en
Feedback
Ethio_news

Ethio_news

Open in Telegram

#ኢትዮ_news የተለያዬ ወቅታዎ ዜናዎችን በፋጥነት ሚያገኙበት ቦታ

Show more
508
Subscribers
No data24 hours
-27 days
-1430 days
Posts Archive
የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ብሔራዊ ፈተና ለመስጠት አስፈላጊው ዝግጅት መጠናቀቁን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ገልጿል። መንግሥት ከክልል ትምህርት ቢሮዎች፣ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት፣ ከጸጥታ
+1
የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ብሔራዊ ፈተና ለመስጠት አስፈላጊው ዝግጅት  መጠናቀቁን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ገልጿል። መንግሥት ከክልል ትምህርት ቢሮዎች፣ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት፣ ከጸጥታ አካላት እና ከሚመለከታቸው ተቋማት ጋር በትብብር እየሠራ መሆኑን የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር እሸቱ ከበደ (ዶ/ር) ለፋና ሚዲያ ተናግረዋል። የፈተና ጥያቄዎች እና የመሰረተ ልማት ዝግጅቶች መጠናቀቃቸውን የገለፁት ዋና ዳይሬክተሩ፤ ኩረጃን ለማስቀረት ፈተናዎች በከፍተኛ ስብጥር እንዲዘጋጁ መደረጉን ገልፀዋል። በፈተና ወቅት ስልክን ጨምሮ ኤሌክትሮኒክስ ነገሮችን መያዝ መከልከሉንና ይዘው የተገኙ ተፈታኞች ውጤታቸው እንደሚሰረዝ አስገንዝበዋል። የ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ከሰኔ 23/2017 ዓ.ም እስከ ሐምሌ 8/2017 ዓ.ም ይሰጣል። ፈተናውን ለመውሰድ 608 ሺህ ተማሪዎች የተመዘገቡ ሲሆን፤ 150 ሺህ የሚሆኑት በበይነ መረብ የሚፈተኑ ናቸው። ትምህርት ሚኒስቴር ተጨማሪ ትምህርታዊ መረጃ ለማግኘት ቻናላችን ይቀላቀሉ ‼️ https://t.me/Tmhrt_Minister https://t.me/Tmhrt_Minister

በኢራን እና እስራኤል ግጭት አሜሪካ ወታደራዊ ተሳትፎ ካደረገች ከፍተኛ አደጋ ሊከሰት ይችላል ሲሉ የኢራን መንፈሳዊ መሪ አያቶላህ አሊ ሀሚኒ አስጠነቀቁ፡፡ የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ኢራን
በኢራን እና እስራኤል ግጭት አሜሪካ ወታደራዊ ተሳትፎ ካደረገች ከፍተኛ አደጋ ሊከሰት ይችላል ሲሉ የኢራን መንፈሳዊ መሪ አያቶላህ አሊ ሀሚኒ አስጠነቀቁ፡፡ የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ኢራን በፍጥነት እጅ እንድትስጥ ማሳሰባቸውን ተከትሎ የኢራን መንፈሳዊ መሪ አያቶላህ አሊ ሀሚኒ ሀገራቸው በቀላሉ የምትንበረከክ እንዳልሆነች ማስታወቃቸውን የሀገሪቱ ብሔራዊ ቴሌቪዥን ዘግቧል:: FMC

በኢራን እና እስራኤል ጦርነት ምክንያት የዓለም አቀፍ የነዳጅ ዋጋ እንዳሻቀበ ነው። ዛሬ ላይ አንድ በርሜል ብሬንት ድፍድፍ ነዳጅ 76.45 ዶላር እንዲሁም በአሜሪካ ነዳጅ ገበያ እንደመለኪያ በሚታየው
በኢራን እና እስራኤል ጦርነት ምክንያት የዓለም አቀፍ የነዳጅ ዋጋ እንዳሻቀበ ነው። ዛሬ ላይ አንድ በርሜል ብሬንት ድፍድፍ ነዳጅ 76.45 ዶላር እንዲሁም በአሜሪካ ነዳጅ ገበያ እንደመለኪያ በሚታየው ዌስት ቴክሳስ ኢንተርሚዴት አንድ በርሜል ነዳጅ 74.84 ዶላር እየተሸጠ ነው። ጦርነቱ ከቀጠለ እና ሌሎችም ሀገራት የሚሳተፉበት ከሆነ የዓለም ነዳጅ ዋጋ በከፍተኛ ሁኔታ ሊጨምር ይችላል ተብሎ ተሰግቷል።

