en
Feedback
Jema Insider

Jema Insider

Open in Telegram
1 087
Subscribers
No data24 hours
-77 days
-2630 days
Posts Archive
photo content
+9

የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ የ102ኛ ኮር 12ኛ ክፍለጦር 3ኛ ሻለቃ መንደፈራ ቀበሌ በአገዛዙ ላይ መብረቃዊ የደፈጣ ጥቃት ፈፀሙ! የ102ኛ ኮር 12ኛ ክፍለጦር 3ኛ ሻለቃ የሰራዊት አባላት ዛሬ ሐምሌ11/2018ዓ/ም በሰሜን ወሎ ዞን በራያ ቆቦ ወረዳ ከቆቦ ከተማ በቅርብ ርቀት ልዩ ስሙ መንደፈራ በተባለ አካባቢ በአገዛዙ ሰራዊት ላይ የደፈጣ ጥቃት ወሰዱ። ጥቃቱን የፈፀሙት የ12ኛ ክፍለጦር 3ኛ ሻለቃ የሰራዊት አባላት የአገዛዙ ሰራዊት ከጮሬና ቀዩ ጋሪያ መነሻውን በማድረግ በቀዩ ጋሪያና መንደፈራ መካከል ያለውን ወታደራዊ ገዢ መሬት ለመያዝ በመጓዝ ላይ እያለ በከበባ ውስጥ በማስገባት ነው። በመሆኑም የ12ኛ ክፍለጦር የ3ኛ ሻለቃ ነበልባሎች ጠላት አዘውትሮ የሚውልበትን ምሽግ በሌሊት ተስቦ በመያዝ በወሰዱት ማጥቃት 15 የመከላከያ ሰራዊት ሲገደሉ 18 የሚሆኑት ደግሞ በከፍተኛ ጉዳት ወደ ቆቦ ሆስፒታል መግባታቸውን የውስጥ መረጃዎች በዝርዝር ገልፀዋል። በጥቃቱ የጠላት ሻምበሏን ጠርንፎ ሲመራ የነበረ ሻምበል መሪ እና ግዳጅ የተሰጣት ሙሉ የሰራዊት አባል ተደምስሰዋል። በተጨማሪም አገዛዙ በዚሁ ቀጠና በተለያዩ የሀገሪቱ ትምህርት ቤቶች በአፈና ሰብስቦ ያመጣቸው አዲስ ወታደራዊ ሰልጣኞች በስልጠና ላይ እያሉ ወደ ውጊያ እንድገቡ በመደረጋቸው ምክኒያት የገፈቱ ቀማሽ ሆነዋል። ጨፍጫፊውና እብሪተኛው የብልፅግና አገዛዝ በመላው አማራ ህዝብ በደረሰበት የፖለቲካ ኪሳራ ከፍተኛ ውዝግብ ላይ መሆኑ ይታወቃል። በመሆኑም ለሴትና ህፃናት እንዲሁም ከተማ ለሚኖሩ አዛውንት ሲቪሊያን የማይጨነቀውና በደረሰበት የንስሮቹ ፈጣን የደፈጣ ጥቃት የተወዛገበው የብልግና ሰራዊት ዛሬም እንደ ትናንቱ የቁጣ ማብረጃቸው ምስኪን የአማራ ገበሬ ላይ የከባድ መሳሪያ ድብደባ አድርገዋል። በዚህ ምክኒያት በርካታ ንፁሀን አርሶ አደሮች መሰዋትነት የከፈሉ ሲሆን ገሚሱ በከፍተኛ ጉዳት ላይ እንደሆኑ የአካባቢው ማህብሰብ ገልጿል። እንዲሁም የአማራን ህዝብ ጭፍጨፋ እውን ለማድረግ የመጣው አገዛዙ በከባድ መሳሪያ ድብደባ የአቶ ተመስገን መለሰ 7 ከብት እና የአቶ ታደሰ መርሻ 5 ከብት በድምሩ 12 የቁም እንስሳት በመግደልና በርካታ የአርሶ አደር ሰብል አቃጥሏል። በመጨረሻም በዚህ የደፈጣ ጥቃት የደረሰ የጥላት የሰባዊና ቁሳዊ ኪሳራ 1ኛ.Ak ክላሽንኮቭ መሳሪያ------10 2ኛ. F1 ቦንብ--------------------- 9 3ኛ. የተደመሰሰ ---------------------15 4ኛ.የቆሰለ ----------------------------18 መሆኑን የ12ኛ ክፍለጦር ህዝብ ግንኙነት ገልጿል። መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልዉና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል! ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! የአፋብን ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ ዕዝ የ102ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት መምሪያ ሐምሌ 11/2018 ዓ.ም

