en
Feedback
ASTU Network ®️

ASTU Network ®️

Open in Telegram

🛜 ASTU Network ®️ ➲ Join us || @ASTU_Network || || @ASTU_Network_Group || 📚 Library: @ASTU_Network_Library 👁‍🗨 We are here to keep you updated! ➲ Admin 📩 👤 @NS_Nazu Ⓝ Ŋazarene Ŝon [🥷] |➲| @ASTU_Network

Show more
4 847
Subscribers
+824 hours
+587 days
+31330 days
Posts Archive
ሰላም ቤተሰብ 👋 እነሆ እረፍት እየተገባደደ በመሆኑ ምን ይሰማችኋል❓🤔😁 .

Ethiopian Airlines-Results.PDF14.91 MB

DO NOT MISS THIS CHANCE!     የLinkedIn አካውንቶ ገንዘብ መስራት እንደሚችልያውቃሉ። ክፍያዎትን ባንክ ሆነ በባይናንስ መቀበል ይችላሉ። እኛ ጋር ሲመጡ   •100-299 connections: $7 በየሳምንቱ   • 300-499 connections: $12 በየሳምንቱ   • 500-999 connections: $14 በየሳምንቱ   • 1000-1999 connections: $19 በየሳምንቱ   • 2000+ connections: $24 በየሳምንቱ super deal for only 3 first comers 💯💯💯. ⛑⛑⛑ 50+ $7 100+ $8 300+ $15 500+ $20 1000+ $25 2000+ $30 🚨 አካውንቱ ከአንድ አመት በላይ ያገለገለ መሆን አለበት። 🚨Password በጭራሽ አይቀየርም። 🚨 በፈለጉበት ሰዓት አካውንቶን መልሰው መውሰድ ይችላሉ። 📌 Your Account is Used Only for Business Networking ለተጨማሪ መረጃ 👉 @Lali88 https://t.me/linkedinrentalservice0 join fast

የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሙሉ ለሙሉ ወደ ተመደቡበት የተልዕኮ መስክ ይገባሉ — ትምህርት ሚኒስቴር የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ኮራ ጦሽኔ (ዶ/ር) እንደተናገሩት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ካለፈው ዓ
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሙሉ ለሙሉ ወደ ተመደቡበት የተልዕኮ መስክ ይገባሉ — ትምህርት ሚኒስቴር የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ኮራ ጦሽኔ (ዶ/ር) እንደተናገሩት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ካለፈው ዓመት ጀምሮ በተመደቡባቸው የአጠቃላይ የተግባር እና የምርምር መስኮች ገብተዋል፡፡ በተለያየ ደረጃ ቢሆንም ሁሉም የከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ወደ ተልዕኮ መስካቸው መግባታቸውን ገልጸው ÷ ዩኒቨርሲቲዎች ሙሉ ለሙሉ ወደ ተልዕኮ መስካቸው እንዲገቡ እየተሰራ ነው ብለዋል። ዩኒቨርሲቲዎችን በተልዕኮ መስክ መለየት ክህሎት ያለው የሰው ሀይል ለማፍራት ይሰራል ነው ያሉት። ኢንዱስትሪዎች ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በመምጣት ለተማሪዎች ስልጠና እንዲሰጡ እና  ስታርትአፖች እንዲፈጠሩ የሚደረግ መሆኑንም አመልክተዋል። በአሁኑ ወቅት የትምህርት ፕሮግራሞችን እና የሰው ሀይል ክለሳ እየተካሄደ መሆኑንም ጠቅሰው፤ የሚታጠፉ ወይም አዲስ የሚጀመሩ የትምህርት ፕሮግራሞች ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል፡፡ በ2021 ዓ.ም ሙሉ በሙሉ ራስ ገዝ የምርምር ዩኒቨርሲቲ ለመሆን ህጎች እና የሰነድ ዝግጅት እየተደረገ ነው ብለዋል። በአፕላይድ ሳይንስ ዘርፍ የተለየው የአርሲ ዩኒቨርሲቲ አካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዚዳንት በበኩላቸው÷  ዩኒቨርሲቲው በግብርና፣ በቴክኖሎጂ፣ በኢንጂነሪንግ እንዲሁም ጤና ላይ ይሰራል ነው ያሉት። የትምህርት ፕሮግራሞች ክለሳ እየተካሄደ መሆኑን ገልጸው፤ ከንድፈ ሀሳብ በዘለለ ተግባር ተኮር ትምህርቶች ላይ ሰፊ ትኩረት መሰጠቱን ጠቅሰዋል፡፡ ተማሪዎች በኢንተርንሽፕ እና በኤክስተርንሽፕ በኢንዱስትሪዎች እንዲለማመዱ ከ44 ኢንዱስትሪዎች ጋር ስምምነት ተደርጓል ብለዋል። || @ASTU_Network