አዲስ የተሾሙት የኢራን የጦርነት ጊዜ ዋና አዛዥ በእስራኤል ተገደለ። የእስራኤል መከላከያ ሠራዊት የኢራን የጦርነት ጊዜ ዋና አዛዥ እና ከአገዛዙ ከፍተኛ የጦር አዛዦች አንዱ የሆኑትን አሊ ሻድማኒ መ
+1
አዲስ የተሾሙት የኢራን የጦርነት ጊዜ ዋና አዛዥ በእስራኤል ተገደለ። የእስራኤል መከላከያ ሠራዊት የኢራን የጦርነት ጊዜ ዋና አዛዥ እና ከአገዛዙ ከፍተኛ የጦር አዛዦች አንዱ የሆኑትን አሊ ሻድማኒ  መገደሉን አስታውቋል። ዋና አዛዡ የተገደሉት በማዕከላዊ ቴህራን በሚገኘው ዋና መሥሪያ ቤት ላይ በተደረገ የአየር ድብደባ መሆኑም ተዘግቧል።

ከግኝቱ በመነሳት እየተሰራ መሆኑን ጠቁመው በጥናቱ መሰረት “32% ደርሷል፤ የግፊት ፕሬቫለንሲ፤ የስኳር ደግሞ 12% ደርሷል። አንዱ በሽታ አንዱን ያመጣል። ግፊትና ስኳር እየበዛ በሄደ ቁጥር የኩላሊት በሽታም እየበዛ ነው” ብለዋል። ብዙዎች ሳያውቁት ተጠቅተው እየተገኙ በመሆኑ በተለይ የስኳር በሽታን በተመለከተ በየወቅቱ የጤና ምርመራ ማድረግ እንደሚገባ ማሳሰቢያ ተሰጥቷል።

“ ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች በአሁኑ ጊዜ በከፍተኛ ሁኔታ ጨምረዋል ” - ጤና ሳይንስ ኮሌጁ ከተላላፊዎቹ ይልቅ ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች ህዝቡን ለሞት እያጋለጡት መሆኑን እና በህፃናት የሚስተዋለው የ
“ ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች በአሁኑ ጊዜ በከፍተኛ ሁኔታ ጨምረዋል ” - ጤና ሳይንስ ኮሌጁ ከተላላፊዎቹ ይልቅ ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች ህዝቡን ለሞት እያጋለጡት መሆኑን እና በህፃናት የሚስተዋለው የስኳር በሽታ አሳሳቢ ስለመሆኑ የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል። የኮሌጁ ኤክስኩዩቲቭ ዳይሬክተር ተባባሪ ፕሮፌሰር አለሙ ጫሚሶ በገለጹት መሠረት፣ “ድሮ ተላላፊ በሽታዎች ነበሩ፤ አሁን ግን ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች ናቸው ህዝቡን ለሞትና ለጤና ችግር እያጋለጡት ያሉት”። ክትባትን ጨምሮ የተለያየ ሥራዎች በመሰራቸው በተላላፊ በሽታዎች የሚያጋጥሙ ሞቶች መቀነስ ትችሎ እንደነበር አስታውሰው፣ “በብዙ ምክንያቶች ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች በአሁኑ ጊዜ በከፍተኛ ሁኔታ ጨምረዋል” ብለዋል። በከፍተኛ ሁኔታ መጨመሩ ተጓዳኝ በሽታ በማምጣት፣ በጤናና በፋይናንስ ጉዳይ በህዝቡ ላይ ጫና መፍጠሩን ገልጸው፣ “ድሮ ታይፎድ፣ ታይፈስ ነበር፤ አሁን ግን ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎችን ነው የምናክመው” ነው ያሉት። “ህፃናት ላይ ስኳርና ካንሰር በጣም በዝቷል። እዛ አካባቢ ያለው ህክምናም ወጪው በጣም ከባድ ነው” ሲሉ ተባባሪ ፕሮፌሰሩ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስረድተዋል። መንስኤው ምንድን ነው? ዩኒቨርሲቲው ጥናት አጥንቶ እንደነበር የገለጹት ተባባሪ ፕሮፌሰሩ፣ “በእኛ የተለዩ ነገሮች አሉ፤ የበሽታው ስርጭት ሲዳማ በስድስት ወረዳዎች የግፊትና ስኳር በሽታ ከሌሎቹ ይሰፋል። ለምን? የሚለውን ስናጠና አፈር፣ ውሃ ላይ በተለየ ሁኔታ መጥናት ያለባቸው ነገሮች እንዳሉ” መረዳታቸውን ገልጸዋል።

