ASTU Network ®️
Open in Telegram
🛜 ASTU Network ®️ ➲ Join us || @ASTU_Network || || @ASTU_Network_Group || 📚 Library: @ASTU_Network_Library 👁🗨 We are here to keep you updated! ➲ Admin 📩 👤 @NS_Nazu Ⓝ Ŋazarene Ŝon [🥷] |➲| @ASTU_Network
Show more4 847
Subscribers
+824 hours
+557 days
+30230 days
Posts Archive
4 847
#Update
ሁሉም ዩኒቨርስቲዎች ማለት በሚቻል ደረጃ ከመስከረም 04-10/2018 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት ቀናት ለተማሪዎቻቸው ጥሪ እያደረጉ ነው።
ይህን ለየት የሚያደርገው ደግሞ የአዲስ አበባ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲም ጭምር የተማሪዎች መግቢያ ከመስከረም 08-09/2018 ዓ.ም እንደሆነ አስታውቋል።
ይህንን ሁሉ ስንመለከት ASTUም ቀድሞ ያወጣውን ካላንደር revise አድርጎ በተመሳሳይ ጊዜ (ከመስከረም 05-10/2018 ዓ.ም) ባለው ጊዜ ውስጥ ሊጠራ ይችላል የሚለው ጥርጣሬያችን ከፍ እንዲል አድርጓል።
ሆኖም ግን ከዩኒቨርስቲው የወጣ ይፋዊ ማስታወቂያም ሆነ መረጃ የለም። ለማንኛውም አሁን ላይ ዩኒቨርስቲዎች እየጠሩ ባሉበት ቀናት ለመውጣት ተዘጋጁ።
አዲስ ነገር ካለ ለማሳወቅ እንሞክራለን። እናንተም አዲስ ነገር ከሰማችሁ በግሩፓችን ላይ አሳውቁን።
|| @ASTU_Network
4 847
Repost from 𝐀𝐒𝐓𝐔 𝐄𝐧𝐭𝐞𝐫𝐭𝐚𝐢𝐧𝐦𝐞𝐧𝐭 ™️
አንድ ዜና ተሰማ 👇... 🌍🎓
የአዲስ አበባ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ያለምንም ሌላ መመዘኛ በያዙት ድግሪ ውጭ ሀገር ስራ ሊያገኙ ነው ተባለየ ASTU ተማሪዎች ምን አሉ❓ 👥: በሌላው ጊዜ "ASTU ይበልጣል... "ASTU ቀዳሚ ነው... ASTUን ሚደርስበት የለም" ሲሉ የነበሩ 👇 🗣 ምን አለበት ያኔ AASTU ብገባ ... ወይኔ እኔ!... ወይኔ በላቸው! 😁 👥: ቀለሜያንሱ 🧠🥸... 👇 🗣 ASTU reform ያስፈልገዋል ከላይ እስከ ታች 😤 👥: ASTUም international degree በቅርቡ መስጠት ይጀምራል ያሉ ተስፈኞች 👇 🗣 ለእኛም ቀን አለ 🤧 👥: አንዳንዶች 👇 🗣 እንዲህ ስትናገሩ አሁን ድግሪውን በትክክል አውቃችሁ ተምራችሁ አሜሪካ ሀገር የምትቀጠሩበት አይመስልም? 😁 👥: ሌሎች 👇 🗣 በ International degree ስራ አጥ መሆንንስ ማን አየበት... 😂 .
4 847
#MAGA
If all these problems are properly resolved and addressed, the old meaning of MAGA will no longer apply.
MAGA = Make America Great Again ❌
Instead, it will stand for the new MAGA:
MAGA = Make ASTU Great Again ☑️✊
😁
4 847
From: ASTU Students
To: The Administrators and Leadership of Adama Science and Technology University
Subject: Request for Improved Transparency and Responsiveness
Dear Esteemed Administrators and Leaders,
First and foremost, we would like to extend our warm greetings and appreciation.
As you know, ASTU is one of the two science and technology universities in Ethiopia. Over the years, it has played a vital role in educating and graduating students in applied and engineering fields, thereby producing skilled science and technology professionals for our country. We are proud to be part of this remarkable institution and its forward-looking vision.
Among the 12 principles of ethical service that guide our university, “Transparency” and “Responsiveness” are particularly important. We strongly believe that upholding all these principles, especially in communication and information-sharing, is essential for ASTU to excel as a leading science and technology university.
