en
Feedback
BONGA FM 97.4

BONGA FM 97.4

Open in Telegram
1 142
Subscribers
No data24 hours
+47 days
+1230 days
Posts Archive
የ2019 ዓ.ም አዲስ ዓመት በዓልን ምክንያት በማድረግ መድፍ ይተኮሳል፦ የመከላከያ ሚኒስቴር ጳጉሜን 5/2018 ዓ.ም (ቦንጋ ኤፍ ኤም 97.4)፦ የ2019 ዓመተ ምህረት የአዲስ ዓመት በዓልን ምክን
የ2019 ዓ.ም አዲስ ዓመት በዓልን ምክንያት በማድረግ መድፍ ይተኮሳል፦ የመከላከያ ሚኒስቴር ጳጉሜን 5/2018 ዓ.ም (ቦንጋ ኤፍ ኤም 97.4)፦ የ2019 ዓመተ ምህረት የአዲስ ዓመት በዓልን ምክንያት በማድረግ ነገ መስከረም 1 ቀን 2019 ዓ.ም ከንጋቱ 12፡00 ሰዓት ላይ 21 ጊዜ መድፍ እንደሚተኮስ ተገለጸ። በኢ.ፌ.ዲ.ሪ መከላከያ ሚኒስቴር የመከላከያ ስፖርትና ኪነ ጥበባት ስራዎች ማዕከል እንደስታወቀው፣ ይህ 21 ጊዜ የሚተኮሰው መድፍ አዲሱን ዓመት በደስታና በብሩህ ተስፋ ለመቀበል የሚደረገው ሀገራዊ የክብር አቀባበል አካል ነው ሲል ኢቢሲ ዘግቧል። የተለያዩ ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት የማህበራዊ ትስስር ገፆቻችንን ይወዳጁ! ፌስቡክ፡ https://www.facebook.com/share/181X2irsqB/ ቴሌግራም፡ https://t.me/bongafm974radiostatio ቲክቶክ፡ https://www.tiktok.com/@bongafm97.4?_t=ZM-90PCjvnnVBz&_r=1 ዩቲዩብ፡ https://www.youtube.com/@BongaFM97.4

የካፋ ልማት ማህበር በቦንጋ ከተማ በፅዳትና ውበት ስራ ለተሰማሩ እናቶች ድጋፍ አደረገ ጳጉሜን 5/2018 ዓ.ም (ቦንጋ ኤፍኤም 97.4) የካፋ ልማት ማህበር የዘመን መለወጫ በዓልን ምክንያት በማድረ
+5
የካፋ ልማት ማህበር በቦንጋ ከተማ በፅዳትና ውበት ስራ ለተሰማሩ እናቶች ድጋፍ አደረገ ጳጉሜን 5/2018 ዓ.ም (ቦንጋ ኤፍኤም 97.4) የካፋ ልማት ማህበር የዘመን መለወጫ በዓልን ምክንያት በማድረግ በቦንጋ ከተማ በፅዳትና ውበት ስራ ላይ ለተሰማሩ ሴቶች የፍጆታ ዕቃዎች ድጋፍ አድርጓል። የካፋ ልማት ማህበር ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ብዙአየሁ ግርማ መረዳዳት የማህበረሰቡ ባህል መሆን እንዳለበት በዚሁ ወቅት አስገንዝበዋል። የቦንጋ ከተማ ውበትና ፅዳት እንዲሻሻል ሴቶቹ ላበረከቱት አስተዋጽኦ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የካፋ ልማት ማህበር በአንደዚህ አይነት የስራ ዘርፎች የተሰማሩትን ለመደገፍ ጥረቱን እንደሚያጠናክርም ጠቁመዋል ሲል የቦንጋ ከተማ የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ዘግቧል። የተለያዩ ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት የማህበራዊ ትስስር ገፆቻችንን ይወዳጁ! ፌስቡክ፡ https://www.facebook.com/share/181X2irsqB/ ቴሌግራም፡ https://t.me/bongafm974radiostatio ቲክቶክ፡ https://www.tiktok.com/@bongafm97.4?_t=ZM-90PCjvnnVBz&_r=1 ዩቲዩብ፡ https://www.youtube.com/@BongaFM97.4

