የኮተቤ ትምህርት ዩኒቨርስቲ ግቢ ጉባኤ
Open in Telegram
የኮተቤ ትምህርት ዩኒቨርሲቲ ግቢ ጉባኤ መደበኛ ቻናል ነው፡፡ በዚህ ቻናል 👉 ትምህርታዊ ጽሑፎች ፤የግቢ ጉባኤው መልዕክት ፤የክፍላት ማስታወቂያዎች ይተላለፉበታል፡፡ ሀሳብ አስተያየት ጥያቄ ካለ @ethiopia_1616 ላይ ይፃፉልን፡፡ contact 0923584792 /0928381616
Show moreThe country is not specifiedThe category is not specified
430
Subscribers
No data24 hours
+17 days
-330 days
Posts Archive
ጤና ይስጥልን!
ዛሬ ረቡዕ ከ 11:30 ጀምሮ የአንደኛ ዓመት ኮርስ እንደተጠበቀ ነው፤ ተቀሳቅሰን በሰዓቱ እንድንገኝ መልእክታችን ነው።
ጤና ይስጥልን!! በእዚህ ደብዳቤ ላይ የተገለፀዉን የምታሟሉ፤ ፍላጎቱ ያላችሁ የግቢ ጉባኤ አባሎቻችን እስከ ዛሬ ማታ 1:00 ሰዓት ድረስ ከታች ባሉት ስልኮች በመደወል እንድታሳውቁን እናሳስባለን።
👉0978141716
👉0910677460
✨✨✨🍂🍂🍂✨✨✨🍂🍂🍂✨✨✨🍂🍂🍂
🍂🍂✨ቅዱስ ዮሐንስ ፍቁረ እግዚእ 🍂🍂✨
አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ በቅዱስ ወንጌሉ እንደነገረን በመንግስተ ሰማያት ታላቁ ሰው ወንጌላዊው ዮሐንስ ነው:: ቅዱሱ ሐዋርያ ከዘብዴዎስና ከማርያም ባውፍልያ ተወልዶ: በገሊላ አካባቢ አድጐ: ገና በወጣትነቱ መድኃኔ ዓለምን ተከትሎታል::
ቅዱስ ዮሐንስ ከሐዋርያት ቀድሞ ጌታን ከመከተሉ ባሻገር በምንም ምክንያት ከጐኑ አይጠፋም ነበር:: ስለ ንጽሕናውና በጐ የፍቅር ሕሊናው ሕጻን ሳለ በወንድሞቹ ሐዋርያት ዘንድ ሞገሱ ከፍ ያለ ነው:: ጌታችንን እስከ እግረ መስቀሉ ድረስ በመከተሉ ድንግል እመቤታችንን ተቀብሏል::
🍂🍂✨
ከእርሷ ጋር ለ15 ዓመታት ቢቀመጥ መዝገበ ምሥጢር ሆነ:: ስንኩዋን ከሰው ልጆች ይቅርና ከልዑላኑ መላዕክትም ማዕረጉ ከፍ አለ:: ሰው ቢበቃ መላእክትን ሊያይ ይቻለዋል:: ቅዱስ ዮሐንስን ግን መላእክት ሊያዩት ይከብዳቸዋል:: ከፍጥረት ወገን ከእመ ብርሃን ቀጥሎ ክቡር እርሱ ነው::
🍂🍂✨የፍቅር ሐዋርያ
ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ዮሐንስን 'የፍቅር ሐዋርያ' ትለዋለች:: ለ70 ዘመናት በቆየ ስብከቱ ስለ ፍቅር ብዙ አስተምሯል:: ፍቅርንም በተግባር አስተምሯል:: በየደቂቃውም "ደቂቅየ ተፋቀሩ በበይናቲክሙ - ልጆቼ ሆይ! እርስ በርሳችሁ ተዋደዱ" እያለ ይሰብክ ነበር::
በተለይ ደግሞ ከፈጣሪው ክርስቶስ ጋር የነበረው ፍቅር ፍጹም የተለየ ነበር:: በዚህ ምክንያትም ጌታ ባረገ ጊዜ እንዲህ ብሎታል:- "ለፍጡር ከሚገለጥ ምሥጢር ከአንተ የምሠውረው የለኝም" ብሎታል::
