ተማሪ
Открыть в Telegram
“አንተ ግን በተማርህበትና በተረዳህበት ነገር ጸንተህ ኑር፥ ከማን እንደ ተማርኸው ታውቃለህና፤” — 2ኛ ጢሞቴዎስ 3፥14
Больше293
Подписчики
-124 часа
-27 дней
-1530 день
Архив постов
293
“ ኃጢአትን አለመሥራት እጅግ መልካም ነው፤ ብትሠራ ግን ንስሐን ባትቃወም ጥሩ ነው፤ ንስሐ ከገባህ ደግሞ ወደ ኃጢአት ባትመለስ የተሸለ ነው፤ ወደ ኃጢአት ካተመለስክ ደግሞ ይህን ያደረገልህን አምላክ ማመስገን መልካም ነው”
ማር ይስሐቅ
293
"የሰው ልጆች ሁሉ አዋቂ ናቸው የሚባለው ስህተት ነው። አዋቂ ማለት መጽሐፍትን ጠንቅቆ ያወቀ ሳይሆን ከኃጢአት በመቆጠብ ነፍሱን የማይጎዳ፣ አምላክን በማመስገን በማያወላውል በቅድስና ሥራ መልካም በመሥራት ነፍሱን የሚመግብ ያ ሰው እሱ ብቻ አዋቂ ተብሎ ይጠራል።"🍁🍁🌿ታላቁ ቅዱስ እንጦንስ
“ተአምራትን ማድረግ ትፈልጋላችሁን? እንኪያስ በዘፈን የደነቆረን ጀሮ መዝሙር እንዲሰማ አድርጉት፡፡ ሴትን በመመኘት የታወረው ዐይን ፈጣሪውን እንዲያይ አድርጉት፡፡ በስርቆት የሰለለ እጅ በምጽዋት እንዲዘረጋ አድርጉት፡፡ ወደ ኃጢአት ቤት በመሄድ ሽባ የሆነውን እግር ወደ እግዚአብሔር ቤት እንዲሮጥ አድርጉት፡፡ ሐሜትን በማውራት ዲዳ የሆነውን ከንፈር መልካም ንግግርን እንዲናገር አድርጉት፡፡ ከተአምራት ሁሉ የበለጠ ተአምር ይሄ ነው፡፡"🍁🍁🌿 ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
"ጌታ ሆይ ዕውሩን ሂድ ብለህ ወደላክህበት ወደ ሰሊሆም መጠመቂያ አሁን ልንሔድ አንችልም። ነገር ግን ሕይወትንና ብርሃንን የተሞላው የከበረ ደምህ ያለበት ጽዋ በእኛ ዘንድ አለ። ከእርሱ በተቀበልን ቁጥር እንነጻለን"🍁🍁🌿 ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ
293
🍁🍁🍁✨✨✨🍁🍁🍁✨✨✨🍁🍁🍁✨✨✨
✨✨መድኃኔዓለም✨✨
" ጌታችንና አምላካችን መድኃኒታችን ክርስቶስ ሆይ ቤተ ክርስቲያንህ ትሰግድልሃለች፣ ሙሽራህም ከፍ ከፍ ታደርግሃለች፣ በልዑላን ጥቅም፣ በሱራፌል ቅዳሴና በኪሩቤል ውዳሴ በመላእክትም ምስጋና፣ በትጉሃን ልመና ፣ በቅዱሳንም ፍጹምነት፣
በአዳም ንጽሕና በኖኅም መሥዋዕት በአብርሃም እንግዳ ተቀባይነት፣ በይስሐቅ ቸርነት፣ በያዕቆብ መገለፅ።
🍁✨✨
በዮሴፍ እሥራት ፣ በኢዮብ ትዕግሥት በሙሴም የዋህነት በኤልያስም ምስጋና።
በሐዋርያትም ማፍቀር፣ በቅዱሳንም ልመና፣ በተሰደዱ ሰዎች ድካም፣ ባልበደሉ ሰዎች ጽድቅ ንጽሕናን ባገኙ ሰዎች ትሕትና፣
በንጹሐን ገድል፣ ከምግብ በተለዩ ሰዎች ትምህርት፣ ፍጹማን ስለሆኑ ቅዱሳን ጽድቅ ፣
🍁✨✨
በምድር ዳርቻ ርቀት፣ በባሕር አዝዋሪም ጥልቅነት፣ በመባርቅት፣ ብልጭታ፣ በደመናትም መውጣት፣
በመላእክት ምስጋና፣በቅዱሳንም ምስጋና፣ በትጉሃን ንጽሕና፣ በልዑላንም መስማማት ፣
በመንፈሳውያን ብርሃን፣ በካህናት ቀኝ ፣ በሰማዕታት መሞት ፣ በምዕመናንም ደም፣
በብርሃናውያን መላእክትም ገናንነት።
🍁✨✨
በልጅህ መመታት በአንድ ልጅህ ሕማማት ሁሉን በያዘ ሥልጣንህም፣ ወደ ጌታችንና ወደ መድኃኒታችን ወደ ኢየሱስ ክርስቶስ አባት በምታርግ ጸሎት። "
✨ቅዳሴ ቄርሎስ
🍁🍁🍁✨✨✨🍁🍁🍁✨✨✨🍁🍁🍁✨✨✨
293
🌱🍂🌱🍂🌱🍂🌱🍂🌱🍂🌱🍂🌱🍂🌱
ጰራቅሊጦስ፦ ማለት መንጽሒ (የሚያነጻ)፣ መጽንዒ (የሚያጸና)፣ መስተፈሥሒ (ደስታን የሚሰጥ)፣ መስተሥርይ (ኃጢአትን ይቅር የሚል)፣ ናዛዚ (የሚያረጋጋ)፣ ከሣቲ (ምሥጢርን የሚገልጥ) የሚል ትርጉምን ይሰጣል መጻሕፍተ ሠለስቱ ሐዲሳት።
"ዐቢየ ተስፋ ዘአስፈዎሙ ይቤሎሙ ኢየሱስ ለአርዳኢሁ እስእሎ ለአቡየ ይፈኑ ለክሙ መንፈሰ ጽድቅ ጰራቅሊጦስ።"
ትርጉም፡-
ታላቅ ተስፋ ያደረገላቸው ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ደቀመዛሙርቱን አባቴን እለምነዋለሁ እውነት መንፈስን ይልክላችኋል።
ሊቁ ቅዱስ ያሬድ።
"ወበ፶ ዕለት ፈነወ ሎሙ መንፈሰ ቅዱሰ ከመ ዘእሳት ወተናገሩ በነገረ ኵሉ በሐዉርት።"
ትርጉም፦
በሃምሳውም ቀን በእሳት አምሳል መንፈስ ቅዱስን ሰደደላቸው በአገሩ ሁሉ ቋንቋ ተናገሩ።
የቅዳሴ ቅዱስ ዲዮስቆሮስ።
🍃🍂🍂🍃🍂🍃🍂🍃🍂🍃🍂🍃🍂🍃🍂
293
✨✨✨🌹🌹🌹✨✨✨🌹🌹🌹✨✨✨🌹🌹🌹
እንኳን አምላክን ለወለደች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በደብረ ምጥማቅ በስሟ በተሠራች ቤተ ክርስቲያን ጉልላት ላይ በብርሃን መርከብ ተቀምጣ ፊቷ በግልጥ ለታየበት ፤ የክርስቲያን ወገኖች ሁሉም ታላቅ በዓልን ላደረጉበት ለተወደደች ዕለት በሰላም አደረሳችሁ🙏
🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀
"አመ ትበርቂ በደብረ ምጥማቅ ኀምሰ ዕለታተ። ትእምርተ ገጽኪ ይርአይ እስከ ይትነሣእ ዘሞተ። ሚ መጠነ ማርያም ታሥተፌሥሒ ትፍሥሕተ። ኅድጊሰ ጽጌ ፍቅርኪ በጊዜ ንቃሑ መዓልተ። ብፁዕ ዘርእየኪ በሕልሙ ሌሊተ"።
ትርጉም፦
✨✨🌹
የፊትሽን መልክ ያይ ዘንድ የሞተ ሰው እስኪነሣ ድረስ በደብረ ምጥማቅ ለአምስት ቀናት ያኽል በተገለጽሽ ጊዜ ማርያም ምን ያኽል ደስ ታሰኚ ኖሯል! በቀን የታየው የፍቅርሽ አበባ ይቅርና ሌሊት በሕልሙ ያየሽ ምስጉን ነው።
አባ ጽጌ ድንግልና
