርሆዎች ላይ የተመሰረተ ነው። ይህ ታላቅ ትግል በሜዳ ላይ የሚደረግ የትጥቅና የአካል ብቃት ፍልሚያ ብቻ ሳይሆን፤ በቃል፣ በፅሁፍ እና በምስል የሚካሄድ የሞራል፣ የሕሊና እና የስትራቴጂክ መረጃ ጦርነት ጭምር መሆኑን ዕዛችን በጥልቀት ይገነዘባል። ስለሆነም የነፃነት ጉዟችን በመረጃ እና በከፍተኛ ስነ-ምግባር የታነፀ የዲጂታል ዲፕሎማሲን አብሮ ማስኬድ ይኖርበታል።
የድርጅታችንም ሆነ የዕዛችን ስም፣ አርማ እና ዓላማ ለግል ጥቅም፣ ለስሜታዊነት መተንፈሻ ወይም ለጠላት የፕሮፓጋንዳ ማጥቂያ እንዲሆኑ መፍቀድ ትግሉን ማዳከም ብቻ ሳይሆን የውስጥ አንድነታችንንም አደጋ ላይ ይጥላል። ዕዛችን እስካሁን ባለው የሚዲያ አጠቃቀም ረገድ የተሻለ ስም አስከብሮ የቆየ ቢሆንም፣ ይህንን ስኬት ወደ ላቀ እና ስልታዊ ደረጃ ለማሸጋገር ከዛሬ ጀምሮ የሚከተለው የሚዲያ ስነ-ምግባር እና የድርጅታዊ ተጠያቂነት አስገዳጅ መመሪያ ወጥቶ ስራ ላይ ውሏል።
1. የኦፊሴላዊ መረጃ መስመሮች (Official Channels)
ማንኛውም የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ - ምኒልክ ዕዝን ስም፣ አርማ ወይም ወታደራዊ እንቅስቃሴ የሚመለከት መረጃ መተላለፍ ያለበት በይፋ በታወቁት የዕዛችን የቴሌግራም፣ የፌስቡክ ገጾች እና እውቅና በተሰጣቸው ሀቀኛ አጋር ሚዲያዎች ላይ ብቻ ነው። ከእነዚህ ውጪ በግልም ሆነ በቡድን ስም የሚለቀቁ ማናቸውም መረጃዎች ዕዙን የማይወክሉ እና የእኛን አቋም የማይገልጹ መሆኑን እናሳውቃለን።
2. የዲጂታል ስነ-ምግባር (ለሚዲያ ባለሙያዎች እና ቲክቶከሮች)
በዕዛችን ስም የሚንቀሳቀሱ እና ድጋፍ የሚሰጡ ማናቸውም የሚዲያ አካላት ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ድንጋጌዎችን፣ የጦርነት ህግጋትን (Rules of Engagement) እና የዲጂታል ደህንነት መርሆዎችን የማክበር ግዴታ አለባቸው። በተለይም ከሌሎች ህዝቦች ጋር ቅራኔን የሚፈጥሩ የጥላቻ ንግግሮችን፣ የዘር ቅስቀሳዎችን ወይም ዕዛችንን ከዓለም አቀፍ ህግጋት ጋር የሚያጋጩ ይዘቶችን ማሰራጨት በጥብቅ የተከለከለ ነው።
3. ድርጅታዊ ዲሲፕሊን እና የውስጥ አንድነት
የዕዛችንን መዋቅር እና ስም ሽፋን በማድረግ የውስጥ አንድነትን የሚያናጉ፣ በየደረጃው ያሉ አመራሮችን ያለአግባብ ስም የሚያጠፉ እና የሚሳደቡ፣ ወይም የድርጅቱን ስልታዊ ምስጢር የሚያባክኑ ግለሰቦች ላይ ጥብቅ ድርጅታዊ እርምጃ ይወሰዳል። የእውነተኛ አርበኛ ዋነኛ መገለጫው ዲሲፕሊን ነው። የዕዙን ስም ለግል ታዋቂነት (የፎሎወር ማብዛት) ወይም ለቡድን ፍላጎት ማሟያ ማድረግ ትግሉን ማቀጨጭ በመሆኑ፣ ዕዛችን በዚህ ላይ ከፍተኛ ቁጥጥር እና ተጠያቂነት ያሰፍናል።
4. የይዘት ቁጥጥር እና ዓለም አቀፍ ህግጋት