🍂🍂✨
ቀጥሎም በንጹሕ አፉ ስሞታል:: ሊቁ:-
"ሰላም ለአፉከ ለዮሐንስ ዘሰዓሞ:
ንጽሐ ኅሊናሁ ወልቡ ለዐይነ ፍትወትከ ሶበ አደሞ" እንዳለው:: (መልክዐ ኢየሱስ)
ቅዱስ ዮሐንስ ከእመቤታችንም ጋር ልዩ ፍቅር ነበረው:: እርሷ እንደ ልጇ ስትወደው: እርሱ ደግሞ እንደ እናቱ ልቡ እስኪነድ ድረስ ይወዳት ነበር:: እስከ እግረ መስቀሉ ድረስ ተከትሎ ያገኛት እመቤቱ ናትና::
🍂🍂✨
ከዚያ ሁሉ ጸጋና ማዕረግ የመድረሱ ምሥጢርም ድንግል ናት:: ለ15 ዓመታት በጽላሎተ ረድኤቷ (በረዳትነቷ ጥላ) ተደግፎ አብሯት ሲኖር ብዙ ተምሯል:: ከመላእክትም በላይ ከብሯል:: ከንጽሕናዋ በረከትም ተካፍሏል::
ስለ ድንግል ማርያምም "ነገረ ማርያም" የሚል ድርሰት ሲኖረው "የሰኔ ጐልጐታንም" የጻፈው እርሱ ነው::
ድንግል ባረፈችበት ቀንም ልክ እንደ ልጇ ክርስቶስ እርሷም ስማው: ታቅፋው ዐርፋለች:: ሊቃውንቱ ለዚህ አይደል በንጹሕ ከንፈሮቿ መሳምን (መባረክን) ሲሹ:-
"በከመ ሰዓምኪ ርዕሰ ዮሐንስ ቀዳሚ:
ስዒሞትየ ማርያም ድግሚ" ያሉት::
🍂🍂✨
ታላቁ ቅዱስ ሐዋርያ ዕድሜው 90 ዓመት በሆነው ጊዜ ተሰውሯል:: ከዚያ አስቀድሞም የዓለምን ፍጻሜ ተመልክቷል:: ዛሬ ያለበትን የየሚያውቅ ቸር ፈጣሪው ነው::
✨✨🍂
ይሕች ዕለት ለሐዋርያው ቅዳሴ ቤቱ ናት::
እናት ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ዮሐንስን ስትጠራው እንዲሕ ነው:-
✨ወንጌላዊ
✨ሐዋርያ
✨ሰማዕት ዘእንበለ ደም
✨አቡቀለምሲስ (ምሥጢራትን ያየ)
✨ታኦሎጐስ (ነባቤ መለኮት)
✨ወልደ ነጐድጉዋድ
✨ደቀ መለኮት ወምሥጢር
✨ፍቁረ እግዚእ
✨ርዕሰ ደናግል (የደናግል አለቃ)
✨ቁጹረ ገጽ
✨ዘረፈቀ ውስተ ሕጽኑ ለኢየሱስ (ከጌታ ጎን የሚቀመጥ)
✨ንስር ሠራሪ
✨ልዑለ ስብከት
✨ምድራዊው መልዐክ
✨ዓምደ ብርሐን
✨ሐዋርያ ትንቢት
✨ቀርነ ቤተ ክርስቲያን
✨ኮከበ ከዋክብት
በቅዱስ ዮሐንስ ላይ ያደረ የእመቤታችን ድንግል ማርያምና የአንድ ልጇ ፍቅር በእኛም ላይ ይደር::
✨✨🍂
ቅዱስ ዮሐንስን የወደደ ጌታ በፍቅሩ ይጠግነን:: ከእናቱ ፍቅር አድርሶ በሐዋርያው በረከት ያስጊጠን::
✨✨✨🍂🍂🍂✨✨✨🍂🍂🍂✨✨✨🍂🍂🍂
ጤና ይስጥልን፤ በእዚህ ደብዳቤ ላይ የተገለጸውን የምታሟሉ ፍላጎቱ ያላችሁ የግቢ ጉባኤ አባሎቻችን እስከ ነገ 6:00 ሰዓት ድረስ በግቢ ጉባኤው ሰብሳቢ ዲን ብርሃኑ ጋር እንድትመዘገቡ ጋብዘናችኋል።
ዕርገተ ክርስቶስ
“አምላክ በእልልታ፥ እግዚአብሔር በመለከት ድምፅ ዐረገ” /መዝ ፵፮ ፥ ፭/።
እንኳን ለብርሃነ ዕርገቱ አደረሳችሁ !!!
የጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ትንሣኤ በተከበረ በዐርባኛው ቀን የሚውለው ዐቢይ በዓል “ዕርገት” ይባላል፡፡ ዕርገት ከጌታችን ከመድኃኒታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ዘጠኙ ዐበይት በዓላት አንዱ ነው፡፡
ጌታችን ከትንሣኤው በኋላ ለቅዱሳን ሐዋርያት ለአርባ ቀናት እየተገለጸ፣ ስለ እግዚአብሔር መንግሥት መጽሐፈ ኪዳንን፣ ትርጓሜ መጻሕፍትን፣ ምሥጢራትን፣ ሕግጋትንና ቀኖናተ ቤተ ክርስቲያንን ሲያስተምር ቆይቶ ወደ ቀደመ ዙፋኑ ወደ ሰማይ በክብር በምስጋና ማረጉን በደስታ የምንዘክርበት ዐቢይ በዓል ነው፡፡
▬▬▬▬▬◈◈◈▬▬▬▬▬
ኮተቤ ት/ት ዩኒቨርሲቲ ግቢ ጉባኤ
ለኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ብርሃን የሆናት ፤ በምስጋና በመዝሙር ያስጌጣት ፤ የክብር ኮከብ ፤ ካህን ፤ መዘምር ፤ ፍፁም መናኝ መነኮስ ፤ የክርስቶስ ፍቅር የበዛለት ፤ ወንጌልን የሰበከ ፤ ቃሉ የጣፈጠ ፤ መፅሐፍትን የተረጎመ ፤ መዓዛው ያማረ ፤ እንደ ጳውሎስ ሰባኪ ፤ እንዴ እንጦንስ መናኒ ፤ እንደ ጊዮርጊስ ሰማዕት ፤ እንደ ሱራፊ ዘማሪ ፤ እንደ ኪሩብ ቀዳሲ ፤
የክርስቶስ ውድ ስጦታችን ቅዱስ ያሬድ የእረፍቱ/መሰወሩ መታሰቢያ ነው ።
የከበረች በረከቱ ከኛ ጋር ትሁን ፤ ሞቱን እና ትንሳኤውን የሰበከውን ፤ የዘመረለትን ፤የተቀኘለትን፤ የመነነለትን የክርስቶስን ፍቅር ያሳድርብን ።
▬▬▬▬▬◈◈◈▬▬▬▬▬
የኮተቤ ት/ት ዩኒቨርሲቲ ግቢ ጉባኤ
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
✨ ጉባኤ ኒቆዲሞስ ✨
ማቴ 18/20 በስሜ በሚሰበሰቡበት በዚያ በመካከላቸው እሆናለሁና።
✨ሰኞ ግንቦት 10✨
ተወዳጇ እና ተናፋቂዋ የአንድነት ጉባኤያችን ጉባኤ ኒቆዲሞስ
📌 በዕለቱ የሚኖሩን መርሐግብራት
ꔰ ጸሎት
ꔰ ትምህርተ ወንጌል
ꔰ የመዝጊያ ጸሎት
ሰዓት፦ 11:30-1:30
ቦታ፦ መ/ቅ/ኢ/ወሐና ቤተክርስቲያን ፍቅረ ሰላም
አዳራሽ
👉በሰዓቱ ጀምረን በሰዓቱ እንድንፈፅም
በሰዓቱ እንገኝ🙏
✨ኮተቤ ግቢ ጉባኤ✨
📖 "እግዚአብሔር ጥበብን ይሰጣልና፤ ከአፉም እውቀትና ማስተዋል ይወጣሉ።" (ምሳሌ 2፡6)📖
ውድ የኮተቤ ት/ት ዩኒቨርሲቲ ግቢ ጉባኤ ተማሪዎችና የቤተክርስቲያን ተስፋዎች፦
ለፋይናል (Final-Exam) ፈተና ወደ መፈተኛ ክፍሎች ስታቀኑ፣ የቅዱሳኑን አምላክ ረድኤትና የቅድስት ድንግል ማርያምን አማላጅነት ተማምናችሁ ይሁን። ጥበብን ለሰሎሞን፣ ማስተዋልን ለዳንኤል፣ ዜማን ለቅዱስ ያሬድ የገለጠ አምላክ የእናንተንም አእምሮ እንዲያበራላችሁ ጸሎታችን ነው።
✨ ጥቂት ማሳሰቢያዎች፦
📍ከፈተና በፊት ጸሎት
📍በፈተና ሰዓት ሰላማዊና ረጋ ያለ መንፈስ ይኑራችሁ።
መልካም የፈተና ጊዜ!