photo content

የጎንደር ፋኖ አርበኞች የአንድነት አዋጅ እና የከሸፈው የብልፅግና ሴራ ! ✍️✍️ ያሬድ ሙሉነህ በቅርቡ የጎንደር አርበኞች ያወጁት ይፋዊ አንድነት እና ያወጡት መግለጫ በአማራ ህዝብ የህልውና ትግል ውስጥ አዲስ ስትራቴጂካዊ ምዕራፍ የከፈተ ክስተት ሆኗል። ይህንን ተከትሎ ግን የገዥው የብልፅግና ፓርቲ የፖለቲካ ክንፍና ተላላኪ ካድሬዎች ይህንን ታሪካዊ አንድነት ከአውድ ውጭ በመተርጎም፣ የጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ ከእናት ድርጅቱ አፋብን እንደተገነጠለና የተለየ አቋም እንደያዘ አድርገው ለማቅረብ አስቂኝ የፕሮፓጋንዳ ዘመቻ ከፍተዋል። የጎንደር አርበኞች ያወጁት አንድነትና ተያይዞ የወጣው መግለጫ የትግሉን ስትራቴጂካዊ ግቦች ይበልጥ ያጠነከረ እንጂ የከፋፈለ አይደለም። የመግለጫው ዋና ይዘትም የሚከተሉትን መሰረታዊ ነጥቦች ያረጋገጠ ነው። 1. የአማራ ህዝብን ጥቅም በዘላቂነት ማስከበርን ያለመ ፦ መግለጫው የአማራ ህዝብ የመታገያ አጀንዳዎች እና ስትራቴጂካዊ ጥቅሞች ሳይሸራረፉ የሚከበሩበትን ግልጽ ፖለቲካዊ አቋም አስቀምጧል። 2. መዋቅራዊ አንድነትን ያጠናከረ፦ መግለጫው አፋብንን የሚቃወም ወይም ከድርጅቱ አቅጣጫየሚለይ ሳይሆን፣ ይልቁንም በትግሉ ውስጥ ያለውን መዋቅራዊ ጥንካሬ ይበልጥ ያረጋገጠ ነው። 3. የውስጥ ጥራት የፈጠረ:-መግለጫው በትግሉ ስም የሚነግዱ፣ ጥቅማጥቅም ፈላጊዎችን እና ህዝባዊ አላማ የሌላቸውን ጥገኛ አካላት ያጋለጠ የመርህ አንድነት መሆኑን ያመላከተ ነው። እውነታው ይህ ሆኖ ሳለ ታድያ የጎንደር አንድነት ያስበረገጋቸው ብልፅግናዊ ስብስቦች እና ስልታዊ ብልፅግናዎች የጎንደር ፋኖ የያዘውን የአንድነት አቋም ከአፋብን ተቃራኒ አድርገው ለመሳል ሲሞክሩ ተስተውለዋል። 🤣 የዚህ ሴራ መሰረታዊ ግብ የጎንደርን አርበኞች ታሪካዊ ሚና በማሳነስ የብልፅግና የፖለቲካ አጀንዳ አስፈጻሚ ለማድረግ ነው። በተግባር ግን የጎንደር ፋኖ ከብልፅግና ጋር ሊደራደር ወይም አጋር ሊሆን ቀርቶ፣ በአሁኑ ወቅት የብልፅግናን ሰራዊት በየግንባሩ እየደመሰሰና እያፈረሰ የሚገኝ የህዝብ አለኝታ ነው። በማንኛውም የትጥቅ ትግል እንቅስቃሴ ውስጥ የፖለቲካ አቋም፣ የአቅጣጫና የርዕዮተ-ዓለም ልዩነቶች መኖራቸው ተፈጥሯዊ ነው። ሆኖም እነዚህ ልዩነቶች ለውጫዊ ጠላቶችና ለስልታዊ ካድሬዎች የመከፋፈያ በር የሚከፈቱ ግን መሆን የለባቸውም። በአፋብን መዋቅር ውስጥ ያሉ ማንኛቸውም የስትራቴጂና የታክቲክ ልዩነቶች በውይይት፣ በውስጠ-ድርጅታዊ ግምገማ እና በመርህ ላይ በተመሰረተ ትግል የሚቀረፉ ናቸው። በዚህ አግባብ ታጋዩ አመራርና አርበኞቹ የጠላትን የመከፋፈል ሴራ ቀድመው የተረዱ በመሆናቸው፣ በውይይት የሚፈቱ የውስጥ ጉዳዮችን ለጠላት ፕሮፓጋንዳ ማደለቢያ አሳልፈው አይሰጡም። የጎንደር አንድነት ለአማራ ህዝብ ህልውና መከበር ዋስትና የሚሰጥ፣ በትግሉ ውስጥ ያሉትን ድክመቶች የሚያርም እና ጥራትን የፈጠረ ታሪካዊ እርምጃ ነው። የብልፅግና ካድሬዎች ይህንን የጥንካሬ መግለጫ እንደ ክፍፍል ቆጥረው የሰጡት የተሳሳተ ትርጓሜም የፖለቲካ ኪሳራቸውን ይበልጥ ከማጋለጥ ውጭ ያመጣው ለውጥ የለም። የጎንደር ፋኖ መሬት ላይ ባለው ተጨባጭ ወታደራዊ እርምጃ የብልፅግናን ሰራዊት እያፈረሰ፣ በፖለቲካዊው ግንባር ደግሞ በአፋብን ጥላ ስር የጠነከረ አንድነቱን እያስመሰከረ ቀጥሏል። የጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝን መግለጫ ከአውድ ውጭ በመተርጎም ልዩነት ተፈጠረ፣ ዕዙ ተገነጠለ እያሉ ሲያላዝኑ የሚውሉ ተስፈኛ ካድሬዎች የትግሉን ስፋትና ጥልቀት ካለመረዳት በመነጨ ስነ-ልቦናዊ ቀውስ የፈጠሩት የምኞት ጩኸት ነው። ድል ለድል አድራጊው ፋኖ 💪💪💪 NB:- ለሚመለከተው ብቻ !!