Unfortunately, we students are facing challenges in accessing timely and reliable information. Despite the presence of the university’s official website, we often struggle to obtain accurate updates. Three specific issues illustrate this concern:
1. Academic Calendar
The academic calendar is not published on the official website, leaving students uncertain and dependent on unofficial sources such as random groups. This creates confusion and affects our ability to plan and manage our studies effectively. We respectfully request that the academic calendar for the upcoming year be made available through official channels as soon as possible.
2. Cutoff Points
For most schools and departments, cutoff points are not officially announced. As a result, students rely on speculation rather than accurate data. Publicly sharing cutoff points is essential not only for current students but also for incoming batches who need clarity when selecting their desired schools or departments. We have observed that other universities provide detailed information, allow re-checking, and enable students to make informed choices—practices that we believe would greatly benefit ASTU as well.
3. Class Schedules
Although class schedules are posted on notice boards, students often struggle to keep up with the latest updates. There are more efficient ways to share this information. If an official website or channel were dedicated to posting class schedules for all students, it would allow timely access, reduce confusion, and save unnecessary effort and time.
Furthermore, when we seek clarification directly from offices, we often face unresponsiveness or, at times, are treated disrespectfully. This discourages us and leaves us without the answers we need. Such experiences undermine the principle of responsiveness and create unnecessary frustration.
We sincerely request that these issues be given due consideration. Ensuring transparency in information-sharing and responsiveness in student services will strengthen ASTU’s reputation, enhance student trust, and help the university achieve its vision.
Thank you for your attention to this matter. We remain proud of our university and hopeful that with your leadership, these concerns will be addressed promptly.
Respectfully,
ASTU Students
|| @ASTU_Network
4 847
#AASTU
የአዲስ አበባ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ያለምንም ሌላ መመዘኛ በያዙት ድግሪ ውጭ ሀገር ስራ ሊያገኙ ነው ተባለተማሪዎች ያላቸውን ድግሪ ተጠቅመው ያለምንም ሌላ መመዘኛ የውጭ ሀገር ስራ እንዲያገኙ ለማድረግ ዕውቅና ማግኘቱን የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ አስታወቀ። እውቀናውን አስመልክተው ጋዜጣዊ መግለጫ የሰጡት የዩኒቨርስቲው ፕሬዚዳንት ደረጃ እንግዳ (ዶ/ር)፤ ዩኒቨርሲቲው በአፕላይድ2 ሳይንስ የትምህርት ዘርፍ ማለትም በባይዮ ቴክኖሎጂ፣ በምግብ ሳይንስና በአመጋግብ ስረዓት፤ በኬሚካል ኢንዱስትሪና በጅኦሎጂ ዓለም አቀፍ ዕውቅና አግኝቷል ብለዋል። አክለውም ዩኒቨርሲቲው ያገኘው ዕውቅና በተለያዩ መርሃግብሮች የተመረቁ ተማሪዎች ያለምንምን መመዘኛ በውጭ ሀገራት ስራ እንዲያገኙ ያደርጋል ሲሉ ገልጸዋል። ከዚህ ቀደም ተማሪዎች የተመረቁበትን ድግሪ ይዘው በውጭ ሀገር ስራ መቀጠር አይችሉም ነበር ያሉት ፕሬዝዳንቱ፤ በሚቀጠሩበት ሀገር መመዘኛ መፈተን ግዴታ ነበር አሁን የተገኘው ዕውቅና ግን በድግሪያቸው ቀጥታ ስራ እንዲቀጠሩ የሚያደርግ ነው ሲሉ አስረድተዋል። አያይዘውም ዓለም አቀፍ ዕውቅና የተገኘባቸውን የትምህርት ፕሮግራሞች ለውጭ ተማሪዎች ለመስጠት እየተሰራ ነው ያሉ ሲሆን የውጭ ተማሪዎች መማራቸውም ለዩኒቨርሲቲው ተጨማሪ ገቢ ያስገኛል ሲሉ ገልጸዋል። በተጨማሪም ዕውቅናው ከጎርጎሮሳውያኑ 2023 ጀምሮ የተመረቁትን እንዳሚያጠቃልል ገልጸው በኢንጀሪንግ ትምህርት ዘጠኝ የትምህርት ፕሮግራሞች ዓለም አቀፍ እውቅና በቀጣይ ህዳር ወር ያገኛሉ ማለታቸውን የዘገበው ኢፕድ ነው። || @ASTU_Network
4 847
Hmm... 🤔😕
የኢፌዴሪ ትምህርት ሚኒስቴር የ2018 የትምህርት ዘመንን አካዳሚክ ካላንደር ይፋ ማድረጉ የሚታወስ ነው። በዚህም መሰረት የሁሉም የቅድመ እና የድህረ ምረቃ መደበኛ እና ኢ-መደበኛ ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርስቲ የሚገቡት ከመስከረም 05-10 ባለው ጊዜ ውስጥ ነው።
ዩኒቨርስቲያችን ASTU ባወጣው አካዳሚክ ካላንደር መሰረት ደግሞ ወደ ዩኒቨርስቲ የምንገባው መስከረም 21 ነው።
አሁን ላይ የተለያዩ የዩኒቨርስቲ ጥሪ ማስታወቂያዎችን ስንመለከት ዩኒቨርስቲዎች በብዛት በትምህርት ሚኒስቴር ካላንደር መሰረት እየጠሩ ይገኛሉ።
ከዚህ በፊት የዩኒቨርስቲያችን የተለመደው ስርዓት አንዴ ካላንደር ከወጣ በኋላ revise ይደረጋል። ነገርግን ለ2018 ተብሎ የወጣው ካላንደር እስካሁን revise አልተደረገም።
ስለዚህ በቀጣይ ሶስት ነገር ሊሆን ይችላል:-
1. ምናልባት ዩኒቨርስቲያችን ካላንደሩን revise አድርጎ በትምህርት ሚኒስቴር ካላንደር መሰረት ሊያደርገው ይችላል።
2. ካላንደሩ revise ተደርጎ ወደ ዩኒቨርስቲ የምንገባበት ቀን ተለውጦ ነገርግን በትምህርት ሚኒሰቴር ካላንደር መሰረት ያልሆነ ሊሆን ይችላል።
3. ዩኒቨርስቲው ምንም ካላንደሩን revise ሳያደርግ አንዴ ባወጣው ካላንደር መሰረት ሊቀጥል ይችላል።
በዚህ ጉዳይ ከዩኒቨርስቲው የተባለ ነገር ወይም የወጣ መረጃ የሌለ ሲሆን ፣ አዲስ ነገር ካለ ለማሳወቅ እንሞክራለን። እናንተም አዲስ ነገር ከሰማችሁ በግሩፓችን ላይ አሳውቁን።
እናመሰግናለን! 🙏
|| @ASTU_Network
4 847
#AASTU
አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ በአራት የአፕላይድ ሳይንስ የትምህርት ፕሮግራሞች ዓለም አቀፍ ዕውቅና አጊኝቷል።
ዩኒቨርሲቲው በባዮ-ቴክኖሎጂ፣ በምግብ ሳይንስና አመጋግብ ስርዓት፣ በኬሚካል ኢንዱስትሪ እንዲሁም በጅኦሎጂ ዓለም አቀፍ ዕውቅና ማግኘቱን የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ደረጃ እንግዳ (ዶ/ር) ተናግረዋል፡፡
ዓለም አቀፍ ዕውቅናው (Accreditation) በትምህርት መስኮቹ የተመረቁ ተማሪዎች 'ያለምንም' መመዘኛ በውጭ ሀገራት ሥራ እንዲያገኙ የሚያስችል መሆኑን ፕሬዝዳንቱ ገልፀዋል፡፡
ዓለም አቀፍ ዕውቅና የተገኘባቸውን የትምህርት ፕሮግራሞች ለውጭ ሀገራት ተማሪዎች ለመስጠት እየተሠራ መሆኑን የጠቆሙት ፕሬዝዳንቱ፤ ዕውቅናው እ.አ.አ ከ2023 ዓ.ም ጀምሮ የተመረቁትን እንደሚያጠቃልል አስረድተዋል።
ዩኒቨርሲቲው በዩናይትድ ስቴትስ ከሚገኘው Accreditation Board of Engineering and Technology (ABET) ተቋም ነው ዕውቅናውን ያገኘው፡፡
@tikvahuniversity
4 847
Repost from 𝐀𝐒𝐓𝐔 𝐄𝐧𝐭𝐞𝐫𝐭𝐚𝐢𝐧𝐦𝐞𝐧𝐭 ™️
The letter ‛h’ in the word “University” stands for happiness... 😁
React only if you get it... 😂😭
.