የ 100 ብር ካርድ ልንሸልሞት ነው channelun subscribe ያድርጉ እና ስልክ ቁጥር ይላኩ 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 👉https://youtube.com/@fua_mediaa?si=HMlEQBPZbESiGzUq 👉https://youtube.com/@fua_mediaa?si=HMlEQBPZbESiGzUq channelun subscribe ያድርጉ እና ስልክ ቁጥር ይላኩ

ካርዲናል ሮበርት ፐሮቭስት 267ኛው የሮማ ካቶሊክ ሊቀ ጳጳስ መሆናቸው ታወቀ።
ካርዲናል ሮበርት ፐሮቭስት 267ኛው የሮማ ካቶሊክ ሊቀ ጳጳስ መሆናቸው ታወቀ።

ነዳጅ ጨመረ የአለም የነዳጅ ዋጋን መነሻ በማድረግ ከሚያዝያ 30 ቀን 2017 ዓ.ም ከምሽቱ 12 ሰዓት ጀምሮ በስራ ላይ የሚቆይ የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በሚከተለዉ መሰረት ስራ ላይ እንዲ
ነዳጅ ጨመረ የአለም የነዳጅ ዋጋን መነሻ በማድረግ ከሚያዝያ 30 ቀን 2017 ዓ.ም ከምሽቱ 12 ሰዓት ጀምሮ በስራ ላይ የሚቆይ የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በሚከተለዉ መሰረት ስራ ላይ እንዲዉል በመንግስት የተወሰነ ሲሆን የሁሉም ከተሞች በችርቻሮ መሸጫ ዋጋ እንደሚከተለው ቀርቧል። 🎯ቤንዚን 122.53ብር 🎯ኬሮሲን 116.49 🎯ነጭ ናፍጣ 116.49 🎯ቀላል ጥቁር ናፍጣ 106.77 🎯ከባድ ጥቁር ናፍጣ 104.08 🎯የአውሮፕላን ነዳጅ 109.56 ብር ሆኗል

በኦሮሚያ ክልል በአንድ ሳምንት ውስጥ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ17 ሰዎች ህይወት አልፏል   በኦሮሚያ ክልል ከሚያዝያ 20 እስከ ሚያዝያ 26 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ ባሉት ቀናቶች በደረሱ የትራፊክ አደጋዎች የ17 ሰዎች ህይወት ሲያልፍ በ36ሰዎች ላይ ከባድና በ30 ሰዎች ላይ ቀላል የአካል ጉዳት ደርሷል፡፡ በአንድ ሳምንት ውስጥ በደረሰ አደጋ ከ11 እስከ 60 ዓመት የእድሜ ክልል ላይ የሚገኙ ሰዎች ህይወታቸው ማለፉን የኦሮሚያ ክልል የትራፊክ ቁጥጥር ክፍል ባለሙያ የሆኑት ኢንስፔክተር መሰለ አበራ ለብስራትሬዲዮና ቴሌቪዥን ተናግረዋል፡፡ አብዛኛዎቹ አደጋዎቹ የተከሰቱት በቀኑ እና በለሊቱ  ክፍለ ጊዜ ሲሆን  አደጋውን ያደረሱት ወንድ  አሽከርካሪዎች ናቸው። በብዛት ከተከሰቱት አደጋዎች መካከል ሰሜን ሸዋ እና ምዕራብ ሀረርጌ ዞኖች እና በተለያዩ ከተሞች የተከሰቱ ናቸው።የሞት አደጋዎች የደረሱት በጭነት፣ በህዝብ ማመላለሻ ፣በባለ ሦስት እግር (ባጃጅ) እና በሞተር ሳይክል የተከሰቱ መሆናቸው ተገልጿል፡፡ የአደጋዎቹ መንስኤዎቹ ያለመንጃ ፍቃድ ማሽከርከር፣ከፍጥነት ወሰን በላይ ማሽከርከር እና ለእግረኛ ቅድሚያ  አለመስጠት መሆኑን  ኢንስፔክተር መሰለ አበራ ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል፡፡ Via-ዳጉ_ጆርናል