photo content

" እቴጌ ጣይቱ ክፍለ ጦር የአመራር ሪፎርም አካሄደ"!! ሐምሌ 08/2018 ዓ.ም የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት የአሳምነው ዕዝ መሀመድ ቢሆነኝ ኮር እቴጌ ጣይቱ ክፍለ ጦር የአመራር ሪፎርም ማካሄዱን
+7
"  እቴጌ ጣይቱ ክፍለ ጦር የአመራር ሪፎርም አካሄደ"!!       ሐምሌ 08/2018 ዓ.ም የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት የአሳምነው ዕዝ መሀመድ ቢሆነኝ ኮር እቴጌ ጣይቱ ክፍለ ጦር የአመራር ሪፎርም ማካሄዱን አስታወቀ።  በተካሄደው የሪፎርም መድረክ ላይ የዕዙ እና የኮሩ ከፍተኛ አመራሮች የተገኙ ሲሆን፤ ይህ የአመራር ለውጥ የተደረገው ከክፍለ ጦር ወደ ኮር ደረጃ በተቀየሩ አመራሮች ምትክ አዳዲስ አመራሮችን ለመተካት ታስቦ መሆኑ ተገልጿል።  ይህ የተከናወነው የሪፎርም መርሃ ግብር ሙሉ በሙሉ ወታደራዊ መዋቅሩን ብቻ የሚመለከት ሲሆን፣ በወቅታዊና በቀጣይ ወታደራዊ ተግባራት ዙሪያ ሰፊ ውይይት ተደርጎበታል። በዚሕ መርሀ ግብር ያለፈውን የአሰራር ውስንነት ገምግሞ ሕዝብና ሠራዊትን ከልብ በማገናኘት ሕዝብን ባማከለ መልኩ  የዕዛችንን ዓላማና ግብ ለማሳካት ጠንካራ አቋም ተወስዷል። ሌላው ቀጣይ በሠራዊቱ በኩል ለሚነሱት የአሰራር ውስንነቶችና ለሚያጋጥሙ ችግሮች መካች ወይም ተጋፋጭ የሆነ ኃይል እዲሁም ብቁ አመራር ለማፍራት እደሚሰሩ ቃል ገብተዋል። ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ መሀመድ ቢሆነኝ ኮር ለሚሰጣቸው ድርጅታዊ ግዳጆች ዝግጁ መሆናቸውን ገልፀው የተያዘው  መድረ በስኬት ተጠናቋል ሲል የኮሩ ህዝብ ግንኙነት ክፍል ገልጿል። " ክብር ለትግሉ ሠማዕታት"! " ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን"! የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