4 847
#TIN
የዚህ ነገር አጠቃላይ ሀሳቡ ምንድነው❓
👉 የወደፊት የግብር ስርዓት:
▬ ተማሪዎች ይማራሉ ፣ ይመረቃሉ ፣ ስራ ይይዛሉ ከዚያም ገንዘብ ያገኛሉ። TIN ሲኖራቸው ወደፊት የሚያገኙትን ገቢ በቀላሉ በማግኘት ግብር የመሰብሰብ ስራን ቀላል ያደርጋል።
👉 የፋይናንስ መለያ(ID):
▬ TIN በሀገሪቱ የፋይናንስ ስርዓት ውስጥ ልክ እንደ መለያ ቁጥር ያገለግላል። ይህም የባንክ አካውንት ሲከፈት ፣ ነፃ የትምህርት እድል ሲገኝ እንዲሁም ከመንግሥት ጋር የተገናኙ ስራዎችን በሀገሪቱ የመረጃ ቋት ለማደራጀት ያግዛል።
👉 ምዝገባ እና ቁጥጥር:
▬ መንግስት የዜጎችን (ተማሪዎችን ጨምሮ) አጠቃላይ መረጃ መያዝ ይፈልጋል። ይሄም ምን ያክል ተመራቂዎች ፣ ሰራተኞች እና እርዳታ የሚያስፈልጋቸው ዜጎች እንዳሉት ለማወቅ ይረዳዋል።
#ማጠቃለያ
👉 ተማሪዎች አሁን TIN ያስፈልጋቸዋል ማለት አሁን ግብር ይከፍላሉ ማለት አይደለም። ይልቁንስ መንግስት የዜጎቹን (የተማሪዎችን ጨምሮ) መረጃ ለመሰብሰብ ፣ ለመመዝገብ ፣ ለመለየት እና ለወደፊቱ አጠናቅሮ ለማዘጋጀት የሚጠቀመው መንገድ ነው።
👉 ኢትዮጵያ የተማሪዎች የወጪ መጋራትን (Cost Sharing) መልሰው የሚከፍሉበትን "Student loan system" እየተገበረች መሆኑን ማሳያ ነው።
👉 TIN ማውጣት ያስፈለገው የዩኒቨርስቲ ቆይታን የወጪ መጋራት (Cost Sharing) ልክ ግብር በ TIN እንደሚከፈለው ስለሚከፈል ነው።
👉 ተማሪዎች ተምረው ፣ ተመርቀው ፣ ስራ ይዘው ገንዘብ ማግኘት ሲጀምሩ መንግስት የ TIN ቁጥርን በመጠቀም የወጪ መጋራት (Cost Sharing) ክፍያን እና ግብርን በቀላሉ እንዲሰበስብ ይረዳዋል።
|| @ASTU_Network
4 847
የመንግሥት ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርሲቲ ሲሄዱ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (TIN) ይዘው እንዲሄዱ ገቢዎች ሚኒስቴር አሳሰበ።
የገቢዎች ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ወጪ መጋራት ክፍያ ለመሰብሰብ እያንዳንዱ የወጪ መጋራት ተጠቃሚ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (TIN) ማውጣት እንዳለበት አስታውሷል።
ሚኒስቴሩ የመንግሥት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት (ዩኒቨርሲቲዎች) አዲስ እና ነባር ተማሪዎች በሙሉ የፋይዳ ቁጥር በመያዝ በአካባቢያቸው በሚገኝ ገቢ ሰብሳቢ ተቋማት (ገቢዎች) ወይም ቢሮ በመቅረብ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (TIN) እንዲያወጡ ማሳሰቡን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከሚኒስቴሩ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
ተማሪዎቹ ወደ ዩኒቨርሲቲ በሚገቡበት ወቅት የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (TIN) ይዘው እንዲቀርቡ አስገንዝቧል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
#TikvahEthiopiaFamily
@tikvahethiopia
4 847
#ዜና
የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች የሚጠበቅባቸውን መሥፈርቶች ካላሟሉ አዳሪ ትምህርት ቤቶች ይደረጋሉ — ትምህርት ሚንስቴር
የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች የሚጠበቅባቸውን መሥፈርቶች ማሟላት ካልቻሉ ሰፋ ያለ ሁለተኛ ደረጃ አዳሪ ትምህርት ቤቶች የሚደረጉበት ሁኔታ ሊኖር እንደሚችል የትምህርት ሚንስትሩ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ አስታወቁ፡፡
ሚንስትሩ ይህን የተናገሩት ነሐሴ 19 ቀን 2017 ዓ.ም. በዳግም ምዝገባ አፈጻጸም ላይ የትምህርት ሚኒስቴርና የትምህርትና ሥልጠና ባለሥልጣን በጋራ ባዘጋጁት የውይይት መድረክ ላይ ነው።
ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ በወቅቱ ለትምህርት ጥራት ከፍተኛ ቦታ እየሰጡ መሄድ ያስፈልጋል በሚል ከግል ተቋማት ጋር ከአራት ዓመታት ጀምሮ እየተሠራ እንደሆነ፣ ዳግም ምዝገባን በተመለከተም ባለፉት ሦስት ዓመታት ስለመሥፈርቱ የማሳወቅ ሥራ ሲከናወንና የማያሟሉ በዘርፉ መቀጠል እንደማይችሉ ሲገለጽ መቆየቱን አንስተዋል።
አያይዘውም መሰል ግምገማ በመንግሥት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ላይም እንደሚደረግ ጠቅሰው በዚሁ አሠራር መሠረት ይዘጋሉ ብለው የሚታሰቡት የግሎቹ ብቻ ሳይሆኑ የመንግሥት ዩኒቨርስቲዎች ጭምር መሆናቸውን ጠቁመዋል።
|| @ASTU_Network
4 847
+1
#RIP
We are deeply saddened by the tragic passing of Firehiwot Getahun, a second-year pre-engineering student. Our hearts go out to her family, friends, and all who knew her. 💔
@Astupost
4 847
+2
የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አስፈላጊውን መስፈርት በማሟላት ዳግም ምዝገባ ሊያደርጉ ይገባል። - የትምህርት ሚኒስትር ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር)
ትምህርት ሚኒስቴር እና የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን በግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የዳግም ምዝገባ አፈጻጸም ሪፖርት ላይ ከትምህርት ተቋማቱ ጋር ውይይት አድርገዋል።
በአዲስ አበባ የሚገኙ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የዳግም ምዝገባ ውጤት በመድረኩ ይፋ ሆኗል።
በዳግም ምዝገባው የተቋማቱ የተሟላ ህጋዊ ሰነድ፣ የንግድ ፍቃድ፣ መተዳደሪያ ደንብ፣ የመምህራን ብቃት እና የሰው ኃይል፣ የሚያስተምሩበት ህንጻና አካባቢ፣ የመረጃ ዲጂታላይዜሽን እና ሌሎች መስፈርቶች መታየታቸው በመድረኩ ተነስቷል።
የትምህርት ተቋማቱ ዳግም ምዝገባ በማካሔድ የተቀመጡ መስፈርቶችን እንዲያሟሉ የትምህርት ሚኒስትር ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) አሳስበዋል።
ተመዝነው ብቃት የሌላቸው ተቋማት ጥናትን መሰረት በማድረግ ከትምህርት ስርዓቱ እንደሚወጡ ገልፀዋል።
የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማቱ ተገቢውን መስፈርት እንዲያሟሉ ተጨማሪ ጊዜ ተሰጥቷቸው መቆየቱን የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር አህመድ አብተው (ዶ/ር) አስታውሰዋል። በዚህም መሻሻል ያሳዩ ተቋማት መኖራቸውን ጠቁመዋል። የጥራት መስፈርት ያላሟሉት ላይ እርምጃ እየተወሰደ ነው ብለዋል።
