ተማሪ
Open in Telegram
“አንተ ግን በተማርህበትና በተረዳህበት ነገር ጸንተህ ኑር፥ ከማን እንደ ተማርኸው ታውቃለህና፤” — 2ኛ ጢሞቴዎስ 3፥14
Show more282
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
-630 days
Posts Archive
282
ውሉደ ያሬድ ሰንበት ትምህርት ቤት:
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
ጳጉሜን የሚለው ስያሜዋ ግን “ሄፓጉሜኔ” ከሚለው የግሪክ ቃል የመጣ መሆኑን አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ ተነግሯል፡፡ “ኤፓጉሜኔ” ማለት ጭማሪ ማለት ነው፡፡ በግእዝ ቋንቋችን ተውሳክ ማለት ነው፡፡ ተውሳክ ማለት ተጨማሪ ማለት ነው፡፡ “ወሰከ - ጨመረ” ከሚለው የግእዝ ግስ የተገኘ ነው፡፡ (ምንጭ መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገበ ቃላት ኪዳነ ወልድ ክፍሌ ገጽ ፱፻፭)፡፡ ምዕራባዊያኑ ጳጉሜን ተጨማሪ ቀን አድርገዋታል፡፡ እኛ ግን የወር ተጨማሪ አድርገናታል፡፡ በጽርዕ ኤፓጉሜኔ ትባል እንጂ ሊቃውንት ግን ተረፍ ይሏታል፡፡ ጳጒሜን የአሮጌው ዓመት ማብቂያ የአዲሱ ዓመት መንደርደሪያ ዕለት እንደሆነች የክርስቶስ ልደትም የዓመተ ፍዳ ማቆሚያ የዓመተ ምሕረት መጀመሪያ በመሆኑ ዕለታቸው ራሱ በተመሳሳይ ቀን ተቀምሮ ይውላል፡፡
የጳጉሜን ወር ‹‹የምሕረት ወር›› ስለመባሏ፡-
ኢትዮጵያ በዓለም ብቸኛዋ የ፲፫ ወራት ጸጋ ባለቤት ስትሆን የጳጉሜን ወርም በኢትዮጵያውያን ዘንድ የምሕረት ወር ተብሎ ይታመናል። በተለይም በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ መሠረት ጸሎት የሚያርግበት ዕለተ ምጽአት የሚታሰብበት የምሕረት ወር መሆኑን ታስተምራለች፡፡ በተለይም በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እምነት መሠረት ምእመናኑ በጳጉሜን ጸበል በመጠመቅ ድኅነት በማግኘታቸው የምሕረት ወር መሆኑን ምእመናን ያብራራሉ፡፡
የጳጉሜን ወር በጸሎት በንስሓ ተወስነን ወደ አዲሱ ዓመት የምንሸጋገርባት ድልድይ ናት፡፡ ከዚህም የተነሳ እግዚአብሔር የፈቀደላቸው የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ምእመናን ጸሎት በመጸለይ ጸበል በመጠመቅ ያስቧታል፡፡ በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ካሉት ሁለት የፈቃድ አጽዋማት መካከል አንዱ በዚህ በጳጉሜን ወር የምንጾመው ሲሆን መሠረት የሚደረገውም ጾመ ዮዲት ነው፡፡ የዮዲት ጾም የሚባለውም እርሷ ስለ ጾመችው ነው፡፡ ይህን መሠረት አድርገው ሕዝቡ ሳይቀር “ጳጉሜን ዕድሜ ትሰጠናለች፤ በኋላም ታድነናለች” ብለው ጾም ይጾሙባታል፡፡ (ምንጭ-ቅዱስ መልከ ጸዴቅ ድርሳን)፤ በሀገራችንም ንግሥት ዘውዲቱ እና ምኒልክ የጾም ሥርዐት ይፈጽሙባት ነበር፡፡ ሌሎችም ሽማግሌዎችና ባልቴቶች አክብረው ይጾሙባታል፡፡ የጳጉሜንን አቆጣጠር አንዱ ከቀን ጋራ ሲያደርገው፣ ሌለኛው ደግሞ ከወር ጋራ ቢያደርገውም በሁሉም አቆጣጠር ውስጥ ሕያዊት ሆና መገኘቷ የታወቀ ነው፡፡
የዐውደ ዓመት መሸጋገሪያ ናት፡
ይህም ጳጉሜን ከአሮጌው ዓመት ወደ አዲሱ ዓመት፣ ከክረምት ወቅት ወደ ጸደይ መሸጋገሪያ ናት፡፡ ጳጉሜን የዓመቱ መጨረሻ ወር ናት፡፡ ወርኃ ጳጉሜ አዲሱን ዓመት ለመቀበል የዝግጅት ጊዜ ናት፡፡ ስለሆነም አዲሱ ዘመን የሰላም፣ የፍቅር፣ የአንድነት፣ የልማት፣ የመተሳሰብ ዘመን እንዲሆንልን በጾምና በጸሎት ማሰብ እጅግ አስፈላጊ ነው፡፡
ነገረ ምጽአት የሚታሰብባት ናት
የጳጉሜን ወር የነገረ ምጽአት የሚታሰብባት ስትሆን ምጽአት ማለት የጌታን መምጣት የሚያስረዳ በመሆኑም ቤተ ክርስቲያን የጌታን ምጽአት በዓመት ሁለት ጊዜ ታስታውሳለች፤ ይኸውም በጳጉሜን ወርና በጌታ ጾም እኩሌታ (በደብረ ዘይት) ነው። ቅዱስ ዳዊት ”እግዚአብሔር ግልጥ ሆኖ ይመጣል፤ ዝም አይልም፤ እሳት በፊቱ ይነዳል፤” እንዲል፤ (መዝሙረ ዳዊት ፵፱ ፣ ፪-፬)፡፡ ይህ ስለ ነገረ ምጽአት ያስረዳል፡፡
ይህም ጳጉሜን ከአሮጌው ዓመት ወደ ዐዲሱ ዓመት፣ ከክረምት ወቅት ወደ ጸደይ ወቅት መሸጋገሪያ እንደሆነች ሁሉ ምጽአትም ከጊዜያዊው ወደ ዘላለማዊ፣ ከምድራዊ ወደ ሰማያዊ፣ ከዚህ ዓለም ወደ ወዲያኛው መሸጋገሪያ ናትና ነው፡፡ ጳጉሜን የክረምቱ ማብቂያ እንደሆነች ሁሉ ምጽአትም በመጨረሻው ዘመን መከራ የሚበዛበት የዚህ ዓለም ማብቂያ ናት፡፡ ወርኃ ጳጉሜን አዲሱን ዓመት ለመቀበል የዝግጅት ጊዜ እንደሆነች ሁሉ ምጽአትም ጻድቃን ዐዲሲቷን ምድር (መንግሥተ ሰማያትን) ለመውረስ ተዘጋጅተው “ኑ የአባቴ ብሩካን ዓለም ሳይፈጠር የተዘጋጀላችሁን የእግዚአብሔር መንግሥት ውረሱ” የሚባሉባት ቀን ናት፡፡ የጌታ አመጣጥ ሳይታሰብ ነውና በተሰጠን ጸጋ ቅዱስ አምላካችንን እያመሰገንን ተዘጋጅተን እንድንጠብቀው የድንግል ማርያም ልጅ መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ይርዳን፤ ቀጣዩ ዘመንም ቃሉን ፈጽመን መልካም ፍሬ የምናፈራበት ዓመት ይሁንልን፤ አሜን !!!
©ማኅበረ ቅዱሳን
282
✝️✝️✝️ ††† እንኳን ለታላቁ ቅዱስ አባ ዮሐንስ ሐጺር ዓመታዊ የፍልሠት በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን! ††† ✝️✝️✝️
††† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፤ አሜን! †††
🌿 ✝️ ቅዱስ አባ ዮሐንስ ሐጺር ✝️ 🌿
“ሰላም ሰላም ዕብሎ በሕቁ፤ ለዮሐንስ ሐጺር ዘነዊኅ ሒሩተ ጽድቁ።”✨ ቁመቱ አጭር፤ ጽድቁ ግን ከፍ ያለ! ✨ ቅዱስ ዮሐንስ ሐጺር በ4ኛው መቶ ዘመን በምድረ ግብጽ ተወለደ። በ18 ዓመቱም ወደ ምናኔ ገብቶ የታላቁ አባ ባይሞይ ደቀ መዝሙር ሆነ። 🌿 የቅዱሱ ታላቅነት በትሕትናው፣ በትዕግሥቱና በመታዘዙ ነበር። አባ ባይሞይ ብዙ ጊዜ ቢያስቸግረውም፣ ቅዱስ ዮሐንስ ግን አልተቆጣም፤ ይልቁንም፦ “አባቴ ሆይ! ማረኝ!” እያለ በትሕትና ይቅርታ ይጠይቅ ነበር። 🕊 አንድ ቀን አባ ባይሞይ ሊያስቸግረው ሲሄድ ሰባቱን ሊቃነ መላእክት ከቅዱሱ ጋር ቆመው ተመለከተ፤ በዚህም እጅግ ተደነቀ። 🌱 የመታዘዝ ፍሬ አባ ባይሞይ ደረቅ እንጨት ሰጥቶት፦ “ትከለውና እንዲያፈራ አድርገው፤ ከዚያም አምጥተህ አብላኝ” አለው። ቅዱስ ዮሐንስም “እሺ” ብሎ ወስዶ ተከለው። ለሁለት ዓመታትም ሳይታክት ውሃ አጠጣው። በሦስተኛው ዓመት ግን ደረቁ እንጨት ለምልሞ አበበ፤ ፍሬም አፈራ! አባ ባይሞይም፦
“ይህ የዛፍ ሳይሆን የመታዘዝ ፍሬ ነው!”ብሎ ተናገረ። 🌿 🕊 የቅዱሱ በረከት ቅዱስ ዮሐንስ ለመምህሩ በታማኝነት አገልግሏል፤ ለ12 ዓመታትም በሕመሙ አስታሞታል። በመጨረሻም አባ ባይሞይ መነኮሳቱን ሰብስቦ፦ “ይህ የያዛችሁት እጅ የሰው ሳይሆን የመልአክ እጅ ነው።” ብሎ መስክሮለት አረፈ። ቅዱስ ዮሐንስም ከጊዜ በኋላ የገዳሙ አበ ምኔት ሆኖ ብዙ ነፍሳትን ወደ ቅድስና መራ። ✨ “ዮሐንስ ሐጺር” ተብሎ ቢጠራም፣ የትሕትናው፣ የትዕግሥቱ፣ የመታዘዙና የጽድቁ ቁመት ግን እጅግ ከፍ ያለ ነበር። 🙏 አምላከ ቅዱሳን የቅዱስ ዮሐንስ ሐጺርን መታዘዝ፣ ትሕትና፣ ትዕግሥትና ቅንነት ያድለን፤ በበረከቱም ይባርከን! አሜን። 🙏 ††† ነሐሴ ፳፱ — የቅዱስ ዮሐንስ ሐጺር የፍልሠት በዓል ††† 📖 “እናንተ ደግሞ የታዘዛችሁትን ሁሉ ባደረጋችሁ ጊዜ፦ ‘የማንጠቅም ባሪያዎች ነን፤ ልናደርገው የሚገባንን አድርገናል’ በሉ።” — ሉቃስ 17፥10 ✝️✝️ ወስብሐት ለእግዚአብሔር! ✝️✝️
282
✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨
“ትሕትና ማለት ራስን መጥላት ሳይሆን፣ ራስን ማወቅ ነው። ራስህን ስታውቅ፣ ያለ እግዚአብሔር ጸጋ ምንም እንደማትሆን ትረዳለህ፤ ያኔ በትክክል ትሑት ትሆናለህ።››
✨ቅዱስ አውግስጢኖስ
የሰው ልጅ የልቡን በር ከውስጥ እንጂ ከውጭ መክፈት አይችልም ፡ እግዚአብሔርም ቢሆን በሩን ያንኳኳል እንጂ ሰብሮ አይገባም ፡ መክፈትና አለመክፈት የአንተ ፈቃድ ነው ፡፡
✨አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ
"ዕለትን የሠጠህ እርሱ ለዕለት የሚበቃህንም ይሠጥሃል!"
✨ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘኑሲስ
“በጠላቶችህ እጅ እንዳትወድቅ ወደ አቆምካቸው ኃጢአቶች አንዳትመለስ በሌሎች ላይ አትፍረድ ምንም እንኳን ምክኒያት ቢኖርህ ማንንም አትንቀፍ ህጉን ለመፈፀም አቅቶት ወንድምህን ብታየው እንኳን አትማው ስሙንም አታጥፋ።''
✨ ቅዱስ አባ አንጦንስ
✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨
282
...እስኪ ንገረኝ በዚህ ምድር የምታጣጥመው ደስታ ምን ዓይነት ነው? እኔ ያስተማርኩህንስ ደስታ በዚህ ዓለም ሳለን ማጣጣም አይቻለንምን? ምን ዓይነት ነፃነትን እንደምታገኝ ልብ በል፤ በጽድቅ የምትመላለስ ከሆነ የትኛውም ሰው ቢሆን አያስፈራህም ወይም አያሸብርህም፤ ጠላትም ቢሆን ወይም በአንተ ላይ የሚሸምቍትም ቢሆኑ ወይም ነገር ሰሪም ቢሆን አበዳሪም ቢሆን ፆታዊ ፍቅርም ቢሆን ክፉ ሰዎችም ቢሆኑ ድህነትም ቢሆን በሽታም ቢሆን ሌሎችም በሰው ላይ የሚመጡ ሁሉ አያስፈሩህም። (https://t.me/beteafework)
ነገር ግን እንደ ልብህ ምኞት ሀብትህ እንደ ጅረት ሆኖ ቢፈስ በዚህ ምክንያት በአንተ ላይ ከሚመጡት ሁከቶች፤ ዓመፃዎችና እንቅፋቶች እንዲሁም ጠቦች ሕይወታቸው በጋለሞታ ከሚመሰቃቀልባቸው ሰዎች ይልቅ የታወከ ነው፡፡ በጋለሞታይቱ ሕይወቱ የተመሰቃቀለበት ያ ሰው ራሱን በከንቱ የሚያስታብይ ክብረ ቢስ ሰው ነው፡፡ ስለዚህ እርሷን ለመማረክ ሲል የፋመ ጠብ ውስጥ ይገባል፡፡ ይህ በብዙ ሺህ እጥፍ ከሞት ይልቅ የከፋ ነው፡፡ ቅጣቱም የሚቋቋሙት አይደለም፡፡ በመንፈሳዊነት ውስጥ ግን እነዚህን የመሰሉ ነገሮች ፈጽሞ የሉም፡፡ ፍሬዎቹም መጽሐፍ እንደሚነግረን፡-“ፍቅር፣ ደስታ፣ ሰላም” (https://t.me/beteafework) ናቸው፡፡
በመንፈሳዊው ሕይወት ውስጥ ይህን የመሰለ ሁከት የለም፤ ወይም ያለ ምክንያት የሚባክን ገንዘብ ወይም ያለአግባብ የሚወጣ ወጪ የለም፤ እንዲሁም ጥቂት ሳንቲም ወይም ቁራሽ እንጀራ ወይም ቀዝቃዛ ውኃ ብትስጥ እርሱ በዝቶ ይሰጥሃል፡፡ እርሱም ቢሆን አንተን የሚያስጨንቅ የሚጎዳ ነገር አያመጣብህም፤ ነገርን በሁሉ ትከብር ዘንድ ይፈልጋል፤ ከሚያዋርድ ነገር ሁሉ ነፃ ያወጣሃል፡፡ የክፋት ሥራዎችን ካልተውናቸው ግን ስለመተላለፋችን ምን መከላከያ ልናቀርብ ይቻለናል? ምን ዓይነት ይቅርታስ እናገኛለን? (https://t.me/beteafework) እኛ ከተፈጥሮአችን በተቃራኒ ለሆነ ሥራ ራሳችንን አሳልፈን ሰጥተናልና ከሚንቀለቀል ዘለዓለማዊ እሳት ውስጥ እንጣላለን፡፡ ስለዚህም በዚህ ደዌ የተያዙ ወገኖች ከዚህ ክፉ ሕማም ራሳቸውን እንዲያርቁ ወደ ጤናቸውም እንዲመለሱና ራሳቸውን ለጥፋት አጋልጠው እንዳይሰጡ እመክራቸዋለሁ::
ያ የጠፋው ልጅ በጣም በተጎሳቆለ ሕይወት ውስጥ ይኖር ነበር፤ ወደ አባቱ ቤት በተመለሰ ጊዜ ግን የቀደመ ክብሩ ተመለሰለት፡፡ ከወንድሙ በላይ ከዚህ በፊት ፈጽሞ ታይቶ በማይታወቅ ፍጹም ደስታ ደስ ተሰኘ፡፡ እኛም እርሱን እንምሰለው፤ ከመንፈሳዊው ሕይወት ርቀን ከሆነ ወደ አባታችን ቤት ለመመለስ እንፋጠን፤ በመንግሥቱ በደስታ መኖርን ገንዘብ ለማድረግ ለኀጢአት ባሪያ ከመሆን እንለይ፤ ራሳችንንም ነፃ እናውጣ፡፡ (https://t.me/beteafework)
(የዮሐንስ ወንጌል በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ቅጽ 2 ገጽ 321-322 በዲያቆን ሽመልስ መርጊያ የተተረጎመ)
282
🌴🌴🌴🌷🌷🌷🌴🌴🌴🌷🌷🌷🌴🌴🌴
ቅዱስ ኒፎን አጋንንት የተለያየ ሰይጣናዊ ሃሳብን፣ በሰዎች ጆሮ እያንሾካሾኩ እንዴት እንደሚፈትኗቸው ይመለከት ነበር።
ሰዎች ግን በተለያየ ዓለማዊ ጉዳዮች ተጠምደው ይሄንን ፈጽሞ አያስተውሉትም።
በዚህም፦ የዲያብሎስ ሃሳብ የራሳቸው እስኪመስላቸው ድረስ፣ ተቀብለው በመፈጸም እና በማስተዋወቅ ተጠምደዋል።
በአብዛኛዎቹ ላይ ቁጣ፥ ሐሜት፥ ዘለፋ፥ ጠብ፥ ክርክር፥ ቅያሜና የመሳሰሉት ተንሰራፍቶባቸዋል።
ራዕየ ኒፎን
ትርጒም በቀሲስ ታምራት ውቤ
ወንድሞቻችን እንግዲህ ከዲያብሎስ ሽንገላ እንርቅ ዘንድ በሐዋርያው ቃል እንመክራችኋለን። እንዲህ እያልን፡-
"በቀረውስ በጌታና በኃይሉ ችሎት የበረታችሁ ሁኑ።የዲያብሎስን ሽንገላ ትቃወሙ ዘንድ እንዲቻላችሁ የእግዚአብሔርን ዕቃ ጦር ሁሉ ልበሱ። መጋደላችን ከደምና ከሥጋ ጋር አይደለምና፥ ከአለቆችና ከሥልጣናት ጋር ከዚህም ከጨለማ ዓለም ገዦች ጋር በሰማያዊም ስፍራ ካለ ከክፋት መንፈሳውያን ሠራዊት ጋር ነው እንጂ።" ኤፌ 6 ፥ 10 - 12🔱⚜🔱⚜🔱⚜🔱⚜🔱⚜🔱⚜🔱⚜
282
ደብረ ታቦር በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
ያኔ በደብረ ታቦር ተራራ ላይ ከጌታችን ከመድኃኒታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር በደመናው ውስጥ የነበሩት ሦስቱ ደቀመዛሙርት እንዴት የተባረኩ ናቸው? እኛም ከወደድን እና ከፈቀድን ክርስቶስ እንደ እነዚህ በተራራ ሳይሆን በሚያስደንቅ በግርማ ብርሃን ውስጥ እናየዋለን።
ክርስቶስ ዳግመኛ በእንዲህ ዓይነት ክብር አይመጣም። ይልቁንም በዚሁ ተራራ ባሳየው ከፊል ብርሃን ጸዳል ሳይሆን በአባቱ ክብር እናየዋለን። ከሙሴና ከኤልያስ ጋር ሳይሆን ከመላእክት፣ ከሊቀነ መላእክት፣ ከኪሩቤል እና ከሌሎች አእላፍ ነገደ መላእክት ጋር ሲመጣ እናየዋለን። ደመናን ይዞ ሳይሆን ለባልዋ እንደተሸለመች ሙሽራ የተዘጋጀችውን አዲሲቷን ኢየሩሳሌም (መንግሥተ ሰማያትን) ይዞ ሲመጣ እናየዋለን።
መጥቶም በጸጋው ዙፋን ሳይሆን በፍርድ ዙፋኑ ይቀመጣል፤ ያኔ ሰው ሁሉ ከመጋረጃው ወጥቶ በፊቱ ይቆማል።
282
🍁🍁🍁✨🍁✨🍁✨🍁🍁🍁
✨ደብረ ታቦር✨
ነሐሴ ዐሥራ ሦስት በዚች ቀን ክብር ይግባውና የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ታላቅና ክቡር በዓል ነው።
በዚች ቀን መድኃኒታችን ሦስቱን ደቀ መዛሙርቶቹን ጴጥሮስን፣ ያዕቆብንና ዮሐንስን ይዞ ወደ ታቦር ተራራ ላይ አወጣቸው። መልኩም በፊታቸው ተለወጠ ልብሱም እንደ በረዶ ነጭ ሆነ። ስለ እነርሱም ጌታችን የሰው ልጅ በጌትነቱ ሲመጣ እስከሚያዩት ድረስ በዚህ ከቆሙት መካከል ሞትን የማይቀምሱት አሉ አለ።
ሰዎች ሁሉ እርሱ ለሙሴ ጌታውና ከሞት ያስነሣው እንደሆነ ለኤልያስም ፈጣሪው እንደሆነና ካሳረገበትም ያወረደው እርሱ እንደሆነ ያውቁ ዘንድ እነሆ ከጌታ ከኢየሱስ ጋራ እየተነጋገሩ ሙሴና ኤልያስ ወደርሱ መጡ።
ስለዚህም ጴጥሮስ ጌታችንን እንዲህ አለው አቤቱ በዚህ ትኖር ዘንድ ትወዳለህን ሦስት ሰቀላዎችንም አንድ ላንተ፣ አንድ ለሙሴ፣ አንድ ለኤልያስ እንሠራ ዘንድ።
🍁✨🍁✨
በዚህም ቃል የደካማነትና የትሕትና ምልክት አለበት። ደካማነት የተባለ ጴጥሮስ ጌታችን ከሰማይ የወረደበትን ሥራ ትቶ በተራራ ላይ ይኖር ዘንድና ራሱን የሚሠውርበትን ቤት ይሠራለት ዘንድ የተናገረው ነው። ትሕትና ያልነውም ጴጥሮስ ለራሱና ለባልንጀሮቹ ሐዋርያት ቤት ይሠራ ዘንድ ስለ አላሰበ ነው። ራሱንና ባልንጀሮቹ ሐዋርያትን እንደ ባሮች ነቢያትን ደግሞ እንደ ጌቶች አድርጎ አስቧልና።
ሰለ ሐዋርያትም የእውቀት ማነስ አታድንቅ በዚያን ጊዜ ፍጹማን አልሆኑምና። እንዲህም በሚልበት ጊዜ ጌታችን በሰው እጅ የተሠራ ማደሪያን የማይሻ መሆኑን ለጴጥሮስ ያሳየው ዘንድ እነሆ ደመና ጋረዳቸው።
የጌታችንን ጌትነቱን የሚገልጽ በሐዋርያትም ልቡና እምነትን የሚያጸና እንዲህ የሚል ቃል ከደመና ውስጥ መጣ። ይህ የምወደው በእርሱ ደስ የሚለኝ ልጄ ይህ ነው እርሱንም ስሙት።
ሙሴና ኤልያስም ከእርሱ ጋራ ሲነጋገሩ ተሰሙ ስለ ርሱ መምጣት የተናገሩትን ትንቢታቸውንም በቸርነቱ አረጋገጠ። ወደ ተራራ ላይ በመውጣቱም ነቢያትና ሐዋርያት ደስ አላቸው።
🍁✨🍁✨
ሁለተኛም የአብን ቃል በሰሙ ጊዜ ከእነርሱ ሥውር የነበረ የወልድ ዋሕድን በእውነት ሰው መሆን በዚያን ጊዜ ተረዱ ያን ጊዜ የጌትነቱ ክብር ተገልጦአልና። ሐዋርያትም ፍጹም አምላክ ፍጹም ሰው የሆነ እርሱ ሙሴን ከመቃብር ያስነሣው ኤልያስንም ያሳረገው አውርዶም ያመጣው እርሱ እንደሆነ አወቁ። ከእርሱ በቀር ማንም ማን የሙሴን መቃብር የሚያውቅ የለምና ከዐሳረገው ከእርሱ በቀር ማንም ማን ኤልያስ ያለበትን የሚያውቅ የለምና። በሰማይና በምድር ሥልጣን ካለው ከሁሉ ጌታ በቀር ሙታንን አድኖ ሊአስነሣቸው ማንም አይችልም።
ደብረ ታቦርም የቤተ ክርስቲያን አምሳል ሆነች ከብሉይና ከሐዲስ በውስጧ ሰብስባለችና። የአብንም ቃል በሰሙ ጊዜ በግምባራቸው ፍግም ብለው በምድር ላይ ወደቁ እንደ ሙታንም ሆኑ። ከዓለም አስቀድሞ ከእርሱ ጋራ በህልውና እንዳለ ለልጁ አብ ምስክርን ሆነ ወዲያውኑ ሙሴ ወደ መቃብሩ ኤልያስም ወደ ቦታው ተመለሱ።
ሐዋርያትንም በአነቃቸው ጊዜ ከብቻው ጌታችን በቀር ማንንም አላገኙም። ከባሕርያችን የተዋሐደና ሥጋችንን የለበሰ ፍጹም አምላክ እንደሆነ በዚህ ሐዋርያት አስተማሩ።
🍁✨🍁✨
እንግዲህ እናስተውል ሰው ካልሆነ ቅዱስ ገብርኤል እመቤታቸንን ድንግል ማርያምን በአበሠራት ጊዜ እግዚአብሔር ከአንቺ ጋራ ነው እንዴት አላት። አምላክ ካልሆነስ ለመንግሥቱ ፍጻሜ የለውም እንዴት አላት። ሰው ካልሆነ በበረት እንዴት አስተኙት። አምላክስ ካልሆነ መላእክት ከሰማይ ወርደው ለእግዚአብሔር በሰማያት ምስጋና በምድርም ሰላም ለሰውም ግዕዛኑ ሊሰጠው እያሉ እንዴት አመሰገኑ።
ሰው ካልሆነ ዮሐንስ በውኃ እንዴት አጠመቀው አምላክስ ካልሆነ አልዓዛርን ከመቃብር እንዴት ሊያስነሣው ቻለ። ይህ ተቀዳሚ ተከታይ የሌለው እንድ ልጅ አካላዊ ቃል እግዚአብሔር እርሱ ያለ መለወጥ ያለ መለየት አንድ አካል አንድ ባሕርይ በመሆን ፍጹም አምላክ ፍጹም ሰው እንደሆነ እናምንበታለን። እርሱም ከአብ ከመንፈስ ቅዱስ ጋራ ሁል ጊዜ አንድ ህላዌ ነው ዛሬም ዘወትርም ለዘላለሙ አሜን።
📚ስንክሳር ዘወርኀ ነሐሴ 13
🍁🍁🍁✨🍁✨🍁✨🍁🍁🍁
282
✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨
ልጅነት ናፈቀኝ
ልጅ መሆን ናፈቀኝ ከደጅሽ እንዳልርቅ፥
እንዳሻኝ እንድሆን በፊትሽ ልቦርቅ፤
ነጠላ አጣጥዬ መሬት እየጠረግሁ፥
ሮጬ ሮጬ ከመቅደሱ ፊት ገጽ ደርሼ እንደቆምሁ፤አሐዱ አብ ቅዱስ ሲባል በፍርሃት፥የእግዚአብሔርን መውረድ በውስጤ እያሰብኩት፤
በፍጹም ፍርሃት በፍጹምም ፍቅር በፊትሽ የቆምኩበት፥
ልጅነት ናፈቀኝ ድጋሚ ቢመጣ በሚል ተመኘሁት፤
ቁርባኔን ቆርቤ እመቅደሱ መሃል ጢቢኛ ስበላ፥
በፍቅርሽ ታሥሬ ሕግጋትን ስጥስ ከልጆች ስጣላ፤
ልጅ መሆን ናፈቀኝ ከደጅሽ እንድቆም እንድትባርኪኝ፥
ፍልሰታ ደረሰች ብዬ እንድደሰት እንደምትናፍቂኝ፤
ወጣትነት አሥሮኝ ከደጅሽ ባልቆምም፥
በጉልምስናዬ ለቅዳሴ ሮጬ አሐዱን ባልቀድምም፥
እንደልጅነቴ ጓደኛዬ ሲቆርብ ቀኝቼ ባልቆርብም፤
ጢቢኛ በኪሴ ይዤ ባልገኝም ባልደባደብም፤
ካለሁበት ሆኜ ትናፍቂኛለሽ ስዕሉ ይታየኛል፥
ፍልሰታ ደረሰች በል ሩጥ እያለ ደርሶ ይገፋኛል፥
ከመቅደሱ ግባ ከቅዳሴው ቅመስ በል ፍጠን ይለኛል፤
ሰላም ለኪ እያልክ ሰዓታቱን አድርስ ትርጓሜ አድምጥ፥
ቁጭ በል ከመቅደስ ውዳሴዋን ጸልይ ከሥዕሏ ተሻሽ፥
ሽምብራ ተቀበል ፍትፍቱን አጣጥም ከሰንበቴ አዳራሽ፤
ከዳቤው አትለፍ ቅዳሴ ጸበሉን ለምዕመናን አዳርስ፥
መጠለያ ግባ ከዝናቡ አምልጥ ደግሞ እንዳትበሰብስ፤
ሱባዔውን ግባ ከቅጽሯ አንድ ጥግ ቦታ አመቻችና፥
ፍልሰታ ደረሰች እንደልጅነትህ በል ሁን እንደገና፤
ለሥጋዬ ስሮጥ ነፍሴ ተሰቃየች ማረፊያ እንዳጣ ወፍ፥
ፍልሰታ ደርሳለች ድንግል ፍቀጂልኝ ከእቅፍሽ ልረፍ፤
ከቅዳሴሽ ልገኝ ከቁርባኑ ልቅረብ ሰዓታቱን ላድርስ፥
የተዘናጋውን የተዳቀቀውን እኔነቴን ላድስ፥
ፍልሰታ ደረሰች እንደልጅነቴ ውዳሴሽን ላድርስ፥
ከሕግ በላይ ልሁን ከእቅፍሽ ገብቼ ነጻነቴን ላድስ፥አርአያ ሥላሴ የሆንኩኝ ልጅሽ በፍቅርሽ ልታደስ።
📝ማርቆስ በላይ
✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨
282
ጽንዕት በድንግልና ስርጉት በቅድስና እመቤታችንጸጋውን ክብሩን እንዳይነሳን ለምኝልን
አእምሮዉን ለብዎዉን ሳይብን አሳድርቢን፡፡
ለቅዱስ ኤፍሬም ለአባ ሕርያቆስ የተለመነች እመቤታችን ዘወትር ትለመነን፤ የልጇ ቸርነት የእርሷ አማላጅነት ዘወትር አይለየን አሜን፡፡ 🙏🙏🙏
ሰባኤውን የበረከት የረድኤት የቸርነት የበጎ ነገሮች ሁሉ ፍጻሜ ታድርግልን አሜን 🙏🙏🙏
282
🌴🌴🌴🌷🌷🌷🌴🌴🌴🌷🌷🌷🌴🌴🌴
📚#በእንተ_ፍልሰታ_ለማርያም#📚
#ቅዳሴ_ማርያም
#አባ_ሕርያቆስ_ስለ_እመቤታችን_ቅድስት_ድንግል_ማርያም
ጐሥዐ ልብየ ቃለ ሠናየ ጐሥዐ ልብየ ቃለ ሠናየ ጐሥዐ ልብየ ቃለ ሠናየ። መጽሐፍ ምሥጢርን ከምሥጢር አያይዞ መናገር ልማዱ ነው። አባቷ ዳዊት ለንጉሠ ሰማይ ወምድር ለእግዚአብሔር ምሥጋና ላቅርብ ባለ ጊዜ ጐሥዐ ልብየ ቃለ ሠናየ ብሎ እንደተናገረ ከዚህም አባ ሕርያቆስም ለንግሥተ ሰማይ ወምድር ለእመቤታችን ምሥጋና ላቅርብ ባለ ጊዜ ጐሥዐ ልብየ ቃለ ሠናየ ብሎ ተናገረ ወአነ አየድዕ ማንሻ፡፡
አንድም በዳዊት አድሮ የተናገረ መንፈስ ቅዱስ በአባ ሕርያቆስም አድሮ ተናገረ፡፡ ልሕኵት ልቦናዬ በመንፈስ ቅዱስ እሳትነት ፈላ፤ ፈላና በጎ በጎ ነገርን አውጥቶ ተናገረ፡፡ ወትጕሥዖሙ ይእቲ ባሕር ለነጋድያን እንዲል ወአነ አየድዕ ማንሻ፡፡
አንድም ልሕኵት ልቦናዬ ስንቡል መንፈስ ቅዱስን ተቀብሎ በጎ በጎ ነገርን ገሣ፡፡ በሀገራቸው የበሉት የጠጡት ያልተስማማቸው እንደሆነ ዑድ ሰንደል የሚባል ሽቱ አለ ያን ተመግበው በጎ በጎ ነገር ገሣሁ እንዲሉ፡፡
ሦስት ጐሥዐ ተናገረ ወአነ አየድዕ ቅዳሴሃ ለማርያም፣ ወአነ አየድዕ ውዳሴሃ ለድንግል፣ ወአነ አየድዕ ዕበያቲሃ ለድንግል ብሎ የሚያመጣው ነውና ለዚያ አርእስት ነው፡፡ ይህስ ለራሱ አርእስት ነው ብሎ ሦስት ጊዜ መላልሶ መናገሩ የሦስትነት ቃሉ አንድ ዐይነት መሆኑ (ያለመለወጡ) የአንድነታቸው ምሳሌ::
አንድም እመቤታችን በዚህ ዓለም፣ በገነት፣ በመንግሥተ ሰማያት ትመሰገናለችና፡፡
አንድም በመንግሥተ ሰማያት ያሉ ጻድቃን የሚያመሰግኗት ስለሆነ አስቀድሞ መንግሥተ ሰማያት የገባ የለም ብሎ ኋላ መንግሥተ ሰማያት የሚገቡ ጻድቃ የሚያመሰግኗት ስለሆነ፤ አንድም በነገደ ሴም፣ በነገደ ካም፣ በነገደ ያፌት ትመሰገናለችና፡፡ አንድም በወጣንያን፣ በማዕከላውያን፣ በፍጹማን አንደበት ትመሰገናለችና፡፡ አንድም በመላእክት፣ በደቂቀ አዳም፣ በካልዕ ፍጥረት ትመሰገናለችና፡፡ አንድም የንጽሐ ሥጋ፣ የንጽሐ ነፍስ፣ የንጽሐ ልቦናዋ ምሳሌ ነው፡፡ እሱስ የተናገረው አንድ ጐሥዐ ነው ቅዱስ ያሬድ ለዜማ ማቅኛ ሦስት አድርጎ ተናግሮታል እንጂ፡፡
ወአነ አየድዕ ውዳሴሃ ለድንግል።
እኔስ የድንግልን ምሥጋና እናገራለሁ:: ሁለት ጐሥዐ ተናግሮ ነበርና ለዚያ አርእስት ይህስ ለራሱ አርእስት ነው ብሎ ኦ ድንግል አኮ ወራዙት ስፉጣን ዘናዘዙኪ አላ መላእክተ ሰማይ ሐወጹኪ መተብህለ ካህናት ወሊቀ ካህናት ብሎ የሚያመጣው ነውና ለዚያ አርእስት ነው᎓᎓
አኮ በአንኆ በቃለ ዝንጋዔ። ይቆየን....
🔱⚜🔱⚜🔱⚜🔱⚜🔱⚜🔱⚜🔱⚜
282
🌿🌿🌿🍁🌿🍁✨✨✨
ድሮኮ ፍልሰታን አልወዳትም ነበር!!!
ክረምት ክረምት ጓደኛዬ አቤል ፍስለታ ሲል እሰማዋለሁ።ምን እንደሆን ግን አላቅም።ህፃን እያለን የቦይ ውሀ ስንገድብ፤ካፊያ ውስጥ ቢራቢሮ ስናባርር፤አኩኩሉ ስንጫወት ቆይተን ልክ 5ሰአት ሲል ተነስቶ ፍስለታ ሄዳለሁ ይለኛል።
ድንገት እየመጣች አባሮሼን ምታበላሸው፤ እቃቃዬን ምትበትነው፤ብቻዬን ምታስውለኝ ፍስለታ ማናት?? እላለሁ።የሚነግረኝ የለም።ብቻ እነ አቤል ተሰብስበው ፍስለታ እያሉ ሲሄዱ፤ነጠላ ለብሰው ሄደው አፋቸውን ሸፍነው ሲመለሱ፤ከዛ በኋላ አንጫወትም ሲሉ ይከፋኛል።ብቻዬን የሆንኩ ያህል ይሰማኛል።አንድ ቀን ታድያ ቢመረኝ እናቴ ጋ ሂጄ እንባ እየቀረረኝ...
ፍስለታ ሄዳለሁ...አልኳት ያው ከጓደኛዬ የሰማሁትን ነው።
ዝጋ አናትህ ይፍለስ!!እንደውም ከዚ በኋላ እጫወታለሁ ብለህ ከቤት ትወጣና....!!!ክፉኛ ዛተችብኝ
🌿🍁✨✨
እናቴ ከሰፈሩ ለየት ያለች ናት።ሰወች በጥቁረቷ የሚጠሏት ይመስለኝ ነበር።"የጠንቋይዋ ልጅ"ሲሉኝ ፈገግ ብዬ እያየኋቸው "አቤ" እል ነበር።ስድብ መሆኑ መች ገብቶኝ.....ያን ቀን ግን እማዬን ተቀየምኳት። መሄዱን ብከለከል መኝታ ቤት ገብቼ የእልህ...
ፍስለታ ፍስለታ ፍስለታ ፍስለታ....( እያልኩ እየለፈለፍኩ እንቅልፍ ይዞኝ ጭልጥ አለ።በነጋታው ከነአቤል ጋ ለመጥፋት ወስኜ ነበር የወጣሁት።እማ የት ታቃለች??ብታቅስ አንድ ቀን ብገረፍ ነው...ዋናው ፍስለታ ልሂድ እንጂ(እያልኩ በጠዋት አቤልጋ ሄጄ "ፍስለታ ውሰደኝ" አልኩት።አቤል እንደሚወደኝ አውቃለሁ።ግን ደሞ ከቤት እንደማይፈቀድ ስለሚያቅ ...
አይሆንም እናትህ ትቆጣለች..አለኝ
እናቴን እንደምሸውዳት የቆጥ የባጡን ቀባጥሬ ተከትዬው ሄድኩ።በህይወቴ ለመጀመርያ ጊዜ ጠባብ ደረቴ ላይ ልቤ ስትነጥር ተሰማኝ።ጓደኞቼ ሁሉ ነጭ ነጠላ ለብሰው እኔ በቁምጣ እና በከነቴራ ጭቃ በከበባት ዚኮ ጫማ እየተከተልኩ ቤተክርስትያን ገባሁ።የሚያምር ሰፊ ጊቢ ብዙ ህፃናት ብዙ ትልልቆች ያሉበት ጊቢ ገባሁ።ጠረኑ ..ከአበበ ጉሬው ሱቅ በላይ ደስ ይላል፤ከናና ከከረሜላ ሽታ በላይ የሚያውድ ደስ የሚል ግቢ ውስጥ ገባው።አቤል መውጫ መግቢያውን ያውቃል ።ከፊት እየቀደመ ግቢ ውስጥ ወዳለ ቤት ሲገባ እኔ ስከተለው ግን ከኋላዬ ሌላ ድምፅ ሰማሁና ደርቄ ቀረሁ
ና ተመለስ አንተ ውሪ!!!
🌿🍁✨✨
ድምፁ ጎረነነ እንጂ ትክክለኛ የእማዬ ስድብ ነው።በቆምኩበት ሽንቴን ልለቅ ስል ሌላ ሰው ድንገት ጀርባዬን እያቀፈኝ
"አቡሽዬ ቆይ ና እሺ"ብሎ ብቻዬን ወሰደኝ።የማላቅበት ቦታ ላይ ብቻዬን መወሰዴን አልፈራሁም።ብቻ ፍስለታ መምጣቴ ደስ ብሎኝ ሰውየውን ተከተልኩት
አቡሽዬ እንደዚ አይገባም እሺ አሁን እግርህን ልጠብህ...
ሰውየው ጥቁረቱ ከእማዬ መለስ ያለ ነው።በዛላይ ሲስቅ ደስ ይላል።ትንንሽ እግሮቼን በመዳፉ እያሸ በዝናብ ውሀ ሲያጥበኝ ሳላቀው ሳቅ አልኩኝ።ትንሽ ቆይቶ ደሞ ከአቤል የበለጠ ረጅም ነጭ ነጠላ ሰጥቶኝ አቤል ወደገባበት ይዞኝ ሲገባ የማላቀው የደስታ የስሜት ባህር ውስጥ እቀዝፍ ያዝኩኝ.....
የሆነ ደስ የሚል የሚያባብል ብሉኝ ብሉኝ የሚል ሽቱ ውስጥ የተዘፈቅኩ መሠለኝ።መሬቱ ንፁህ፤ግርግዳው ስእል፤ሁሉም ክፍሉ መብራት ነው።ከፊቴ አንዲት ምታምር ሴት ልጇን አቅፋ ክንፍ ባላቸው ነጫጭ ሰወች ተከባ ይታየኛል።ሳማት ሳማት ቢለኝም እነአቤል ስር ሂጄ ቁጭ አልኩ።የሆኑ ሽማግሌ ከወጣት ጋ እየተቀባበሉ በዜማ ሲያወሩም ትዝ ይለኛል።ብቻ ያን ቀን ቁርሴን ሳልበላ ሳይርበኝ ፍስለታዬን ሂጄ ምሳዬን በልቼ ተመለስኩ።ምን ያደርጋል....ስመለስ እማዬ ዱላዋን ይዛ በር ላይ ጠበቀቺኝ።አንዴ በአርጩሜ ሲላት በንክሻ እርርር እስክል ገረፈቺኝ።ከዛ ወዲህ ፍስለታ ምትባል ተውኩ።ማን ትሁን..ምን ትሁን ሳልጠይቅ እንደናፈቀቺኝ አመታት አለፈ።
🌿🍁✨✨
እናቴ ጠንቋይ እንደተባለች ስም እንደወጣላት ሰፈር እንደሸሻት 6ኛ ክፍል ስገባ ሞተች።እሷ ብቻ ስላለቺኝ አንድ አመት ትምህርት አቆምኩ።ብቸኛ ሆንኩ።እሷ ሞታ ደሞ ገና በሁለት ወሯ ክረምቱ ሲገባ ጭራሽ ጨነቀኝ።ዘመድ አልባነት ተጫጫነኝ።ያለው አንድ ጓደኛዬ አቤል ነው።ምሳ እያመጣ ያጎርሰኛል።ታድያ አንድ ቀን በሬ በስሱ ተንኳኳ።ያው የማውቀው አቤል ነው ብዬ ስከፍት ቀይ ረጅም ቄስ ከነጭራቸው ቆመው ጠበቁኝ
🌿🍁✨✨
አቤት አባ ሰላም ዋሉ
እግዜሀር ይመስገን ልጄ ደናህን ሰነበትክ??
አዎ አልኳቸው።ውሸቴን እንደሆን ገምተዋል ሰፈራችን ሰው ሁሉ ሚወዳቸው ካህን ናቸው።
በል ና ብቻ ብለው ሲሄዱ ሳልጠይቅ ተከተልኳቸው።በር ላይ አቤል ቆሟል።ሲያየኝ ፈገግ ሲል ሰላም መሆኑ ገባኝ።ከተማ ሄዴን ልብስ ጫማ ገዝተውልኝ ሲያበቁ አስከትለውኝ ወደ እንጦጦ ኪዳነምህረት አመሩ።ለምን እንደሆን ሳላውቅ በሩን እያየሁ እንባዬ እርግፍ እርግፍ ይል ጀመር።አቤል ከሚያወራው ነገር ውጪ ስለ ቤተክርስትያን ምንም አላቅም።ብቻ ህፃን ሆነን ሳለ ያቺ ልጅ አቅፋ የተቀመጠችው ቀይ ሴትዮ ማርያምን ማየት ፈለኩ።ድሮ ስሟን ሳላውቅ እንደዛ የወደድኳትን ማርያምን የከፋኝን ልነግራት "እናት ሁኚኝ"ልላት ፈለኩ።አባም የውስጤን ያወቁልኝ ያህል "በል እንካ "ብለው እንደልጅነቴ ነጠላ አቀበሉኝ።አቤልን ተከትዬ ወደ ቤተመቅደሱ ገባሁኝ።ያቺ የዋህ እናት ስር ገብቼ ስቅስቅቅቅቅ ብዬ አለቀስኩኝ።ከአመታት በፊት የነበረው ውበት ሙሉ ሆኖ ጠበቀኝ።አቤልም ጠጋ ብሎ በጆሮዬ
አይዞህ ማርያም እናትህ ትሆንሀለች እሺ አለኝ(ፍስለታ) ብዬ የወደድኳት በፍልሰታ እናቴን እንደገና ተዋወቅኳት።የጠንቋይ ልጅ ከመባል የማርያም ልጅ ወደመባል ተሸጋገርኩ።ከጥቂት አመታት በኋላ ደሞ ስሜ ዲያቆን ስሙር ተባለ። 🌿🌿🌿🍁🌿🍁✨✨✨
282
ፍልሰታ
1. ሐዋርያት ጾሙን ለምን ጾሙት?
ጾመ ፍልሰታ ማለት ምን ማለት ነው?
«ፍልሰታ» የሚለው ቃል «ፈለሰ» (ከቦታ ወደ ቦታ ተዛወረ/ተሻገረ) ከሚለው የግዕዝ ግሥ የተገኘ ሲሆን፣ «ጾመ ፍልሰታ» ማለት የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሥጋ ከሞተች በኋላ ከምድር ወደ ሰማይ የመፈለሷን (የማረጓን) ምስጢር በማሰብ የሚጾም ጾም ነው።
ለምን እንጾማለን?
👉የሐዋርያትን አርአያ ለመከተል፦ ሐዋርያት የእመቤታችንን ሥጋ አይተው ለመባረክ ያበቃቸው ዘንድ «እሱ(ቅዱስ ቶማስ)ያየውን እኛ ሳናይ» ብለው ያደረጉትን ጾምና ጸሎት አርአያ በማድረግ።
👉 የእመቤታችንን ትንሣኤና ዕርገት ለማሰብ፦ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የእመቤታችንን ሥጋ ከ መቃብር አውጥቶ ወደ ሰማይ ማሳረጉንና መነሳቷን በሃይማኖትና በደስታ ለማሰብ
👉በረከትና ምሕረትን ለማግኘት፦ በጾም፣ በጸሎትና በንስሐ ወደ እግዚአብሔር ቀርበን የነፍስና የሥጋ በረከትን፣ የበደላችንን ይቅርታ ለማግኘት።
2. በጾሙ ወቅት ምን ማድረግ አለብን?
👉በቤተ ክርስቲያን በሚደረጉ የማኅበር ጸሎቶች፣ ቅዳሴና ምህላ ላይ መሳተፍ፣ በግልም ጸሎትና ስግደትን ጭምር።
👉 በንስሐና በቁርባን መዘጋጀት፦ ወደ ንስሐ አባት ቀርቦ ንስሐ መግባትና ተዘጋጅቶ ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን መቀበል።
👉 ለተቸገሩት ወገኖች ምጽዋት መስጠት፣ ሰላምንና ፍቅርን ከሰው ሁሉ ጋር ማጠናከር።
👉ከምግብ ብቻ ሳይሆን ከአንደበት፣ ከአእምሮና ከዓይን ኃጢአት በመጠበቅ በእውነተኛ መንፈሳዊ ህይወት ማለፍ። ድጂታል ሚዲያም እንቀንስ።ዓይን ክፉ ከማየት፥ጆሮም ክፉ ወሬ ከመስማት፥ ይቆጠቡ!
3. የሰበኑ (የልብሷ) ምስጢር
ቅዱስ ቶማስ በደመና ሲመጣ እመቤታችን የተገነዘችበትን ሰበን (ጨርቅ) ሰጥታዋለች። ሐዋርያትም ለበረከት ተካፍለውታል። ዛሬ በቅዳሴ ጊዜ በካህናት እጅ የምናየው ነጭ ጨርቅ (ማኅፈድ) የዚሁ የሰበኗ ምሳሌ ነው!
ጾመ ፍልሰታን በፍቅርና በበረከት እንድንጾም የእመቤታችን አማላጅነት እና እናትነት ፍቅሯ ይደርብን ፡፡
282
✨✨✨🌿🌿✨✨✨🌿🌿✨✨✨🌿🌿
የክርስቶስን አሳብ የተረዱ ጥቂቶች ናቸው፡፡ ከእርሱ የተማሩት ከእርሱ ጋር የተነጋገሩትና እርሱን ያደመጡት እንኳ የዚህን መልካም አስተማሪያቸውን አሳብ የሚቃረን የራሳቸው የሆነ አስተሳሰብ ነበራቸው፡፡
✨✨✨🌿
ጌታችን በአንድ ወቅት ወደ ሳምራውያን መንደር በገባ ጊዜ በዚያች በኃጢአተኞች ከተማ ውስጥ የነበሩ ሰዎች ሊቀበሉት አልወደዱም፡፡ በዚህ ጊዜ ከእርሱ ጋር ከነበሩት ሐዋርያት ሁለቱ ዮሐንስና ያዕቆብ “ጌታ ሆይ ኤልያስ ደግሞ እንዳደረገ እሳት ከሰማይ ወርዶ ያጥፋቸው እንል ዘንድ ትወዳለህን?” ብለውት ነበር። ጌታ ግን ከገሰጻቸው በኋላ
“ምን ዓይነት መንፈስ እንደሆነላችሁ አታውቁም፡፡ የሰው ልጅ የሰውን ነፍስ ሊያድን እንጂ ሊያጠፋ አልመጣም” ነበር ያላቸው:: ሉቃ 9፥52-56፡፡እነዚህ ሁለት ሐዋርያት ያስቡት የነበረው አሳብ መልካሙ አስተማሪያቸው በዚያች ከተማ ውስጥ ለእርሱ የተመረጡ እንዳሉና ሊጠፉ እንደማይገባቸው ያስብ ከነበረው አስተሳሰብ ጋር የማይስማማ አሳብ ነበር፡፡ ሐዋርያቱ እንዲህ በሳምራውያን ላይ ጥላቻ በልቦናቸው እንዲያድር ያደረጋቸው ከፈሪሳውያንና ከጻፎች የሰሙት ትምህርት ነው። ጌታ ግን አሳቡ ድንቅ ስለሆነ ሳምራውያንን ወዶአቸዋል አዝኖላቸዋል። ወደ እርሱም አቅርቦአቸዋል። ስለሆነም ለተከተሉት ሕዝብ ስለ መልካሙ ሳምራዊ ነግሮአቸዋል፡፡ ያቺ ኃጢአተኛዋን ሳምራዊት ሴት ወደ ጽድቅ ለመመለስም ረዥም መንገድ በእግሩ ተጉዞአል፡፡ በዚያች በሳምራውያን ከተማ ለሚኖሩት ሰዎችም አስተምሯል፡፡ ✨✨✨🌿 ስለ አሕዛብም ቢሆን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የራሱ የሆነ ድንቅ አሳብ ነበረው፡፡ አሕዛብ በአይሁድ ዘንድ የተጠሉ ቢሆንም እንኳ ኢየሱስ ክርስቶስ ግን ከአሕዛብ ወገን ስለ ነበረው ስለ ሮማዊው የመቶ አለቃ እንዲህ በማለት መስክሮአል፡፡ “እውነት እላችኋለሁ በእስራኤል እንኳ እንዲህ ያለ ትልቅ እምነት አላገኘሁም፡፡” ማቴ 8፥10። በተጨማሪም ከአሕዛብ ወገን የነበረችውን የከነናዊቷን ሴት እምነትም በማወደስ ተናግሯል። ማቴ 15፥28። ከሰዎች ጋር በሚነጋገርበት ጊዜም ሌሎች የየራሳቸው የሆነ አሳብ ቢኖራቸውም እርሱ የራሱ የሆነና ከእነርሱ የተለየ ድንቅ አሳብ ነበረው፡፡ ያቺ በፈሪሳውያን ኃጢአት ተይዛ ወደ ጌታ የመጣች ሴት ፈሪሳውያን ከበዋት ከአሁን አሁን በድንጋይ ወግረን ልንገድላት ነው እያሉ በሚያሰቡበት ሰዓት የኢየሱስ ክርስቶስ አሳብ ከእነርሱ ፍጹም የተለየ ነበር፡፡ ስለሆነም “ከእናንተ ኃጢአት የሌለበት አስቀድሞ በድንጋይ ይውገራት” አላቸው፡፡ ዮሐ 8፥7። በዚህ ጊዜ ሁሉም ሹልክ እያሉ ሄዱ፡፡ እርሱም “እኔም አልፈርድብሽም ሂጂ፤ ከአሁንም ጀምሮ ደግመሽ ኃጢአት አትሥሪ አላት፡፡ ዮሐ 8፥11። ✨✨✨🌿 ይህ ጨካኝና ስለ ውጪው ብቻ የሚጨነቅ ዓለም እርሱን ትቶ የእርሱን ሥራ እየተመለከተ ሲደነቅ መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሰውን ሁሉ ከሚወድ ልቦናው ጋር ብቻውን ነበር፡፡ ይህንንም ከሚከተለው ከሁለቱ ዓይነ ስውራንና ወደ ጌታ ከመጡት ሕፃናት ታሪክ በግልጽ መረዳት ይቻላል። አንድ ጊዜ ጌታ ከኢያሪኮ ሲወጣ ሁለት ዓይነ ሥውራን በመንገድ ዳር ተቀምጠው ይለምኑ ነበር፡፡ የሚያልፈው ኢየሱስ ክርስቶስ መሆኑን በሰሙ ጊዜም “ጌታ ሆይ የዳዊት ልጅ ማረን” ብለው ጮኹ፡፡ በዚህ ጊዜ ከምድራዊ አስተሳሰቡ ጋር ይጋፋ የነበረው ሕዝብ ጩኸታቸው የክብርን አምላክ የሚረብሸው መስሎ ስለታያቸው ዓይነ ሥውራኑ ዝም እንዲሉ ገሰጹአቸው:: ርኅራኄ የባሕርይ ገንዘቡ የሆነው ኢየሱስ ክርስቶስ ግን ጠራቸውና ዓይኖቻቸውን አበራላቸው፡፡ ማቴ 20፥29-34፡፡ ጩኸታቸውና ልመናቸው ሌሎችን ያበሳጫቸውን ያህል እርሱን አላስቆጨውም፡፡ በሌላ ጊዜም ሕፃናት ወደ እርሱ መጥተው በከበቡት ጊዜ የዚሁ ዓይነት ተመሳሳይ ሁኔታ ተፈጥሮአል፡፡ ደቀ መዛሙርቱ እርሱ የሚቆጣ ስለመሰላቸው ሕፃናቱን ገስጸዋቸዋል፡፡ ጌታ ግን “ሕፃናትን ተዉአቸው ወደ እኔም ይመጡ ዘንድ አትከልክሉአቸው፡፡ መንግሥተ ሰማያት እንደነዚህ ላሉት ናትና' አላቸው፡፡ ማቴ 19፥14፡፡ 📖የነፍስ አርነት 📝አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ 📝አያሌው ዘኢየሱስ እንደተረጎመው ✨✨✨🌿🌿✨✨✨🌿🌿✨✨✨🌿🌿
282
✨🕯✨🕯✨🕯✨🕯✨🕯✨🕯✨🕯✨🕯
ሐምሌ ፳፪ በዚህች ቀን ቅዱስ ዑራኤል ቅዳሴ ቤቱ የሚከበርበትና ለነቢዩ ዕዝራ ሱቱኤል የዕውቀትን ጽዋ ያጠጣበት ዕለት ነው፡፡
የከበረ ቅዱስ ዑራኤል ተረዳኢነቱ አይለየን
✨🕯✨🕯✨🕯✨🕯✨🕯✨🕯✨🕯✨🕯
282
☀️☀️☀️☀️☀️☀️☀️☀️☀️☀️☀️☀️☀️☀️
"እናቴ ሆይ ነፍሴ በአንቺ ዘንድ ትክበር። ስለ ቸርነትሽ እናቴ ነሽ ፤ ስለ ንግሥትነትሽም እመቤቴ ነሽ ፤ ስለ ልጅሽ የመድኃኒት ቀንድ ሆይ አስቢኝ ፤ እንደ ወደቅሁ እቀር ዘንድ አትርሽኝ"
✨አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ✨
🔱⚜🔱⚜🔱⚜🔱⚜🔱⚜🔱⚜🔱⚜
282
ውሉደ ያሬድ ሰንበት ትምህርት ቤት:
✨✨✨💐💐✨✨✨💐💐✨✨✨💐💐
‹‹በእሳትና በውኃ መኻከል አሳለፍኸን›› (መዝ.፷፭፥፲፪)ሥራው ግሩም የሆነ አምላካችን እግዚአብሔር ማዳንም መግደልም የሚችል የባሕርይ አምላክ ነው፡፡ (መዝ.፷፭፥፫) በእርሱ የሚታመኑት ቅዱሳን ሰማዕታት የሚደርስባቸውን መከራና ፈተና ሁሉ በጽናት፣ በልበ ሙሉነት የሚያልፉት ለዚህ ነው፡፡ እሳት ለቅዱሳን ሰማዕታት ጌጣቸው ነው፡፡ በመልክአ ሥላሴ ‹‹የሰማይ ግምጃ ብርሃን ሸማኖች የሆናችሁ ሥላሴ ሆይ ልብሰ ምሕረታችሁ የሰማዕትነት ልብስን ይሁነኝ፤ የእስጢፋኖስ ልብስ ደንጊያ በእኔ ላይ የለምና፤ የሕፃኑ ቂርቆስ ጌጡ የሚሆን እሳትም በእኔ ላይ የለምና›› ብለን የምንጸልየውም ለዚህ ነው፡፡ (መልክአ ሥላሴ፡- ለአትያጺክሙ) ወርቅና ብር በእሳት ተፈትነው እንደሚጠሩ ቅዱሳን ሰማዕታትም በመከራ ውስጥ ተፈትነው እግዚአብሔርን አስደስተው ለእኛም የጽናት ምልክት ሆነው የክብር አክሊልን በመቀዳጀት ከገቡ መውጣት፣ ካገኙ ማጣት እና መከራ ወደ ሌለበት ዘለዓለማዊ ማረፊያቸው ይሄዳሉ፡፡ ቅዱሳን ሰማዕታት በመከራ ነፍስ ከመፈተን በመከራ ሥጋ መፈተንን መርጠው፣ ነፍሳቸውን በእሳተ ገሃነም ከመፈተን በምድራዊው ሰው ሠራሹ እሳት ውስጥ ሥጋቸውን ሳይሰቅቁ በመጨመር በመፈተን ዘለዓማዊ ዕረፍት ማግኘትን መርጠዋል፡፡ ሰው በባሕርዩ እንዲራባ በክፉ ግብር የሚራቡ አጋንንት እያደሩባቸው ዓላውያን ነገሥታት ቅዱሳን ሰማዕታት ላይ በጠላትነት እየተነሡ ያልፈፀሙት ክፉ ሥራ የለም፡፡ በሐምሌ ፲፱ ቀን የመላእክት አለቃ ቅዱስ ገብርኤል ተራዳኢነትን ያገኙት ልጅ እና እናት ቅዱስ ቂርቆስ እና ቅድስት ኢየሉጣም ስለ ንጽሕት ሃይማኖታቸው ለመመስከር ፈተናቸው የመጣውም ከዓላውያን ነገሥታት አንዱ በሆነው በእለ እስክንድሮስ ነው፡፡ ይህ ከሓዲ መኮንን ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስን ይዞ ‹‹ስምህ ማነው›› ብሎ በጠየቀው ጊዜ ‹‹ነቅዕ ዘእምዐዘቅት ንጸሕ ወእማይ ዘኢይማስን ክርስቲያን ስምየ፤ ከንጹሕ ዐዘቅትና ከማይለወጥ ከማይጠፋ ውኃ የተገኘ ስሜ ክርስቲያን ነው›› በማለት መልሶለታል፡፡ ሹሙ እለ እስክንድሮስ በቅዱስ ቂርቆስና በቅድስት ኢየሉጣ ብዛት ያላቸውን መከራ አድርሶም ስላልረካ ጭፍሮቹን በብረት ጋን ውስጥ ሰም፣ ጨው፣ ባሩድ፣ ሙጫ፣ የዶሮ ማር እና እርሳስ ብረትን በማስጨመር ሊያሠቃያቸው ፈለገ፡፡ ከጋኑ የሚወጣው ድምፅም እንደ ነጎድጓድ የሚሰማና ወላፈኑም እንደ ፀሐይ የሚያንጸባርቅ ነበር፡፡ ይህ የጋኑ ፍላት ግርማው እጅግ ያስፈራ ነበርና ቅድስት ኢየሉጣ ተሸበረች፡፡ ልጇ ቅዱስ ቂርቆስ ግን ይህን ፍርሃት ለማራቅ እግዚአብሔር ከእነርሱ በፊት በነበሩት ቅዱሳን በአናንያ፣ በአዛርያ እና በሚሳኤል፣ በሶስና እና በዳንኤል ሕይወት ሥራ ውስጥ የነበረውን የማዳን ችሎታ (ከሃሊነት) እያነሣ ሊያበረታት ሞከረ፡፡ ‹‹እናቴ ሆይ፥ ከሚያልፈው ዓለም ጭንቅና መከራ ለማምለጥ ስትዪ በማያልፈው ዘለዓለማዊ እሳት መቀጣት አይገባሽምና ጽኚ›› አላት፡፡ እንዲሁም ዓይኖቹን ወደ ሰማይ አቅንቶ ወደ እግዚአብሔር እጅግ ልብን የሚነካ ጸሎት አደረሰ፡፡ ‹‹ባርያህ የሆነች እናቴ የሌለችበት ለእኔ ያዘጋጀሃት ርስት ውስጥ ከምገባ ከሕይወት መጽሐፍ ፋቀኝ፤ እርሻውን ልታቃጥል ፍሬውን ልትባርክ፣ ዕንጨቱን ቁረጡና አንድዱት፤ ቅጠሉን ጠብቁት፤ ልትል አይገባም፤ ጠላት ዲያብሎስ የአንተ የሆነውን ቅዱሳኑን ድል ነሳኋቸው ብሎ እንዳይመካና ከመንጋውም አንድ በግ ቀማሁ እንዳይል አቤቱ የኃይል መንፈስ ለእናቴ በመስጠት አበርታት›› በማለት ጸለየ ፡፡ የዚህ ሕፃን ሲሆን በመንግሥተ ሰማያት ለእናቱ አባት የሆነ ቅዱስ ጸሎት ከእግዚአብሔር ደርሶ እናቱን አጽንቶ ጭራሽ የብረት ጋኑን ውኃ በምንጭ ላይ በዝቶ እንደሚወርድ ጠል ሁኖ አሳያት፤ ወዲያውም ሁለቱንም ከብረት ጋን ውስጥ ጨመሯቸው፡፡ እሳቱ ዓርባ ክንድ ወደላይ ተመዝዞ ወጥቷል (ወተለዓለ ነበልባል መጠነ አርብዓ በእመት) ፣ የሁለቱ ቅዱሳን ሰማዕታት አምላክም ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤልን ከሰማይ ልኮ በብርሃን በትር ቢመታው እንዳደረ ውርጭ ሆኗል፡፡ የብረት ጋኑም እሳት ጠፍቶ አንዳች ሳይጎዱ ምስክርነታቸውን ፈፀሙ፡፡ በዚህም አስቀድሞ ቅዱስ ዳዊት በመዝሙሩ የዘመረው ቃል ተፈፀመ፡፡ ይህም፡- ‹‹አኅለፍከነ ማዕከለ እሳት ወማይ፤ በእሳትና በውኃ መካከል አሳለፍኸን፡፡›› በቀደመ ግብሩ እሳት የነበረ በኋላ ግብሩ ውኃ ሆነ፡፡ (መዝ.፷፭፥፲፪) ቃሉ የማይታበል ልዑል እግዚአብሔር አስቀድሞ በነቢየ ልዑል ቅዱስ ኢሳይያስ የተናገረውን ቃልም በሁለቱ ቅዱሳን ሰማዕታት ተፈፅሞ አገኘነው፡፡ ‹‹ወእመኒ ዐደውከ ማየ አነ: ሀሎኩ ምስሌከ: ወአፍላግኒ ኢያሰጥሙከ ወእመኒ ዐደውከ እሳተ ነበልባል ኢያውዕየከ፤ በውኃ ውስጥ ባለፍህ ጊዜ ከአንተ ጋር እሆናለሁ፤ በወንዞችም ውስጥ ባለፍህ ጊዜ አያሰጥሙህም፤ በእሳትም ውስጥ በሄድህ ጊዜ አትቃጠልም፤ ነበልባሉም አይፈጅህም፡፡›› (ኢሳ.፵፪፥፪) እኛ እንደነ ቅዱስ ቂርቆስ እና ቅድስት ኢየሉጣ ከእሳት እና ከፈላ ውኃ ውስጥ ጨክኖ በመግባት በእምነት መውጣት የምንችልበት አቅምም ሆነ የጸሎት ኃይል ባይኖረንም በልባችን ጋን ውስጥ እየነደደ ለሀገራችን ኢትዮጵያም የተረፈው በፍቅርና በአንድነት እንዳንኖር ያስቸገረንን ክፉ እሳት አምላካችን ልዑል እግዚአብሔር መልአኩ ቅዱስ ገብርኤልን ልኮ እንዲያጠፋልን መለመን ይገባል፡፡ ለዚህም የአምላካችን ልዑል እግዚአብሔር ቸርነት፣ የመልአኩ ቅዱስ ገብርኤል አማላጅነት አይለየን! ምንጭ ፡- • መጽሐፍ ቅዱስ • ድርሳነ ቅዱስ ገብርኤል ዘሐምሌ • የመዝሙረ ዳዊት ትርጓሜ • መጽሐፈ ስንክሳር • መልክአ ሥላሴ © ማኅበረ ቅዱሳን ✨✨✨💐💐✨✨✨💐💐✨✨✨💐💐
282
✨✨✨🍂✨🍂✨🍂
ኃጥእ በደለኛ ነህን? ተስፋ አትቁረጥ! ወደ ቤተክርስቲያን መጥተህም ንስሓ ግባ፡፡ ኃጢአት ሠርተሃልን? እግዚአብሔርን “በድያለሁ” በለው፡፡ “በድያለሁ” ብለህ ለመናዘዝ የሚጠይቅህ ድካምና ጥረት እንደ ምን ያለ ነው? “በድያለሁ [ይቅር በለኝ]” ለማለት የሚጠይቅህ ዓይነት የሕይወት መንገድ ወይም እንደ ምን ያለ መከራ ነው? “በድያለሁ” ብሎ አንዲት ቃል ለመናገር ክብደቱ ምኑ ላይ ነው? ምናልባት ኃጥእ ነኝ ብለህ ራስህን ባትጠራ፥ ዲያብሎስ በዚህ እንደማይነቅፍህ አስበህ ነውን?
✨✨🍂
በፍጹም! እንዲያውም ንስሓ ባትገባ ይህን ከዲያብሎስ የሚመጣ ነቀፋ እንደሚኖር ጠብቅ፡፡ የከሳሽ ግብሩ ንስሓ እንዳትገባ መከልከል በዚያ ንስሓ ባልገባህበት በደልም አንተን መውቀስ ነውና ንስሓ ባትገባ ይህን ጠብቅ፡፡ ስለዚህ ለቅጽበት ያህልስ እንኳን የማይተኛ ከሳሽ እንዳለህ ዐውቀህ ለምን እንዳይወቅስህ አትከለክለውም? ለምን በደልህን ተናዝዘሃት አታስወግዳትም?
✨✨🍂
ኃጢአት ሠርተሃልን? ወደ ቤተ ክርስቲያን ና፡፡ “በድያለሁ” ብለህ ለእግዚአብሔር ንገረው፡፡ እኔ ከዚህ ውጪ ከአንተ የምፈልገው ሌላ ምንም ነገር የለኝም፡፡ መጽሐፍ ሲናገር፡- “ትከብር ዘንድ አንተ አስቀድመህ ኃጢአትህን ተናገር” ይላል (ኢሳ.43፡26)፡፡
ስለዚህ ኃጢአትህን ታስወግዳት ዘንድ ተናዘዛት፡፡ ይህን ለማድረግ ድካም ጥረት አይጠይቅህም፡፡ አንደበተ ርቱዕ መኾን አያሻህም፡፡ ገንዘብ መክፈል አያስፈልግህም፡፡ ወይም እነዚህን የመሰሉ ሌሎች ነገሮች አያስፈልጉህም። አስቀድመህ በደልህን በሰቂለ ሕሊና በነቂሐ ልቡና ኾነህ አስባትና አንዲት ቃል ተናገር፡- “በድያለሁ” ብለህ ተናዘዛት፡፡
✨ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ፣ "ንስሐና ምጽዋት"
📚ገጽ 28
📖በገብረ እግዚአብሔር ኪደ የተተረጎመ
✨✨✨🍂✨🍂✨🍂