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የመረቁት ዘመናዊ የሞጆ ሎጂስቲክስ ማዕከል ማስፋፊያ ፕሮጀክት የመጀመሪያ ምዕራፍ በምስል፡-
+9
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የመረቁት ዘመናዊ የሞጆ ሎጂስቲክስ ማዕከል ማስፋፊያ ፕሮጀክት የመጀመሪያ ምዕራፍ በምስል፡-

"መቻቻልና ተከባብሮ የመኖር እሴቶችን በማስቀጠል አዲሱን አመት መጀመር ይገባል":- አባ አድማሱ ገብሬ ጳጉሜን 5/2018 ዓ.ም (ቦንጋ ኤፍ ኤም 97.4)፦ መቻቻልና ተከባብሮ የመኖር ኢትዮጰያዊ እሴ
+3
"መቻቻልና ተከባብሮ የመኖር እሴቶችን በማስቀጠል አዲሱን አመት መጀመር ይገባል":- አባ አድማሱ ገብሬ ጳጉሜን 5/2018 ዓ.ም (ቦንጋ ኤፍ ኤም 97.4)፦ መቻቻልና ተከባብሮ የመኖር ኢትዮጰያዊ እሴቶችን በማስቀጠል አዲሱን አመት መጀመር ይገባል ሲሉ በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ጅማ-ቦንጋ ሀገረ-ስብከት የማህበረ ልዑክ ካህን ክቡር አባ አድማሱ ገብሬ አሳሰቡ ። የአማን ጽሰታ ማርያም ካቶሊክ ቤተክርስቲያን መዕመን መምህር አሸናፊ አሸንጎ በሰጡት አስተያየት 2018 ዓመተ-ምህረትን የቤተክርስቲያናቸውን አስተምህሮ መሰረት በማድረግ መልካም ነገሮችን በማከናወን ማሳለፋቸውን ተናግረዋል፡፡ በጾም፣ በጸሎት እንዲሁም መልካም ነገሮችን በማድረግ ማሳለፋቸውን ጠቁመው በአዲሱ አመትም አጠናክረው እንደሚያስቀጥሉ ገልጸዋል፡፡ የሙቲ-ደቂያ አካባቢ ካቶሊክ ቤተ-ክርስቲያን ምዕመን አቶ ወንድሙ ወልደማርያም እና የጊቻ ጽዮን ማርያም ካቶሊክ ቤተ-ክርስቲያን ምዕመን አቶ አድማሱ ወልደሰንበት አሮጌውን ዓመት የተጣሉትን በማስታረቅ፣ ለሀገር ሰላም እና አንድነት በመፆምና በመጸለይ ማሳለፋቸውን ተናግረዋል፡፡ ለተጨማሪው .....https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=pfbid0pJknHBrLs55sg8GYMpVTKtjvpSYCCiejosiV5oTjKJZwQtF8KZopx9DJGeahNWcXl&id=100082472124834&mibextid=Nif5oz