ሁለት የአሜሪካ ሴናተሮች በግዙፉ ድርጅት ሜታ መተግበሪያዎች ላይ ምርመራ እንዲጀመር ጠየቁ። እንደ ዋትስአፕ፣ ፌስቡክ እና ኢንስታግራም ያሉ መተግበሪያዎችን በባለቤትነት የሚያስተዳድረው ሜታ ከሰሞኑ የ
ሁለት የአሜሪካ ሴናተሮች በግዙፉ ድርጅት ሜታ መተግበሪያዎች ላይ ምርመራ እንዲጀመር ጠየቁ። እንደ ዋትስአፕ፣ ፌስቡክ እና ኢንስታግራም ያሉ መተግበሪያዎችን በባለቤትነት የሚያስተዳድረው ሜታ ከሰሞኑ የድርጅቱ የሰው ሰራሽ አስተውህሎት ፖሊሲ ቻትቦቶች ህፃናትን በፍቅር እና ስሜታዊ መንገድ እንዲያወሩ ይፈቅዳል የሚል የውስጥ ፖሊሲ ሰነድ  ይፋ ከሆነ በኋላ መነጋገሪያ ሆኗል። በሪፖርቱ ቲሸርት አላደረገም ለተባለ የ8 አመት ህፃን ቻትቦቱ ሁለመናህ ቆንጆ እና የሚወደድ ነው የሚል ምላሽ እንደሰጠው ተዘግቧል። ሜታም የዶክመንቱን ትክክለኛነት አረጋግጦ በዚህ ወር በዚሁ ጉዳይ ላይ ከሮይተርስ ጥያቄ ከቀረበለት በኋላ ቻትቦቶቹ ህፃናትን እንዲያማልሉ እና በፍቅር እንዲያወሩ የሚፈቅደውን ሐረግ መሰረዙን ገልጿል። የአሜሪካ ሴናተሮች ዶክመንቱ በይፋ ከተሰራጨ በኋላ ነው ሜታ የሰረዘው ሲሉ ኮንግረሱ በአስቸኳይ ምርመራ እንዲጀምርበት ጠይቀዋል። ሴናተሩች ሜታ ውድ ልጆቻችን በመጠበቅ አንፃር ደካማ ነው ብለዋል። አሜሪካ የሰው ሰራሽ አስተውህሎትን የሚቆጣጠር የፌደራል ህግ የላትም ሲባል ግዛቶቿ ግን የየራሳቸውን ህግ አውጥተው ልጆች ወሲባዊ ነገሮችን ከሚፈጥሩ ቴክኖሎጂዎች እንዲርቁ ያደርጋሉ ተብሏል። የሰው ልጅ ከሰው ሰራሽ አስተውህሎት መተግበሪያዎች ጋር ያለው ግንኙነት እየጨመረ ሲሆን ከወሲባዊ ንግግሮች በተጨማሪ አንዳንድ መተግበሪያዎች ሰዎች ከመተግበሪያው ጋር ያላቸውን ንግግር ሲጨርሱ አትውጣ፤ ላንተ ብቻ ነው ያለሁት እንደዚሁም የምንግርህ ነገር አለኝ እያሉ እንዲቆዩ እንደሚያደርጉ የሃርቫርድ ቢዝነስ ትምህርት ቤት  አረጋግጧል። በሃርቫርድ ጥናት ሰዎች አቋርጠው ሊወጡ ሲሉ እንደዚህ አይነት መልዕክት ሲደርሳቸው በ14 እጥፍ የተሻለ ጊዜ ይቆያሉ ተብሏል። የሰው ሰራሽ አስተውህሎት መተግበሪያዎች ሰዎችን ከመጥቀም ባለፈ በተለይ ህፃናት ላይ የማይሆኑ ምስሎችን በመፍጠር ለአልባሌ ነገር እንደሚዳርጉ በርካታ ዘገባዎች ሲሰሩ ቆይተዋል። በዘመኑ ሁሉም ኢንተርኔት ተጠቃሚ ማለት በሚቻል መልኩ ከሰው ሰራሽ አስተውህሎት መተግበሪያ ጋር ንግግር የሚያደርግ ሲሆን የመተግበሪያዎቹን አሰራር እና ፖሊሲ ከመረዳት አንፃር ግን ክፍተቶች ይታያሉ። እኛስ እንደ ግለሰብ እና ማህበረሰብ እነዚህን ፖሊሲዎች ከመረዳት እንደዚሁም መተግበሪያዎቹ የሚፈጥሩትን ጥፋት ከመገንዘብ አንፃር ምን ያህል ዝግጁ ነን የሚለው ሁላችንም እራሳችንን የምንጠይቀው ጥያቄ መሆን ይገባዋል። Source: FORBES, THE MANILA TIMES @TikvahethMagazine