አባ ገብረ ማርያም
በማኅሌተ ጽጌ።
✨✨✨🌹🌹🌹✨✨✨🌹🌹🌹✨✨✨🌹🌹🌹
293
ውሉደ ያሬድ ሰንበት ትምህርት ቤት:
✨✨✨🍂🍂🍂✨✨✨🍂🍂🍂✨✨✨🍂🍂🍂
🍂🍂✨ቅዱስ ዮሐንስ ፍቁረ እግዚእ 🍂🍂✨
አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ በቅዱስ ወንጌሉ እንደነገረን በመንግስተ ሰማያት ታላቁ ሰው ወንጌላዊው ዮሐንስ ነው:: ቅዱሱ ሐዋርያ ከዘብዴዎስና ከማርያም ባውፍልያ ተወልዶ: በገሊላ አካባቢ አድጐ: ገና በወጣትነቱ መድኃኔ ዓለምን ተከትሎታል::
ቅዱስ ዮሐንስ ከሐዋርያት ቀድሞ ጌታን ከመከተሉ ባሻገር በምንም ምክንያት ከጐኑ አይጠፋም ነበር:: ስለ ንጽሕናውና በጐ የፍቅር ሕሊናው ሕጻን ሳለ በወንድሞቹ ሐዋርያት ዘንድ ሞገሱ ከፍ ያለ ነው:: ጌታችንን እስከ እግረ መስቀሉ ድረስ በመከተሉ ድንግል እመቤታችንን ተቀብሏል::
🍂🍂✨
ከእርሷ ጋር ለ15 ዓመታት ቢቀመጥ መዝገበ ምሥጢር ሆነ:: ስንኩዋን ከሰው ልጆች ይቅርና ከልዑላኑ መላዕክትም ማዕረጉ ከፍ አለ:: ሰው ቢበቃ መላእክትን ሊያይ ይቻለዋል:: ቅዱስ ዮሐንስን ግን መላእክት ሊያዩት ይከብዳቸዋል:: ከፍጥረት ወገን ከእመ ብርሃን ቀጥሎ ክቡር እርሱ ነው::
🍂🍂✨የፍቅር ሐዋርያ
ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ዮሐንስን 'የፍቅር ሐዋርያ' ትለዋለች:: ለ70 ዘመናት በቆየ ስብከቱ ስለ ፍቅር ብዙ አስተምሯል:: ፍቅርንም በተግባር አስተምሯል:: በየደቂቃውም "ደቂቅየ ተፋቀሩ በበይናቲክሙ - ልጆቼ ሆይ! እርስ በርሳችሁ ተዋደዱ" እያለ ይሰብክ ነበር::
በተለይ ደግሞ ከፈጣሪው ክርስቶስ ጋር የነበረው ፍቅር ፍጹም የተለየ ነበር:: በዚህ ምክንያትም ጌታ ባረገ ጊዜ እንዲህ ብሎታል:- "ለፍጡር ከሚገለጥ ምሥጢር ከአንተ የምሠውረው የለኝም" ብሎታል::
🍂🍂✨
ቀጥሎም በንጹሕ አፉ ስሞታል:: ሊቁ:-
"ሰላም ለአፉከ ለዮሐንስ ዘሰዓሞ:
ንጽሐ ኅሊናሁ ወልቡ ለዐይነ ፍትወትከ ሶበ አደሞ" እንዳለው:: (መልክዐ ኢየሱስ)
ቅዱስ ዮሐንስ ከእመቤታችንም ጋር ልዩ ፍቅር ነበረው:: እርሷ እንደ ልጇ ስትወደው: እርሱ ደግሞ እንደ እናቱ ልቡ እስኪነድ ድረስ ይወዳት ነበር:: እስከ እግረ መስቀሉ ድረስ ተከትሎ ያገኛት እመቤቱ ናትና::
🍂🍂✨
ከዚያ ሁሉ ጸጋና ማዕረግ የመድረሱ ምሥጢርም ድንግል ናት:: ለ15 ዓመታት በጽላሎተ ረድኤቷ (በረዳትነቷ ጥላ) ተደግፎ አብሯት ሲኖር ብዙ ተምሯል:: ከመላእክትም በላይ ከብሯል:: ከንጽሕናዋ በረከትም ተካፍሏል::
ስለ ድንግል ማርያምም "ነገረ ማርያም" የሚል ድርሰት ሲኖረው "የሰኔ ጐልጐታንም" የጻፈው እርሱ ነው::
ድንግል ባረፈችበት ቀንም ልክ እንደ ልጇ ክርስቶስ እርሷም ስማው: ታቅፋው ዐርፋለች:: ሊቃውንቱ ለዚህ አይደል በንጹሕ ከንፈሮቿ መሳምን (መባረክን) ሲሹ:-
"በከመ ሰዓምኪ ርዕሰ ዮሐንስ ቀዳሚ:
ስዒሞትየ ማርያም ድግሚ" ያሉት::
🍂🍂✨
ታላቁ ቅዱስ ሐዋርያ ዕድሜው 90 ዓመት በሆነው ጊዜ ተሰውሯል:: ከዚያ አስቀድሞም የዓለምን ፍጻሜ ተመልክቷል:: ዛሬ ያለበትን የየሚያውቅ ቸር ፈጣሪው ነው::
✨✨🍂
ይሕች ዕለት ለሐዋርያው ቅዳሴ ቤቱ ናት::
እናት ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ዮሐንስን ስትጠራው እንዲሕ ነው:-
✨ወንጌላዊ
✨ሐዋርያ
✨ሰማዕት ዘእንበለ ደም
✨አቡቀለምሲስ (ምሥጢራትን ያየ)
✨ታኦሎጐስ (ነባቤ መለኮት)
✨ወልደ ነጐድጉዋድ
✨ደቀ መለኮት ወምሥጢር
✨ፍቁረ እግዚእ
✨ርዕሰ ደናግል (የደናግል አለቃ)
✨ቁጹረ ገጽ
✨ዘረፈቀ ውስተ ሕጽኑ ለኢየሱስ (ከጌታ ጎን የሚቀመጥ)
✨ንስር ሠራሪ
✨ልዑለ ስብከት
✨ምድራዊው መልዐክ
✨ዓምደ ብርሐን
✨ሐዋርያ ትንቢት
✨ቀርነ ቤተ ክርስቲያን
✨ኮከበ ከዋክብት
በቅዱስ ዮሐንስ ላይ ያደረ የእመቤታችን ድንግል ማርያምና የአንድ ልጇ ፍቅር በእኛም ላይ ይደር::
✨✨🍂
ቅዱስ ዮሐንስን የወደደ ጌታ በፍቅሩ ይጠግነን:: ከእናቱ ፍቅር አድርሶ በሐዋርያው በረከት ያስጊጠን::
✨✨✨🍂🍂🍂✨✨✨🍂🍂🍂✨✨✨🍂🍂🍂
293
✨️️️️️️️✨️️️️️️️✨️️️️️️️🍂✨️️️️️️️✨️️️️️️️✨️️️️️️️🍂✨️️️️️️️✨️️️️️️️✨️️️️️️️🍂
✨️️️️️️️ልዩ ፍርድ ቤት✨️️️️️️️
ብዙዎቻችን ወንድሞቻችንን ለማማት የፈጠንን ነን፡፡ የራሳችንን ግንድ ትተን የሰውን ጉድፍ ለማውጣት የምንቻኮል ነን፡፡ በወንድሞቻችን ላይ ለመፍረድ፥ እኅቶቻችንን ለመኰነን የምንጣደፍ ነን፡፡