"የኢትዮጵያን ዲጂታል አሰራር ራዕይ ለማሳካት ጥረት እየተደረገ ነው፦ አቶ ሚሊየን ሀይሌ ጳጉሜን 4/2018 ዓ.ም (ቦንጋ ኤፍ ኤም 97.4)፦ ኢትዮጵያ ወደ ዲጂታል አሰራር ለመሸጋገር የጀመረችውን ራ
"የኢትዮጵያን ዲጂታል አሰራር ራዕይ ለማሳካት ጥረት እየተደረገ ነው፦ አቶ ሚሊየን ሀይሌ  ጳጉሜን 4/2018 ዓ.ም (ቦንጋ ኤፍ ኤም 97.4)፦ ኢትዮጵያ ወደ ዲጂታል አሰራር ለመሸጋገር የጀመረችውን ራዕይ ለማሳካት ጥረት እየተደረገ መሆኑን የካፋ ዞን ሥራና ክህሎት መምሪያ ገለጸ። ጳጉሜን 5 “የነገ ቀን” በቦንጋ ከተማ ተከብሯል።   በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የካፋ ዞን ሥራና ክህሎት መምሪያ ኃላፊ አቶ ሚልዮን ሀይሌ እንደገለፁት ኢትዮጵያ ወደ ዲጂታል አሰራር ለመሸጋገር የጀመረችውን ራዕይ ለማሳካት ጥረት እየተደረገ ነው። የጳጉሜ ቀናት ኢትዮጵያ ያሳካቻቸውን ስኬቶች የምትዘክርበት ብቻ ሳይሆን፣ ከቀድሞ ችግሮችና ተግዳሮቶች ተላቅቃ ወደ ቀጣይ የልማትና የማንሰራራት ዘመን የምትሸጋገርበት ነው ብለዋል። ለተጨማሪው .....https://www.facebook.com/share/p/1BmGYB5NAF/

የነገው ቀን፦ የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀገራዊ የቴክኖሎጂ ሽግግር መልዕክት ጳጉሜን 5/2018 ዓ.ም (ቦንጋ ኤፍ ኤም 97.4) ፦ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ኢትዮጵያ
+5
የነገው ቀን፦ የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀገራዊ የቴክኖሎጂ ሽግግር መልዕክት ጳጉሜን 5/2018 ዓ.ም (ቦንጋ ኤፍ ኤም 97.4) ፦ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ኢትዮጵያ ከወረቀት አሠራር ወደ ዲጂታል፣ እንዲሁም ከቴክኖሎጂ ተጠቃሚነት ወደ ፈጣሪነት የተሸጋገረችበትን ታሪካዊ ምዕራፍ በጳጉሜንን 5 ነገው ቀን አስመልክተው መልዕክት አስተላለፉ። በመልዕክታቸውም ትናንትን በመማርና በማረም፣ ዛሬን ደግሞ በላቀ ትጋት በመገንባት ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን የዕለት ተዕለት ባህላችን እየሆነ መምጣቱን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገልጸዋል። ይህ የዲጂታል ሽግግር ንግድና አገልግሎትን የሚያቀላጥፍ፣ መረጃዎችን ተደራሽ የሚያደርግ እና ልዩ ልዩ ዘርፎችን የሚያዘምን እንደሆነም አብራርተዋል። በተጨማሪም የ5 ሚሊዮን ኢትዮጵያ ኮደሮች ንቅናቄ ወጣቶችን የሰው ሰራሽ አስተውሎት ፈጣሪ በማድረግ በአሁኑ ወቅት ወደ 7 ሚሊዮን ግቡ እያመራ እንደሚገኝ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ጠቁመው፣ ይህም የዲጂታል አገልግሎት ተደራሽነትና ጥራትን ማረጋገጡን አስታውቀዋል። በሀገር በቀል አቅም የበለጸገው የሳይበር ሉዓላዊነታችን የማይቆጣጠሯቸው ቴክኖሎጂዎች ጥገኝነትን ማስቀረቱን ያመለከቱት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ፤ አዲሷ ኢትዮጵያ በዲጂታል ኢኮኖሚ በራስ አቅሟ የምትቆምበት ታላቅ ምዕራፍ ላይ መሆኗን አብስረዋል።

ጳጉሜን 5- "የነገ ቀን"
ጳጉሜን 5- "የነገ ቀን"

