የኮተቤ ትምህርት ዩኒቨርስቲ ግቢ ጉባኤ
Open in Telegram
የኮተቤ ትምህርት ዩኒቨርሲቲ ግቢ ጉባኤ መደበኛ ቻናል ነው፡፡ በዚህ ቻናል 👉 ትምህርታዊ ጽሑፎች ፤የግቢ ጉባኤው መልዕክት ፤የክፍላት ማስታወቂያዎች ይተላለፉበታል፡፡ ሀሳብ አስተያየት ጥያቄ ካለ @ethiopia_1616 ላይ ይፃፉልን፡፡ contact 0923584792 /0928381616
Show moreThe country is not specifiedThe category is not specified
430
Subscribers
-124 hours
No data7 days
-230 days
Posts Archive
ዛሬ ሐሙስ የተተኪ ስራ አመራር ስልጠና ይጀመራል ሁላችንም እንቀስቅስ የመጀመሪያ እና የሁለተኛ አመት ተማሪዎች ሁላቸውም የመገኘት ግዴታ አለባቸው 3rd አመት ተማሪዎች ስልጠናውን ያልወሰዱ ይገኙ 11:30 ጀምሮ ሀና ማርያም ላልስሙ እናሰማ
ከአባላት ክፍል
ማንንም አልተቀየመችም
በምድር ላይ እንደ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ያዘነ፤ ሊያዝንም የሚችል ሰው ሊኖር አይችልም። አንድ ልጇን ይዛ ገና በልጅነቷ ነበር ወደማታውቀው ስደት የገባችው። ከጠላት ለመደበቅ ቀንና ሌሊት ያለ እረፍት ተጉዛለች።
ልጇ በሠላሳ ዓመቱ ወደ አደባባይ ወጥቶ ሲያስተምርም በብዙ መልኩ ሲፈተንና ሲነቀፍ አይታለች።
ምንም በደል ሳይኖርበት በሐሰት ተከስሶ ሲፈረድበት “ልጅሽ በአደባባይ ሊሰቀል ነው ነይ እይ” ተብላ ስትጠራ በጅራፍ ሲገረፍ፣ ራቁቱን አደባባይ ላይ ተሰቅሎ ምንም ልታደርግለት እንደማትችል ምስኪን ከመስቀል ስር ቆማ ደም አልቅሳለች።
እኔን የሚደንቀኝ ይሄ ሁሉ ሆኖባትም እርሷ ግን ማንንም አልተቀየመችም፤ ኧረ ቂሙን ተዉት ማዘኗን እንኳ አልነገረችንም። ዓለም ተሰብስቦ አንዱን ንጹሕ ልጄን ሰቀሉብኝ ብላ አልተናገረችም፤ ጴጥሮስን
'ለምን ልጄን ጥለኽው ሸሸህ?' አላለችውም። ሁሉንም በልቧ ጠበቀችው።
እኛ ልጃችን ተሰቅሎ አይደለም 'ሰው ገላመጠኝ ፤ ክብሬን ነካው' ብለን የምንጣላና የምንኳረፍና የምንጠላላ ግብዞች አሁን እውን እመቤታችንን «እናቴ» የማለት ምግባር አለን? እንደው ትኩር ብለው ቢያዩን ግን ምናችን የድንግል ማርያም ልጅ ይመስላል?
ሰአሊ ለነ ቅድስት!
❝ምንተኑ ንሰምየኪ ኦ ምልዕተ ጸጋ፥ አንቀጸ መድኃኒት አንቲ፤ ኆኅተ ብርሃን አንቲ፤ ወለተ መንግሥት አንቲ፤ ሰማይኑ ንብለኪ? ፀሐየ ጽድቅ ወልድኪ ... ❞— አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
✨ ጉባኤ ኒቆዲሞስ ✨
ማቴ 18/20 በስሜ በሚሰበሰቡበት በዚያ በመካከላቸው እሆናለሁና።
እንኳን ለቅዱስ ገብርኤል ወርሐዊ በዓል አደረሳችሁ እያልን
✨ሰኞ ሚያዚያ 19✨
ተወዳጇ እና ተናፋቂዋ የአንድነት ጉባኤያችን ጉባኤ ኒቆዲሞስ።
📌 በዕለቱ የሚኖሩን መርሐግብራት
ꔰ ጸሎት
ꔰ ትምህርተ ወንጌል
ꔰ የመዝጊያ ጸሎት
ሰዓት፦ 11፡15(30)-1:30
ቦታ፦ መ/ቅ/ኢ/ወሐና ቤተክርስቲያን ፍቅረ ሰላም