ወዳጄ ሆይ! መፍረድ የእግዚአብሔር እንጂ ያንተ ሥልጣን አይደለምና ተጠንቀቅ፡፡ እህቴ ሆይ! በአምላክ ዙፋን ላይ ለመቀመጥ አታስቢ፡፡ወዳጄ ሆይ! መፍረድ አማረኽን? እንኪያስ ምንም ወቀሳ የሌለበት፣ ይልቁንም ብዙ ጥቅም የሚያስገኝ የፍርድ ችሎት አለልህ፡፡ በራስህ ላይ መፍረድ ትችላለህና ተቀመጥ፡፡ ከኹሉም አስቀድመህ የበደልህን መዝገብ በፊትህ አኑረው፡፡ ነፍስህ የሠራችውንም ወንጀል በሙሉ በጥንቃቄ መርምር፡፡ ከዚያም “ነፍሴ ሆይ! ይኽንና ያንን በደል የፈጸምሽው ስለምንድነው?” በላት፡፡ የበደለችበትን ምክንያት ትታ በሌሎች ላይ ለማሳበብና በሌሎች ላይ ለመፍረድ ከዠመረችም “የተከሰስሽው በራስሽ ወንጀል እንጂ በሌላ ሰው ወንጀል አይደለም፡፡ እዚኽ ፍርድ ቤት የመጣሽው ስለእነዚያ ሰዎች ለመመስከር አይደለም፡፡ ስለዚኸ ንገሪኝ! ይኽን ያኽል በደል የፈጸምሽው፣ ይኽን ያንን ኹሉ ጥፋት ያጠፋሽው ስለምንድነው?” በላት፡፡ ዘወትር ይኽን የመሰለ አስጨናቂ ጥያቄ ጠይቃት፡፡ አፍራ የምትመልሰው ከሌላትም አስፈላጊውን ፍርድ (ቀኖና) ወስንባት፡፡ ይኽን ልዩ ፍርድ ቤት ዘወትር የምትቀመጥ ከኾነ ያንን የእሳት ባሕር፣ ያ እሳቱ የማይጠፋው ትሉ የማያንቀላፋው ስቃይ በልቡናህ ይቀረጻል፡፡ ✨️️️️️️️🍂 “ወደ እኔ መጥቶ ነው፤ እርሱ አታልሎኝ ነው፤ እርሱ ፈትኖኝ ነው" እያለች በዲያብሎስ እንድታመካኝም አትፍቀድላት፡፡ ይልቁንም፡- "አንቺ ባትፈቅጂ ነው እንጂ እነዚኸ ኹሉ በአንቺ ላይ ሥልጣን የላቸውም" ብለህ ንገራት፡፡ "እኔ እኮ ሥጋ ለባሽ ነኝ፤ የምኖረውም በዚኽ ኃጢአት በሞላበት ዓለም ነው" ካለችህም "ይኽ ኹሉ ሰበብና ምክንያት ነው፡፡ ብዙዎች አንቺ የለበስሽውን ሥጋ ለብሰው በዚኽ ዓለም ኑረው ጻድቃንና ሰማዕታት ኾነዋል፡፡ አንቺ ራስሽ አንዳንድ ጊዜ መልካም ምግባራትን ስታደርጊ ይኸ አኹን የምታሳብቢበትን ሥጋ ለብሰሽ ነው" በላት፡፡ ይኽን ስትላት ቢያማትም እጅህን አታንሳባት፡፡ ምክንያቱም ቀኖናው ከሞት የሚታደጋት መንፈሳዊ ልምምድ እንጂ የሚገድላት ቅጣት አይደለምና፡፡ ስለዚኽ ምክንያት የምታበዛብህ ከኾነ “እባብ አሳተኝ" ብላ ከተጠያቂነት ያለመለጠችውን ሔዋንን አስታውሳት፡፡ ይኽን ኹሉ ስታደርግም ከአጠገብህ ማንም አይኑር፡፡ የሚረብሽህ ሰው ከአጠገብህ አይገኝ፡፡ ይልቁንም ዳኛ በፍርድ ወንበር ላይ እንደሚቀመጥ አንተም በፍርድ ወንበር ፈንታ በምቹ ጊዜና ቦታ በጽሞና ተቀመጥ፡፡ ነቢዩ “በመኝታችሁ ሳላችሁ በልባችሁ የምታስቡት ይታወቃችሁ" እንዳለው /መዝ.4፥4/ ይኽ ቦታና ጊዜ ከኹሉም ይልቅ ተስማሚ ነውና እራትህን ከበላህ በኋላ ዘወትር ይኽን የፍርድ ወንበር ወደ መኝታ ክፍልህ ይዘኸው ሒድ፡፡ ዕለት ዕለት ይኸን የምታደርግ ከኾነ ሐዋርያው “እኛ በራሳችን ብንፈርድ ኖሮ ባልተፈረደብንም ነበር" እንዲል (1ኛ ቆሮ.1፥31) በዚያ አስፈሪው የፍርድ ወንበር ፊት ያለ ፍርሐት ትቆማለህ፡፡ 📝ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ 📚ሰማዕትነት አያምልጣችሁ እና ሌሎች ✨️️️️️️️ገጽ 42-42 📝በገብረ እግዚአብሔር ኪደ የተተረጎመ ✨️️️️️️️✨️️️️️️️✨️️️️️️️🍂✨️️️️️️️✨️️️️️️️✨️️️️️️️🍂✨️️️️️️️✨️️️️️️️✨️️️️️️️🍂
293
💐🌹💐🌹💐🌹💐🌹💐🌹💐🌹💐🌹💐🌹
እንኳን ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የልደት በዓል በሰላም አደረሳችኹ🙏
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
"ሰላም ለማርያም ቅድስት እሙ ለፀሓየ ጽድቅ፤ ማኅደረ መለኮት፤ ዘኤዶም ገነት እንተ ዕፀዊሃ ስርግዋን በሥነ ሕይወት፤ እለ ይፈርዩ አፈዋተ፤ ወእለ ይጸግዩ በረከት፤ ዘአበው በአተ መዛግብት እንተ ውስቴታ ዕንቊ ወያክንት።
የአባቶች የሐብታቸው ማከማቻ በር (መግብያ)፤ በውስጦቿ ዕንቊና ያክንት ያሉባት፤ ሽቶን የማያፈሩ በረከትንም የሚያብቡ ዕንጨቶቿም የሕይወት ውበት ያጌጡ የተሸለሙ የኤዶም ገነት የተባለች፤ የመለኮት ማደርያ የፀሓይ ጽድቅ እናቱ ቅድስት (ንጽሕት፣ ጽንዕት፣ ክብርት፣ ልዩ) ለኾነች ማርያም ሰላምታ ይገባል።"
ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ - በተአምኆ ቅዱሳን
💐🌹💐🌹💐🌹💐🌹💐🌹💐🌹💐🌹💐🌹
293
✨✨✨🍁✨✨✨
✨አላወቁትም ነበር✨
ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከተነሣ በሃያ አምስተኛው ቀን ደቀ መዛሙርቱን በገሊላ ባሕር ዳርቻ አገኛቸው።
አስቀድሞ እሱ ቢያውቃቸውም እነሱ ያወቁት ዘግይተው ነው። “ጌታ እኮ ነው” ዮሐ. 21፥7 ብሎ ጌታ ይወደው የነበረ ደቀ መዝሙሩ ቅዱስ ዮሐንስ እስኪናገር ድረስ ማንም ያወቀው አልነበረም።
በአጠገባቸው ቆሞ አላወቁትም፤
“ልጆች ሆይ አንዳች የሚበላ አላችሁን?” ሲላቸውም አላወቁትም፤ “የለንም” ብለው መለሱለት።
“መረባችሁን በመርከቡ በስተቀኝ በኩል ጣሉት ታገኙማላችሁ” አላቸው፤ ስምዖን ጴጥሮስ እና ሌሎችም ደቀ መዛሙርት ለቃሉታዝዘው መረባቸውን ሲጥሉ ጌታ መሆኑን አውቀውት አይደለም፤ በባሕር አጠገብ ስላገኙት ዓሣ የማጥመድ ልምድ ያለው ሰው መስሏቸው ነበር እንጂ።
✨✨🍁
ለሚያውቃቸው ጌታ ሳያውቁት ታዘዙለት፤ በባሕር ውስጥ ያለውን የሚያውቅ ጌታ በባሕር ውስጥ ያሉ ዓሣዎችን በደቀ መዛሙርቱ መረብ እንዲገቡ አዘዛቸው።
ዮናስ ወደ ባሕር በተጣለ ጊዜ የሚውጠው ታላቅ ዓሣ ያሰናዳ እርሱ ነው፤ ዛሬም የደቀ መዛሙርቱን መረብ የሚሞላ ዓሣ በባሕር ውስጥ ያሰናዳ እርሱ ነው።
ያኔ ባሕር በቃሉ የተገሠጸችለት ማቴ. 8፥23 ዛሬም ዓሣ የገበረችለት እርሱ ነው። ይህ እስኪሆን ድረስ ደቀመዛሙርቱ አላወቁትም ነበር።
ሌሊቱን ሙሉ ባዶ የነበረው መረብ በአንድ ጊዜ በዓሣ ተሞላ፤ ስቦ ማውጣት ተሳናቸው። በዚህ ጊዜ ነው ደቀ መዛሙርቱ ጌታ መሆኑን መነጋገር የጀመሩት። መልኩን አይተው ባያውቁትም ሥራውን አይተው አወቁት።
✨✨🍁
ከባሕሩ ዳርቻ ሲቆም ከገሊላ ሰዎች እንደ አንዱ ሆኖ ነበርና በምን ያውቁታል?