የሀገራዊ ምክክሮች ዓለም አቀፍ ተሞክሮ እና የብልፅግናው አገዛዝ ቅድመ-ምክክር መክሸፎች ! ✍️✍️ ያሬድ ሙሉነህ ሀገራዊ ምክክር በራሱ ግብ ሳይሆን ወደ መግባባት የመድረሻ አንድ መንገድ ነው። ሆኖም መንገዱ በቅንነት፣ በገለልተኝነት እና በሁሉን አቀፍ ተሳትፎ ካልተመራ የባሰ አውዳሚ መሆኑ ግን አይቀሬ ነው። በአሁኑ ሰዓት በኢትዮጵያ እየተካሄደ ያለው ህገ-ወጥ የምክክር ሂደትም.. 1. መሬት ላይ ያለውን እውነተኛ ሁኔታ ያላገናዘበ 2. ዋና ዋና የፖለቲካ እና የታጠቁ ኃይሎችን ያገለለ እና ፍትሃዊ ውክልና የሌለው 3. ከሀገራዊ መግባባት ይልቅ የስርዓቱን የፖለቲካ እና የኢኮኖሚ ህልውና ለመታደግ የተወጠነ በመሆኑ የመክሸፍ እና ሀገሪቱን ወደ ባሰ የእርስ በእርስ ግጭት የመክተት ዕድሉ እጅግ ከፍተኛ ነው። ሂደቱ ግልጽ የሆነ ተኩስ አቁም ለማድረግ ታጣቂ ኃይሎች ያልተስማሙት፣ ገለልተኛ አደራዳሪ አካል ያልተሰየመበት እና ሁሉም ወገኖች እኩል የመደራደር ስልጣን ሳይኖራቸው የሚቀጥል በመሆኑም ታሪካዊ ስህተትን ከመድገም የዘለለ ፋይዳ አይኖረውም። የከሸፉ ሀገራዊ ምክክሮች እና ውጤታቸውን እንመልከት ! 1. የየመን ብሔራዊ ውይይት ኮንፈረንስ፤ የመን በ"ዓረብ አብዮት" ማግስት የነበረባትን የፖለቲካ ቀውስ ለመፍታት የተካሄደው ምክክር በዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ዘንድ ትልቅ ተስፋ ተጥሎበት ነበር። ነገር ግን ምክክሩ በተጨባጭ መሬት ላይ ያሉ ኃይሎችን በተለይም የሁቲ አማፂያንን እና የደቡብ የመን ተገንጣዮችን በአግባቡ ማሳተፍ አልቻለም። ሂደቱ በጥቂት የፖለቲካ ልሂቃን ቁጥጥር ስር መውደቁ እና በመሬት ላይ የነበረው ግጭት አለመቆሙ ምክክሩ እንዳበቃ ሀገሪቱ ወደ አስከፊ የእርስ በእርስ ጦርነት እንድትገባ አድርጓታል። ዛሬም ድረስ የመን ከዚህ ቀውስ አልወጣችም። 2. የሊቢያ ብሔራዊ ምክክር ሙከራዎች፤ ከጋዳፊ ውድቀት በኋላ በሊቢያ የተደረጉ በርካታ የሰላምና የምክክር ጥረቶች መሬት ላይ ካሉ የታጠቁ ኃይሎች ይልቅ በስልጣን ላይ ባሉ ቡድኖች ፍላጎት ላይ ብቻ ያተኮሩ ነበሩ። የሃይል ሚዛኑን ያላገናዘቡ እና ሁሉንም ወገን ያላካተቱ በመሆናቸው ሊቢያን ወደ ተከፋፈለች እና ለሁለት አስርት ዓመታት ወደማይረጋጋ ቀውስ ውስጥ እንድትገባ አድርገዋታል። በሌላ በኩል ከተሳኩ ሀገራዊ ምክክሮች ተሞክሮዎች መካከል አንደኛው የቱኒዚያ ብሔራዊ ውይይት ሲሆን ቱኒዚያ ከእርስ በእርስ ጦርነት አፋፍ የዳነችው በአራት የሲቪክ ማህበራት አደራዳሪነት በተካሄደ ገለልተኛ ምክክር ነበር። ሀገራዊ ምክክሮች (National Dialogues) በአንድ ሀገር ውስጥ ለዓመታት የተከማቹ ፖለቲካዊ፣ ታሪካዊ እና መዋቅራዊ ቅራኔዎችን በጠረጴዛ ዙሪያ ለመፍታት የሚዘጋጁ ከፍተኛ የፖለቲካ መድረኮች ናቸው። በተለይም በሽግግር ወቅት ወይም እጅግ የከረሩ የእርስ በእርስ ግጭቶች ባሉባቸው ሀገራት ውስጥ ዘላቂ ሰላምን ለማምጣት እንደ መፍትሄ ይወሰዳሉ። ሆኖም ግን ታሪክ እንደሚነግረን ሀገራዊ ምክክሮች ሁልጊዜ ስኬታማ አይደሉም። ይልቁንም ቅድመ-ሁኔታዎች ባልተሟሉበት፣ ፍትሃዊ ውክልና በሌለበት እና በጦርነት ጥላ ስር የሚደረጉ ምክክሮች ሀገሪቱን ወደባሰ ቀውስ እና የእርስ በእርስ እልቂት ሊዳርጉ የሚችሉበት እድል ሰፊ ነው። በታሪክ ውስጥ ስኬታማ የሆኑ ሀገራዊ ምክክሮች ሁሉ ከመጀመራቸው በፊት ቢያንስ ጊዜያዊ "የተኩስ አቁም" ወይም የሰላም ስምምነት ይደረጋል። በኢትዮጵያ ግን ሁኔታው ፍጹም ተቃራኒ ነው። ብልፅግና የሰላም ስምምነት አድርገው ተስማሙ የሚላቸው ታጣቂዎች እና የፖለቲካ ኃይሎች አገዛዙን ከሚቃወሙ ኃይሎች አኳያ ሲነፃፀሩ አንድ እፍኝ አይሞሉም። በአማራ ክልል በፋኖ ኃይሎች እና በብልፅግና ሰራዊት መካከል ያለው ውጊያ በጥልቀትና በስፋት ቀጥሏል። ከ120 ሺህ በላይ የሚገመት የአማራ ፋኖ ተዋጊ ኃይል የክልሉን በርካታ አካባቢዎች ተቆጣጥሮ በማስተዳደር ላይ ይገኛል። በኦሮሞ ክልል በኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት (OLA) እና በኦህዴድ ብልፅግና መካከል ያለው ግጭት በተመሳሳይ መንገድ አሁንም አለ። በትግራይ ከፕሪቶሪያው ስምምነት ማግስት በኋላ ከማዕከሉ ጋር ያለው ትስስር ተበጥሷል። የጦርነት ስጋቶችም ባሉበት ቀጥለዋል። የቤንሻንጉል ጉምዝ እና የጋምቤላ ድንበሮች ላይ ዛሬም ጦርነቶች እየተካሄዱ ነው። ከዚህ አኳያ በጦርነት ውስጥ ያሉ ዋና ዋና ተዋናዮች በሌሉበት የሚደረግ ምክክር በመሬት ላይ ያለውን ግጭት ሊያስቆም እንደማይችል በቀላሉ ማረጋገጥ ይቻላል። ከተመሰረተበት ጊዜ ጀምሮ በገለልተኝነት እና በአካታችነት እንዲሁም በስርዓቱ አገልጋይነት ጥያቄ የሚነሳበት ብሔራዊ ምክክር ኮሚሽን የተባለው ተቋም ያዘጋጀው ሀሰተኛ ምክክርንም ዋና ዋና የሚባሉ የፖለቲካ ድርጅቶች፣ የብሔር ተሟጋቾች እና የታጠቁ ኃይሎች ሂደቱን በግልጽ ቦይኮት አድርገውታል። ሚሊዮኖች በሚፈናቀሉበት፣ የሀሳብ ነጻነት በተገደበበት እና የመገናኛ ብዙሃን እና የሲቪክ ማህበራት እጅግ በጠበበ ቦታ ውስጥ በሚንቀሳቀሱበት በአገዛዙ የሚመረጡ "የህዝብ ተወካዮች" ትክክለኛውን የህዝብ ድምጽ እና ጥያቄም ሊወክሉ አይችሉም። ይህ ውክልና የሌለው ሂደት ደግሞ ልክ እንደ የመኑ ምክክር የስረዓቱ ሰዎች የቤት ውስጥ ጨዋታ ብቻ ሆኖ ከመቅረት ወደ ኋላ አይልም። በአጠቃላይ በብልፅግና ከበሮ የሚደለቅለት ምክክር እውነተኛ ሀገራዊ እርቅ እና ፍትህን የሚያመጣ ሳይሆን፣ ከምዕራባውያን የሚገኘውን የገንዘብ እርዳታ ለማስቀጠል፣ የኢኮኖሚ ቀውሱን ለማለፍ እና አደጋ ውስጥ የገባውን የኦህዴድ ብልፅግና የስልጣን የበላይነትን ለማደስ የተሸመነ የአብይ አህመድ አገዛዝ ሴራ ነው። !!!

photo content

ሰበር መረጃ የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ ቀጠናዊ አንድነቱን ማጠናቀቁ ታውጇል። ድል ለአማራ ፋኖ 💪💪