በአዲስ አበባ በተካሄደው የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ዳግም ምዝገባ እና የጥራት መስፈርት ማረጋገጫ መሰረት፥ ውስን ተቋማት መስፈርቱን ማሟላታቸውን በባለሥልጣኑ የከፍተኛ ትምህርት ፍቃድ አሰጣጥ መሪ ስራ አስፈጻሚ ህይወት አሰፋ ገልፀዋል።
መስፈርቱን ያላሟሉ ተቋማት ከስድስት ወር እስከ አንድ ዓመት ባለው ጊዜ ውስጥ እንዲያሟሉ የጊዜ ገደብ እንደተሰጣቸው ተናግረዋል። #ኢዜአ
@tikvahuniversity
4 847
#ጥቆማ
በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ስር የሚገኘው የኢትዮጵያ ባለ ተሰጥኦና ተውህቦ ማበልጸግ ትምህርት ቤት በተለያዩ ዘርፎች የአጭር ጊዜ ስልጠና ለመስጠት ምዝገባ በማድረግ ላይ ይገኛል።
የስልጠና ዘርፎች፦
🌐 ዲጂታል እና ኢመርጂንግ ቴክኖሎጂ
🤖 ሮቦቲክስ እና ኤሌክትሮኒክስ
🛰️ አስትሮኖሚ እና የጠፈር ቴክኖሎጂ
🧬 ባዮቴክኖሎጂ
🔬 ስቴም
መስፈርቶች፦
➫ ዕድሜ ከ15-21
➫ በሳይንስ ወይም በፈጠራ ሀሳቦች የተሻለ አፈጻጸም ያለው
➫ ሀሳባቸውን ለመግለፅ የ3 ደቂቃ ቪዲዮ ማስገባት የሚችል/የምትችል
ምዝገባው የሚጠናቀቀው፦
ጳጉሜን 02/2017 ዓ.ም
ለመመዝገብ 👉 https://egate.et
ለተጨማሪ መረጃ፦
-0925 518 888 ወይም በኢሜል
mesay.hallemariam@mint.gov.et
@tikvahuniversity
4 847
In the first-ever brain scan research on ChatGPT users, scientists at MIT tracked cognitive activity over four months and discovered something unexpected: using AI might actually dull your brain, not sharpen it.
AI is a powerful tool, but how we use it matters. Use it intentionally as a thinking partner, not a replacement for your mind. Speed is great, but deep engagement and mental strength are what truly drive growth. MIT's early research is a powerful reminder that just because AI can think for us, doesn't mean it should.
4 847
ለወጣት ፈጠራ ባለሞያዎች የቀረበ የስልጠና ጥሪ
=============================
በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ስር የሚገኘው የኢትዮጵያ ባለ ተሰጥኦና ተውህቦ ማበልጸግ ትምህርት ቤት የአጭር ጊዜ የሥልጠና መርሃ ግብሮች በተለያዩ ዘርፎች አዘጋጅቶ በመመዝገብ ላይ ይገኛል።
👉 የስልጠና ዘርፎቹ
🌐 ዲጂታል እና ኢመርጂንግ ቴክኖሎጂ
🤖 ሮቦቲክስ እና ኤሌክትሮኒክስ
🛰️ አስትሮኖሚ እና የጠፈር ቴክኖሎጂ
🧬 ባዮቴክኖሎጂ
🔬 ስቴም
👉 ስልጠናውን ለመውሰድ ማን ማመልከት ይችላል?
✔️ እድሜ 15-21
✔️ በሳይንስ ወይም በፈጠራ ሀሳቦች የተሻለ አፈጻጸም ያለው
✔️ ሃሳባቸውን ለመግለጽ የ3 ደቂቃ ቪዲዮ ማስገባት የሚችል
👉 ምዝገባው የሚጠናቀቀው፡ ጷግሜ 2/2017/ ሴፕቴምበር 7፣ 2025
👉 የምዝገባው ሊንክ
👉 በስልጠናው ዙርያ ለጥያቄዎች ካሏችው፡-
📞 +251 925 518 888
📦mesay.hallemariam@mint.gov.et
ተሰጥኦና ተውህቦን ማበልጸግ የነገውን ትውልድ በመቅረጽ ውስጥ የማይተካ ድርሻ አለው!