ባሕሩ ሲታዘዝለት ግን ከገሊላ ሰዎች ተለየባቸው።
“አንዳች የሚበላ አላችሁን?” ብሎ ሲጠይቃቸው ከተራቡ ሰዎች እንደአንዱ መስሏቸው ነበር፤ የተራበውን መረባቸውን በአንድ ቃል ሲሞላላቸው ግን ጌታ መሆኑን አወቁት።
መረብ የለውም፤ ነገር ግን መረብ ላላችቸው ሰዎች መረብ መጣልን የሚያስተምር ሆኖ ቢያገኙት አወቁት።
ዓሣ ሲያጠምድ አላዩትም፤ ነገር ግን ዓሣ ለሚያጠምዱ ሰዎች ዓሣ ማጥመድን ሲያስተምር ሲሰሙት አመኑበት።
“በስተቀኝ በኩል ጣሉት ታገኙማላችሁ” ሲላቸው እስኪ ካገኘህ አንተሞክር “እኛስ ሌሊቱን ሙሉ ደከምን ያገኘነው ምንም የለም” ያለው የለም።
“ባሕሩን የምናውቀው እኛ ነን አንተ ዓሣ ያለበትን እንዴት ታውቃለህ?” አላሉትም። ለማያውቁት ታዘዙለት፤ ከመካከላቸው ላልነበረው፤ ተስፋ በቆረጡ ጊዜ ቀና ሲሉ ከባሕሩ ዳርቻ ቆሞ ለተመለከቱት ሰው ቃል እሺ በጄ ብለው መረባቸውን ጣሉለት።
ቃሉን መስማታቸው የቃሉን ባለቤት ወደ ማወቅ አደረሳቸው። እሱም የነገራቸው የሚያውቀውን እንጂ የገመተውን አልነበረምና መረባቸውን በጣሉ ቅጽበት ከሚያስፈልጋቸው በላይ የተትረፈረፈ ስጦታን ሰጣቸው።
ጴጥሮስና ሌሎችም ደቀ መዛሙርት ዓሣ ለማጥመድ የመረጡት ጊዜ ዓሣ አጥማጆች የሚመርጡት ጊዜ ነው፤ ብዙ ጊዜ ዓሣዎች ሰፊ እንቅስቃሴ የሚያደርጉበት ጊዜ ሙቀት የሌለበትን ጊዜ ስለሚመርጡ ነው። ነገር ግን ክርስቶስ የመጣበትም ሰዓት ሲነጋ ስለመጣ ሊመረጥ የሚችል ሰዓት ነበር፤ የፀሐይ ሙቀት ገና በስሱ ምድርን እየተቆጣጠረ የነበረበት ጊዜ ነበርና። ይኽ ሰዓት የሌሊቱ ድካማቸው ውጤት የሚያስገኝበት ጊዜ ቢሆንም ስላጡት ነገር በመጨነቅ ላይ ስለነበሩ ስለሚያገኙት ነገር ተስፋ በልባቸው አልነበራቸውም።
✨✨🍁
መረባቸው ብቻ ሳይሆን ልባቸውም ባዶ ነው።
የደቀ መዛሙርቱ ታሪክ መንገዱን የሚለውጠው ከዚያ ሰዓት ጀምሮ ነው፤ የታሪክ መጀመሪያህ እግዚአብሔርን በማወቅ የሚጀምር ከሆነ የተለወጠውን ታሪክህን ሊያበላሽ የሚችል ምንም ነገር የለም። ያለፈውን ሌሊት የሚያስረሳ ዘመን ይመጣል፤ ባዶ መረብ ይዞ መመላለስ የሚያቆምበት ሰዓት ይደርሳል፤ ያሰብነውን ብቻ ሳይሆን ያላሰብነውንም ሊሰጠን መድኃኔ ዓለም ወደ እኛ ይመጣል።
አስቀድሞ ራሱን አይገልጥም፤ በዚህ ዓለም እንዳሉ አጭበርባሪዎችም ከስጦታው አስቀድሞ የምናገኘውን እያሰብን በማይሆን ተስፋ ሆዳችንን አይሞላም። እንዲያውም ምንም እንደሌለን እያወቀ “የሚበላአላችሁን?” የሚል ምስኪን ሰው ሊመስለን ይችላል። ያስተዋለ ሰው ብቻ የሚያገኛት በረከቱን መታዘዝ ስንጀምር ብቻ መቀበል እንጀምራለን።መታዘዝ እንጀምር፤ የጠየቅነውን እንቀበላለን። ታሪክ የሚለወጠው በእግዚአብሔር ቃል ስንኖር ነው። በታንኳችን በስተቀኝ በኩል የጣልነው መረብ በመለኮታዊ ስልጣን የምትተዳደር ነፍስ ምሳሌ ነው፤ ነፍሳችንን ለመለኮታዊ ፈቃዱ እናስገዛ፤ ያንጊዜ ለውጡ በሕይወታችን ይጀምራል። 📝ሊቀ ሊቃውንት ስምዓኮነ መልአክ ✨✨✨🍁✨✨✨
293
+ በራስህ ክፉ ነገር አታድርግ +
ይድረስ ለተከፋኸው ወንድሜ
መኖር ለደከመህ ፣ ሕይወት ለታከተህ ፣ የሚሰማህ ላጣኸው ፣ የሚረዳህ ሰው ላላገኘኸው መከረኛው ወዳጄ!
ከሞት ውጪ ሌላ መፍትሔ አልታይ ካለህ የአንተ ቢጤ መከረኞቹ ጳውሎስና ሲላስ እስር ቤት ውስጥ ሆነው እንዲህ ይሉሃል::
“በራስህ ክፉ ነገር አታድርግ” ሐዋ. 16:28
አውቃለሁ ዙሪያው ገደል ሆኖብሃል:: ምነው ባልተፈጠርሁ እስክትል ድረስ ተጨንቀሃል::
ግን ይህ ስሜት በአንተ አልተጀመረም:: ሰው ሆኖ ተፈጥሮ ኑሮ ያልመረረው ማን አለ? መሞት ያልተመኘስ ማን አለ?
ሞት ያማረህ አንተን ብቻ መሰለህ?
“ ስለ ምን ከማኅፀን አወጣኸኝ? ዓይን ሳያየኝ ምነው በሞትሁ” ያለውን ጻድቅ ኢዮብ አልሰማህም? (ኢዮ. 10:18)
“ከአባቶቼ አልበልጥምና ነፍሴን ውሰድ” ብሎ እንዲሞት የለመነውን ኤልያስን አላየኸውም? 1ነገሥ. 19:4
ዮናስንስ “አሁንም፥ አቤቱ፥ ከሕይወት ሞት ይሻለኛልና እባክህ፥ ነፍሴን ከእኔ ውሰድ፡ አለው” ሲል አልሰማኸውም? (ዮናስ 4:3)
ወንድሜ እመነኝ ምክንያቱ ምንም ይሁን ምን መኖር ያላስጠላው ሰው በታሪክ ፈልገህ አታገኝም::
ሞት ሞት የሸተተው ልቡ የተሰበረ ብዙ ነው:: አንተ ላይ ብቻ የደረሰ ልዩ ፈተና የለም:: “ለሰው ሁሉ ከሚሆነው በቀር ምንም ፈተና አልደረሰባችሁም፤ ነገር ግን ከሚቻላችሁ መጠን ይልቅ ትፈተኑ ዘንድ የማይፈቅድ እግዚአብሔር የታመነ ነው፥ ትታገሡም ዘንድ እንድትችሉ ከፈተናው ጋር መውጫውን ደግሞ ያደርግላችኋል” ይላል መጽሐፍ:: 1ኛ ቆሮ. 10:13
ምናልባት የልብህን መሰበር የኀዘንህን ጥልቀት አይቶ ምቹ ጊዜ አገኘሁ ብሎ ራስህን እንድትጎዳ ሰይጣን ሊገፋፋህ ይችላል:: እንዴት እንዲህ ዓይነት ሃሳብ በልቤ ሊመጣ ቻለ ብለህ አትረበሽ:: ሰይጣን ይህንን ክፉ ሃሳብ ላንተ ብቻ ሳይሆን ለክርስቶስም አቅርቦለታል::
“የእግዚአብሔር ልጅስ ከሆንህ፥ ወደ ታች ራስህን ወርውር” ብሎ ክርስቶስን እንኳን [ማንነቱን ሳያውቅ] ራሱን እንዲወረውር ሊገፋፋው የሞከረ ደፋር ነው:: የእግዚአብሔር ልጅ የሆነ ሰው ግን ራሱን አይጎዳም:: “ጌታ አምላክህን አትፈታተነው” “ሒድ አንተ ሰይጣን” ብለህ ሰይጣንን ገሠፀው::
ሰይጣን ክርስቶስን “ከሕንፃ ጫፍ በመወርወር የእግዚአብሔር ልጅ መሆንህን አሳይ” ሲለው ክርስቶስ ሰይጣንን ሒድልኝ ብሎ በመገሠጹ በክብር ወደ ሰማይ ዐርጎ በእግዚአብሔር ቀኝ ተቀመጠ::
ወንድሜ ሆይ አንተም ሰይጣንን አትስማው ሃሳቡ ራስህን ጎድተህ ከፈጣሪህ እንድትጣላ ሊያደርግህ ነው:: ሰይጣንን ከገሠጽከው በእግዚአብሔር ቀኝ ከበጎቹ ጋር ትቆማለህ::
አሁን ያለህበት ችግር ያልፋል:: የሚሰማህ ክፉ ስሜት መቼም የማይለወጥ አይምሰልህ:: ኀዘኑም ፣ ብቸኝነቱም ፣ ተስፋ ቢስነቱም ያልፋል:: ጨለማው ይነጋል:: የተዘጋው በር ይከፈታል:: ችግሩ ሲፈታ አንተ ከሌለህ ግን ትርጉም የለውም::
ስለዚህ ለሚፈታ ችግር የማይቀለበስ ውሳኔ አትወስን:: ራስን ማጥፋት ከጊዜያዊ ችግር ለመሸሽ ሲሉ ዘላቂ ችግር ውስጥ መግባት ነው:: ጊዜያዊ ሕመምን ለማስታገስ የዘላለም ሕመምን ለምን ትመርጣለህ? “የሞተ ተገላገለ” ሲሉ ሰምተህ እንዳትታለል ሞት ዕረፍት የሚሆነው ራሱ እግዚአብሔር ሲጠራህ ብቻ ነው::
“እናንተ ደካሞች ሸክማችሁ የከበደ ወደ እኔ ኑ እኔም አሳርፋችኋለሁ” ያለው ጌታ ሳይጠራህ ራስን ማጥፋት የዘላለም ስቃይ ያመጣል::
ወዳጄ “በራስህ አንዳች ክፉ አታድርግ”
የሕይወትህን ዋጋ ታውቅ ይሆን? አንተ እኮ የእግዚአብሔር ልጅ ለአንተ ሲል የሞተልህ ነህ:: ሊፈውስህ የቆሰለ ፣ ሊያከብርህ የተዋረደ ፣ ሊያረካህ የተጠማ ፣ ሊያለብስህ የተራቆተ ለአንተ እኮ ነው::
ክርስቶስ ስለ አንተ ሞቶአል:: አንተን ግን የጠየቀህ እንድትሞትለት ሳይሆን እንድትኖርለት ነው::
ለሞተልህ አምላክ እንዴት መኖር ያቅትሃል?