🛩 #Result_announcement Result announcement for Ethiopian Airline different job possition applicants. ♦️You can find your nam
🛩 #Result_announcement
Result announcement for Ethiopian Airline different job possition applicants.
♦️You can find your name if you passed this phase screening. Please visit the | link | @AAUNEWS1

#MoE ትምህርት ሚኒስቴር የ2018 ትምህርት ዘመን የከፍተኛ ትምህርት አካዳሚክ ካላንደርን ይፋ አድርጓል፡፡ በትምህርት ሚኒስትር ዲኤታ ኮራ ጡሹኔ በቀን ነሐሴ 12/2017 ዓ.ም የተፈረመ የ2018
+3
#MoE ትምህርት ሚኒስቴር የ2018 ትምህርት ዘመን የከፍተኛ ትምህርት አካዳሚክ ካላንደርን ይፋ አድርጓል፡፡ በትምህርት ሚኒስትር ዲኤታ ኮራ ጡሹኔ በቀን ነሐሴ 12/2017 ዓ.ም የተፈረመ የ2018 ትምህርት ዘመን የከፍተኛ ትምህርት አካዳሚክ ካላንደር ዝርዝር ለሁሉም ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተልኳል፡፡ መስከረም 05-06/2018 ዓ.ም የመጀመሪያ ዓመት የቅድመ ምረቃ ተማሪዎች (ሪሚዲያል ተማሪዎችን ጨምሮ) በየተመደቡበት ዩኒቨርሲቲ ሪፖርት ያደርጋሉ፡፡ መስከረም 08-09/2018 ዓ.ም ➫ የሁሉም የቅድመ እና የድኅረ ምረቃ መደበኛ እና ኢ-መደበኛ ተማሪዎች (ሪሚዲያል ተማሪዎችን ጨምሮ) ምዝገባ ያደርጋሉ፡፡ መስከረም 12/2018 ዓ.ም ➫ የሁሉም የቅድመ እና የድኅረ ምረቃ መደበኛ እና ኢ-መደበኛ ተማሪዎች በቅጣት ምዝገባ፣ የ2018 ዓ.ም የመጀመሪያ ሴሚስተር ትምህርት ይጀመራል፡፡ (ሙሉ የ2018 ትምህርት ዘመን የከፍተኛ ትምህርት አካዳሚክ ካላንደር ከላይ ተያይዟል፡፡) @tikvahuniversity