ምኒልክ ዕዝ በዓለም አቀፍ ህግ የተከለከሉ እና እንደ ጦር ወንጀል ሊያስቆጥሩ የሚችሉ ምስሎችን፣ ቪዲዮዎችን ወይም መመሪያዎችን ማሰራጨትን ፈጽሞ አይቀበልም። የሰብአዊ መብት ጥሰት የሚታይባቸውን ምስሎች ማጋራት የትግሉን ገጽታ ከማበላሸቱም በላይ፣ ነገ ለምናደርገው ህጋዊና ፖለቲካዊ ትግል ትልቅ እንቅፋት ነው። በመሆኑም መሰል ይዘቶችን የሚለቅ ማንኛውም አካል በህግና በድርጅት ፊት ሙሉ ኃላፊነቱን ይወስዳል።
5. አስመሳይነትንና የሃሰት ወሬዎችን ስለመከላከል
በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ ሀገር ሆናችሁ በቲክቶክ፣ በዩቲዩብ እና በሌሎች የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በቀጥታ ስርጭት (Live) በመግባት፣ ከዕዙ ጋር ግንኙነት እንዳላችሁ በማስመሰል የራስን አጀንዳ የሚያራምዱ ግለሰቦች ከምኒልክ ዕዝ ጋር ምንም ዓይነት ትስስር የሌላቸው መሆኑን በይፋ እንገልጻለን። ከዚህ ማሳሰቢያ በኋላ ሕዝብን በሚያደናግር መልኩ ዕዙን አስመስሎ የሚንቀሳቀስ ማንኛውም የሚዲያ ተጠቃሚ ላይ ዕዙ ህጋዊና ድርጅታዊ እርምጃ ይወስዳል።
6. ክትትልና ተጠያቂነት
ከዚህ መመሪያ ውጭ የሚንቀሳቀሱ፣ ወሬ የሚያናፍሱ እና ዲሲፕሊን የጎደላቸው ግለሰቦች ጉዳይ በየደረጃው በሚገኙ የዕዛችን የደህንነት እና የህግ መምሪያዎች በጥብቅ የሚመረመር ሲሆን፣ እንደ ጥፋቱ ክብደት ፅኑ ድርጅታዊ ቅጣት ይጠብቃቸዋል።
ማጠቃለያ ማሳሰቢያ፦
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ - ምኒልክ ዕዝ ስም ለተቀደሰና ለታላቅ ዓላማ የቆመ እንጂ ለግል ምኞት መጫወቻ አይደለም። ይህንን መመሪያ ጥሰው በሚገኙ አካላት ላይ ዕዙ ግንኙነቱን ሙሉ በሙሉ የሚያቋርጥ ሲሆን፣ አስገዳጅ ሆኖ ሲገኝም ጉዳያቸው ለሕዝብ ይፋ ይደረጋል።
መላው የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ አባላት እና ደጋፊዎች ይህንን መመሪያ በንቃት በመተግበር የትግላችንን ስም፣ ክብር እና ድል እንድታስጠብቁ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።
ማሳሰቢያ ለደገፊ ሚዲያዎች፦ የተከበራችሁና የተወደዳችሁ የትግላችን ደጋፊ ሚዲያዎች በሙሉ፤ ከዕዙ ሕዝብ ግንኙነት እንዲሁም ሚዲያና ኮሚኒኬሽን የሚወጡ ይፋዊ መግለጫዎችን ሳይጨመርና ሳይቀነስ (ባሉበት ይዘት) ለሕዝብ ማድረስ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።
ህልዉናችን በተባበረ ክንዳችን!
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ - ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ የህዝብ ግንኙነት መምሪያ
1 087
አፄ ምኒልክ ክፍለ ጦር በደፈጣ ጥቃት በጠላት ላይ ድል መቀዳጀቱን ሲገልፅ፡ የሀገር መሠረተ ልማቶች በሕዝብና አባት አርበኞች መሠራቱ ተገለፀ!!
