Eagle College
Open in Telegram
432
Subscribers
No data24 hours
-27 days
-930 days
Posts Archive
ማስታወቂያ
ውድ የ2015 ዓ.ም ተመራቂ ተማሪዎች!
በቀጣይ በሀገር አቀፍ ደረጃ በሚሰጠው የመውጫ ፈተና ላይ ለመቀመጥ ማድረግ ያሚገባችሁን ከወዲሁ ጥቆማ ለመስጠት ያክል :-
1. የት/ት ሚኒስቴር በቅርብ ቀናት አዘጋጅቶ የሚለቀው ድህረ ገጽ አለ።
2. በቅርብ ቀን በሚለቀቀው ድህረ ገጽ ላይ ሙሉ መረጃችሁን በመስጠት የት/ት ሚኒስቴር የሚጠይቀውን ክፍያ በቴሌ ብር በመክፈል በፈለጋችሁበት ዩኒቨርሲቲ የመውጫ ፈተናውን መውሰድ የምትችሉ መሆኑ።
3. ለተጨማሪ እርዳታ lnbox ማድረግ ትችላላችሁ።
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
+1
#AddisAbaba
25 የግል ኮሌጆች ለ2016 ዓ.ም ምንም አይነት አዲስ ሰልጣኝ መቀበል እንዳይችሉ እግድ ተጣለባቸው።
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ፤ የግል ኮሌጆች የምዝገባ ፍቃድ ለመውሰድ መረጃ እንዲያቀርቡ በደባድቤ የጠየቃቸው ኮሌጆች መረጃ ለማቅረብ ፍቃደኛ ሳይሆኑ በመቅረታቸው እግድ እንደጣለባቸው አሳውቋል።
በመሆኑም፦
- ኩዊንስ ኮሌጅ ሃና ማርያም ካምፓስ
- ኩዊንስ ኮሌጅ መድሃኒዓለም ካምፓስ
- ሪፍት ቫሊ ዩኒቨርሲቲ አቢቹ ካምፓስ
- ሮያል ኮሌጅ ፒያሳ ካምፓስ
- ማይክሮሊንክ ኮሌጅ
- ላየን ኢትየጵያ ሆቴልነና ቢዝነስ ኮሌጅ 4 ኪሎ
- ዩኒየን ቪዥን ኮሌጅ
- ትሮፒካል ኮሌጅ ኦፍ ሚድሲን
- አዲስ ኮሌጅ
- ኩዊንስ ኮሌጅ ቤቴል ዐለም ባንክ ካምፓስ
- ኦርቢት ኮሌጅ
- ባዮስ ኮሌጅ
- ብራይት ኮሌጅ ጀሞ
- ስታንዳርድ ኮሌጅ ዩኒቨርሳል
- አይ ኪዉ ኮሌጅ
- ኬቢ ኢንተርናሽናል የቢዝነስና ቴክኖሎጂ ኮሌጅ
- ካፒታል ሆቴልና ማኔጅመንት ኮሌጅ
- አንድነት ኢንተረናሽናል ኮሌጅ ላም በረት
- ሪፍት ቫሊ ዩኒቨርሲቲ ፊንፊኔ ካምፓስ
- ሪፍት ቫሊ ዩኒቨርሲቲ ላንቻ ካምፓስ
- ሪፍት ቫሊ ዩኒቨርሲቲ ካራ አሎ ካምፓስ
- ኩዊንስ ኮሌጅ መካኒሳ ካምፓ
- ኩዊንስ ኮሌጅ ልደታ ካምፓስ
- ኩዊንስ ኩሌጅ ሜክሲኮ ኬኬር በባለስልጣን መ/ቤቱ በመመሪያ መሰረት የምዘና ግብ ሳያሳኩና የምዝገባ ፍቃድ ሳያገኙ ለ2016 ዓ.ም ምንም አይነት አዲስ ሰልጣኝ መቀበል እንደማይችሉ አሳስቧል።
ተቋማቱ ለመጨረሻ ጊዜ አስፈላጊውን የሰልጣኞች የመረጃ እስከ 30/03/2016 ዓ.ም እንዲያቀርቡ ማስጠንቀቂያ የተሰጣቸው ሲሆን ይህ ባያደርጉ በመመሪያ 02/2012 እና 01/2014 መሰረት እውቅና ፍቃዳቸው እንደሚሰረዝ አስጠንቅቋል።
(የእግዱ ደብዳቤ ከላይ ተያይዟል)
@tikvahethiopia