#MoE ትምህርት ሚኒስቴር ተቀራራቢ ይዘት ባላቸው የከፍተኛ ትምህርት ፕሮግራሞች ስያሜ እና ስርዓተ ትምህርት ላይ ክለሳ በማድረግ ወደ ትግበራ ገብቷል። ሚኒስቴሩ ከሰኔ 2014 ዓ.ም እስከ ግንቦት 2
+4
#MoE ትምህርት ሚኒስቴር ተቀራራቢ ይዘት ባላቸው የከፍተኛ ትምህርት ፕሮግራሞች ስያሜ እና ስርዓተ ትምህርት ላይ ክለሳ በማድረግ ወደ ትግበራ ገብቷል። ሚኒስቴሩ ከሰኔ 2014 ዓ.ም እስከ ግንቦት 2017 ዓ.ም ድረስ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚሰጡ ተቀራራቢ ይዘት እና ስያሜ የነበራቸው ፕሮግራሞችን በመለየት ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች እና ኢንዱስትሪዎች ከተውጣጡ የዘርፉ ባለሙያዎች ጋር በመሆን በፕሮግራሞቹ ስያሜ እና ስርዓተ ትምህርት ላይ ማስተካከያ አድርጓል፡፡ ተቀራራብ ይዘት ያላቸው ፕሮግራሞችን በማጠፍ/በማዋሃድ አዳዲስ የፕሮግራሞች ስያሜዎች መሰጠቱን በአካዳሚክ ጉዳዮች ዋና ስራ አስፈፃሚ ኤባ ሚጀና (ዶ/ር) ተፈርሞ ለሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች የተላከው ደብዳቤ ያሳያል። በዚህም 147 ፕሮግራሞችን ወደ 54 በመጠቅለል አዳዲስ የፕሮግራሞች ስያሜ መሠጠቱ ተገልጿል። በተወሰኑ ፕሮግራሞች ላይ ማስተካከያ የተደረጉ ሲሆን የታጠፉ ፕሮግራሞች እንዳሉም ለማወቅ ተችሏል። ይህም በሁሉም ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተግባራዊ እንዲደረግ ሚኒስቴሩ አሳስቧል። (የፕሮግራሞቹ ዝርዝር ከላይ ተያይዟል።) @tikvahuniversity

#AI 🤖 25 AI Tools You Can’t Ignore in 2025 1. ChatGPT.com – solves anything 2. Syllaby.io – create and publish videos 3. MidJourney.com – generates art 4. Replit.com – writes and runs code 5. Heygen.com – creates AI avatars 6. Soundraw.io – produces music in seconds 7. Ranked.ai – rank higher on Google 8. Submagic.co – turn long videos into shorts 9. SlidesAI.io – makes presentations for you 10. PicWish.com – edits photos fast 11. Fastread.io - create ebooks 12. Bibley.io - ai for Bible study 13. Manus.im - code any app 14. Capsho.com - podcast into content 15. Webinarkit.com - ai for webinars 16. Creatorunlock.com - ai for YouTube 17. sociable.how - write viral comments 18. Adcreative.ai - ai tool for advertising 19. Canva.com - design anything 20. Fastphoto.io - create ai headshots 21. askcoachken.com - ai relationship coach 22. threadmaster.ai - create viral Facebook thread 23. V0.dev - create frontend mockups 24. suno.com - create ai music 25. keywordsearch.com - boost ad conversions || @ASTU_Network

DO NOT MISS THIS CHANCE!     የLinkedIn አካውንቶ ገንዘብ መስራት እንደሚችልያውቃሉ። ክፍያዎትን ባንክ ሆነ በባይናንስ መቀበል ይችላሉ። እኛ ጋር ሲመጡ   •100-299 connections: $7 በየሳምንቱ   • 300-499 connections: $12 በየሳምንቱ   • 500-999 connections: $14 በየሳምንቱ   • 1000-1999 connections: $19 በየሳምንቱ   • 2000+ connections: $24 በየሳምንቱ super deal for only 3 first comers 💯💯💯. ⛑⛑⛑ 50+ $7 100+ $8 300+ $15 500+ $20 1000+ $25 2000+ $30 🚨 አካውንቱ ከአንድ አመት በላይ ያገለገለ መሆን አለበት። 🚨Password በጭራሽ አይቀየርም። 🚨 በፈለጉበት ሰዓት አካውንቶን መልሰው መውሰድ ይችላሉ። 📌 Your Account is Used Only for Business Networking ለተጨማሪ መረጃ 👉 @Lali88 https://t.me/linkedinrentalservice0 join fast

photo content
+4

photo content
+4

photo content
+4

#Telegram's12thAnniversary ❝Telegram turns 12 today!❞ — Pavel Durov, Founder and CEO of Telegram .