ቀን 29/10/2018 ዓ.ም
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ አፄ አምደ ፅዮን ኮር ስር የሚንቀሳቀሰው የአፄ ምኒልክ ክፍለጦር በቅርቡ የሪፎርም ስራ ካከናወነ በኋላ፣ በአገዛዙ ኃይሎች ላይ የተሳካ የደፈጣ ጥቃት መፈፀሙን አስታወቀ ።
ሰኔ 28 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 2:00 ላይ ከመንዝ ቀያ ክላስተር ዘመሮ ከተማ በመነሳት ወደ ዘረት ሲንቀሳቀስ በነበረው የመከላከያ ሰራዊት ላይ የአፄ ምኒልክ ክፍለ ጦር 2ኛ ሻለቃ አባላት አስደናቂ ድል አስመዝግበዋል። በዚሕ የደፈጣ ጥቃት የጠላት ኃይል ክፉኛ መጎዳቱን የኮሩ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ክፍል ከግንባር በደረሰው መረጃ አረጋግጧል።
ጠላት የደረሰበት ጉዳት ፧ በተሰነዘረው የደፈጣ ጥቃት 6 የአገዛዙ ኃይሎች የተገደሉ ሲሆን፣ ቁጥራቸው በውል ያልተረጋገጠ ቁስለኞች በዘመሮ ከተማ ሆስፒታል በሕክምና ላይ እንደሚገኙ ዕዙ አረጋግጧል ።
የብልፅግናው ሰራዊት የደረሰበትን ምት መቋቋም አቅቶት ሙትና ቁስለኛ ይዞ፣ ያሰበውን ዓላማ ሳያሳካ ወደመጣበት ለመመለስ ተገድዷል ።
በቅርቡ የአመራር ሪፎርም ያደረገው የአፄ ምኒልክ ክፍለጦር፣ በአሁኑ ወቅት የተሻሉ ግዳጆችን በመፈፀም ላይ የሚገኝ ሲሆን፥ ክፍለ ጦሩ ራሱን ለግዳጆች በማዘጋጀት ላይ ከመሆኑም በላይ፣ በከፍተኛ የሰው ኃይል ግንባታ ላይ እንደሚገኝ የአፄ አምደ ፅዮን ኮር ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ክፍል በሰጠው መግለጫ አመልክቷል ።
በተያያዘ ዜና የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ከትጥቅ ትግሉ ጎን ለጎን ሕዝቡን በማስተባበር የመሰረተ ልማት ስራ እየሰራ ይገኛል። ሰኔ 29/2018 ዓ/ም በይፋትና ጥሙጋ አውራጃ ቀወት ወረዳ ተሬ ክላስተር የጃበርና ጎልጎዲሳ ጎጥ ለመንገድ መሰረተ ልማት ስራ ዘመቻ በነቂስ በመውጣት ከትጥቅ ትግሉ ጎን ለጎን በሞራል ሲሰሩ ውለዋል።
እንዲሁም በተጨማሪ በተመሳሳይ በቀን 29/10/2018 ዓ/ም በዚሁ አውራጃ ማጀቴ ክላስተር የ"አየለ አባተ ብርጌድ" አባት አርበኞች ክረምትን የዋጀ መሠረተ ልማት ተሠርቷል። የማህበረሰቡን እንቅስቃሴ እዳይገታ ተብሎ የታሠበው የጃራ ወንዝ ጋቢዮን ስራ አባት አርበኞቹ በሞራልና በትብብር የወንዙን ፍሰት መቆጣጠር የሚያስችል ስራ አከናውነዋል።
" ክብር ለትግሉ ሠማዕታት!
"ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ
1 087
ትውልድ የማይረሳው የሸዋሮቢት ወጣቶች መሥዋዕትነት !
በወለጋ ዞኖች ከ2000 በላይ በሚሆኑ ንፁሃን አማራዎች ላይ በኦህዴድና በሸኔ ጥምረት ዘግናኝ ጭፍጨፋ መፈፀሙን በመቃወም ሰኔ 22 ቀን 2014 ዓ.ም በኦሮሚያ የአማራው እልቂት በአስቸኳይ ይቁም በሚል በሸዋሮቢት ከተማ "የበቃን!" ሰላማዊ ሰልፍ አደረግን።
ሰላማዊ ሰልፍ ማካሄዳችንን ያላስደሰተው አገዛዙ የህዝቡን ብሶት ከማዳመጥ ይልቅ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ጦር በማሰማራት፣ በቅድሚያ እኔን፣ በመቀጠልም አሁን የፋኖ አመራርና አባል የሆነውን አዶናይ አበበን ሰኔ 24/በቁጥጥር አዋለን። እንዳለ ድንበሩን የተባለ ወንድማችንም ሰኔ 26 በተመሳሳይ መንገድ ታፍኖ ተቀላቀለን።
ይሁን እንጂ ሰኔ 24 ቀን የከተማዋ ቆራጥ ወጣቶች ይህንን ግፍ በዝምታ አላለፉትም። በሺዎች የሚቆጠሩ የሸዋሮቢት ወጣቶች፣ "በወለጋ በአሰቃቂ ሁኔታ የታረዱት ወገኖቻችን ጉዳይ ሳያሳስባችሁ፣ የህዝብ ድምፅ ለመሆን የጣሩ ወንድሞቻችንን እንዴት ታስራላችሁ?" በሚል ፅኑ አቋም ተቃውሟቸውን አሰሙ።
በጊዜው ወዴት እንደሚወስዱን ባይታወቅም ስርዓቱ በድብቅ ወደሚያሰቃይባቸው እስር ቤት ልንወሰድ መሆኑን መሰማቱን ተከትሎ፤ ከጠዋቱ 4:00 እስከ ምሽቱ 1:00 ድረስ "ወንድሞቻችን የትም አይንቀሳቀሱም፤የሚጠየቁትም ካለ እዚሁ ይጠየቁ'' በማለት መሳሪያ ካነገበው የአድማ ብተና ኃይል ጋር ፊት ለፊት ተፋጠጡ።
በሚያሳዝን ሁኔታ ግን፣ ከምሽቱ 1 ሰዓት በኋላ ኃላፊነት በጎደላቸው አመራሮች ትዕዛዝ የነገሮች መልክ ፈፅሞ ተቀየረ።
የደም ጎርፍ በፈሰሰበት በዛ የጭካኔ ምሽት ..