▬▬▬▬▬◈◈◈▬▬▬▬▬
ኮተቤ ት/ት ዩኒቨርሲቲ ግቢ ጉባኤ
የዕለቱ ስንቅ"ፍቅር የምንለውን ትርጓሜውን ከእርሱ እንማር ዘንድ እርሱ ስለ እኛ ነፍሱን አሳልፎ ሰጠ... እንግዲህ ፍቅር ከሁሉ ነገር በላይ ነው፤ ከርሱም የሚበልጥ የለም። እርሱ የሕግ ሁሉ ፍጻሜ ነው፤ እርሱ የነቢያት ሁሉ መሠረት ነው፤ እርሱ የሐዋርያት ሁሉ ድል ነው፤ እርሱ የሰማዕታት ሁሉ አክሊል ነው።" ቅዱስ ሳዊሮስ ዘአንጾኪያ፣ የካቴድራል ስብከት 77 ✨✨✨ ሠናይ ዕለተ ሰንበት ✨✨✨ ▬▬▬▬▬▬◈◈◈▬▬▬▬▬▬
የእለቱ ስንቅ
ቂም የነፍስ የጨለማ መጋረጃዋ ነው። ይኸውም ለክፉ ክፉ መመለስን ከመውደድ የሚመጣ በቀል ነው። ከተበቀለ በኋላ ግን በጸጸት ጅራፍ ይገረፋል።
ቂምስ ምን ትመስላለች ትለኝ እንደሆነ የእናታቸውን ማኅፀን የሚበሉ የትሎችን ልጆች ትመስላለች ብየ እመልስልሃለሁ። የልብ ቂም በቀልን ያወርሳል፤ በቀልም አጥንትን ይሰብራል። የልቡና ቂም በጎ ሥነ ምግባራትን ሁሉ ያጠፋቸዋል። ቂም በእውነት እግረ ነፍስን እንደወደደች እንዳትራመድ የሚገታ የሚጎዳ ማሰሪያ ነው። ቂም ለእግዚአብሔር የሚገባውን ሁሉ ከማድረግ እንድናቋርጥ ያደርጋል።
ቂም የዚህን ዓለም ሐሳብ በመፈለግ በጠማማ ጎዳና እንዲቆሙ ያደርጋል፤ የልብ ፍላጎት በቂም ገመድ ታስሯልና። ጁባን የለበሰ ቦርቦርቴን የደፋ ሰው የተወረወረ ጦር የተነቀነቀ ዘገር የሠረረ ቀስት እንደማያገኘው እግዚአብሔርን የሚፈራ ሰውንም ቂም ወይም በቀል አያገኘውም። ቂም በልቡናው ያደረበት ሰው ከበቀል አይርቅም፤ ከዓለምም መራቅ መመነን አይቻለውም። እርሱ በቂም ሆኖ ሌሎችን የሚገሥጽ ራሱንም ንጹሕ እንደሆነ የሚያስብ የተናቀ ወራዳ ነው።
ዓለምን የናቃት ሰው ዘወትር ደስተኛ ነው፤ ቂምና የልብ ፍትወት ከጸና ዘንድ ግን ወደ አፍቅሮ ንዋይ ይወስዳል። ጥሪት ቁሪትን ገንዘብን የሚወድ ሰው ግን ፈጽሞ ደስ ይለዋል። በምንም በምን ስለ እርሱ አይጨነቅም። የጠቢብ ሰው መታሰብ በሁሉ ዘንድ ያማረ የተወደደ ነው፤ ቂምና የልብ ፍትወት ግን ደካማ ነው።
ሰናይ ዕለተ አርብ!
ጤና ይስጥልኝ፤ የቀድሞ ተመራቂ አባሎቻችን የስለት ብር ለማስገባት ወይም ደግሞ ግቢውን ለመርዳት አስበው አካውንት እየጠየቁን ነው፤ የግቢ ጉባኤውን ጣምራ አካውንት (joint account) ብንሰጣቸው ምን ያህል ብር እንደገባ ማወቅ ስለማንችል በእኛ አሁን ባለው ስራ አስፈፃሚ ተሰብስቦ ወደ አካውንታችን እንዲገባ ስለፈለግን ሒሳብ እና ንብረት ክፍል ተጠሪያችን መስታይት ደረሰ የንግድ ባንክ ቁጥር
1000 4010 24356 (መስታይት ደረሰ አለም ነው) በማስገባት ደረሰኝ ደግሞ @diacon122119 እንዲልኩልን በአክብሮት እንጠይቃለን።
የቅዱስ ያሬድ ልደት
ꔰ ኢትዮጵያዊው ቅዱስ ያሬድ ሚያዚያ 5 ቀን በ505 ዓ.ም. ከአባቱ ይስሐቅ(አብድዩ) ከእናቱ ክርስቲና (ታውክልያ) በአኵሱም ከተማ ተወለደ፡፡ (አንዳንዶች ልደቱን 493 ዓ.ም. ነው ይላሉ፤ እንዲሁም አባቱ ኖኅ ነው ይሉና መሪጌታ ይስሐቅ የቀለም አባቱ /መመህሩ/ ነው ይላሉ፡፡)
ꔰ የስሙም ትርጓሜም ያሬድ ማለት እንዚራ፣ በገና፣ መሰንቆ ማለት ነው ፡፡ እነዚህ መሣሪያዎች በስልት በስልት ሲመቱ ለሚሰማቸው ደስ እንዲያሰኙ የያሬድም ዜማ በንጉሠ ነገሥቱ ክርስቶስ አደባባይ በቤተ ክርስቲያን ሲሰማ መላእክትን፥ ሰውንና እንስሳትን ደስ ያሰኛልና፡፡
፨ አንድም ያሬድ ርደት፣ ወሪድ፤ መውረድ ማለት ነው፡፡ ቅዱስ ያሬድ ሰማያዊውን ልዩ ጣዕመ ዜማ ወደ ኢትዮጵያ አውርዷልና፡፡
፨ አንድም ያሬድ ማለት ንብ ማለት ነው፤ ንብ የማይቀስመው አበባ እንደሌለ ሁሉ ቅዱስ ያሬድም ከመጻሕፍት የማይጠቅሰው የማይቀሰመው የለም፤
፨ አንድም ያሬድ ማለት ረአዬ ምሥጢር፥ ነጻሬ ኅቡአት ማለት ነው፤ የመላእክት ምሥጢራት የነበሩትን ጸዋትወ ዜማ አምልቶ አስፍቶ ተናግሯልና፣ ነጻሬ ኅቡአት አለ፥ ኅቡእ (ስውር) የሆነ የጻድቃን፣ የሰማዕታት የነቢያት የሐዋርያትን ገድል አምልቶ አስፍቶም ይናገራልና፡፡
-ዐፄ ካሌብ ቤተ እስራኤል፣ ገብረክርስቶስና ገብረ መስቀል የሚባሉ ልጆች ነበሩት፤ ቅዱስ ያሬድ የተነሳው ከእነዚህ ውስጥ በዓፄ ገብረመስቀል ዘመን ነው፡፡
ኮ/ት/ዩ/ግ/ጉ
ጤና ይስጥልኝ!
ከዚህ በላይ የተለቀቁት ዶክመንቶች በተከታታይ ለ 3 ሳምንታት ለ PGDT ተማሪዎች ሲሰጥ የነበረ ነው። ታነቡት ዘንድ አጋርተናችኋል!!