አዳራሽ
👉በሰዓቱ ጀምረን በሰዓቱ እንድንፈፅም
በሰዓቱ እንገኝ🙏
✨ኮተቤ ግቢ ጉባኤ✨
የዕለቱ ስንቅ
"አሻጋሪዎች"
ሰባኪው በአንድ ቤተክርስቲያን እየተገኘ ዘወትር
ያስተምራል። በየእለቱ በርካታ ምእመናን በቦታው እየተገኙ ይሰበካሉ (ይማራሉ)። ከእነዚህ በርካታ ምእመናን ውስጥ አንደኛው ራቅ ካለ ቦታ ነው ሚመጣው። ወደ ቤተክርስቲያን ሲመጣም ሆነ ሲመለስ መሻገሪያ ድልድይ የሌለውን ወንዝ እየዞረ ስለሆነ ከሌሎች ይልቅ ብዙ የሚደክመው እሱ ነው።
አንድ ቀን ግን እንዲህ ሆነ፦
ሰባኪው የሚያስተምረው ስለ ጽኑ እምነት ነበር። " የሰናፍጭ ቅንጣት የሚያህል እምነት ቢኖራችሁ፥ ይህን ተራራ፦ ከዚህ ወደዚያ እለፍ ብትሉት ያልፋል፤ የሚሳናችሁም ነገር የለም።” የሚለውን ማቴ. 17፥20 ያለውን የመጽሃፍ ቅዱስ ኃይለ ቃል ጠቅሶ ሰው በእምነቱ ጽኑ ሲሆን የሚሳነው ነገር እንደሌለ ለምእመኑ አስረዳና የዕለቱን ስብከት አጠናቀቀ።
መሻገሪያ በሌለው ትልቅ ወንዝ ምክንያት ከሌሎቹ ምእመን ይልቅ ብዙ የሚደክመው ያ ሰው ከቤተክርስቲያኑ ቅጥር ወጥቶ ወደ ቤቱ ሲያቀና እንደተለመደው እዛ ድልድይ አልባ ወንዝ ላይ ደረሰ። ወንዙን ሲያየው ሰባኪው ያስተማረው የእምነት ትምህርት ድቅን አለበት። ወዲያውኑ "እኔ እኮ በእግዚአብሔር አምናለሁ እግዚአብሔርም ይህን ለእኔ ማድረግ አይሳነውም" በማለት በፍጹም እምነት ወደ ጥልቁ ወንዝ በመሄድ ረገጠው እንዳለውም ተሳካለት መራመድም ቻለ። ያን ዙሪያ ጥምጥም የሆነ የቤቱን ጎዳና በጣም አጭር በሆነ ደቂቃ አጠናቆ ቤቱ ግባ።
ሚስቱም በመደንገጥ "ቤተክርስቲያን አልሄድክም እንዴ? ምነው በጊዜ መጣህ?" ብላ ብትጠይቀው የሆነውን ሁሉ ነገራት። እሷም በጣም ተደንቃ "ባለቤቴ ይህ ተዐምር ከተደረገለት መምህሩማ ምን ያህል ኣምላክ የመረጠው ቅዱስ ነው" ብላ "በል ነገ ይዘኸው ና! ቤታችንን በበረከት ይጎብኝልን።" በማለት ባለቤቷን ተማጸነች።
በማግስቱ የዋሁ ባል ያለምንም ፍርሃት እና ጥርጣሬ በወንዙ ላይ ተረማምዶ ከተሻገረ በኋላ ትምህርቱን ተከታትሎ ጉባኤው ሲፈጸም ሰባኪውን ሄዶ፥ "ባለቤቴ እቤት እየጠበቀችን ነው እባክህን አብረን እንሂድ አለው።" ሰባኪውም ግብዣውን ተቀብሎ ጉዞ ጀመሩ። ሁለቱም እዚያ ወንዝ አጠገብ ሲደርሱ የዋሁ ሰውዬ እንደለመደው በውሃው ላይ እየተራመደ ጥቂት ከተጓዘ በኋላ ዞር ብሎ ሰባኪውን ሲመለከት ከወንዙ ዳር እንደቆመ ነው። በሰባኪው መቆም ተገርሞ "ና እንጂ መምህር ምን ሆነሃል?" ሲል ጠየቀው። ሰባኪውም "ፈራሁ" ሲል ይመልስለታል። ውሃውን እየረገጠ ወደኋላ ተመልሶ "ምነው መምህር? እኔን ለዚህ አብቅተህ እንዴት ትፈራለህ? ና ተሻገር እባክህን" ሲል ጠየቀው በሰውዬው ንግግር ጭንቅላቱ የተነካው መምህርም፡ "ወዳጄ እኛ እናሻግራለን እንጂ አንሻገርም!" ሲል መለሰለት።
እኛስ የምንናገረውንና የምናዳምጠውን፣ የምናስተምረውንና የምንማረውን፣ የምንሰብከውንና የምንሰበከውን እየኖርን ነውን?
ሠናይ ዕለተ ሰንበተ ክርስቲያን!