" መምህሯ ላይ እምርጃ ወስደናል " - ትምህርት ቢሮ " የቤት ስራ አልሰራሽም " በማለት ተማሪዋን ተገቢ ያልሆነና አጸያፊ የሆነ ቅጣት የቀጣችው መምህርት ከስራ ታግዳ በህግ ቁጥጥር ስር ተደረገች።
" መምህሯ ላይ እምርጃ ወስደናል " - ትምህርት ቢሮ " የቤት ስራ አልሰራሽም " በማለት ተማሪዋን ተገቢ ያልሆነና አጸያፊ የሆነ ቅጣት የቀጣችው መምህርት ከስራ ታግዳ በህግ ቁጥጥር ስር ተደረገች። የአዲሰ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ በኮልፌ ቀራኒዮ ክ/ ከተማ በሰላም በር ቅድመ አንደኛና አንደኛ ደረጃ ት ቤት የ2ኛ ክፍል ተማሪን " የቤት ስራ አልሰራሽም " በማለት ተገቢ ያልሆነ ቅጣት በፈጸመችው መምህርት ላይ እርምጃ መውሰዱን አሳውቋል። መምህርቷ ላይ ከስራ የማገድ በህግ ጥላ ስር እንድትሆን የማድረግ እርምጃ መወሰደኑን ነው የጠቆመው። በህግ ከላላ ስር እንድትሆን የተደረገው መምህርቷ ጉዳይዋ በህግ አግባብ እንዲታይና ፍትህ እንዲያገኝ ቢሮው እንደሚሰራ ቢሮ ገልጿል። " ተማሪዋ ህክምና አግኝታ በጥሩ የጤንነት ሁኔታ ላይ ትገኛለች " ያለው ቢሮው " በነገው እለትም ትምህርቷን ትጀምራለች " ብሏል።

" የመንግስት አካላት በተደጋጋሚ የኢትዮጵያ ሰራተኞች ለሚያቀርቧቸው ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት ዳተኛ ሆነዋል " - ኢሰማኮ የኢትዮጵያ ሰራተኛ ማህበራት ኮንፌዴሬሽን (ኢሰማኮ) ምን አለ ? " በኢትዮጵ
" የመንግስት አካላት በተደጋጋሚ የኢትዮጵያ ሰራተኞች ለሚያቀርቧቸው ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት ዳተኛ ሆነዋል " - ኢሰማኮ የኢትዮጵያ ሰራተኛ ማህበራት ኮንፌዴሬሽን (ኢሰማኮ) ምን አለ ? " በኢትዮጵያ ዝቅተኛ የደመወዝ ወለል እንዲወሰን እንዲሁም እስከ 35 በመቶ የደረሰው ከደመወዝ ላይ የሚቆረጠው ግብር እንዲቀንስ ከዚህ ቀደም ጠቅላይ ሚኒስትሩን ጨምሮ በተዋረድ ያሉ የስራ ሃላፊዎችን ብንጠይቅም እስካሁን ሁነኛ ምላሽ አላገኘንም " ብሏል። የኢሰማኮ ፕሬዝዳንት አቶ ካሳሁን ፎሎ ፥ ከ1 ዓመት ከ6 ወር በፊት ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ጋር ተወያይቶ እንደነበር ይህን ተከትሎ ጠቅላይ ሚኒስትሩ የሚመለከታቸውን የመንግስት አካላት በጉዳዩ ላይ ጥናት አድርገው እንዲያቀርቡ አቅጣጫ ሰጥተው እንደነበር አስታውሰዋል። " ጥናት እንዲከወን አቅጣጫ ቢሰጥም፤ ምላሽ ባለማግኘታችን ጠቅላይ ሚኒስትሩን በድጋሚ በደብዳቤ ለመጠየቅ ተገድደናል " ብለዋል። ጥያቄዎቹ በጠቅላይ ሚኒስትሩ ተቀባይነት ቢያገኙም  ጥናቱን አከናውኑ የተባሉ የመንግስት መስሪያ ቤቶችን " ከምን ደረሰ ?  ብለን በተደጋጋሚ ደጅ ብንጠናም ምላሽ አጥተናል " ብለዋል። ዝቅተኛ የደሞዝ ወለል መወሰን እንደ ሃገር በልቶ ማደር የሚችል እንዲኖር ያስችላል ምርታማነትንም ይጨምራል "  ያሉት አቶ ካሳሁን " ኮንፌደሬሽኑም በጉዳዩ ዙሪያ የበኩሉን ጥናት እየከወነ ነው " ብለዋል። በሌላ በኩል እስከ 35 በመቶ የሚደርሰው ከደሞዝ ላይ የሚቆረጠው ግብር እንዲቀንስ ጥያቄ እየቀረበ ነው። በተለይም በጣም ዝቅ ያለ ደመወዝ የሚከፈላቸው ሰራተኞች በኑሮ ውድነቱ ምክንያት በልቶ ለማደር እየከበዳቸው ነው። አቶ ካሳሁን በዚህም ላይ ጥናት እንዲያደርጉ አቅጣጫ የተሰጣቸው ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች እንዳሉና ኢሰማኮ ጉዳዩን ከዳር ለማድረስ ግፊት እያደረገ እንደሆነ ጠቁመዋል።