#AI 🤖 Best AI Tools You Have to Know 1. ChatGPT.com → Solve anything 2. LightPDF.com → Chat with files 3. Tome.app → Build presentations 4. Pika.art → Create videos 5. Gamma.app → Design docs 6. Suno.ai → Make music 7. PicWish.com → Image editing 8. Perplexity.ai → Research assistant 9. Krea.ai → Logo design 10. Fliki.ai → Voiceovers 11. Runway.ml → Film editing 12. Relume.io → Web design 13. Descript.com → Edit audio 14. ElevenLabs.io → Clone voices ➕ Join us 👇 || @ASTU_Network

#MoE የመውጫ ፈተና መሰጠት ከተጀመረ ወዲህ ትምህርታቸውን ላጠናቀቁ፥ የዲግሪ ህትመት የሚዘጋጀው የመውጫ ፈተናውን ላለፉ ተማሪዎች ብቻ እንደሆነ ትምህርት ሚኒስቴር አሳወቀ፡፡ ሚኒስቴሩ የዲግሪ ህትመ
+1
#MoE የመውጫ ፈተና መሰጠት ከተጀመረ ወዲህ ትምህርታቸውን ላጠናቀቁ፥ የዲግሪ ህትመት የሚዘጋጀው የመውጫ ፈተናውን ላለፉ ተማሪዎች ብቻ እንደሆነ ትምህርት ሚኒስቴር አሳወቀ፡፡ ሚኒስቴሩ የዲግሪ ህትመትን የተመለከተና በሚኒስትር ዲኤታ ኮራ ጡሹኔ በቀን ነሐሴ 06/2017 ዓ.ም የተፈረመ ደብዳቤ ለሁሉም የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች እና የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ልኳል፡፡  በዚህም የዲግሪ ማስረጃ ወይም ሰርተፊኬት ህትመት በሀገር አቀፍ ደረጃ በማዕከል የሚታተም መሆኑን መጋቢት 02/2017 ዓ.ም ለሁሉም የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች እና የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በላከው ደብዳቤ ማሳወቁን አስታውሷል፡፡  ከ2017 ዓ.ም ጀምሮ ለተመረቁ እና ከዚህ በፊት ተመርቀው መረጃውን ያልወሰዱ ከተመረቁ ጊዜ ጀምሮ ህትመቱ በማዕከል ተከናውኖ በዩኒቨርሲቲው ወይም በተቋሙ በኩል የሚሠራ ወይም የሚሰጥ መሆኑን ገልጿል፡፡ በመሆኑም ከፍተኛ ትምህርት ተቋሙ ሊሠራለት የሚገባውን የሰርተፍኬት ይዘት (በውስጡ የሚገለፁ ይዘቶችን፣ ሎጎዎች እና ተጨማሪ መብት ያላቸው ጉዳዮች) በማካተት እጅግ ቢዘገይ እስከ ሐሙስ ነሐሴ 08/2017 ዓ.ም ባሉት ቀናት ውስጥ እንዲያሳውቁ አሳስቧል፡፡ የመውጫ ፈተና መሰጠት ከተጀመረ ወዲህ ያለው ህትመት የሚዘጋጀው፣ የመውጫ ፈተናውን ላለፉ ተማሪዎች ብቻ መሆኑን ጠቁሟል፡፡ (ከትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን ያገኘነው ደብዳቤ ከላይ ተያይዟል፡፡) @tikvahuniversity

