የንስሀ መዝሙር ዘምር ዘምር አለኝ
1 977
Subscribers
-224 hours
-107 days
+22730 days
- Subscribers
- Post coverage
- ER - engagement ratio
Data loading in progress...
Subscriber growth rate
Data loading in progress...
እዩና እመኑ ሰዎች
እዩና እመኑ ሰዎች
ድንጋዩ ተፈነቃቅሏል
ኢየሱስ በኩለ ሌሊት
በሀይሉ ሞትን ድል ነስቷል/2/
እልልታ ለዚህ ይገባል
ግርግርታ ለዚህ ይገባል
የሞት ሀይል ተዋርዷል ዛሬ
ሲኦልም ተመሰቃቅሏል/2/
መላዕክቱ ነጭ ለብሰዉ
ምስራቹን አበሰሩ
ተነስቷል ኢየሱስ ብለው
ለዓለም እዲናገሩ/2/
👥@yemezmurgetemoche
✍ t.me/KIDAN_MEHRET_ENATEbot
@EthiopianOrthodoxTewahdoMezmurs
❤ 5
#እርሱ_ነው_ቀን_የሚይወጣ
ከዳን እስከ ቤርሳቤህ
ዛሬ ሞልቷል ምስጋናህ
ተነሳ ልቤ ዘምር
ለጌታ ለእግዚአብሔር 3
አዝ።።።።።።።።።።።።።።
በገና ተነስ እንዚራ
ማዳኑን እንድናወራ
ብትቀርቡ ብትከተሉ
ሁላችው ሆሳህና በሉ 2
አዝ።።።።።።።።።።።።።
እግዚአብሔር ዘመን ከሰጠ
ይዘምር የተለወጠ
እልልታ ይሁን ለስሙ
ለዋጀን በወርቅ ደሙ 2
አዝ።።።።።።።።።።።።።።።።።
የክብሬ የቤቴ ጌታ
የነፍሴ ባለውለታ
ኤፉድ ነው በፍታ ነው ልብሴ
ዘማሪ ነኝ ለንጉሴ 2
አዝ።።።።።።።።።።።።።።።።።
ሰገነት ላይ የወጣችው
ዝምታን የመረጣችው
ከአፋችው ወረት አይውጣ
እሱ ነው ቀን የሚያወጣ 2
አዝ።።።።።።።።።።።።።።።
✝️✝️✝️2አንችን ብቻ ቤተልሔም✝️✝️
✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️
አንቺን ብቻ ቤተልሔም
አንቺን ብቻ በዚያ ግርግም
ዮሀንስነ በገሊላ በኤፍራታ አላየንም
አንቺን ብቻ ቀራንዮ አንቺን በኮረብታ
ዮሴፍንም አላየንም ሊጣስትራ ጎልጎታ
አዝ...
ገና በማለዳ በናዝሬቷ መቅደስ
ገብርኤል በስራት ይዞ ከገሊላ ሲደርስ
ያን ዜና ስሰሚ ደነገጥሽ በብርቱ
አንቺ ብቻ ነበርሽ ብላቴናይቱ
አዝ....
ሕፃኑን ስትወልጅ ግርግም የነበሩ
የሉም በመከራው ቀራንዮን ፈሩ
በልደቱ እንጂ የታሉ በሞቱ
አብረሹ ነበርሽ አንቺ ብቻ እናቱ
አዝ...
የግብፅ በረሀ አብረውሽ የወጡ
በቀያፋ ግቢ እንደምን አልመጡ
እርሱ ለሚገረፍ እነሱ እያፈሩ
አንቺን ብቻ ትተው በመንደር ነበሩ
አዝ..
ሐሙስ ዕለት ፋሲካን ሲበሉ ያመሹ
አርብ ዕለት ተነሥተው ከቶ ወዴት ሸሹ
ቃል ገብተው ነበር ላይክዱት መሀላ
ድንግል ካንቺ በቀር ማን ነበር ሌላ
አዝ...
በሠላሳ ዘመን በሥጋ ወራቱ
መች ነበሩ ከቶ ደቀመዛሙርቱ
የእጆቹን ታምራት ቀን ከሌሊት እያየሽ
በቃሉ በርታት ፊት አንቺ ነበርሽ
አዝ...