“የዲጂታል ኢኮኖሚና መሰረተ ልማትን በማስፋት አንድነትንና ልማትን የሚያጠናክር ነገን እየገነባን ነው” - ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) ጵጉሜን 4/2018 ዓ.ም (ቦንጋ ኤፍ ኤም 97.4) የኢትዮጵያ
“የዲጂታል ኢኮኖሚና መሰረተ ልማትን በማስፋት አንድነትንና ልማትን የሚያጠናክር ነገን እየገነባን ነው” - ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) ጵጉሜን 4/2018 ዓ.ም (ቦንጋ ኤፍ ኤም 97.4) የኢትዮጵያን የዲጂታል ኢኮኖሚና መሰረተ ልማት በማስፋት አንድነትና ልማትን የሚያጠናክር አውድ መፍጠር የሚያስችል ነገን እየገነባን ነው ሲሉ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) ገለጹ። የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ከሌሎች የፌዴራል ተቋማት ጋር በመተባበር ነገ ጳጉሜን 5 ቀን 2018 ዓ.ም የሚከብረውን የ"ነገ ቀን" በማስመልከት መግለጫ ሰጥቷል። የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ መንግሥት የጳጉሜን ቀናት በተለያዩ ስያሜዎች እያከበረ ይገኛል። የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ከሌሎች ተቋማት ጋር በመተባበር በዲጂታል ኢኮኖሚ የዳበረች ኢትዮጵያን ለማስረከብ የሚከናወኑ ተግባራትን የሚያሳየው የነገ ቀን ይከበራል ብለዋል። ኢትዮጵያ ፖሊሲዎችና ስትራቴጂዎችን በመቅረጽ የዲጂታል ኢኮኖሚ መገንባት የሚያስችል ሥራ እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። በዲጂታል ቴክኖሎጂ አቅም የጎለበተ፣ ዘመኑን የዋጀ ሲቪል ሰርቪስ በመገንባት፣ ፈጣንና ቀልጣፋ የመንግሥት አገልግሎት በመስጠት ምን ዓይነት ነገን እንገንባ በሚለው ላይ መሠረት እየጣልን ነው ብለዋል። ነገ ማለት ወጣቶች የሚረከቧት ኢትዮጵያ ማለት ነው ያሉት ሚኒስትሩ፤ ለትውልዱ የአንድነት፣ የሰላምና የልማት አውድ መፍጠር የሚያስችል ነገን ለመገንባት መሆኑን ገልጸዋል። አዲስ ዓመት አዲስ ተስፋና ሀሳብ መፈጠሪያ መሆኑን ገልጸው፤ ለሕዝባችን የገባነውን ቃል በተግባር መፈጸም ይገባናል ማለታቸውን የዘገበው ኢዜአ ነው። አዲሱ ዓመት ፈተናዎችን አልፈን የተሳካ ሰላምና ልማት የምናስመዘግብበት እንዲሆን እመኛለሁ ብለዋል።

ጳጉሜን 4 የህብር ቀን “ የኢትዮጵያ ማንሰራራት” https://youtube.com/watch?v=thmhB7ePEjQ&si=UQwABsailYHFYA6Z

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለአፍሪካ ሕብረት ቀን የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ ጳጉሜን 4/2018 ዓ.ም (ቦንጋ ኤፍ ኤም 97.4) ፦ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለአፍሪካ ሕብረት ቀን የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ ጳጉሜን 4/2018 ዓ.ም (ቦንጋ ኤፍ ኤም 97.4) ፦ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለ24ኛ የአፍሪካ ሕብረት ቀን  የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል፡- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ(ዶ/ር) በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ባሰፈሩት መልዕክት፣ ኢትዮጵያ ከቀድሞው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት ጀምሮ እስከ አሁኑ  የአፍሪካ ሕብረት ድረስ በአህጉሪቱ ጉዞ ውስጥ ጽኑ ድምፅ ሆና የቆየችና አሁንም ያለች ሀገር ነች፤ አዲስ አበባም የአህጉራዊ ሕብረታችን መኖሪያ ሆና ታገለግላለች ብለዋል። የተለያዩ ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት የማህበራዊ ትስስር ገፆቻችንን ይወዳጁ! ፌስቡክ፡ https://www.facebook.com/share/181X2irsqB/ ቴሌግራም፡ https://t.me/bongafm974radiostatio ቲክቶክ፡ https://www.tiktok.com/@bongafm97.4?_t=ZM-90PCjvnnVBz&_r=1 ዩቲዩብ፡ https://www.youtube.com/@BongaFM97.4

"በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ስኬታማ ተግባራት ተከናውነዋል" አቶ ፍሬው አበበ ጳጉሜን 4/2018 ዓ.ም (ቦንጋ ኤፍ ኤም 97.4) በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት በከተማው በ14 መስኮች ስኬታማ
+4
"በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ስኬታማ ተግባራት ተከናውነዋል" አቶ ፍሬው አበበ ጳጉሜን 4/2018 ዓ.ም (ቦንጋ ኤፍ ኤም 97.4) በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት በከተማው በ14 መስኮች ስኬታማ ተግባራት መከናወናቸውን የቦንጋ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ፍሬው አበበ ተናገሩ። በከተማው የ"ህብር ቀን"ን አስመልክቶ ለአቅመ ደካማ ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስና የጽዳት ዕቃዎች ድጋፍ ተደርጓል። ቀኑን አስመልክቶ ለተማሪዎቹ የተሰበሰበውን ድጋፍ ያስረከቡት የቦንጋ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ጽህፈት ቤት ኃላፊና የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ፍሬው አበበ ፤ ብልጽግና ፓርቲ በሰው ተኮር ተግባራት ያስጀመረው ኢንሼቲቭ ከፍተኛ ውጤት እያስመዘገበ ነው ብለዋል። በከተማው በክረምት ወቅት በ14 መስኮች የበጎ ፈቃድ አገልግሎት እየተከናወኑ መቆየታቸውን አንስተው ፤ በዚህም የማህብረሰቡን ችግር መፍታት የሚችሉ ስራዎች መከናወናቸውን ጠቁመዋል። በጎ ተግባርን ማከናወን የአንድ ወቅት ስራ ብቻ አለመሆኑን የተናገሩት አቶ ፍሬዉ ማህበረሰቡ የርስበርስ መደጋገፍ ባህልን ማጠናከር እንደሚገባዉም አስገንዝበዋል። ለተጨማሪው ......https://www.facebook.com/share/p/1Aw533gUiE/

"ልከፋፍሉን ከሚችሉ አጀንዳዎች በመራቅ ህብረታችንን ማጠናከር አለብን"፦ አቶ ደመላሽ ንጉሴ ጳጉሜን 4/2018 ዓ.ም (ቦንጋ ኤፍ ኤም 97.4) ልከፋፍሉን ከሚችሉ አጀንዳዎች በመራቅ ህብረታችንን ማጠ
+2
"ልከፋፍሉን ከሚችሉ አጀንዳዎች በመራቅ  ህብረታችንን ማጠናከር አለብን"፦ አቶ ደመላሽ ንጉሴ ጳጉሜን 4/2018 ዓ.ም (ቦንጋ ኤፍ ኤም 97.4) ልከፋፍሉን ከሚችሉ አጀንዳዎች በመራቅ  ህብረታችንን ማጠናከር አለብን ሲሉ የካፋ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና የገቢዎች መምሪያ ኃላፊ አቶ ደመላሽ ንጉሴ ገለጹ። ጳጉሜን 4 የህብር ቀን “ የኢትዮጵያ ማንሰራራት” በሚል መሪ ቃል በቦንጋ ከተማ ተከብሯል። በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የካፋ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና የገቢዎች መምሪያ ኃላፊ አቶ ደመላሽ ንጉሴ በኢትዮጵያ ያሉ የሃይማኖት፣ የቋንቋና የብሄር ብዝሃነት ውበታችን በመሆናቸው ልንጠብቃቸው እና ልንገጥባቸው ይገባል ብለዋል። እነኚህን እሴቶች የውቤታችን መገለጫ በመሆናቸው ልከፋፍሉን ከሚችሉ አጀንዳዎች በመራቅ ህብረታችንን ማጠናከር አለብን ሲሉ ገልጸዋል። ኢትዮጵያዊያን ከዉስጥና ከውጭ የሚገጥሟቸውን ችግሮች ለመሻገር ህብረታቸው ትልቁን ሚና ተጫውቷል ብለዋል። ባለፉት ዓመታት የኢትዮጵያን ህብረ ብሔራዊነት የሚያረጋግጡ በርካታ ስራዎች ተሰርተዋል ያሉት አቶ ደመላሽ ሀገራዊ ምክክር እና የህዳሴ ግድብን ለአብነት አንስተዋል። ለተጨማሪ .....https://www.facebook.com/share/p/1DggaoJPMq/