#MoE በኃላፊነት ላይ ያለ የመንግስት ሹመኛ ወይም ተመራጭ ለ #ክብር_ዶክትሬት እንዳይታጭ የሚከለክል መመሪያ የትምህርት ሚኒስቴር አወጣ፡፡ መመሪያው 8 ዙር ተማሪዎችን ያላስመረቁ እና ሶስተኛ ዲግሪ
+1
#MoE በኃላፊነት ላይ ያለ የመንግስት ሹመኛ ወይም ተመራጭ ለ #ክብር_ዶክትሬት እንዳይታጭ የሚከለክል መመሪያ የትምህርት ሚኒስቴር አወጣ፡፡ መመሪያው 8 ዙር ተማሪዎችን ያላስመረቁ እና ሶስተኛ ዲግሪ ወይም (PhD) የማያስተምሩ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የክብር ዶክትሬት እንዳይሰጡ ይከለክላል፡፡ በትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ሃምሌ 15 ቀን 2017 ዓ.ም ተፈርሞ ለሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት የተመራው ይህ መመሪያ በቅርብ ጊዜ የተመሰረቱ የትምህርት ተቋማት የክብር ዶክትሬት እንዳይሰጡ ይከለክላል፡፡ በመመሪያው ክፍል ሁለት ላይ የክብር ዶክትሬት የሚሰጡ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት መስፈርትን በተመለከተ የተቀመጠው ድንጋጌ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የክብር ዶክትሬት ለመስጠት ቢያንስ ከ8 ጊዜ በላይ ተማሪዎችን ያስመረቁ እና የሶስተኛ ዲግሪ የሚሰጡ መሆን እንዳለባቸው ያስገድዳል፡፡ በዚህም መሰረት ሰላሌ፣ ደምቢ ዶሎ፣ መቅደላ አምባ፣ ራያ፣ ደባርቅ እና መሰል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ስምንት ዙር ተማሪዎችን ስላላስመረቁ በመመሪያው መሰረት የክብር ዶክትሬት መሰጠት አይችሉም፡፡ በዚሁ ክፍል ስር ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የክብር ዶክትሬት ማዕረግ ለመስጠት አገር እና አለም አቀፍ መስፈርቶችን ማሟላት እንዳለባቸው ሰፍሯል፡፡ በሞያ መስኩ የተለየ ስራ ያበረከተ ከሆነ ኢትዮጵያዊም ሆነ ሌላ ዜጋ የክብር ዶክትሬት ማዓረግ ማግኘት እንደሚችል የዘረዘረው መመሪያው መስፍርቱን ካሟሉ ለግለሰብም ይሁን ለቡድን መስጠት እንደሚቻል አመላክቷል፡፡ በሕይወት ላለም ይሁን ለሌለ ሰው ማዕረጉን መስጠት እንደሚቻል የሚፈቅደው ይህ መመሪያው የክብር ዶክትሬት ለማግኘት የማይቻልባቸውን ገደቦችም በክፍል ሁለት አንቀጽ 10 ስር ዘርዝሯል፡፡ በዚህም መሰረት የከፍተኛ ትምህርት ተቋሙ የሙሉ ሰዓት ተቀጣሪ ሰራተኛ፣ የሴኔት አባላት ወይም የአስተዳደር አካላት ከተቋሙ ጋር ያላቸው ቀጥተኛ ግንኙነት እስካላበቃ ድረስ ለክብር ዶክትሬት መታጨት እንደማይችሉ ደንግጓል፡፡ መመሪያው በስራ ላይ ያሉ የመንግስት ሹሞች ወይም ባለስልጣናት ለክብር ዶክትሬት እንዳይታጩም የሚከለክል ነው፡፡ የክብር ዶክትሬት የተሰጠው ግለሰብ ዶክተር፣ የክብር ዶክተር እና መሰል መጠሪያዎችን ከሰጪው ተቋም ውጪ በየትኛውም ድርጅት ውስጥ መጠቀም እንደማይችሉም ደንግጓል፡፡ የትምህርት ሚኒስቴር በለፈው ዓመት በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በሽምያ የሚሰጡ የክብር ዶክትሬት ማዕረጎች መመሪያ እስኪወጣ ድረስ እንዲያቆሙ ማዘዙ ይታወሳል፡፡ መረጃው የሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ሬድዮ ጣቢያ ነው። @tikvahethiopia