የራስ አበበ አረጋይ ክፍለ ጦር በደገም ወረዳ በጠላት ላይ የማያዳግም የድል እርምጃ ወሰደ!! ሐምሌ 04/2018 ዓ.ም በግራሪያ (ፍቸ ሰላሌ) አውራጃ ነዋሪዎች ላይ ብሔርና ሃይማኖት ሳይለይ የዘረፋ
+9
የራስ አበበ አረጋይ ክፍለ ጦር በደገም ወረዳ በጠላት ላይ የማያዳግም የድል እርምጃ ወሰደ!!         ሐምሌ 04/2018 ዓ.ም በግራሪያ (ፍቸ ሰላሌ) አውራጃ ነዋሪዎች ላይ ብሔርና ሃይማኖት ሳይለይ የዘረፋ ተግባር ሲፈጽም በነበረው የሸኔ ቡድን ላይ የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ አፄ አምደጽዮን ኮር ራስ አበበ አረጋይ ክፍለ ጦር (2ኛ አሊ ሻለቃ) ደገም ወረዳ ውስጥ በሚገኙት ሀሮ እና አቦ ለሊሳ ቡድኑ የሰፈረባቸው ቦታዎች ላይ መብረቃዊና የማያዳግም እርምጃ ወስዷል። ከንጋቱ 12:00 እስከ ቀኑ 5:00 ድረስ በተደረገው በዚህ ስልታዊና ልዩ ኦፕሬሽን፣ የሻለቃው አናብስቶች የጠላትን ካምፕ በመስበር ከፍተኛ የድል ዜና አብስረዋል። በኦፕሬሽኑ በርካታ የቡድኑ አባላት ተደምስሰዋል። ➡➡በግዳጁ የተገኙ ግብአቶች፦➡ ✔.7 የጦር መሣሪያዎችና በርካታ ተተኳሾች ተማርከዋል። ✔.9 የቀንድ ከብቶች እንዲሁም 15 በግና ፍየሎች ከዘራፊው እጅ  ለአርሷደሮቹ ተመልሰዋል። ✔.ወታደራዊ ሻንጣዎች፣ ካዝናዎች፣ ልዩ ልዩ ቦምቦችና የወገብ ትጥቆች በቁጥጥር ሥር ውለዋል። " ክብር ለትግሉ ሠማዕታት! "ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

ሰበር የድል ዜና ❗❗ ከኮላሽ ተራራማ ስፍራ እስከ አለም ከተማ ጫፍ በናደው ክፍለጦር ታሪክ ሰራ! ሐምሌ 04 ቀን 2018 ዓ.ም ሸዋ ጠቅላይ ግዛት — አሳምነው ዕዝ አፄ ዘርያዕቆብ ፩ኛ ኮር ናደው ክፍለ ጦር በመርሐቤቴ አውራጃ በታሪካዊቷ የኮላሽ ተራራማ ስፍራና በአለም ከተማ ዙሪያ ሰፍሮ በነበረው የብልፅግና አገዛዝ ሰራዊት ላይ የናደው ክፍለጦር ጀግኖች መብረቃዊ ጥቃት በመሰንዘር አኩሪ ድል አስመዝግበዋል። ዛሬ ከሌሊቱ 10:00 ጀምሮ በላይ ቤት ኮላሽ ተራራ ላይ የገባው የክፍለጦሩ ሻለቃ የጠላትን የቁም ምሽግ ሙሉ በሙሉ በመበተን አካባቢውን በቁጥጥሩ ስር በማድረግ ፤ በተጨማሪም በዞማ ዙሪያ እና ከአለም ከተማ መውጫ በአከያ መስክ ላይ የሠፈረውን የጠላት ኃይል ሌላኛዋ የክፍለጦሩ ሻለቆች በቅንጅት ተቆልፎ የተያዘ ሲሆን፣ በተደረገው የጨበጣ ውጊያ የጠላት ክፉኛ ተመቷል። በዚህ አስደናቂ ውጊያ አንድ ሙሉ የአገዛዙን ታጣቂ የጫነ ኦራል ተሽከርካሪ ልዩ ስሙ ዘይታ በተባለ ቀበሌ በቦንብ ተመቶ ከነጫነው የሰው ሀይል ወደ አመድነት ተቀይሯል። ሽንፈቱን ተከትሎ ከፌጥራ እስከ አለም ከተማ ያለውን ጥምር ኃይል በማንቀሳቀስ የኮላሹን ኃይል ለመታደግ የሞከረው የጠላት እቅድ፣ በአለም ከተማ አቅራቢያ በተጣለበት አስደንጋጭ ደፈጣ መክኗል። በአሁኑ ሰዓት ጀግኖቹ ቦታቸውን ይበልጥ እያሻሻሉ ሲሆን፣ በጀግኖቹ የአልሞ ገዳይ (ስናይፐር) ቡድን ክፉኛ የተመታውና የተበታተነው የጠላት ኃይል ሙትና ቁስለኛውን ለመሰብሰብ በመወራጨት ላይ ይገኛል። ነገር ግን ከጀግኖቹ ባሩድ የተረፈ የለም። የጠላት ኃይል በኮላሽ ተራራማ ቦታ ከአመራሮቹ ጋር ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ የተደመሰሰ ሲሆን፣ የሚከተሉት ወታደራዊ ቁሳቁሶች እና የጠላት ሀይል በጀግኖቹ ቁጥጥር ስር ውለዋል፦ ✔ 03 የኮማንዶ አመራሮች ተማርከዋል ✔.01 ብሬን (ከነሙሉ ሸንሸሉ) ✔.07 ክላሽንኮቭ ጠመንጃ ✔.03 ማውዘር (መንቶፍ) ✔.02 መገናኛ ራዲዮ ✔.02 ኤፍ-1 ቦንብ ✔.12 ካዝና እና ✔. 07 የደረት ትጥቅ 360 የክላሽ ተተኳሽ ጥይቶችና ሌሎች ልዩ ልዩ ወታደራዊ ቁሳቁሶች መማረክ ተችሏል። የተስፋ መቁረጥ እርምጃ በጀግናው ናደው ክፍለጦር ክንድ የደረሰበትን ከባድ ኪሳራ መቋቋም ያልቻለው የአገዛዙ ኃይል፣ በተለመደው የሽንፈት ባህሪው ዙ-23 እና ሞርተር በመጠቀም በንፁሃን አርሶ አደሮች መኖሪያ ቤቶችና ንብረቶች ላይ የበቀል ጥቃት በመሰንዘር ላይ ይገኛል። ኮሩ ከግንባር ያደረሰው መረጃ እንደሚያመለክተው፣ አሁን የተጀመረው ስልታዊ ማጥቃት ተጠናክሮ የሚቀጥል ሲሆን ጠላትን በእያንዳንዱ ምሽግ የመቅበሩ ስራ ይቀጥላል ሲል ገልጿል ።ሌሎች ተያያዢ ዝርዝር መረጃዎችን በሚደርሰን መረጃ ይዘን የምንመለስ ይሆናል። " ክብር ለትግሉ ሰማዕታት! " ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

+8

📌 በትግላችን ውስጥ ካሉ መልካም ጅምሮች ወደ ላቀ ተቋማዊ ስኬት! የትግላችን ጉዞ እስካሁን ባሳያቸው ተስፋ ሰጪ ድሎች፣ በጀግኖች ፋኖዎቻችን ተጋድሎ እና በሕዝባችን ጽናት እዚህ ደርሷል። ይሁን እንጂ የጀመርነውን ትግል በትንሽ መሥዋዕትነት ወደ አስተማማኝ ድል ለማድረስ፣ አሁን ካለንበት የወታደራዊና የፖለቲካ ምዕራፍ ጋር የሚመጥን ተቋማዊ አደረጃጀት፣ ደንብና ግልጽ ፍኖተ-ካርታ ማበጀት ይኖርብናል። ይህ በትግሉ ውስጥ ያለን ሁላችንም (አመራሮች፣ ታጋዮች፣ ሕዝብና ዲያስፖራ) ልናስብባቸውና ልናሳድጋቸው የሚገቡ 5 ዋና ዋና ስትራቴጂካዊ ነጥቦች ናቸው፡- 1. ስልታዊ ድሎችን ወደ ተቋማዊ የበላይነት መቀየር (Institutional Discipline) በየአካባቢው ጠላትን በመማረክና በመደምሰስ የምናገኛቸው ወታደራዊ ድሎች በጣም የሚያበረቱ ናቸው። እነዚህን ድሎች ይበልጥ ዘላቂ ለማድረግ፣ ከመንደርና ከአካባቢያዊ ስሜት በላቀ መንገድ አንድ ወጥ የዕዝ ሰንሰለት እና ጥብቅ ወታደራዊ ዲሲፕሊን መፍጠር አለብን። በታሪክ ስኬታማ የሆኑ የሕዝብ ትግሎች (ለምሳሌ የቪየትናም ነፃ አውጪዎች) ውጤታማ የሆኑት ገና በጫካ ሳሉ ጥብቅ "የአመራርና የወታደር የሥነ-ምግባር ደንብ" አውጥተው፣ ድላቸውን በተቋም መምራት ሲችሉ ብቻ ነው። 2. ግልጽ የፖለቲካ ፍኖተ-ካርታ እና የጊዜ ገደብ (Strategic Roadmap) በታማኝነትና በጀግንነት እየተዋጋን ነው። "ከዚህ ምዕራፍ በኋላ ምን እናደርጋለን? ከማንኛቸውም ኃይሎች ጋርስ በምን መርህ ላይ የተመሠረተ ጥምረት እንፈጥራለን?" የሚለውን የሚመልስ ግልጽ ፍኖተ-ካርታ በሰነድ መኖር አለበት። ትግሉን በደረጃዎች ከፋፍሎ፣ ተለዋዋጭ ግን ግልጽ የጊዜ ሰሌዳ ማስቀመጥ የአመራሩንና የሕዝቡን ራዕይ አንድ ያደርገዋል። 3. የሕዝባችንን ማኅበራዊና አስተዳደራዊ መሠረት ማጠናከር (Civil Administration) ሕዝባችን ደጋፊና ስንቅ አቅራቢ ሆኖ በትግሉ ጎን ቆሟል። ትግሉ ይበልጥ ሥር እንዲሰድድ፣ ፋኖ በተቆጣጠራቸው አካባቢዎች ሁሉ ሲቪል መስተዳድሮችን በመፍጠር፣ ፍትሕና ሰላምን ማስፈን መቻል አለበት። ሕዝቡ በነፃነት አካባቢውን ማስተዳደር ሲጀምር በትግሉ ላይ ያለው ባለቤትነት ይበልጥ ይጨምራል። 4. የዲያስፖራውን ድጋፍ በተደራጀ አቅም መምራት (Institutionalizing Diaspora Support) በውጭ ያለው ወገናችን በትግሉ መጀመሪያ ጀምሮ ትልቅ የሞራልና የፋይናንስ ድጋፍ እያደረገ ይገኛል። ይህ ድጋፍ በግለሰቦች ግንኙነት ወይም በጊዜያዊ ስሜት ላይ ብቻ እንዳይመሠረት፣ በአንድ ማዕከላዊና ግልጽነት ባለው አሠራር እንዲመራ ማድረግ ያስፈልጋል። ይህ ሲሆን የሀብት ብክነት ይቆማል፣ የረጅም ጊዜ አቅምም ይገነባል። 5. የሚዲያ፣ የአክቲቪስትና የጋዜጠኞች አዲስ ስልታዊ ሚና (Strategic Media & Narratives) ሚዲያዎቻችንና አክቲቪስቶቻችን የሕዝቡን ድምፅ በማሰማት ረገድ ትልቅ ሥራ ሰርተዋል። ከአካባቢያዊ ዜናዎች ማጋነን ወይም አንዳንዴ በውስጥ ጉዳዮች ላይ ከሚፈጠሩ አለመግባባቶች ወጥተን፣ ትኩረታችንን በትግሉ ዋና ስትራቴጂ ላይ ማድረግ አለብን። የሚዲያ ሥራ የስነ-ልቦና ጦርነት አካል በመሆኑ፣ ወገንን በሚያጠናክር፣ ጠላትን በሚያዳክም እና የትግሉን ዲሲፕሊን በሚጠብቅ ስልጡን መንገድ መመራት አለበት። እስካሁን የመጣንበት መንገድ የጀግንነት ነው፤ ወደፊት የምንጓዝበት መንገድ ደግሞ የስትራቴጂ፣ የደንብና የተቋም መሆን አለበት። ሁላችንም በየተሰማራንበት መስክ ይሄንን ተቋማዊነት ለመገንባት በጋራ እንረባረብ። ድል ለሕዝባችን!

አፋብን ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ ዕዝ 106ኛ ኮር 34ኛ ክፍለጦር ድልን ተጎናጽፈዋል ። የአገዛዙ የ61ኛ እና 65ኛ ክፈለ ጦሮች ከጋዞ ወረዳ እስተይሽ ከተማ መነሻውን ያደረገው ሲሆን 4ሬጅመንት ሀይሎች በጋዞ ወረዳ እና በላስታ ወረዳ በረሃማ ቦታዎች በጓጓጉላ ማሪያም ፣በስናጭራ መድሀኒያለም እና በዋሮ በተለያዬ ቦታ ፋኖን እመታለሁ ብሎ የተንቀሳቀሰ ቢሆንም ይህን የተረዱት የጦር ጠበብቶቹ ወደ መግደያ ቦታ ስቦ በማስገባት ከባድ ቆሳዊ እና አካላዊ ጉዳት እንዲደርስበት አድርገዉታል። በዚህ ጥቃት ከባድ ጉዳትን ያስተናገደው የአገዛ ሰራዊት የሞተበትን እንኳን ሳይቀብርና ሳያነሳ ወደ መጣበት እግር አውጭኝ በማለት ፈርጥጧል። ከጥዋቱ 12:00 ሰዓት ጀምሮ እስከ ምሽቱ 10:00 ሰዓት በተደረገ እልህ አስጨራሽ ውጊያ የተደረገ ሲሆን ለከበባ የመጣው የብልፅግና ጥምር ሰራዊት እራሱ ተከቦ ሞራላዊና ቁሳዊ ጉዳትን ተሸክሞ በእፍረትና ሽንፈት ወደ ከተማ ጉሪያቸው ተመልሰዋል። መዳረሻውን ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ሕዝብ የሕልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲል106ኛ ኮር 34ኛ ክፍለጦር ህዝብ ግንኙነት ክፍል መረጃውን አድርሷል!!! መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!! ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ!! ሀምሌ 03/11/2018 ዓ/ም

photo content

ኮንስታብል እሱባለው ሀብታሙ ከነ ሙሉ ትጥቁ በመካነሰላም ግንባር ፋኖን ተቀላቀለ!! በየቀኑ በቡድንም በተናጠልም የጠላት ኃይል ወደ ፋኖ እየገባ ነው:: በዚህም መሰረት የአድማ ብተና አባሉ ኮንስታብል እሱባለው ሀብታሙ ከጠላት ጋር በማበር የራሴን ህዝብ ከዚህ በላይ ልበድል አልፈልግም በማለት የአፋብን ወሎ ቤተ- አማራ ምኒልክ እዝ 105 ኛ ኮር 29ኛ ክፍለ ጦር ሰራዊትን በዛሬው እለት ተቀላቅሏል:: የክፍለ ጦሩ ህዝብ ግንኙነት ዘርፍ ም/ኃላፊ አርበኛ አበራ አቢ ከጓዶቹ ጋር ሆኖ ኮንስታብሉን ተቀብሎታል:: የአማራን ህዝብ ላይ በምድርም በሰማይም እየተኮሰ ካለው የአብይ አህመድ መንግስት ጋር የተሰለፉ የፀጥታ ኃይል አባላት እየፈፀሙ ያሉት የግፍ ግፍ አንገሽግሾት ወደ ፋኖ መምጣቱን የገለፀው ኮንስታብሉ መከላከያ ሰራዊት አድማ ብተና እና ፓሊስ እንድሁም ሚሊሻን እንደት እየተጠቀመበት እንደሆነም አብራርቷል:: እንደ ኮንስታብሉ ገለፃ የአማራ ክልል የፀጥታ ሀይል አባላት ለመከላከያ ጥይት ማብረጃ ሆነዋል:: ከፊት ግቡ እየተባልን እንገደዳለን ሲልም ነው ኮንስታብሉ የነበረውን ሁኔታ በማስታወስ የገለፀው:: አማራ ሆኜ በአማራ ላይ ስተኩስ የነበረው ሴራው ስላልገባኝ ነበር አሁን ህዝቤን ለመካስ መጥቻለሁ ሲልም ኮንስታብል እሱባለው ተናግሯል:: መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!! ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ሚዲያና ኮሚዩነኒኬሽን መምሪያ ሀምሌ 2/2018 ዓ.ም