🌟 የምስረታ በዓል በረከት ከግቢ ጉባኤያችን! 🌟
በጉጉት ስንጠብቀው የነበረው በየዓመቱ የምስረታ በዓል በማስመልከት በግቢ ጉባኤያችን የሚዘጋጀው በአሁኑ ዓመትም ለየት ባለ መንገድ ታላላቅ እጣዎችን ይዘን ወደ እናንተ መጥተናል።
🎁 ዕጣዎቻችን ⚡️1ኛ ዕጣ 1ኛ ደረጃ በገና ⚡️2ተኛ ዕጣ መጽሐፍ ቅዱስ (ህያው የሆነው የእግዚአብሔር ቃል የምናነብበት) ⚡️3ተኛ ዕጣ ትልቁ ስዕለ አድህኖ (frame) ⚡️4ተኛ ዕጣ ፍትሀ ነገስት ማብራሪያ ⚡️5ተኛ ዕጣ መፅሐፍ በአዲሱ ስርዓተ ት/ት የታተመ (ሐይማኖት እና ሳይንስ)📍ሎተሪውን የት ያገኙታል? 👉በሁሉም የክፍላት ተወካዮች 👉በግቢ ጉባኤያችን የቀድሞ ምሩቃን 👉ወደ ግቢ ጉባኤ በሚመጡበት በማንኛውም ጊዜ 🎟️ እጣውን አሁኑኑ ይቁረጡ! ይህንን በጎ ዕድል በመጠቀም የበረከቱ ተሳታፊ ይሁኑ!" ▬▬▬▬▬▬◈◈◈▬▬▬▬▬ ከልማት ክፍል
ሰላም ውድ የእግዚአብሔር ቤተሰቦች
እሕትና ወንድሞቼ እንደምን አላችሁ? ደህናናችሁ? የ2018 ዓ.ም ትምህርት እና አገልግሎት እንዴት ይዟችሗል? በርቱልን የምር ግቢ በጣም የሚናፈቅና የወደፊት ስንቅ የሚሰነቅበት ጥሩ እና ብዙ የሕይወት ሙያ የሚለምዱበት ትልቅ ኪችን(የምግብ ማዘጋጃ ክፍል) ነው ብለው አልሳሳትም እና በርቱልኝ በጣም እወዳችሗለሁ ሰላማችሁ ይብዛ።
ታዲያ እግረ መንገዴን አንድ የሶሻል ሜዲያ ፔጅ ላይ ስዘዋወር ያገኘዋትን አጠር ያለች ግን ሰፊ መልእክት ያላትን
በጣም ጠቃሚ ምክር ላጋራችሁ ወደድኩ....ምናልባት ብዙዎቻችሁ ታውቁት ይሆናል ማወቁ ብቻ ግን ትርጉም አይኖረውም ይልቁንም በተግባር መኖር እንጂ...
🏨 👩🎓🧑🎓👨💻👩💻 በአንድ ዩኒቨርሲቲ የሳይኮሎጂ ዲፓርትመንት መምህሯ ተማሪወቿን አንድ Assignment መስጠት ፈለገች..!! ተማሪወቿን ድንች ይዘዉ እንዲመጡ አዘዘች ፡፡ ድንቾቹ ላይም የሚጠሏቸዉን ሰወች ስም እንዲፅፉ አዘዘቻቸዉ ፡፡
፡
🥔🥔🥔 የሚያመጡት የድንች ብዛትም በሚጠሏቸዉ ሰወች ብዛት ልክ እንዲሆን አለች ፡፡ በሁለተኛዉ ቀን አንዳንዶቹ 3 ሌሎች 5 ቀሪዎቹ ደግሞ 8 ድንቾቹን የሚጠሏቸዉን ሰወች ስም ፅፈዉ አመጡ ፡፡ መምሯ ደግሞ ከዛሬ ጀምሮ ለአንድ ሳምንት እኒህን ድንቾች በሻንጣችሁ ይዛችሁ ትዞራላችሁ ፡፡ ሽንት ቤት ስትሄዱ እንኳ መተዉ አትችሉም! ብላ አዘዘች ፡፡
፡
🤦♀️🤦 ቀኑ እየጨመረ ሲሄድ ድንቹ በመበላሸቱ ሽታዉ ይረብሻቸዉ ስለጀመረ ተማሪዎቹ ቅሬታ ማቅረብ ጀመሩ ፡፡ በተለይም 8 የያዙት ከሽታው በተጨማሪ ክብደቱ እንደበዛባቸው መናገር ጀመሩ ፡፡
፡
👩💻 ከሳምንት በኋላ የአሳይመንቱ ገደብ ስላበቃ ተማሪወች ድንቹን አዉጥተዉ እንዲጥሉ ተፈቀደላቸዉ
፡
👩💻 ከዛም መምህሯ እህ እንዴት ነበር ? ብላ ጠየቀቻቸዉ ፡፡ ሁሉም ማጉረምረም ጀመሩ ፡፡ "አረረረ ከክብደቱ ሽታዉ ፡፡ አረ በጣም ነዉ የሚያስጠላዉ" አሉ
፡
👩💻 መምህሯ አያችሁ በልባችሁ የምትሸከሙት ጥላቻም እንዲሁ ነዉ ፡፡ ጥላቻ ልብን ይመርዛል ፡፡ በምትሄዱበት ሁሉም እየተከተለ ይረብሻችኋል ፡፡ ለአንድ ሳምንት የተበላሸ ድንችን ሽታ መቋቋም አልቻላችሁም ፡፡ አስቡት ደሞ በጥላቻ የተመረዘን ልብ እድሜ ልካችሁን ይዛችሁ ስትኖሩ !! አለቻቸዉ ፡፡
፡
🔥 እናም ውድ እሕትና ወንድሞቼ ጥላቻን ከዉስጣችን አዉጥተን ከእዳ የፀዳን እንሁን!! እዉነተኛ ፍቅር እንከን አልባን ሰዉ ማፍቀር ሳይሆን ንፁህ ያልሆነን ሰዉ በንፁህነት መዉደድ ነዉና !!!