#seed Seed ቀጥታ ወደ exchange claim ማድረግ አይኖርም እያሉ ነው። ቶኮናችን connect ወደ አደረግነው sui ዋሌት ይገባል ከዛ ወደ exchange መላክ እንችላለን። እንደዛ ከሆነ
#seed Seed ቀጥታ ወደ exchange claim ማድረግ አይኖርም እያሉ ነው። ቶኮናችን connect ወደ አደረግነው sui ዋሌት ይገባል ከዛ ወደ exchange መላክ እንችላለን። እንደዛ ከሆነ በርግጠኝነት ለfee sui ያስፈልጋል ማለት ነው። ለማንኛውም የበለጠ መረጃ ይፋ ያደርጋሉ እናያለን እስኪ ✌️

Blum TGE ከማርች 30 እስከ ጁን 20 ባሉት ቀናቶች እንደሚሆን ይፋ አድርገዋል ። ቀጣይ ሳምንት ሌላም መረጃ እንደሚያጋሩ ገልፀዋል
Blum TGE ከማርች 30 እስከ ጁን 20 ባሉት ቀናቶች እንደሚሆን ይፋ አድርገዋል ። ቀጣይ ሳምንት ሌላም መረጃ እንደሚያጋሩ ገልፀዋል

Seed በ Mexc ኤክስቼንጅ ኤፕሪል 1 ሊስት ይደረጋል
Seed በ Mexc ኤክስቼንጅ ኤፕሪል 1 ሊስት ይደረጋል

$SEED 3 CEX CONFIRMED LISTING! Kucoin BingX MEXC Seed is coming big
$SEED 3 CEX CONFIRMED LISTING! Kucoin BingX MEXC Seed is coming big

🌼ባል፦ከመሞቴ በፊት የምነግርሽ ነገር አለኝ 🌼ሚስት፦እንደዚህ ታመህ ምንም ማውራት የለብህም ዝም በል! 🌻ባል፦ተናግሬ ይውጣልኝ! ከእህትሽ ጋር አላስፈላጊ ግንኙነት ነበረኝ ፧ ፧ : 🌻ሚስት፦አውቃለሁ የኔ ማር የኔ ውድ ለዚህ ነው መርዝ ያበላሁህ🤣😂 የምን አይቶ ዝም ነዉ አይከፈልበት 😂

የድሮ የት/ት ቤት ጓደኛዬ መንገድ ላይ በቆሎ እየጠበሰ አይቼው ወደሱ ስሄድ ተደበቀብኝ። አላወቀም እንጂ እኔም ከሰል እየሸጥኩ ስለሆነ ከእኔ እንዲገዛ ልነግረው ነበር

የድሮ የት/ት ቤት ጓደኛዬ መንገድ ላይ በቆሎ እየጠበሰ አይቼው ወደሱ ስሄድ ተደበቀብኝ። አላወቀም እንጂ እኔም ከሰል እየሸጥኩ ስለሆነ ከእኔ እንዲገዛ ልነግረው ነበር