photo content

ሰበር ዜና❗❗ የብልፅግና መዋቅር መፈራረስ እና የፋኖ የትጥቅ ትግል ስኬት!! ቀን 01/11/2018 ዓ.ም ከትጥቅ ትግል ስልትና ስነ-ልቦና አንፃር፣ የወራሪ ወይም የጨቋኝ ሀይል መፈራረስ የሚጀምረው ከውስጥ በሚፈጠር መከፋፈል እና በወታደሩ መክዳት ነው። ዛሬ በሸዋ ጠቅላይ ግዛት መርሀቤቴ አውራጃ የታየው ክስተት ይህንን እውነታ ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ሲሆን፣ የፋኖን የትጥቅ ትግል ወደ ላቀ ስልታዊ ምዕራፍ አሸጋግሮታል። የብልፅግና አገዛዝ ላለፉት ሶስት አመታት በአማራ ህዝብ ላይ የከፈተውን ዘመቻ ለማሳካትና የተዳከመውን መደበኛ ሰራዊቱን ለመተካት አዲስ ወታደራዊ ሴራ ቀይሶ ነበር። ይኸውም እስከ 40,000 የሚደርሱ የአማራ ክልል ሚሊሻዎችንና የአድማ ብተና አባላትን ያለምንም ህጋዊ መስፈርት ወደ መከላከያ በመቀየር "አማራን በአማራ" የማጋጨት ስልት ነበር። ሆኖም ይህ ሴራ በትጥቅ ትግሉ የህዝባዊነት አስተሳሰብና በፋኖ የፅናት ክንድ ፊት ሊቆም አልቻለም። የአገዛዙን ወታደራዊ ተንኮል አስቀድመው የተረዱት፣ የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ስር ሃያ አንድ ( 21) የሚሊሻ አባላት የአገዛዙን የጦር መዋቅር ከውስጥ በመናድ ታሪክ ሰርተዋል። እነዚህ ጀግኖች የክፍለ ጦሮቹን የአፋብን ሸ/ጠ/ግ/አ/ዕዝ የአፄ አምደጽዮን ኮር፣ 17ቱ አፄ ዳዊት ክፍለ ጦርን እና 4ቱ ራስ አበበ አረጋይ ክፍለ ጦርን በበሳል የፖለቲካ ስራ በማሳመን፣ የጨቋኙን ሴራ በመረዳት የታሪክ ተጠያቂነት ላለመሆን ከነሙሉ ትጥቃቸው የህዝባቸውን ጋሻ ፋኖን ተቀላቅለዋል። ➡ ይህ ክስተት በትጥቅ ትግሉ ሂደት ውስጥ ትልቅ ስልታዊ ድል ነው። ምክንያቱም፦ ✔ የጠላት ኃይል መዳከምን ያሳያል፦ የጠላትን ሰራዊትና ትጥቅ በመቀነስ፣ የፋኖን የሰው ኃይልና ወታደራዊ አቅም በአንድ ጀምበር ያጠናከረ እርምጃ ነው። ✔ የስነ-ልቦና የበላይነት፦ በአገዛዙ መዋቅር ውስጥ ፍርሀትና መፈራረስን ሲዘራ፣ በነፃነት ታጋዮችና በህዝቡ ዘንድ ደግሞ የድል ስሜትንና መተማመንን አንግሷል። ✔ የመከላከያ መስመር መናጋት፦ አገዛዙ እንደ ትልቅ የጦር ስትራቴጂ የያዘውን ዕቅድ ገና ሳይተገበር አክሽፎታል። የአማራ ህዝብ ህልውና በተባበረ ክንድ እንደሚረጋገጥ ይህ አምሳያ የሌለው ጀግንነት ማረጋገጫ ነው። በትጥቅ ትግሉ ጎዳና ላይ የጠላትን ምሽግ ሰብሮ መግባት ብቻ ሳይሆን፣ የጠላትን ሰራዊት ወደ ነፃነት ሃይል መቀየር የድሉን መቅረብ ያበስራል። " ክብር ለትግሉ ሰማዕታት! " ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

photo content
+1

የሱዳን ጦር ስትራቴጂካዊቷን የኩርሙክ ከተማ መቆጣጠሩ ተገለፀ። የብልፅግና ሠራዊትና የRSF የድንበር ላይ አሰላለፍ አዳዲስ ውጥረቶችን ፈጥሯል። ባለፉት ሳምንታት ከኢትዮጵያ ድንበር በቅርብ ርቀት ላይ በሚገኘው የብሉ ናይል ግዛት ውስጥ መጠነ ሰፊ ወታደራዊ ዘመቻ ሲያካሂድ የቆየው የጄነራል አል-ቡርሃን የሱዳን መደበኛ ጦር፣ በዛሬው ዕለት እጅግ ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ ያላትን የኩርሙክ ከተማን ሙሉ በሙሉ መቆጣጠሩን በይፋ አስታውቋል። የሱዳን ጦር ከተማዋን ለመያዝ ካለፈው ሳምንት ዓርብ ጀምሮ ከተቀናቃኙ የጄነራል መሐመድ ሀምዳን ዳጋሎ (ሄሜቲ) የፈጥኖ ደራሽ ኃይል RSF ጋር እጅግ ከባድና ደም አፋሳሽ ትንቅንቅ ሲያደርግ ቆይቷል። ሁለቱም ኃይሎች በከባድ መሣሪያዎች የታገዘ ውጊያ ካደረጉ በኋላ፣ በመጨረሻም የሱዳን መደበኛ ጦር የበላይነቱን በመያዝ ከተማዋን ከRSF ኃይሎች ማስለቀቅ መቻሉ ታውቋል። የኩርሙክ ከተማ በኢትዮጵያና በሱዳን መካከል ቀጥተኛ የየብሥ ግንኙነት መስመር በመሆኗ፣ ለአገራቱ የሁለትዮሽ የንግድ ልውውጥ ብቻ ሳይሆን ለድንበር ቀጣናው ወታደራዊና ሎጂስቲክስ እንቅስቃሴ እጅግ ወሳኝ የደህንነት መተላለፊያ ተደርጋ ትወሰዳለች። ከተማዋ በሱዳን መደበኛ ጦር እጅ መውደቋ በድንበሩ አካባቢ ያለውን የወታደራዊ ኃይል ሚዛን በእጅጉ ሊቀይረው እንደሚችል ይገመታል። በሌላ በኩል፣ ከዚሁ የድንበር ውጊያ ጋር ተያይዞ በጄነራል ሄሜቲ የሚመራው የሱዳን ተቃዋሚ ጦር (RSF) በኢትዮጵያ ድንበር አካባቢ ከብልፅግና ሠራዊት ጋር በጋራ መሠለፉ ታውቋል። ይህ አዲስ ወታደራዊ አሰላለፍ በሱዳን የውስጥ ፖለቲካና በኢትዮጵያ የድንበር ደህንነት ላይ አዲስ መልክ ፈጥሯል። ነውሩን የማይመለከተው የብልፅግና አገዛዝ የአማራ ፋኖን "ከብሔራዊ ጠላቶቼ ጋር አብራችሁ እየሠራችሁ ነው" በሚል በተደጋጋሚ ሲከስና ቢቆይም፣ ራሱ የብልፅግና ሠራዊት ግን በሱዳን የእርስ በእርስ ጦርነት ውስጥ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ እጁን ዘፍቆ ይገኛል። ይህ በኢትዮ-ሱዳን ድንበር አካባቢ እየታየ ያለው አዲስ ወታደራዊና ፖለቲካዊ እንቅስቃሴ በቀጣናው ጂኦፖለቲካ እና በብልፅግናው አገዛዝ ላይ ጫና መፍጠሩ አይቀሬ ነው።