"የሚወዷ፟ችኹን ብትወዱ ምን ዋጋ አላችሁ ቀራጮችስ ያንኑ ያደርጉ የለምን?" ማቴ 5፥46
መልካም አዳር የያዕቆብ ሌሊት ይሆንላችሁ ዘንድ ተመኘሁ!!!!
መንፈሳዊ ዝሙት እና መንፈሳዊ ጋለሞቶች !
በኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ትምህርት መዝሙር ማለት ዝም ብሎ ዜማ ወይም የቃላት ስብስብ አይደለም፤ መዝሙር ጸሎት፣ ትምህርተ መለኮትን የያዘ ነው። ታዲያ የሌላ እምነት መዝሙር መስማት እንዴት ይታያል? ለምንስ ከመንፈሳዊ ዝሙት ጋር ይያያዛል?
በቅዱስ መጽሐፍ ትምህርት መሠረት ዝሙት በሁለት ይከፈላል፤ ሥጋዊ [የሰውነት መርከስ] እና መንፈሳዊ [የልብና የሃይማኖት መርከስ]።የእግዚአብሔር ነቢይ የሆነው ሆሴዕ "ልባቸው ወደ ሌላ አምላክ በመሄዱ አመነዘሩ" [ሆሴዕ 4፥12] ይላል። አንዲት ነፍስ ለክርስቶስ በኦርቶዶክሳዊት እምነት ታጭታ ሳለች የሌላን እምነት[መናፍቃኑን] ትምህርትና ዜማ በልቧ ስትቀበል መንፈሳዊ ዝሙት ይባላል። ምክንያቱም ሃይማኖት እንደ ጋብቻ ነው፤ መከፋፈልን አይፈቅድም።
በቤተክርስቲያናችን መዝሙር ዜማ ብቻ ሳይሆን ዶግማ እና ሃይማኖት ነው። በፕሮቴስታንት 'መዝሙሮች' ውስጥ የቅዱሳን አማላጅነት፣ የድንግል ማርያም ክብር እና የቤተክርስቲያን ምስጢራት ቦታ የላቸውም። አባቶቻችን 'ጥሩ ውኃ የሚገኘው ከንጹሕ ምንጭ ነው' ይላሉ። የቤተክርስቲያን መዝሙሮች በጾም፣ በጸሎትና በሥርዓት የተቃኙ ናቸው። የሌላ እምነት መዝሙሮች ግን ከቤተክርስቲያን ቀኖና ውጭ ስለሆኑ መንፈሳዊ ማንነትን ይበክላሉ። ብጹዕ ጳውሎስ "ከክርስቶስ ይልቅ ሰውን ደስ ለማሰኘት የምትፈልጉ ከሆነ የክርስቶስ ባሪያዎች አይደላችሁም" [ገላ 1፥10] ይለናል ይህም የሌላ እምነት 'መዝሙር' ጆሮን ቢያስደስትም፣ ነፍስን ግን ከእውነተኛው የኦርቶዶክስ መስመር ያስወጣታል።
ስለዚህ እናንተ ለሁለት ጌታ የምትገዙ መንፈሳዊ ጋለሞቶች ሆይ ንቁ! በአንደበታችሁ "ኦርቶዶክሳዊ ነኝ" እያላችሁ በጆሯችሁና በልባችሁ ግን የሌላን እምነት ትምህርትና ዜማ የምትጋቱ ሆይ፤ ይህ የማንነት ስርቆትና መንፈሳዊ ግልሙትና ነው። ቅድስት ቤተክርስቲያን በሥጋ ወደሙ ቀድሳና አንጽታ በቅዱስ ቅብዐ ሜሮን ለክርስቶስ አጭታችሁ ሳለ እናንተ ግን ነፍሳችሁን ለባዕድ ትምህርት አሳልፋችሁ ሸጣችኋል። ቅዱሳት መጻሕፍት እንደሚሉን "ሁለት ልብ ላለው በመንገዱም ሁሉ ለሚወላውል ሰው ወዮለት!" (ያዕቆብ 1፡8)።
ዛሬ ቤተክርስቲያን ሳትከለክላችሁ፣ እናንተ ግን ዜማው ደስ ይላል በሚል ሰበብ ከእውነት ምንጭ ወጥታችሁ ከተመረዘ ኩሬ ትጠጣላችሁ። ይህ በጋብቻ ላይ ማመንዘር እንደሆነ ሁሉ በሃይማኖት ላይም ማመንዘር ነው ግልጽ ጋለሞትነታችሁን እየገለጻችሁ እና እያወጃችሁ ነው።
እናንተ ጋለሞቶች ሆይ፦ ብርሃን ከጨለማ ጋር ምን ኅብረት አለው? ክርስቶስስ ከቤልሆር ጋር ምን መስማማት አለው? [2ቆሮ 6፥14-15]። ኦርቶዶክሳዊነት ሙሉነት ነው፤ ጭማሪ ወይም ድብልቅልቅ አያስፈልገውም። ወይ ከዝሙታችሁ ተመለሱ ወይ ከቤተክርስቲያን ጫንቃ እና አስመሳይነታችሁ ተለይታችሁ ውጡ!!