4 847
+3
#ዜና_ቴክኖሎጂ
በአሜሪካ ላሞች ላይ የVR መነጽር በማድረግ ጭንቀታቸው እንዲቀንስ እየተደረገ ነው ተባለ
መነጽሩ አረንጓዴ ሜዳዎችን እንዲያዩና ብዙ ወተት እንዲያመርቱ ያግዛቸዋል ነው የተባለው
በአሜሪካ በሚገኙ አንዳንድ እርሻዎች ላሞች በረት ውስጥ ሆነው አረንጓዴ ሜዳዎችን እንዲያዩ የሚያስችላቸው የVR መነጽር እየተደረገላቸው ነው ተብሏል፡፡
የመነጸሩ ዋናው ዓላማ የላሞችን የጭንቀት መጠን በመቀነስና ምቾታቸውን በማሻሻል የወተት ምርታቸውን መጨመር ነው ተብሏል።
የVR መነጽሮቹ የሜዳማና ፀሐያማ አካባቢዎችን ምስሎች በማሳየት ላሞቹ ይበልጥ ዘና እንዲሉ ይረዳል የተባለ ሲሆን የመጀመሪያዎቹ የሙከራ ውጤቶችም በወተት ምርት ላይ እንዲሁም በባህሪያቸው ላይ ትንሽ ቢሆንም የሚታይ ለውጥ አሳይተዋል ተብሏል ያለው መናኸሪያ ነው።
|| @ASTU_Network
4 847
Repost from 𝐀𝐒𝐓𝐔 𝐄𝐧𝐭𝐞𝐫𝐭𝐚𝐢𝐧𝐦𝐞𝐧𝐭 ™️
#Life 🙂 #ዳሰሳ 🎓
👉 ትምህርት ሚኒስቴር ከተወሰኑ አመታት በፊት “ተማሪዎችን ለማጣራት እና አቅማቸውን ለመመዘን” በሚል ከጨመረው የፍሬሽማን የትምህርት አመት በተጨማሪ ፣ “ተማሪዎች ማህበረሰቡን ቀርበው አገልግለው የተግባር ትምህርት የሚወስዱበት ጊዜ ያስፈልጋል” በሚል በተማሪዎች የዩኒቨርስቲ ቆይታ ላይ አንድ ተጨማሪ አመት መጨመሩ የሚታወስ ነው።
👉 ይህም ተማሪዎች ለመመረቅ አንድ አመት ሲቀራቸው የሚደረግ ነው ፤ ማለትም አራት አመት የሚማሩ ተማሪዎች የሶስተኛ አመት ትምህርታቸውን እንዳጠናቀቁ ወደ አራተኛው አመት ሳይገቡ በፊት ፣ እንዲሁም አምስት አመት የሚማሩ ተማሪዎች የአራተኛ አመት ትምህርታቸው እንዳጠናቀቁ ወደ አምስተኛው አመት ሳይገቡ በፊት ማለት ነው። በዚህም ምክንያት አራት አመት ሲማሩ የነበሩ ተማሪዎች በአጠቃላይ የዩኒቨርስቲ ትምህርታቸውን የሚያጠናቅቁት በአምስት አመት ሲሆን ፣ አምስት አመት ሲማሩ የነበሩት ደግሞ በስድስት አመት ትምህርታቸውን ያጠናቅቃሉ ማለት ነው።
👉 እንደሚታወቀው ደግሞ በዩኒቨርስቲያችን ያሉት አብዛኛዎቹ ተማሪዎች የኢንጂነሪንግ ተማሪዎች ስለሆኑ ዩኒቨርስቲ ከገቡበት እስከሚመረቁበት ድረስ ስድስት አመት ይፈጃል ማለት ነው።
👉 አንድ ተማሪ ዩኒቨርስቲ ሲገባ እና ሲመረቅ የሚኖረውን እድሜ እንመልከት 👇
ዩኒቨርስቲ ሲገባ ➕ ሲመረቅ 🎓
*18 18+6 24
*19 19+6 25
*20 20+6 26
*21 21+6 27
*22 22+6 28
👉 በአማካይ አንድ ተማሪ በ 25 አመቱ ነው ተመርቆ ከግቢ የሚወጣው ማለት ነው። በእርግጥ ከዚያ በኋላ ያሉት እንደ የግል ህይወት ፣ ፍላጎት ፣ ህልም፣ ስራ ፣ ገንዘብ ማግኘት ፣ መለወጥ ፣ የቤተሰብ ጫና እና የመሳሰሉት ሌሎች ነገሮች ለሁሉም ሰው የተለያዩ ቢሆኑም ፣ ነገርግን አንድ የማይካድ እውነት አለ ፣ እሱም «ተመራቂዎች በሙሉ ጊዜያቸው እና አቅማቸው ስራ መስራት የሚጀምሩት አርፍደው መሆኑ» ነው!
ይሄ NORMAL አይደለም‼️
ምን ታስባላችሁ❓🤔
.
Available now! Telegram Research 2025 — the year's key insights 