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መጪዉን አዲስ ዓመት በዓልን አስመልክቶ፣ለጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት ሠራተኞች የበዓል ስጦታዎችን አበርክተዋል

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት መጪዉን የ2019 ዓ.ም የኢትዮጵያ አዲስ ዓመት በዓልን አስመልክቶ፣ ለጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት ሠራተኞች የበዓል ስጦታዎችን አበርክተዋል:: እንዲሁ
+3
የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት መጪዉን የ2019 ዓ.ም የኢትዮጵያ አዲስ ዓመት በዓልን አስመልክቶ፣ ለጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት ሠራተኞች የበዓል ስጦታዎችን አበርክተዋል:: እንዲሁም በጽ/ቤቱ ድጋፍ ለሚያድጉ ሕፃናት የትምህርት መርጃ ቁሳቁስ አበርክተዋል።

ከመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት የተሰጠ የፕሬስ መግለጫ ብዝኃነታችን የምንደምቅበት ጌጥ፣ የተደመረ ዐቅማችን ማሳያ ነው! ኢትዮጵያ የብዝኃ ማንነቶች ድምር ናት፡፡ ኢትዮጵያውያን ከሚኖሩበት የአየር ን
ከመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት የተሰጠ የፕሬስ መግለጫ ብዝኃነታችን የምንደምቅበት ጌጥ፣ የተደመረ ዐቅማችን ማሳያ ነው! ኢትዮጵያ የብዝኃ ማንነቶች ድምር ናት፡፡ ኢትዮጵያውያን ከሚኖሩበት የአየር ንብረት እስከ አመጋገባቸው፤ ከአመራረታው እስከ አለባበሳቸው፤ ከሃይማኖታቸው እስከ ፖለቲካዊ አመለካከታቸው በርካታ ብዝኃነቶች ያስጌጧቸዋል፡፡ የእነዚህ ብዝኃነቶች ድምር ደግሞ የኢትዮጵያ የማድረግ ዐቅም ነው፡፡ የኢትዮጵያውያን ብዝኃነት ለዘመናት የማይታረቁ የልዩነትና ግጭት ምንጭ ተደርጎ እንዲታይ ታሪካዊ ጠላቶቻችን ያለመታከት ሠርተዋል፡፡ በዚህም በየዘመኑ የታዩ ስኬታማ ድሎችን በአጭር እየቀጩ ኢትዮጵያን የማይገባት ደረጃ ላይ እንድትገኝ ለማድረግ ጥረዋል፡፡ ይህ ትውልድ ግን የጠላቶቻችን ምኞትና የብዝኃነትን ዐቅም የተረዳ፣ የበለጸገች ኢትዮጵያን እውን የሚያደርግ ባለታሪክ ለመኾን የልዩነት ሰንኮፎቹን በምክክር ለመንቀል ወስኗል፤ የጋራ ዕጣ ፋንታዉን በጋራ ተልሟል፡፡ ዛሬ ላይ ኢትዮጵያውያን የከፍታ ጉዞን ነጠብጣብ እንዳይኾን መሥመር አስይዘነዋል፡፡ ችግሮቻችንን እና የግጭት ምንጭ ኾነዉ ለባዕዳ መግቢያ ቀዳዳ፣ ለባንዳ መሹለኪያ የነበሩ ክፍተቶችን ለመድፈን በጋራ መክረናለ፡፡ ኢትዮጵያውያን በሰላማዊ ትግል ያነበሩት የለውጥ መንግሥት ባለፉት የለውጥ ዓመታት እየደረጀ መጥቶ ኢትዮጵያን በጽኑ መሠረት ላይ መገንባት የሚያስችል ዓውድ ፈጥሯል፡፡ የመልክአ ምድር፣ የአመጋገብ፣ የአለባበስ፣ የቋንቋ፣ የሃይማኖት፣ የፖለቲካዊ አመለካከትና ሌሎች ልዩነቶቻችን የኢትዮጵያ ጌጥ እና ዐቅም እንደኾኑ የጋራ አቋም ወስደናል፡፡ ብዝኃነታችን ውበት እና የካበተ ሥልጣኔያችን ማሳያ... ሙሉውን ለማንበብ ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ https://www.facebook.com/share/p/1DfEhKZHQJ/