“ወይስ ሥጋችሁ ከእግዚአብሔር የተቀበላችሁት በእናንተ የሚኖረው የመንፈስ ቅዱስ ቤተ መቅደስ እንደ ሆነ አታውቁምን? በዋጋ ተገዝታችኋልና ለራሳችሁ አይደላችሁም፤ ስለዚህ በሥጋችሁ እግዚአብሔርን አክብሩ።”— 1ኛ ቆሮንቶስ 6፥19-20ክርስቶስ ተንሥአ እሙታን፣ በአማን ተንሥአ!! ▬▬▬▬▬▬◈◈◈▬▬▬▬▬ 📍የኮተቤ ት/ት ዩንቨርሲቲ ግቢ ጉባኤ📍
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
✨ ጉባኤ ኒቆዲሞስ ✨
ማቴ 18/20 በስሜ በሚሰበሰቡበት በዚያ በመካከላቸው እሆናለሁና።
✨ሰኞ ሚያዚያ 12✨
ተወዳጇ እና ተናፋቂዋ የአንድነት ጉባኤያችን ጉባኤ ኒቆዲሞስ።
📌 በዕለቱ የሚኖሩን መርሐግብራት
ꔰ ጸሎት
ꔰ ትምህርተ ወንጌል
ꔰ የመዝጊያ ጸሎት
ሰዓት፦ 11፡15(30)-1:30
ቦታ፦ መ/ቅ/ኢ/ወሐና ቤተክርስቲያን ፍቅረ ሰላም
አዳራሽ
👉በሰዓቱ ጀምረን በሰዓቱ እንድንፈፅም
በሰዓቱ እንገኝ🙏
✨ኮተቤ ግቢ ጉባኤ✨
ዳግማይ ትንሣኤ
ዳግማይ ትንሣኤ (ሁለተኛው ትንሳኤ) ማለት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶ ከሙታን ተለይቶ በተነሳ በስምንተኛው ቀን በዕለተ እሑድ ደቀመዛሙርቱ በአንድነት ተሰብስበው ሳሉ ለሁለተኛ ጊዜ ተገልጦ ትንሳኤው ምትሐት ያይደለ ፍጹም አማናዊ እንደሆነና እንደ ቶማስ የተጠራጠረውን ና ንካኝ በማለት ያሳመነበት ዕለት ነው፡፡ዳግማይ (ሁለተኛ) ያሰኘው መገለጡን ይዞ ነው፡፡ቅድስት ቤተ ክርስቲያንም ትንሳኤ ባለፈ የሚመጣውን እሑድ ሰይማ ታከብረዋለች፡፡ /ዮሐ20፤24-30/
ጌታችን ስለምን ዳግመኛ ተገለጠ(
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለሐዋርያቱ ቀድሞ በተዘጋ ግንብ ገብቶ ሰላም ለእናንተ ይሁን ብሎ ተገልጦላቸው ነበር ዳግመኛም ሐዋርያው ቶማስ ባለበት ተገለጠላቸው ምክንያቱም ደግሞ
1ኛ.ካልዳሰስኩ አላምንም ያለ ሐዋርያው ቶማስን ሊያሳምነው ፡- ቶማስን ደቀመዛሙርቱ መጥተው ጌታችንን በመካከላችን ተገልጦ አየነው ብለው ሲነግሩት ‹‹የችንካሩን ምልክት በእጄ ካላየሁ ጣቱንም ወደ ተቸነከረበት ካልጨመርሁ እጄንም ወደ ጎኑ ካላገባሁ አላምንም ›› ብሎ ነበርና ና ንካኝ ብሎ አሳምኖታል፡፡ቶማስ ለምን ተጠራጠረ ብንል ፈሪሳዊ ስለነበረ ነው፡፡ፈሪሳውያን ትንሳኤ ሙታን የለም ብለው ያምናሉ /በማቴ.ወ22፤23-33/ ሃይ.አበው 48፤8-13 ገጽ255/ እርሱም ከሞት በኋላ ሕይወት አለ ብሎ አያስብም ነበር፡፡የጌታችንን ጎን የነካች የቶማስ እጅ በኋላ ላይ ሳትበሰብስ በሕያውነት ለብዙ ዘመናት ኖራለች፡፡ሀገረ ስብከቱና ሰማዕትነት በተቀበለባት በሕንድ ሀገር ከታቦት ጋር ከመንበሩ ላይ ያኖሯት ነበር፡፡በዓመት በዓመት በእመቤታችን በዓል በአስተርዕ ሊያጥኑ ሲገቡ የሚሾመውን ወጥታ ቀኝ እጁን ትይዘዋለች ዓመት አገልግሎ ያርፋል በዓመቱ ሊያጥን ሲገባ ትይዘዋለች እንዲህ እያለች ትኖራለች፡፡