ቤተልሄም ያሉ ቀራንዮ የሉም
ቀራንዮም ያሉ ግርግም አልነበሩም
በሆነበት ዘመን በመስቀል ሞቱ
አብረሹ ነበርሽ አንቺ ብቻ እናቱ
👍 2
✞ሆሣዕና✞
ሆሣዕና በአርያም ሆሣዕና በአርያም ሆሣዕና በአርያም
ሆሣዕና ሆሣዕና ሆሣዕና ለወልደ ዳዊት
ህፃናቱ ሁሉ ድንጋዮች ሳይቀሩ ለዘመሩለት
ሆሣዕና ለወልደ ዳዊት
በእግዚአብሔር ስም የሚመጣ እርሱ
የተባረከ ነው ቅዱስ ነው መንፈሱ
ሰላምን የሚሰብክ የሚናገር ፍቅርን
በአህያ ውርንጫ መጥቷል ንጉሣችን
አዝ= = = = =
ዘንባባውን ይዘው ህፃን አዛውንቱ
ልብሳቸውን ሳይቀር አንጥፈው በፊቱ
ሆሳሣና ብለው ዘመሩ በእልልታ
ግባ ንጉሣችን የሠራዊት ጌታ
አዝ= = = = =
ዘመንን ለሰጠን እንዘምርለት
የምስጋናን መስዋዕት በፊቱ እንሰዋለት
እንኳን እኛን ቀርቶ ድንጋይ ያናግራል
ከሚጠቡ አንደበት ምስጋናን ይወስዳል
አዝ= = = = =
መድሃኒት ለሰው ልጅ ስለተገለጠ
የመርገም ጨርቃችን ስለተወጠ
ሰላም በሰማያት ሆነ በምድር
ክብርና ምስጋና ለእርሱ ለእግዚአብሔር
አዝ= = = = =
እኛ ለክርስቶስ እናስፈልጋለን
ቅዱሳኑን ልኮ መፈታትን ይስጠን
በትህትና ወድቀን በልባችን ይግባ
እንደ ህፃናቱ እንያዝ ዘንባባ
መዝሙር
ዲያቆን ቀዳሜጸጋ ዮሐንስ
የዮሐንስ ወንጌል ፲፪፥፲፫
መዝ ፰፥፪
✞የዘመን ፍፃሜ✞
የዘመን ፍፃሜ እስከዚህ የሌለህ
ዘላለም የምትኖር (፫)ፍጹም አምላክነህ
🌿ሆሳዕና (፫) በአርያም🌿
ቡሩክ ሆሳዕና አምላከ እስራኤል
ተቀምጦ መጣ (፫) በአህያ ግልገል
አዝ= = = = = 🌿
ትንሹም ትልቁም በአንድነት ዘመሩ
አመሰገኑት (፫) ሆሳዕና እያሉ
🌿 አዝ= = = = =
በጣም ደስ ይበልሽ እልል በይጽዮን
ንጉሥሽ መጣልሽ (፫) ሊሆንሽ መድኅን
🌿 🌿
╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮
✞ ምስጋናዬን ✞
ምስጋናዬን ላምላኬ አቀርባለው
በማደሪያው ገብቼ ሠግድለታለው
ኤልሻዳይ ነው ጌታ ሁሉን ቻይ
ይፈፀማል አምናለሁ የልቤን ጉዳይ(2)
ዘንባባዬን ይዤ እደህፃናቱ
ሆሣና ልበለው ሠግጄ በፈቱ
ምንም ባዶብሆን እውቀት ቢጎድለኝ
ለሥሙ ልዘምር ከልካይም የለኝ(2)
አዝ= = = = =
አምላኬ በፈትህ ቃል አለብኝ እኔ
ቋንቋዬ መዝሙር ነው ያንተ እደመሆኔ
ባሚናዳ ደጃፍ በቅድመ ታቦቱ
ያየክብርህ ውደር ጠራኝ ማህሌቱ (2)
አዝ= = = = =
የህይወት ትርጉሜ አንተነህ ደሥታዬ
ስምህን ማገልገል ክብሬነው ሥራዬ
ለታመነው ጌታ ምስክር የሆኑ
ከብረው ተመለሱ ለበረከት ሆኑ(2)
አዝ= = = = =
መነሻዬ አንተነህ ጉልበቴና ክብሬ
መድረሻዬም አንተ መደምደሚያ ቅጥሬ
በፂሆን ተራራ ስትገለጥ ያኔ
ነጩን ልብሥ አልብሠህ አስነሳኸኝ ለቅኔ (2)
መዝሙር በ
ሊቀ መዘምራን ዲያቆን ቴድሮስ ዮሴፍ
╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮
❤ 2
🌿ሆሳዕና በአርያም🌿