በወቅቱ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር በነበሩት በይልቃል ከፋለ፣ የአማራ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር በነበሩት ተኮላ አይፎክሩ እና ቡድናቸው፣ የሰሜን ሸዋ ዞን አስተዳዳሪ ታደሰ ገብረፃዲቅ እና ቡድናቸው፣ እንዲሁም በሸዋሮቢት ከተማ አስተዳደርና በሌሎች የጊዜው አመራሮች ቀጥተኛ ትዕዛዝ፣ ሰላማዊ ወጣቶቹ ላይ የጥይት እሩምታ እንዲከፈት አቅጣጫ ተሰጠ።
በዚያች አስከፊና ጨለማ ምሽት፣ ማይክራፎንና መፈክር ብቻ በያዙት ወጣቶች ላይ የብሬን ጥይት እንደ ዝናብ ዘነበባቸው።
ጭስ ቢተተኮሰባቸው በሚበተኑ ንፁሃን ወጣቶች ላይ የብአዴን/ብልፅግና ጨካኝ መዋቅር ርህራሄ የለሽ እሩምታ ለቀቀ። እኛም በጠበበው የእስር ክፍል ውስጥ ሆነን ያንን አሰቃቂ የጥይትና የሰቆቃ ድምፅ በከፍተኛ የህሊና ስቃይ ለማዳመጥ ተገደድን።
በግርግሩ መካከል የእስር ቤቱን በር እንዳንሰብር በማሰብ፣ ታጉረንበት በነበረው ክፍል አካባቢ ሳይቀር በየመሃሉ ጥይት ይተኮስ ነበር።
በዚያች ሌሊት ለፍትህና ለነፃነት አደባባይ የወጡ የሸዋሮቢት ወጣቶች በአገዛዙ አፈሙዝ ተረሽነው ወደቁ።
አስቀያሚ የሰቆቃ ምሽቶች አለፉ። ንጋት ላይ ለመጠየቅ በተፈቀደላቸው ቤተሰቦቻችን በኩል መረጃውን ስንሰማ፣ 12 ወጣቶች በግፍ መገደላቸውን በለቅሶ ተነገረን፤ ይህ ክስተት በልባችን ውስጥ የማይሽር ዘላለማዊ ቁስልና ጥልቅ ቁጭት ጥሎ አልፏል።
እኛ "የወለጋ ወገኖቻችን ለምን ይገደላሉ?" በማለታችን ወደ ዘብጥያ ስንወረወር፤ እነርሱ ደግሞ ለፍትህ ድምፅ የሆኑ ወንድሞቻችን "ለምን ይታሰራሉ?" ብለው በመጠየቃቸው ብቻ፣ በተተኮሰባቸው አፈሙዝ ለእውነት ሲሉ ወደቁ። ህመም ነው።
እዚህ ላይ በዝርዝር የማልገልፃቸው በርካታ ፈተናዎችና ጉዳዮች ቢኖሩም፣ ዛሬም ድረስ በፅናት ከምንታገልላቸው ዐቢይ ምክንያቶች አንዱ ግን፣ በዚያች እለት ውድ ህይወታቸውን ለከፈሉት ወንድሞቻችን የገባነውን የትግል አደራ ለመጠበቅ ጭምር ነው።
ከሁሉ በላይ የሚያሳዝነውና የድርጊቱን አረመኔያዊነት የሚያሳየው ደግሞ፣ አገዛዙ እኛን በእስር ቤት አጉሮ ወንድሞቻችንን በውጭ መግደሉ ሳያንስ፣ እኛው ላይ "በነፍስ ማጥፋት ወንጀል" ክስ መመስረቱ ነው። ዋና ዓላማቸውም ከእስር እንዳንወጣ ለማድረግ ነበር። ከእስር ባሻገር ሌላ የከፋ ነገር ቢደርስብን እንኳን ወንድሞቻችንን በግፍ ለተነጠቅነው ለእኛ ትልቁ ጉዳያችን አልነበረም።
ለወራት ከዘለቀው እስር በኋላ፣ የተሰውትንና የማናውቃቸውን ወንድሞቻችንን ማንነት አጣርተን ለታሪክ ለማስቀመጥ ወደ ታከሙበት ሆስፒታል ብናመራም፣ ስርዓቱ የንፁሃኑን የህክምና መዛግብት (ፋይሎች) ሙሉ በሙሉ አውድሞ ጠበቀን። ይህ እጅግ ልብ የሚሰብር ተግባር ነበር።
ዝርዝሩ ብዙ ነው ..
በአገዛዙ ኃይሎች በወጣቶቹ ላይ ከተከፈተው ተኩስ በኋላ የከተማው ህዝብ በከፍተኛ ቁጣ ገንፍሎ ነበር። ሁኔታው ያሰጋውና የጨነቀው ብአዴን፣ ሰኔ 25/2014 ዓ.ም ማለዳ ተጨማሪ ሁለት አይሱዙ የጫነ የአድማ ብተና ኃይል ከደብረብርሃን ከተማ መላኩ ተሰማ። ይሁን እንጂ፣ ትጥቅ የነበራቸው የከተማው ደም መላሾች፣ የእሸቴ ሞገስ ድል አብሳሪዎች ኃይሉን የከተማው መግቢያ ላይ በደፈጣ ጠብቀው፣ ለነጋሪ ሳያስቀሩ ደምስሰውት ተሰወሩ። ( ይህ ከእስር ከወጣን በኋላ የተነገረን ሀቅ ነው)
በጥቃቱ 20 የአድማ ብተና አባላት ተገደሉ፣ የንፁሃን ወንድሞቻችን ደም ሳይውል ሳያድር ተመለሰ። ሆኖም፣ "በፍትህ ከሄደች በቅሎዬ ይልቅ፣ ያለ ፍትህ የሄደች ጭብጦዬ" ብሎ ለሚያምነው የአማራ ህዝብ፣ ለተጨማሪ ጭፍጨፋ ከተሰማራ ነፍጥ አንጋች ኃይል ጋር የለጋ ወጣቶቻችን ንፁህ ነፍስ መጥፋት ፈፅሞ የሚመጣጠንና የሚወዳደር አይደለም።
ታሪኩን በአጭሩ ለማጠቃለል፦ ለወራት በእስር ከተሰቃየን በኋላ፣ በክልሉ ከተዋቀረው የደህንነት ግብረ-ኃይል፣ "ትግል ካላቆማችሁና ዳግም ካገኘናችሁ እንገድላችኋለን" የሚል ጥብቅ ማስጠንቀቂያና ዛቻ ተሰጥቶን ተፈታን። ነገር ግን ሞትን ብንፈራ ኖሮ ትግሉን ገና ከጅምሩ አንቀላቀልም ነበር፤ ያንንም ሰልፍ ያደረግነው በአፈሙዝ ተከበን መሆኑን ጠንቅቀን እናውቃለን።
ታሪኩ ከብዙ በጥቂቱ ነው ..
ዛሬ ላይ ሆኖ ይህንን መለስ ብሎ ማስታወስ፣ በመላው አማራ ላይ እየተፈፀመ ካለው ሰፊ ስርዓታዊ ጭፍጨፋ እና በቀናት ውስጥ በሺዎች የሚቆጠሩ ንፁሃን በአገዛዙ አፈሙዝ ከሚያልቁበት ነባራዊ ሁኔታ አንፃር ሲታይ፣ እንደ አንድ ተራ ክስተት ሊቆጠር ይችላል። ነገር ግን እነዚህ ወጣቶች የራሳቸው የሆነ ትልቅ ታሪክ አላቸው። የአማራ ህዝብ ነፃነቱን ለማረጋገጥ እየከፈለው ባለው መስዋዕትነት ውስጥ፣ ምንጊዜም የምናስባቸው ንፁህ የትግል ሰማዕታት ናቸው።
እነሆ፣ ለነፃነትና ለፍትህ ሲሉ ውድ ህይወታቸውን የሰጡበት 4ኛ ዓመት የመሥዋዕትነት ቀን ዛሬ ነው።
መስዋዕትነታችሁ የትግል አደራችን ነው፤ ፍፁም አንረሳችሁም!
ነፍሳችሁን በአፀደ ገነት ያኑርልን!🙏🙏🙏🙏