ሌላው ቶማስን ‹‹ ና ጎኔን ንካ›› ሲለው በኋላ በዓለም ዞሮ ወንጌልን የሚሰብክ ነውና ሐዋርያ ከሆነ ዘንድ ደግሞ ‹‹ሐዋርያት እንዳሉት ጌታችን ተነስቷል›› ብሎ ያስተምር ዘንድ አይገባውም ይልቁንም እንደ ወንጌላዊው ዮሐንስ ‹‹በጆሮአችን የሰማነውን በዓይኖቻችንም ያየነውንን የተመለከትነውን እጆቻችን የዳሰሱትን እንነግራችኋለን ሕይወት ለእኛ ተገልጻለችና አየናት›› 1ኛዮሐ1፤1-2 እንዳለው ቶማስን ና ንካኝ ብሎታል፡፡በእርግጥ ‹‹ሐዋርያት እንዲህ አለ›› ብሎ ማስተማር ስህተት ሆኖ አይደለም ምክንያቱም እነ ጳውሎስ ጌታችን ሲነሳ አላዩም ግን እንደ ሐዋርያት በዓለም ወንጌልን አዳርሷል ፡፡ነገር ግን ቶማስ ከ12ቱ ሐዋርያት አንዱ ስለሆነ ግድ ሆኖበታል፡፡
2ኛ.ሰንበትን ሲያጸናልን ፡- የክርስቲያኖች ሰንበት የምንላት ዕለተ እሑድ ጌታችን ሞትን ድል አድርጎ የተነሳባት በመሆኗ የእረፍት የመንግስተ ሰማይ አምሳል ብለን እናከብራታለን፡፡ የዕለቲቱንም ክብርትነት እንድናስብና ዕለተ እሑድ በመጣች ቁጥር ጌታችን የተነሳባትና ለሐዋርያቱ ትንሳኤውን ደግሞ የገለጠባት እንደሆነ እንድናስብ ለአክብሮተ ሰንበት ደግሞ ተገለጠላቸው፡፡አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ‹‹የእሑድ ቀን የክርስቶስ ቀን ናት እሑድ ሰንበትም ተባለች›› መጽ.ምስ ገጽ296
3ኛ.ትንሳኤው ምትሐት እንዳልሆነ ለማስረዳት፡-ጌታችን ራሱ የተገለጠበትን ዓላማ ሲነግራቸው ‹‹እጄን እግሬን እዩ ዳስሱኝም እኔ እንደሆንኩ ዕወቁ በእኔ እንደምታዩት ለምትሐት አጥንትና ሥጋ የለውምና›› ሉቃ24፤39 እንዳላቸው የጌታችን ትንሳኤ ምትሐት ያይደለ አማናዊ በቀደመው ተዋሕዶ ባለመለወጥ እንደተነሳ ለማጠየቅ ተገለጠላቸው፡፡ሲገለጥም በተዘጋ ግንብ መግባቱ መለኮት አለመለየቱንና ወደ ሥጋ መለወጥ እንዳላገኘው ያስረዳል፡፡
▬▬▬▬▬◈◈◈▬▬▬▬▬
ኮተቤ ት/ት ዩኒቨርሲቲ ግቢ ጉባኤ
የእለቱ ስንቅ
👉፯ቱ አርዕስተ ኃጣውዕ፣የኃጢአት ራሶች ፯ ናቸው።
➛ኃጢአተ አዳም፣ቅትለተ አቤል፣ጥቅመ ሰናዖር፣ኃጢአተ ሰዶም፣ኃጠአተ እሰራኤል፣ቅትለተ ዘካርያስ፣ሞተ ወልደ እግዚአብሔር፣ናቸው።
👉፯ቱ ፍጥረታት፦ከ፳፪ቱ ፍጥረታት ውስጥ ያለ ነቢብ (ያለ ግብር እምግብር)፯ ፍጥረታትን ፈጥሯል።እነርሱም፦
➛መሬት፣ውሃ፣እሳት፣ነፋስ፣ጨለማ፣ሰማያት፣መላእክት፣ናቸው ከዚህ የተረፈውን (፲፭ቱን ፍጥረታት ግብር እምግብር ፈጥሯቸዋል።
👉፯ቱ መቅረዞች፦ጌታ ሙሴን “ወትገብራ ለመክሊተ ወርቅ ተቅዋመ’’ብሎታል ግበራ ሲለው ነው።ጌታ መክሊተ ወርቁን ተቅዋመ ወርቅ አድርገህ ፮ አዕጹቅ አብጅለት ፯ኛውን ስረ ወጥ አድርህ ሥራው በሥረወጡ የተቀዳው ዘይት ፮ቱን አዕጹቅ እንዲመላቸው ማኅቶተ ቤተ መቅደስን ባለ ፯አዕጹቅ አድርጎ እንዲሠራቸው አዝዞታል።ይህ ሰፊ ምሥጢር አለው።