🌿ለወልደ ዳዊት🌿
ሆሣዕና በአርያም
የዳዊት ልጅ ገባ ኢየሩሳሌም(፪)
ቤቱን ቢያደርጉበት የዓመጽ መደብር
በጌትነት ገባ የሰው ልጅ በክብር(፪)
አዝ= = = = =
በአህያ ተቀምጦ ሲመጣ ቢያዩት
ሕጻናት በአንድነት አመሰገኑት(፪)
አዝ= = = = =
ሊቃነ ካህናት በጣም ተቆጥተው ይማከሩ ጀመር ብለው እንስቀለው(፪)
╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮
✞ሆሳዕና✞
ሆሳዕና በአርያም ሆሳዕና
ሆሳዕና ብለን እናቅርብ ምስጋና
ሆሳዕና በሉ - - - ሆሳዕና
ለወልደ አምላክ - - - ሆሳዕና
ትህትናን አሳየን - - - ሆሳዕና
ስሙ ይባረክ - - - ሆሳዕና
አዝ= = = = =
ሆሳዕና በሉ - - - ሆሳዕና
ለሰማይ ንጉስ - - - ሆሳዕና
ግርማ ለብሶ መጣ - - - ሆሳዕና
እኛን ሊቀድስ - - - ሆሳዕና
አዝ= = = = =
ሆሳዕና በሉ - - - ሆሳዕና
ለወልደ ዳዊት - - - ሆሳዕና
ነብያት በትንቢት - - - ሆሳዕና
ለተናገሩለት - - - ሆሳዕና
ሐዋርያት በወንጌል - - - ሆሳዕና
ለሰበኩለት - - - ሆሳዕና
አዝ= = = = =
ሆሳዕና በሉ - - - ሆሳዕና
ለአምላከ ምህረት - - - ሆሳዕና
ተወልዶ ከድንግል - - - ሆሳዕና
እንደ ህጻናት - - - ሆሳዕና
እረኞች በዋሻ - - - ሆሳዕና
የሰገዱለት - - - ሆሳዕና
የአዳም ልጆች ሁሉ - - - ሆሳዕና
ደግሞም መላእክት - - - ሆሳዕና
═•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ═
#ብርና_ወርቅ_ሳይዙ
ብርና ወርቅ ሳይዙ ዓለማትን ዞሩ
ቅዱሳን ሐዋርያት ቃሉን እየዘሩ
ሙታን እያስነሡ ድውያን ፈወሱ
ስሙን ብቻ ይዘው(፪)ታምነው በንጉሡ
ከቀራጩ መደብ ከሐጥያት ገበታ
ከጥብርያዶስ ባሕር ከጠራቸው ጌታ
ስሙን ተሸክመው ቃሉን መሰከሩ
በመንፈስ ቅዱስ ኃይል ድንቅን እየሠሩ
#አዝ
የነገስታቱን ቃል ዛቻውን ሳይፈሩ
የመንግስቱን ወንጌል ለዓለም አስተማሩ
ይሻለናል አሉ ማድላት ለእግዚአብሔር
ለሰው ከመታዘዝ ዘላለም ለማይኖር
#አዝ
ቆዳቸው ተገፎ በሰይፍ ተሰየፉ
ስለጌታ ፍቅር በመከራ አለፉ
የድንጋዩን ናዳ የእሣቱን ነበልባል
የጀርባን ግርፋት በእምነት ታግሰዋል
#አዝ
ስደት ነው መከራ ረሀብ ነው ወይስ ጥም
ከክርስቶስ ወንጌል ከእውነት የሚያስቆም
በእርሱ ስላመኑ በፅድቅ ተጋደሉ
ደግሞም በእርሱ በላይ እንዳለ በቃሉ
#አዝ
በዙርያችን ከበው ካሉ እንደ ደመና
እነርሱን እያሰብን በእምነት እንፅና
በእውነት እንደኖሩ መሥለው ክርስቶስን
እኛም በኑሮችን እንምሰል እነርሱን
✞ ሆሣዕና እምርት ✞
ሆሣዕና እምርት እንተ አቡነ ዳዊት(፪)
ቡርክት እንተ ትመጽእ መንግስት(፬)
ትርጉም:-የታወቀችይቱ የድኅነት ቀን
የምትመጣይቱ የአባታችን የዳዊት መንግስት ቡርክት ናት
╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