ወዳጄ ሆይ ሰውነትህ በአምላክ ደም የተገዛ ክቡር ሰውነት ነው:: አካልህ “አንተ” እንጂ “ያንተ” አይደለም:: “በዋጋ ተገዝታችኋልና ለራሳችሁ አይደላችሁም፤ ስለዚህ በሥጋችሁ እግዚአብሔርን አክብሩ” ይላል
ስለዚህ በከበረ የእግዚአብሔር ልጅ ደም የተገዛ ሰውነትህን ለሰይጣን በርካሽ አትሽጠው:: አትግደል የሚለው ሕግ ራስህንም ይጨምራል:: ቤተ መቅደስ የሆነ ሰውነትህን ለማፍረስ አታስብ::
“ማንም የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ ቢያፈርስ እግዚአብሔር እርሱን ያፈርሰዋል፤ የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ቅዱስ ነውና፥ ያውም እናንተ ናችሁ” 1ኛ ቆሮ. 3:17
ሰዎች አስቀይመውህ ይሆን?
“አሳያቸዋለሁ ፤ ስሞት የእኔን ነገር ይገባቸዋል” ብለህ በሰዎች ተቀይመህ ራስህን አትጉዳ:: እመነኝ ብትሞት ሰዎች ከሳምንት በላይ አያስታውሱህም:: ለሕይወትህ ዋጋ ያልሠጡ ሰዎች ለሞትህ ዋጋ አይሠጡም:: ፈጥነውም ይረሱሃል:: ለሚረሱህ ሰዎች ብለህ የማይረሳህን አምላክ አታሳዝን:: ሰው ስለ አንተ ግድ የለውም እግዚአብሔር ግን የራስህን ጸጉር ሳይቀር በቁጥር ያውቀዋል :: እንኳንስ ራስህን ልትጎዳ አንዲት ጸጉር እንኳን ከአንተ እንድትወድቅ አይፈልግም::
እግዚአብሔርን በኃጢአት ብታሳዝነው እንኳን ኖረህ ንስሓ እንድትገባ እንጂ እንድትሞት አይፈልግም:: አባትህ ነውና ከእርሱ ጋር ባትሆንም እንድትኖር ይፈልጋል:: በምሳሌ ልንገርህ :-
ሁለት ሴቶች አንድን ሕፃን “የኔ ልጄ ነው” ብለው እየተከራከሩ ጠቢቡ ሰሎሞን ፊት ቀረቡ:: ጠቢቡ ሰሎሞን ሰይፍ አመጣና “ልጁን ቆርጬ ለሁለት ላካፍላችሁ” አላቸው:: አንደኛዋ ሴት “እሺ እንካፈል” ስትል እውነተኛዋ እናት ግን “ልጄ ከሚሞት እርስዋ ትውሰደው” አለች:: እናት መሆንዋም በዚህ ታወቀ::
ወዳጄ ያንተም ኑሮህ ከእግዚአብሔር ጋር ላይሆን ይችላል:: ዓለም የራስዋ አድርጋህም ይሆናል:: በሱስ ውስጥ ትዘፍቀህ ፣ እንደ ሶምሶን በደሊላ እቅፍ ፣ እንደ ዴማስ በተሰሎንቄ ውበት ተማርከህ ይሆናል:: እግዚአብሔር ግን አባትህ ነውና ሞትህን አይፈልግም::
“ልጄ ከሚሞት እርስዋ ትውሰደው” እንዳለችው እናት ፈጣሪህ ከነኃጢአትህም ቢሆን እንድትሞት አይፈልግም:: ከእርሱ ጋር ባትኖርም መኖርህን ይፈልጋል:: “የሟቹን ሞት አልፈቅድምና፥ ይላል ጌታ እግዚአብሔር፤ ስለዚህ ተመለሱና በሕይወት ኑሩ” ሕዝ. 18:32
የይሁዳ ኃጢአቱ ጌታውን መሸጡ አልነበረም:: ራሱን መግደሉ ነው:: እግዚአብሔር የሚያዝነው ከበደልህ በላይ በእርሱ ተስፋ ቆርጠህ ራስህን ስትጎዳ ነው::
ወዳጄ የአንተን መኖር የሚፈልጉ ብዙ ናቸው:: ፈጣሪ ወደዚህች ዓለም ያለ ምክንያት አላመጣህም:: በአንተ አለመኖርም የሚጎድል ነገር አለ:: አንተን የሚመስል ሌላ ሰው አልፈጠረምና ለዚህ ዓለም አንተን የሚተካ የለም:: በክብር ወደዚህ ዓለም ያመጣህ አምላክ በክብር ወደራሱ እስኪወስድህ ድረስ “በራስህ ላይ ክፉ ነገር አታድርግ”
“የወኅኒውም ጠባቂ ከእንቅልፉ ነቅቶ የወኅኒው ደጆች ተከፍተው ባየ ጊዜ፥ እስረኞቹ ያመለጡ መስሎት ራሱን ይገድል ዘንድ አስቦ ሰይፉን መዘዘ።
ጳውሎስ ግን በታላቅ ድምፅ፦ ሁላችን ከዚህ አለንና በራስህ ክፉ ነገር አታድርግ፡ ብሎ ጮኸ” ሐዋ. 16:27-28
ይህ ሰው እስረኛ ያመለጠ መስሎት ራሱን ሊያጠፋ ሲል ጳውሎስ “ሁላችን ከዚህ አለንና በራስህ ክፉ ነገር አታድርግ” አለው::
ወዳጄ አንተስ ተስፋ የቆረጥኸው ምን ያመለጠ መስሎህ ነው?
293
✨ የዛሬን ዕድል ለነገ አታስተላልፍ! ✨
"ዲያብሎስ 'ነገ' በሚል የተስፋ ቃል ዛሬን ይነጥቀናል። ዛሬን ካልተጠቀምንባት ነገም እንደዚሁ በከንቱ ታልፋለች።" ⏳
😈 የሰይጣን ዋና ስልቱ በአሁኑ ሰዓት ልናደርገው የሚገባንን በጎ ነገር እንድናዘገይ ማድረግ ነው፤ ምክንያቱም፦
አንድን መልካም ሥራ ለነገ ካስተላለፍነው...
ያቺ ነገ ስትመጣም ለሌላ ነገ እንድናስተላልፋት ያደርገናል!
በመጨረሻም ዕድሜአችንን በሙሉ በከንቱ ቀጠሮ እንድንጨርስ ይፈልጋል። 🛑
💡 እውነተኛው ጥበብ ግን፦ ዛሬ በእጃችን ያለችውን ሰዓት ለበጎ ሥራና ለንስሐ መጠቀም ነው። ⛪️
🙏 "ነገ የኛ አይደለችም፤ ያለችን ዛሬ ብቻ ናት!"
(ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ - የቅዱስ ማቴዎስ ወንጌል ትርጓሜ)
293
+ ዓይንህ ማንን ያያል? +
ክርስቶስ ከመረጣቸው አሥራ ሁለት ደቀ-መዛሙርት መካከል ሦስት ዓይነት ሰዎችን እናገኛለን።
የመጀመሪያው ዮሐንስ ነው። ዮሐንስ ከመጠራቱ አንስቶ እስከ መስቀል ድረስ ጌታችንን የተከተለ ደቀ መዝሙር ነው። ፍቅሩ ፍጹም ነው። የተጠራበትን አገልግሎት የሕይወት ጥሪው አድርጎ በመውሰድ በጽናት እስከመጨረሻው ድረስ የተጓዘ ነው። ሁለተኛው ድግሞ ጴጥሮስ ነው። ጴጥሮስ እድሜው ገፋ ካለ በኋላ የተጠራ ደቀ መዝሙር ነው። ብዙ እድሜውን በዓለማዊ ነገር አሳልፏል። ብዙ ባክኗል፥ ብዙ አጥቷል፥ በመጠራቱ ደግሞ ብዙ አትርፏል። ጴጥሮስ ራሱን መልካም ደቀ መዝሙር አድርጎ ያስብ የነበረ፥ ክርስቶስን ‘አላውቀውም’ ለማለት ግን ትንሽ ነገር የበቃው ሰው ነው። የጴጥሮስ ታሪክ ግን መጨረሻው ያምራል። በፍጹም ንስሃ ተመልሶ የሐዋርያት አለቃ እስከመሆን የደረሰ፥ በሰማዕትነትም ጌታውን መስሎ ያረፈ ሰው ነው። በሦስተኛ ደረጃ ደግሞ ይሁዳ አለ። ይሁዳ ከከፋ ሕይወት የተጠራ፥ ሌባ ሆኖ ሳለ የገንዘብ ባለሟል ተደርጎ የተሾመ ነው። ይሁዳ ገንዘብ ያሰከረው፥ ጥቅም ያሳወረው፥ ክርስቶስን በመሳም አሳልፎ የሰጠ፥ ለክብር የጠራውንም ጌታ የካደ ነው።
ጌታችን ክርስቶስ ጠርቷቸው ከዋለበት እየዋሉ፥ ካደረበት እያደሩ፥ የቃሉን ትምህርት ብቻ ሳይሆን ተዓምራቱን ሳይቀር እየተመለከቱ ከተማሩ አሥራ ሁለት ሐዋርያት መካከል ዮሐንስ፥ ጴጥሮስ እና ይሁዳ ተገኝተዋል። ታዲያ በክርስቶስ ደቀ መዛሙርት መካከል ይሁዳን ካገኘን፥ በቤተክርስቲያን ውስጥ ይሁዳዎችን ስናገኝ የምንደነቀው ለምን ይሆን? ቤተክርስቲያን ሦስቱንም ዓይነት ደቀ መዛሙርት ይኖሯታል። ቤተክርስቲያን በጥሪያቸው ጸንተው እስከ መጨረሻው የሚኖሩ ዮሐንሶች ይኖሯታል። ቤተክርስቲያን ክርስቶስን ‘አላውቅህም’ ብለው በንስሃ ግን ፍጹም ሆነው የተመለሱ ጴጥሮሶችም አሏች። ቤተክርስቲያን ጌታቸውን በአላዋቂነት፥ በገንዘብ ፍቅር፥ በድንዛሬ ‘በመሳም’ አሳልፈው የሰጡ ይሁዳዎችም ይኖሯታል።
ቤተክርስቲያንን ስታይ ዓይንህ ማንን ያያል? ቤተክርስቲያን ውስጥ ዮሐንሶች ብቻ ያሉ መስሎህ አለመሆኑን ስታውቅ አዝነህ ይሆን? በቤተክርስቲያን ውስጥ ያሉ ጴጥሮሶችን ጥፋታቸውን አይተህ ንስሃቸውን ሳትመለከት ተሰናክለህባቸው ይሆን? የቤተክርስቲያን ይሁዳዎችን ተመልክተህ 'አምላክ ለምን አይፈርድም!' ብለህ ከፈጣሪ ተሟግተህ ይሆን? እንግዲያውስ፥ አንተ የተጠራኸው የክርስቶስ ደቀ መዝሙር ልትሆን ነውና፥ ዓይንህን በጌታህን ላይ አድርግ። ደቀ መዛሙርቱን መመልከት ካለብህ ደግሞ የቤተክርስቲያን ዮሐንሶችን እየተመለከትክ በእምነት ምሰላቸው። የቤተክርስቲያንን ጴጥሮሶች እየተመለከትክም በፍጹም ንስሃቸው ምሰላቸው።
ይሁዳዎቹን ግን ተዋቸው!
293
መዝሙረ ዳዊት🎯መዝሙረ ዳዊት ለቤተክርስቲያን እና ለግል ጸሎት እጅግ የተወደደ ለሐዘን ለደስታ ለመልካምም ሆነ ክፉ ለማንኛውም ሁኔታ የሚያመሰግኑበት ፡ የሚጸልዩበት ፡ የመዝሙር እና የጸሎት መጽሐፍ ነው። በዚህ መጽሐፍ እየተጠቀመ ሰው ከእግዚአብሔር ጋር ሊገናኝ ፡ ኅብረቱም ሊያድግ በመንፈሳዊነትም ሊያድግ ይችላል። ✅መዝሙረ ዳዊት አጠቃላይ መዝሙሩ 150 ሲሆን ከዚህ ውስጥ 82ቱ የዳዊት መሆኑ ተገልጿል የቀረው የሙሴና የቆሬ የአሳፍ የሐጌና ዘካርያስ የሚሉና ደራሲው ያልታወቀ ይገኝበታል። ✅መዝሙሮቹ በመንፈስ ቅዱስ ምሪት የተገለጡ ጸሎትና ውዳሴ ናቸው። ሰው ከእግዚአብሔር ጋር ባለው ኅብረት የሰውን ጥልቅ የልብ ስሜት ይገልጻሉ። እነርሱም መታመንን ፤ ፍቅርን ፤ ልዕልናን ፤ ምስጋናንና ውዳሴን ፤ ከእግዚአብሔር ጋር የጠበቀ ኅብረት እንዲኖር መናፈቅን እግዚአብሔርን ተስፋ ማድረግን ፤ ከበደል ነጻ እንዲሆን መጠየቅን ፤ ከእግዚአብሔር ትድግና ለማግኘት ፣መማጸንን ውዳሴውና ምስጋናው እግዚአብሔር በማንነቱ ስላደረገው ታላቅና ድንቅ ነገር ሁሉ ለማመስገን ነው። አንዳንዶቹ መዝሙሮች ስለመሲሑ ዋና ዋና የሆኑትን ክፍሎች ይዘው ይገኛሉ። ✅መዝሙረ ዳዊት የሰውን የህይወት ዘመን ሳይለይ ሰው በሕይወቱ የሚያጋጥሙትን ኃዘንና ደስታ ፡ መልካምና ክፉ ፡ መውደቅና መነሣት ፡ ችግርና ምቾት ፡ ከእግዚአብሔር መራቅና ወደ እግዚአብሔር መቅረብ የያዘ መጽሐፍ ነው። ✅ለቤተክርስቲያን የጸሎትና የመዝሙር መጻሕፍት መሠረታቸው መዝሙረ ዳዊት ነው። መዝሙረ ዳዊት መዘምራን በዜማ ስልት የሚገለገሉበት መነኮሳት እና ካህናት በመዓልት በሌሊት በቤተ ክርስቲያን እግዚአብሔርን የሚያመሰግኑበት ፡ ምእመናን በያሉበት ሆነው እየጸለዩ መላእክተ ብርሃንን የሚያቀርቡበት ፡ መላእክተ ጽልመትን የሚያርቁበት ፡ ሕሙማን የሚፈወሱበት እጅግ ጠቃሚ የሆነው መጽሐፍ ነው። ✅መዝሙረ ዳዊት ሰዎች በዚህች ዓለም በሚኖሩበት ጊዜ ስለ ሚያጋጥሟቸው ሁኔታዎች በሙሉ ምን መጸለይ እንደሚገባቸው የሚያስረዳ መጽሐፍ ስለሆነ ከዚህ ቀጥሎ እንደቀረበው የመጽሐፉን አብዛኛውን ይዘት መረዳት ይቻላል፡፡
👉ለእግዚአብሔር ምስጋና ለማቅረብ መዝ.፰፣ መዝ.፳፱፣ መዝ.፴፫ መዝ.፴፮፣ መዝ.፹፱፣ መዝ.፺፬፣ መዝ.፩፻፫፣ መዝ.፩፻፬፣ መዝ.፩፻፭፣ መዝ.፩፻፮፣ መዝ. ፩፻፲፩፣ መዝ. ፩፻፲፰፣ መዝ.፩፻፴፰፣ መዝ.፩፻፵፭፡፡
👉የእግዚአብሔርን የባሕርይ ልዕልና ለመግለጥና ለማወደስ መዝሙር ፰፣ ፲፱፣ ፳፱፣ ፴፫፣ ፵፯፣ ፷፭፣ ፰፮፣ ፰፰፣ ፸፮፣ ፹፩፣ ፹፱፣ ፺፪፣ ፺፭፣ ፳፮፣ ፺፰፣ ፩፻፴፭፣ ፩፴፮፣ ፩፻፵፯፣ ፩፻፵፰፣ ፩፶፻
👉አንድ ኃጢአተኛ ከኃጢአቱ በንስሐ ተመልሶ የእግዚአብሔርን ይቅርታ የሚጠይቅበት መዝሙር፦ ፮፣ ፴፩፣ ፴፯፣ ፶፣ ፹፭፣ ፳፻፩፣ ፳፻፪ ፣ ፩፵፪
👉ጭንቀት፣ፈተና፣ ውርደት፣ ሐዘን፣ ስደትና ጭቆና በሚያጋጥም ጊዜ መዝሙር፡-፪፣ ፮፣ ፲፫፣ ፳፩፣ ፴፭፣ ፵፩፣ ፵፫፣ ፵፬፣ ፶፪ ፣ ፶፭ ፡ ፶፮፣ ፶፱፣ ፷፬፣ ፷፰፣ ፸፬፣ ፸፯፡፸፱፣ ፹፣ ፹፣ ፹፰፣ ፺፡፺፬፡፩፻፪፣ ፩፻፱፣ ፩፻፵፡፩፻፵፫