➛ስድስቱ አዕጹቅ ናቸው ሰባተኛው ስረ ወጽ ነው በስረ ወጹ የተቀዳው ለስድስቱ ይተርፋቸዋል በቤተ መቅደስ ይገኛል።
👉፯ቱ አጽራሐ መስቀል፦ጌታ በዕለተ ዓርብ በመስቀል ላይ ተሰቅሎ ሳለ ፯ ነገሮችን ተናግሯል።
➛አምላኪየ አምላኪየ ነጽረኒ፣አባ ሥረይ ሎሙ፣ዮም ትሄሉ ምስሌየ፣ነያ እምከ፣ነዋ ወልድኪ፣ጸማዕኩ፣ወይቤ ተፈጸመ ኩሉ፣አባ አመኀፅን ነፍስየ፣ብሎ።
👉፯ቱ ዲያቆናት፦ዲያቆናትን ፯ አድርጎ መርጧቸዋል።
➛እስጢፋኖስ፣ ፊልጶስን፣ ጵሮኮሮስን፣ ኒቃሮናን፣ጢሞናን፣ ጳርሜናን፣ ወደ ይሁዲነት ገብቶ የነበረውን የአንጾኪያውን ኒቆላዎስንም፣ መረጡ።የሐዋ ሥራ ፮÷፭
👉ስለዚህ የቀመረ ጥበባትን መርሆ በ፯ ቁጥር አያይዞታል ያለ ፯ ቁጥር በጥበብ መድከም ከንቱ ነው በተቆለፈ በር መፍቻ ሳይዙ እገባለሁ ብሎ እንደ መታገል ያለ ነው።
መልካም ቀን
⛪️ አርብ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን
በዚህ ዕለት የሚታሰበው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በክቡር ደሙ ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን እንደመሠረተ ነው፡፡ በሐዋርያት ሥራ ላይ ቅዱስ ሉቃስ ‹‹…እግዚአብሔር በደሙ የዋጃትን ቤተክርስቲያን ትጠብቁ ዘንድ እናንተን ጳጳሳት አድርጎ ለሾመ ….›› በማለት እንደገለጸው ቅድስት ቤተ ክርስቲያን የተመሠረተችው በጌታችን በመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ደም ነው፡፡ (የሐ.ሥራ ፳፥፳፰) ይህ ዕለት የዚህ መታሰቢያው ነው፡፡
"ከዚህ በኃላ የሞትን ስልጣን አጠፋ ዲያቢሎስንና ኃይሉን ሻረ የብረት መዝጊያዎችን ሰበረ ሲዖልን በዘበዘ የጣዖት ቤቶችን አፈረሰ የምህረትን በር ከፈተ ይህችውም በደሙ የከበረች ቤተ ክርስቲያን ናት "
👉 ሃይማኖተ አበው ዘቅዱስ ቴዎድስዮስ
በዚህ ዕለት ቤተክርስቲያን በክርስቶስ ሞትና ትንሣኤ ስለመመስረቷ ይሰበካል፡፡ ክርስቶስ ስለ እርሷ ራሱን አሳልፎ ሰጥቶ ቤዛ ሆኖ በደሙ አንጽቶ በትንሣኤው ድል ሰጥቶ እንዳከበራት ይነገራል
ኢትዮጵያዊው ሊቅ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በመጽሐፈ ምሥጢር ላይ
"ዕፀ መስቀል በአይሁድ እጅ ተተከለ፤ ቤተ ክርስቲያንም በኢየሱስ ክርስቶስ እጅ ተሠራች የእግዚአብሔር በግ በሰቃዮች እጅ በዕፀ መስቀል ላይ ተሠዋ፤ የበረከት ማዕድ ለምእመናን ተዘጋጀ፤ መድኃኒታችን ተወጋ፣ የቤተ ክርስቲያን ደጃፎቿ በሙሽራዋ ደም ተቀቡ" እንዳሉ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያንን በደሙ እንደመሠረታት ለማሰብ ይሄን የስሙነ ትንሣኤ አምስተኛ ቀን ዕለተ አርብን ቤተ ክርስቲያን ብለው አባቶቻችን ሰይመዋታል።
አርብ ለክርስቶስ የመከራ የስቅለት ቀን እንደነበረች ቤተ ክርስቲያንም ሙሽራዋ ክርስቶስ እስኪመጣ ድረስ በመከራ ውስጥ እንደምትቆይ ለማሳየት ይሄን ዕለት ቤተ ክርስቲያን ተብሏል።