" ዩኒቨርሲቲዎች ስለተማሪዎቻቸውና ስለሚሠሩት ሥራ ትክክለኛ መረጃ ስጡን ብለን ከጠየቅን ሦስት ዓመት አልፎናል፡፡ ሆኖም እስካሁን የተሟላ መረጃ ለማግኘት ችግር ሆኖብናል፡፡ በዩኒቨርሲቲዎች ዘንድ እው
+1
" ዩኒቨርሲቲዎች ስለተማሪዎቻቸውና ስለሚሠሩት ሥራ ትክክለኛ መረጃ ስጡን ብለን ከጠየቅን ሦስት ዓመት አልፎናል፡፡ ሆኖም እስካሁን የተሟላ መረጃ ለማግኘት ችግር ሆኖብናል፡፡ በዩኒቨርሲቲዎች ዘንድ እውነተኛ መረጃ መስጠት አልተለመደም፡፡ ባለፈው ዓመት ከተማሪዎች ምገባ ጋር ተያይዞ የውሸት ሪፖርት ሲቀርብ ነበር፡፡ ዩኒቨርሲቲዎች የተማሪ ቁጥር በውሸት በመጨመር በጀት እንዲጨመርላቸው ያደርጉ ነበር። ዩኒቨርሲቲዎች አሉን የሚሏቸውን የተማሪዎች መረጃ ከእነፎቷቸው አምጡ ስንል ግን፣ አሉን ብለው ካስመዘገቧቸው ተማሪዎች 251 ሺህ ያህሉ የት እንደገቡ አያውቁም፥ ለማምጣትም አልቻሉም፡፡ አንድ ዕውቀት ላይ እሠራለሁ የሚል ተቋም በዚህ ደረጃ ላይ የሚገኝ ከሆነና እውነተኛ መረጃ መስጠት የማይፈልግ ከሆነ፣ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እንዲመጣ የምንፈልገውን ለውጥ አዝጋሚ ያደርገዋል። " - የትምህርት ሚኒስትር ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) የዩኒቨርሲቲዎች መረጃ አሰጣጥን በተመለከተ የተናገሩት፦ Via @tikvahuniversity

ውሃችንን የሚሻማን አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ እያንዳንዱ ከChatGpt ጋር በምናደርጋቸው ንግግሮች መተግበሪያው መልስ ለመስጠት የማንኪያን 1/15 ውሃ ወይም 0.32 ሚሊ ሊትር ውሃን ይጠቀማል። እንደ
ውሃችንን የሚሻማን አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ እያንዳንዱ ከChatGpt ጋር በምናደርጋቸው ንግግሮች መተግበሪያው መልስ ለመስጠት የማንኪያን 1/15 ውሃ ወይም 0.32 ሚሊ ሊትር ውሃን ይጠቀማል። እንደ OpenAI ዋና ስራ አስፈፃሚው ሳም ኦልትማን ከሆነ ወደ ChatGpt ብቻ በየቀኑ ከ1 ቢሊየን በላይ መልዕክቶች ይላካሉ። ከአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ መተግበሪያዎች በምናደርጋቸው 10 የመልዕክት ልውውጦችም መተግበሪያዎቹ ምላሽ ለመስጠት እስከ 500 ሚሊ ሊትር ውሃ መተግበሪያዎቹ ይጠቀማሉ። ጥያቄዎችን ስንጠይቅ መተግበሪያዎቹ ምላሽ ለመስጠት ሲያስቡ በመረጃ ማዕከላት የሚኖርን ሙቀት ለማቀዝቀዝ ውሃን ይጠቀማሉ። ከዚህ በተጨማሪ የመረጃ ማዕከላቱ ለመስራት የኤሌክትሪክ ኃይል ሲፈልጉ በ2030 አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ላይ የሚሰሩ ማዕከላት የሚያስፈልጋቸው ኃይል 300 ቴራዋት ሰዓት ይሆናል ተብሎ ይገመታል፤ ይህም የዩናይትድ ኪንግደም አመታዊ የኤሌክትሪክ ፍጆታ ነው። ትናንሽ የመረጃ ማዕከላት ብቻ በቀን 1000 አባወራዎች ሊጠቀሙ የሚችሉትን ያህል ውሃ እንደሚጠቀሙ ይገመታል። አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ከሚሰጠን ጥቅም በተጨማሪ ለተለያዩ አገልግሎት ሊውል የሚችልን ውሃ እየተጋራን ይገኛል። አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ለምን እና እንዴት ይህን ያህል ውሃ እንደሚጠቀም ከነዚህ ቪዲዮዎች ይመልከቱ። ቢቢሲ- How AI uses our drinking water አልጄዚራ- Could thirsty AI worsen the water crisis? @TikvahethMagazine