👉ፍርሃትና ፈተና ሲያጋጥም በእግዚአብሔር ለመተማመን መዝሙር፦ ፲፩፣ ፲፮፣ ፲፰፣፳፣ ፳፭፣ ፳፯፣ ፳፰፣ ፴፣ ፴፪፣ ፴፯፣ ፵፮፣ ፶፬፣ ፶፯፣ ፷፪፣ ሮ፣ ፸፩፣ ፻፩፣ ፩፻፲፭፣ ፻፳፬፣ ፻፳፩፣ ፻፵፬፣ ፩፵፮
👉የእግዚአብሔር፣ ሕጉና ቤቱ በሚናፈቅበት ጊዜ መዝሙር፡ ፲፮፣ ፲፯፣ ፲፰፣ ፣ ፵፩፣ ፵፬፣ ፷፫፣ ፸፪፣ ፹፫፣ ፩፻፲፱፣ ፩፻፳፩፣ ፩፻፴፩
👉ካህናት የቤተ መቅደስን ደረጃዎች ሲወጡ የሚዘምሩአቸው የመዓርግ መዝሙሮች ከመዝሙር ፩፻፪ እስከ ፩፻፴፫👉እነዚህ መዝሙሮቹ ለእግዚአብሔር ስምና ለጽድቁ ከተነሣ ታላቅ ቅንአትና ኀጠአትን፤ከፋትን ከመጥላት የተነሣ ጻድቅ ፍርዱን በማምጣት ከፉዎችን አዋርዶ ጻድቃንን ከፍ ከፍ እንዲየደርግ ምልጃን የሚያቀርቡ ናቸው። ✅መዝሙረ ዳዊት ከእግዚአብሔርና ከሰው ግንኙነት አኳያ ሲታይ የሰውን ሰሜት ና ፍላጎት በየደረጃው ከዳር እስከዳር እንደዚህ አድርጎ የገለጸ መጽሐፍ ነው ውዳሴና ተመስጦ ጥልቀት ባለው ሁኔታ ተገልጿል።የማይመች ሁኔታ ባጋጠመ ጊዜ ድንቅ የሆነ የእምነት ጸሎት ያቀርባል። ✅መዝሙረ ዳዊት በሐዲስ ኪዳን ብዙ ጊዜና በተደጋጋሚ የተጠቀሰ መጽሐፍ ነው። ከመጽሐፍ ቅዱስ እጅግ የሚወደዱ መዝሙሮችን የያዘ መጽሐፍ ነው።
293
✨️️✨️️✨️️🌿🌿🌿✨️️✨️️✨️️🌿🌿🌿✨️️✨️️✨️️🌿🌿🌿
"በአንዳች ነገር መጠን ባለፈ ሁኔታ እየተጨነቅንና እየተበሳጨን ከሆነ ፈቃድህ ይሁን ብለን ብንጸልይም እንደ ጌታ ፈቃድ ያለመኖራችንና ለእግዚአብሔር ፈቃድ ሙሉ በሙሉ እጅ እንዳልሰጠን ማሳያ ነው።እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ የሚኖር ሰው ስለ ምንም ነገር አይጨነቅም።ፈቃድህ ይሁን ብሎ እራሱን እና ፍላጎቱን ለእግዚአብሔር አሳልፎ ስለሚሰጥ የሚፈልገውን ባያገኝ እንኳን በትዕግስት ጸንቶ ጌታን ያመሰግናል።
ለእግዚአብሔር ፈቃድ የተገዛች የክርስቲያን ነፍስ በምንም ነገር አትታወክም አትፈራም አትጨነቅምም።ትናንትን ያሻገራት ዛሬን የሚጠብቃት ነገን ከበረከት ጋር የሚያሳያት ጌታ እንዳላት ታምናለችና። "
✨️️✨️️🌿 ቅዱስ ሰሎዎስ ዘአቶናዊ
"በመንፈስ ቅድስና ያለው ሰው በላዩ የሚያበራው ብርሃን ከቅድስት ሥላሴ ስለሆነ፥ መንግሥተ ሰማያት በልቡ አለች፡፡ የሚተነፍሰው አየር፥ አጽናኝ የሆነ መንፈስ ቅዱስ ነው፡፡ ወዳጆቹም ሰማያውያን መላእክት ናቸው፡፡ ደስታውና እርካታውም የብርሃን አምላክ የሆነው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው"
✨️️✨️️🌿 ቅዱስ የሐንስ ሳባ
"የጥበብ አገሯ ወዴት ነው? ጥበብ ግን መድኃኒታችን ነው።በሥጋው መሥዋዕትነት ያዳነን ፣ በደሙም ፈሳሽነት የተወዳጀን፣ለመንግሥቱም የመረጠን፣ ለዘለዓለሙ።"
✨️️✨️️🌿 ቅዳሴ ኤጲፋንዮስ
"ቤተክርስትያንን መርዳት ከፈለክ ሌሎችን ለማረም ከማሰብ በፊት በቅድሚያ እራስን ማስተካከል ይበጃል። እራስህን ካስተካከልክ አንድ የቤተክርስትያን ክፍል ዳነ ወይም ተስተካከለ ማለት ነው። ሁሉም ሰው ይህን ማድረግ ከቻለ ቤተክርስትያን ጤናማ ትሆናለች። ስለዚህ ላስተዋለው ሰው ሌሎች ላይ መፍረድ እጅግ በጣም ቀላል ነው እራስን ማስተካከል ግን ጥረት ይጠይቃል።"
✨️️✨️️🌿 ቅዱስ ፓሲዮስ
✨️️✨️️✨️️🌿🌿🌿✨️️✨️️✨️️🌿🌿🌿✨️️✨️️✨️️🌿🌿🌿
293
✨✨✨🌿🌿✨🌿🌿✨🌿🌿
የቤተ ክርስቲያን አባቶች ስለ ትዳር ያላቸው ዕይታ እጅግ የረቀቀና ጥልቅ የሆነ ነገረ መለኮታዊ ሥነ ውበት መሠረት ያለው ነው።" ከሐመር መጽሔት " የነገዋ ቤተ ክርስቲያን ዐምድ ሚያዚያ 2018✨🌿🌿✨ የኅትመት ዘመን ፦ ሚያዝያ ፳፻፲፰ ዓ.ም አዘጋጅ ፦በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ማኀበረ ቅዱሳን በሚዲያ አገልግሎት ተቋም በመጽሔት ዝግጅት ክፍል የሚዘጋጅ ትምህርታዊ መጽሔት • ገጽ ብዛት፦፳፰ ዋጋ ፦፵ ብር ✨✨✨🌿🌿✨🌿🌿✨🌿🌿
የቤተ ክርስቲያን አባቶች ስለ ትዳር ያላቸው ዕይታ እጅግ የረቀቀና ጥልቅ የሆነ ነገረ መለኮታዊ ሥነ ውበት መሠረት ያለው ነው።" ከሐመር መጽሔት "የነገዋ ቤተ ክርስቲያን ዐምድ ሚያዚያ 2018 ✨🌿🌿✨ የኅትመት ዘመን ፦ ሚያዝያ ፳፻፲፰ ዓ.ም አዘጋጅ ፦በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ማኀበረ ቅዱሳን በሚዲያ አገልግሎት ተቋም በመጽሔት ዝግጅት ክፍል የሚዘጋጅ ትምህርታዊ መጽሔት • ገጽ ብዛት፦፳፰ ዋጋ ፦፵ ብር • ሐመር መጽሔት ፴፫ኛ ዓመት ቁጥር ፬ ሚያዝያ ፳፻፲፰ ዓ.ም መልእክት ዘማኅበረ ቅዱሳን " የገዳማትና የከብያተ ክርስቲናት ስጋት የእኛም ስጋት ሊሆን ይገባል ። "በሚል በመልእክት ዐምዷ ታስነብባለች። ✨🌿🌿✨ "ዐውደ ስብከት ሥር” «መከራ ሲያጸኑበት አልተቀየማቸውም "በሚል ርእስ በመልአከ ሰላም ቀሲስ ደጀኔ ሺፈራው የተዘጋጀ ስብከት በስፋት ታስነብባለች። በትምህርተ ሃይማኖት ዐምድ ሥር “እግዚአብሔር ከእንቅልፍ እንደሚነቃ ተነሣ" በሚል ዐቢይ ርእስ ስለክርስቶስ ትንሣኤ ሰፊ ትምህርት በመጋቤ ሐዲስ ኃይለ እግዚእ አሰፋ (በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ/መንበረ ፓትርያርክ ጠ/ቤተ ክህነት የትምህርትና ማሠልጠኛ መምሪያ ዋና ኃላፊ) ተዘጋጅቷል ። ዐቢይ ጉዳይ ዐምድ ሥር ደግሞ “የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ፈተናዎች ከትናንት እስከ ዛሬ " በሚል ሰፊ ጉዳዮች ይዛለች። እንደ ማሳያም በትግራይ ክልል የነበረውን ጦርነት ተከትሎ ፣በአካባቢው ያሉ አባቶች ከቅዱስ ሲኖዶስ ጋር ያላቸውን ግንኙነት በማቋረጥ «መንበረ ሰላማ» የተባለ መዋቅር መመሥረት፣ በተመሳሳይ መልኩም «የኦሮሚያ ቤተክህነት» በሚል ስያሜ ከሕጋዊው ሲኖዶስ ውጭ የተደረገው የጳጳሳት ሹመት ሙከራ፣ቤተ ክርስቲያንን ለከፍተኛ ደም መፋሰስና ውስጣዊ ቀውስ ዳርጓት ነበር። ጠባሳ ግን አሁንም ተቋማዊ ስጋት ሆኖ ቀጥሏል።• •ክርስትና በማኀበራዊ ዐምድ ሥር ደግሞ