ሊቁ ቅዱስ ያሬድ በዝማሬው "የምናገረውን አውቅ ዘንድ እግዚአብሔር የጥበብ አንደበትን ይስጠኝ፤ አቤቱ ቃሌን አድምጥ፤ አቤቱ የቤተ ክርስቲያንን ሕጓን ሥርዓቷን አውቅ ዘንድ ግለጥልኝ፤ ወደ እርሷ ፈጽሞ የሚገሠግሥ ሁሉ አይደክምም፤ እርሷ እንግዳ ተቀባይ ናትና " እንዳለ ቢጠብቁት ሕይወትን የሚሰጥ ሕግ እና ሥርዓቷን አውቀን እንኖር ዘንድ ከደካማችን እና ኃጢአታችን በቃለ እግዚአብሔር እና በንስሐ ወደ ምታድሰን ወደ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን እንገስግስ።
መልካም ቀን🥰
▬▬▬▬▬◈◈◈▬▬▬▬▬
ኮተቤ ት/ት ዩኒቨርሲቲ ግቢ ጉባኤ
ሐሙስ (አዳም ሐሙስ)
አዳም በበደለ ጊዜ በደሉን አምኖ ንስሓ ገባ፤ ተጸጸተ፤ እግዚአብሔርን መበደሉንና ትእዛዙን መጣሱን አምኖ ለብዙ ዓመት ሲያለቅስ ኖረ፤ ጠላትም አስጨንቆ ገዛው፤ የዕዳ ደብዳቤ አጽፎ “አዳም ገብሩ ለዲያቢሎስ፣ ሔዋን ዓመቷ ለዲያቢሎስ” የሚል የዕዳ ደብዳቤ አጻፋቸው፤ አዳምም ስለ በደሉ መሥዋዕትን ለእግዚአብሔር አቀረበ፤ ጌታችንም የአዳምን መጸጸትና መመለስ ተቀብሎለት አምስት ሺ አምስት መቶ ዘመን ሲፈጸም ከልጅ ልጁ ተወልዶ እንደሚያድነው ቃል ኪዳን ገባለት፤ ይህም ዕለት በዚህ ቀን ይታሰባል፤ አዳም ሐሙስ መባሉ ለዚህ ነው፡፡
▬▬▬▬▬◈◈◈▬▬▬▬▬
ኮተቤ ት/ት ዩኒቨርሲቲ ግቢ ጉባኤ
Repost from ማኅበረ ቅዱሳን አዲስ አበባ ማእከል ሚዲያ
ብሒለ አበው
ሰላም ጤና ይስጥልን ውድና የተከበራችሁ የማኅበረ ቅዱሳን አዲስ አበባ ማእከል ሚዲያ ተከታታዮች ዘወትር ረቡዕ " ብሒለ አበው" የተሰኘ መርሐግብር ወደእናንተ ይቀርባል ።መልካም ንባብ ይሁንላችሁ።ክፍል 8
"ልባችንን ጠፊና በስባሽ ከኾነው ከምድራዊው ምኞት ርቀን ከበደል በንስሐ ነፃ ካደረግነው በጸጋ መንፈስ ቅዱስየተሞላን እንሆናለን፡፡"አባ አብርሃም መፍቀራ ነዳያን
"በመንፈሳዊ መንገድ ውስጥ ዝግ ብለህ አትጓዝ፡፡ በጎዳና ላይበምትመለከታቸው ትዕይንቶች አማካይነት አትማረክ፤ አትቁምም ጠላቶችህም ሆኑ ወዳጆችህ ያሰናክሉህ ዘንድ አት ፍቀድላቸው ::"አቡነ ሺኖዳ
"አንድ ሰው ለቤተ ክርስቲያን መሰረታዊ ሥራ ሊያከ ናውን የሚችለው የሚሠራ ወዲያ ወዲህ ከማለት ይልቅ በአንድ ቦታ ረግቶ ሲኖር ነው፡፡"አባ እንየው
"ከልባቸው የእግዚአብሔር አገልጋዮች በሆኑ ሰዎችና ተስ ፋቸውን በእግዚአብሔር ላይ በጣሉት ሰዎች ላይ ዲያብሎስ ጌታ ሊሆን አይችልም ጌታ የሆነው እግዚአብሔር እንጂ፡፡"እረኛው ሄርማን
"ለምናስተምረው ትምህርት እውነተኛነት ማስረጃው ከቅ ዱሳን ሐዋርያት በደቀ መዛሙርቶቻቸውና አሠረፍኖታቸውን በተከተሉ ቅዱሳን አበው በኩል ያገኘነውና የወረስ ነው ትውፊት ከኛ ጋር መኖሩ ነው፡፡"ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘኑሲስ