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ያስተላለፉት መልዕክት፡- የኅብር ቀን ኢትዮጵያችን በሀገር በቀል እሴቶቿ፤ የነገውን ብሩህ ተስፋዋን በገዛ እጆቿ እየቀረጸች ትገኛለች! በትውልድ ቅብብሎሽ ያገ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ያስተላለፉት መልዕክት፡- የኅብር ቀን ኢትዮጵያችን በሀገር በቀል እሴቶቿ፤ የነገውን ብሩህ ተስፋዋን በገዛ እጆቿ እየቀረጸች ትገኛለች! በትውልድ ቅብብሎሽ ያገኘናቸውን ድንቅ የሀገር በቀል እሴቶቻችንን በማጎልበት እና በመደመር ፍልስፍና በመመራት፣ ለጽኑ ኅብረብሔራዊ አንድነታችን የማይናወጥ መሠረት ጥለናል። ታሪካዊውን ሀገራዊ ምክክር የመጀመር የታሪክ እጥፋት ተነስተን፣ የሁሉም ዜጎቻችንን ሕይወት ከሚለውጡ ሰው-ተኮር የኮሪደር ልማታችን፣ የበጎ ፈቃድ ስራዎቻችን እንዲሁም የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃግብርን በተግባር እውን እስከማድረግ ድረስ፤ ሁላችንም በአንድነት ስንቆም የጋራ ትርክቶቻችን ወደ ጋራ ስኬት እንደሚያሻግሩን በተግባር አሳይተናል። እኛ የምንገነባው አካታች የሆነች፣ በኢኮኖሚ ራሷን የቻለች፣ የአብሮነትና መረዳዳት ባህል የጎለበተባት ጠንካራ ሀገር ብቻ ሳይሆን የሁሉንም ኢትዮጵያውያን የጋራ ታላቅነትና እምቅ አቅም በተግባር እያረጋገጥን እንገኛለን። በአንድነት ወደ ብልጽግና ጉዟችን እንቀጥላለን። አንድ ህዝብ፣ ታላቅ ሀገር ኢትዮጵያ!

ጳጉሜን 4 - የኅብር ቀን
ጳጉሜን 4 - የኅብር ቀን

ጳጉሜ 3- የጽናት ቀን አከባበር ላይ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) ከተናገሩት የተወሰደ።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ፍትህ ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ቤተልሔም ዳንኤል በጋና በተደረገ የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር ላይ ተሳተፉ። ጳጉሜን 3/2018 ዓ.ም (ቦንጋ ኤፍ ኤም 97.4) የደቡብ
+6
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ፍትህ ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ቤተልሔም ዳንኤል በጋና በተደረገ የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር ላይ ተሳተፉ። ጳጉሜን 3/2018 ዓ.ም (ቦንጋ ኤፍ ኤም 97.4) የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ፍትህ ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ቤተልሔም ዳንኤል በሀገረ-ጋና በተካሄደውና በአፍሪካ የወንድማማችነት እሳቤን ማጠናከርን ዓላማው ባደረገ የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር ላይ ተሳተፉ። በጋና ዋና ከተማ አክራ የተካሄደው ይህ መርሃ-ግብር “Plant Africa Fraternity Initiative” የተሰኘ ሲሆን፤ የብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ክንፍና የጋና ወጣቶች በጋራ የችግኝ ተከላ አካሂደዋል። የኢትዮጵያ ብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ክንፍና የጋና NDC ፓርቲ የታላቋ አክራ ክልል ወጣቶች ክንፍ በ“Plant Africa Fraternity Initiative” ማዕቀፍ ነው የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብሩን ያካሄዱት። የብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ክንፍ ሰባት ስራ አስፈጻሚዎችን ጨምሮ ከ150 በላይ ተሳታፊዎች ተገኝተዋል። መርሃ-ግብሩ ከችግኝ ተከላ ባለፈ የሁለቱን ሀገራት ወጣቶች በማቀራረብ ወዳጅነታቸውን ለማጠናከርና ለአካባቢ ጥበቃና ለአረንጓዴ ልማት ያላቸውን የጋራ ቁርጠኝነት ለማሳየት ጥሩ አጋጣሚ መሆኑን ብልጽግና ፓርቲ በማህበራዊ ትስስር ገፁ አስታውቋል። ሙሉውን ለማንበብ ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ https://www.facebook.com/share/p/1ch26peZfF/

"በዓሉ በሰላም እንዲከበር የቅድመ ዝግጅት ሥራ ተጠናቅቆ ወደሥራ ተገብቷል" :- የካፋ ዞን ፖሊስ እና የዞኑ ሠላም ፀጥታ እና ሚሊሻ መምሪያዎች ጳጉሜን 3/2018 ዓ.ም (ቦንጋ ኤፍ ኤም 97.4) የ
+1
"በዓሉ በሰላም እንዲከበር የቅድመ ዝግጅት ሥራ ተጠናቅቆ ወደሥራ ተገብቷል" :- የካፋ ዞን ፖሊስ እና የዞኑ ሠላም ፀጥታ እና ሚሊሻ መምሪያዎች ጳጉሜን 3/2018 ዓ.ም (ቦንጋ ኤፍ ኤም 97.4) የካፋ ዞን ፖሊስ እና የዞኑ ሠላም ፀጥታ እና ሚሊሻ መምሪያ ኃላፊዎች በዓሉን አስመልክተው ለመገናኛ ብዙኃን መግለጫ ሰጥተዋል፡፡ የካፋ ዞን ፖሊስ መምሪያ አዛዥ ኢንስፐክተር ዳዊት ደሳለኝ፣ በዓሉ በሰላም ተከብሮ እንዲያልፍ በሁሉም የዞኑ መዋቅሮች ፖሊስ የቅድመ ዝግጅት ሥራ አጠናቅቆ ወደሥራ ገብቷል ብለዋል፡፡ ከበዓል በፊት እና ከበዓል ማግስት በሚል ልዩ ዕቅድ ተዘጋጅቶ በሁሉም ወረዳዎችና ከተማ አስተዳደሮች ላይ ሰፊ ሥራ እየተከናወነ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ በተለይ ከበዓላት ውቅት ጋር ተያይዞ ሊከሰቱ የሚችሉ የትራፊክ አደጋዎችን የመከላከል እና ከታሪፍ በላይ የማስከፈል ድርጊቶችን የመከላከሉ ሥራ መጀመሩን አስታውቀዋል፡፡ ለተጨማሪው .....https://www.facebook.com/share/p/18g5LwuoJm/