#Job_Vacancy 💼 ✨ የኢትዮጲያ አየር መንገድ በ0 አመት ልምድ ስራ ማውጣቱ የሚታወስ ነው ✅ የሥራ መደብ 1፦ Trainee Cabin Crew ➤ ተፈላጊ የትምህርት ደረጃ፦ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ሰርተፊኬት ቢያንስ 200 ውጤት ያለው/ያላት ➤ ዕድሜ፦  ከ 21-30 ➤ ቁመት፦  1.58ሜ እና በላይ ለሴት ፤ 1.70ሜ እና በላይ ለወንድ ➤ ክብደት፦ ከቁመት ጋር ተመጣጣኝ የሆነ ➤ ቋንቋ፦ የእንግሊዝኛ ቋንቋ ክህሎት ደረጃ III የሆነ/የሆነችየሥራ መደብ 2፦ Trainee Pilot ➤ ተፈላጊ የትምህርት ደረጃ፦ BSC ዲግሪ በኢንጂነሪንግ፣ ቴክኖሎጂ፣ ሳይንስ ተዛማጅ መስኮች ዕውቅና ካለው ከፍተኛ ትምህርት ተቋም የተመረቀ/የተመረቀች እና CGPA 2.75 ያለው/ያላት ወይም BSC/BA ዲግሪ በየትኛውም የትምህርት መስክ ዕውቅና ካለው ከፍተኛ ትምህርት ተቋም የተመረቀ/የተመረቀች እና CGPA 3.00 ያለው/ያላት እንዲሁም በ10ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በሒሳብ፣ ፊዚክስ እና እንግሊዝኛ ‘B’ ያመጣ/ያመጣች ወይም በ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በሒሳብ፣ ፊዚክስ እና እንግሊዝኛ 50% ነጥብ ያመጣ/ያመጣች ➤ ዕድሜ፦ ከ 18-25 ➤ ቁመት፦ 1.70ሜ እና በላይ ለወንድ ፤ 1.65ሜ እና በላይ ለሴትየሥራ መደብ 3፦ School of Marketing Trainee ➤ ተፈላጊ የትምህርት ደረጃ፦ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ቢያንስ 300 ውጤት ያለው/ያላት ➤ ዕድሜ፦ ከ 18-25 የምዝገባ ቀናት፦ ከነሐሴ 05-09/2017 ዓ.ም የምዝገባ ቦታዎች፦ ➫ አዲስ አበባ፦ በኦንላይን ➫ አዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ፣ አዳማ ➫ አምቦ ዩኒቨርሲቲ፣ አምቦ ➫ አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ፣ አርባ ምንጭ ➫ አሶሳ ዩኒቨርሲቲ፣ አሶሳ ➫ ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ፣ ባህር ዳር ➫ ወሎ ዩኒቨርሲቲ፣ ወሎ ➫ ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ፣ ድሬዳዋ ➫ ጋምቤላ ዩኒቨርሲቲ፣ ጋምቤላ ➫ ጎንደር ዩኒቨርሲቲ፣ ጎንደር ➫ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ፣ ሐረር ካምፓስ፣ ሐረር ➫ ሀዋሳ ኤርፖርት፣ ሀዋሳ ➫ ጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ፣ ጅግጅጋ ➫ ጅማ ዩኒቨርሲቲ፣ ጅማ ➫ መቐለ ዩኒቨርሲቲ፣ መቐለ ➫ መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ፣ ሮቤ ➫ ወለጋ ዩኒቨርሲቲ፣ ነቀምቴ ➫ ሰመራ ዩኒቨርሲቲ፣ ሰመራ ➫ ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ፣ ወልቂጤ ➫ ሻሸመኔ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ፦ ሻሸመኔ ለምዝገባ የሚያስፈልጉ፦ አንድ ፓስፖርት መጠን ፎቶግራፍ፣ የ8ኛ ክፍል ካርድ፣ የ10ኛ ክፍል ሰርተፊኬት፣ የ12ኛ ክፍል ሰርተፊኬት፣ የትምህርት ማስረጃ ዲግሪ፣ የልደት ሰርተፊኬት እና የቀበሌ መታወቂያ፡፡ የሰነዶችዎንና የትምህርት ማስረጃዎችዎን ዋናውንና ኮፒውን ስካን በማድረግ ማያያዝ ይጠበቅብዎታል፡፡ ከአዲስ አበባ ውጪ፣ አመልካቾች በተገለፁት ቦታዎች በአካል በመገኘት ማመልከት ይጠበቅባቸዋል፡፡ ለአዲስ አበባ የመመዝገቢያ ሊንክ በሚወጣበት ጊዜ እናሳውቃለን። የስራውን ዝርዝር መረጃ ለማየት ከፈለጉ 👇👇👇
https://effoysira.com/ethiopian-airlines-vacancy-for-fresh-graduates/
|| @ASTU_Network