"እግዚአብሔርን የምንመስልበት ሥራ "በሚል ርእስ ከዘመነ ትንሣኤ ጋር በተያያዘ መሠራት ያለባቸውን ጹሑፍ ታሰነብባለች። ✨🌿🌿✨ በእናስተዋውቃችሁ ዐምድ ሥር በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሚገኘውን “የደብረ ይባቤ ቅዱስ ያሬድ ቤተ ክርስቲያን " ክፍል _፩ ታስቃኛለች ። የቅዱስ ያሬድ ዜማ የመጀመሪያውና የመጨረሻው ብቸኛው ሰማያዊ ዜማ በመሆኑ ቤተ ክርስቲያን ከአንድ ሺህ ሦስት መቶ ዘመናት በላይ ስትጠቀምበት ኖራለች ፣ ወደፊትም ትጠቀምበታለች።ሙሉውን ከመጽሔቱ እንድታነቡ እጋብዛለሁ ። በነገዋ ቤተ ክርስቲያን ዐምድ ሥር “ ትንሿን ቤተ ክርስቲያን የመታደግ ስልት (Strategy )ይጠቁማል ። በኪነ ጥበብ ዐምድ
" ለኃጥአን የመጣ ለጻድቃን ... "በሚል ኪነ ጥበብ ታስነብባለች ። •የጥያቄዎቻችሁ መልስ ዐምድ "የክህነት አሰጣጥ ችግሮችና መፍትሔዎች" ክፍል ፩ ከመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የሊቃውንት ጉባኤ የሆኑትን ሊቀ ሊቃውንት ዮሴፍ ደሳለኝም ጋር የተደረገውን ጥያቄና መልስ ይዛለች ። ሐመር መጽሔት ፴፫ ኛ ዓመት ቁጥር_፬ በማሰራጨት ፡በማንበብና በማስነበብ የድርሻችን እንወጣ ! ሐመር መጽሔት ዝግጅት ክፍል Mahibere Kidusan - ማኅበረ ቅዱሳን ዋናው ማእከል ✨✨✨🌿🌿✨🌿🌿✨🌿🌿
293
✨✨✨🍀🍀🍀✨✨✨🍀🍀🍀✨✨✨🍀🍀🍀
"አምላክ ከንጉስ ሔሮድስ ሴት ልጅ ቢወለድ ኖሮ አልጋ ወራሽ በሆነና ባልተሰደደ ነበር ። እርሱ ግን የድሆች የሆነችውን ድንግልን መረጠ።"
✨✨✨ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ።
"ጌታ ሆይ ዕውሩን ሂድ ብለህ ወደ ላክህበት ወደ ሰሊሆም መጠመቂያ አሁን ልንሄድ አንችልም። ነገር ግን ሕይወትንና ብርሃንን የተሞላው የከበረ ደምህ ያለበት ጽዋ በእኛ ዘንድ አለ። ከእርሱ በተቀበልን ቁጥር እንነጻለን። "
✨✨✨ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊው
"ኃጢአት ከጣለችው ይልቅ ወዳሴ ከንቱ የጣለችው ሰው ይበዛል ።"
✨✨✨ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
"ንግግርህ ምንም ያህል እውነተኛ ቢሆን በቁጣ ከተናገርክ ሁሉንም ነገር ታጠፋዋለህ "
✨✨✨ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
"በኃጢአት በወደቅህ ጊዜ ተስፋ ቆርጠህ ጸሎትህን እንዳታቆም ። ንስሐ እስከምገባ ድረስ ብለህ ጸሎት ካቆምክ መቼም ንስሐ አትገባም። ምክኒያቱም ጸሎት ራሱ የእውነተኛ ንስሐ መግቢያ በር ነው"
✨✨✨ቅዱስ ቄርሎስ ሳድሳዊ
"በስግብግቦች ዘንድ እንደ በላተኛ ተቆጠረ፣በሚያቁት ዘንድ ግን እርሱ የሁሉ መጋቢ ነዉ።በሰካራሞች ዘንድ እንደሚጠጣ ተቆጠረ፣በሚያስተዉሉት ዘንድ ግን እርሱ የሁሉን ጥም የሚያረካ ነበረ።"
✨✨ ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ
✨✨✨🍀🍀🍀✨✨✨🍀🍀🍀✨✨✨🍀🍀🍀
293
✨️️️️✨️️️️✨️️️️ 🍁🍁🍁✨️️️️✨️️️️✨️️️️ 🍁🍁🍁✨️️️️✨️️️️✨️️️️ 🍁🍁🍁
✨️️️️✨️️️️ 🍁አታስመስል✨️️️️✨️️️️ 🍁
ጌታችን ከአደገባት ናዝሬት ወደ ስድስት ኪሎ ሜትር ርቃ ያለች ሴፎሪስ (Sepphoris) የምትባል በገሊላ የምትገኝ ከተማ ነበረች። ይህችም ከተማ በጣም ደማቅ በመሆኗ "የገሊላ ጌጥ" ተብላ ትጠራለች። በውስጧም ታላቅ የቴያትር አዳራሽ ነበራት። በጥንታውያን የሮምና የግሪክ ቴያትር ታሪክ ልክ እንደ ዛሬው ገጸ ባሕርይን ለመላበስ (ለመምሰል) የሚረዳ የሜካፕ ሙያ ሳይመጣ በፊት፣ ተዋናይዎቹ የኃዘንና የደስታ መልክ ያላቸውን ጭንብሎች ለብሰው ነበር የሚተውኑት።
እነዚህም ጭንብሎች "persona" የሚል መጠሪያ ሲኖራቸው ትርጉሙም "ጭንብል"/"mask" ማለት ነው። (በነገራችን ላይ personality የሚለው ቃል persona or mask ከተባለው ከዚሁ ግንድ መውጣቱን ልብ ይሏል።)
✨️️️️✨️️️️ 🍁
የሥነ ቅርስ ተመራማሪዎችን ትኩረት ከሳቡ እና በብዛት የኀሠሣ ቁፋሮ ከሚደረግባቸው የዓለማችን ክፍሎች አንዷ ሴፎሪስ ነች። ታዲያ ጌታችን ላደገባት ናዝሬት ቅርብ በሆነች በዚህች ከተማ በተደረገ የarcheology ቁፋሮ የተለያዩ የቴያትር ጭንብሎች ተገኝተው ነበር።
ጌታችን በወንጌል ጻፎችና ፈሪሳውያንን "ግብዞች"
እያለ ይጠራቸው ነበር። ግብዝ የሚለው ቃል ደግሞ በግሪኩ "Hypocrite" የሚለው ሲሆን ትርጉሙም "ተዋናይ"/"Actor or play maker" ማለት ነው። በመሆኑም መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የሚናገሩትን የማይኖሩ ነገር ግን በሰው ፊት ፍጹም መስለው ለመታየት የሚፈልጉትን አይሁድ፣ በዘመኑ በነበሩትና ጭንብል ለብሰው በሚጫወቱት የቴያትር ባለሙያዎች ስም "ተዋናይ" ብሎ መጥራቱ ያለ ምክንያት አይደለም።
✨️️️️✨️️️️ 🍁
ኑሮው በግልጽ የሚታወቅ እውነተኛ ሰው ቢሳሳት እንኳን ተመክሮ የመታረምና የመመለስ እድል አለው። የሚያስመስል ሰው ግን ለትምህርትና ለተግሳጽ እንኳን ያስቸግራል። እንዲሁ እንዳስመሰለም የእውነት ሳይኖር ይሞታል። ታዲያ ከዚህ ሰው በላይ ራሱን የሚበድል ከየት ይገኛል?
ጻድቅ መስሎ በሕዝብ ተከብሮ ከመኖር ይልቅ ድክመቱን ያመነ ኃጥእ ሆኖ በሰው ፊት መመላለስ ይሻላል። ፈጣሪ አንድ ቀን የኃጢአቱን ብዛት የሚቀንስለት፣ ከእሳት ነጥቆ የሚያወጣው ቸር መካሪ አያሳጣውምና። ከአስመሳይ ጻድቅ እውነተኛ ኃጥእ ይሻላል!
✍ ዲያቆን አቤል ካሳሁን
✨️️️️✨️️️️✨️️️️ 🍁🍁🍁✨️️️️✨️️️️✨️️️️ 🍁🍁🍁✨️️️️✨️️️️✨️️️️ 🍁🍁🍁
293
🍁🌹✨✨✨🍁🌹✨✨✨
የሰርግ ወቅት ስለሆነ...
"ባልና ሚስት ሆይ! ስሙ፦
ባል ሆይ ሚስትህን ክርስቶስ ቤተክርስቲያንን እንደወደዳት ውደዳት።ክርስቶስ ስለ ቤተክርስቲያን ራሱን አሳልፎ እንደሰጠ፣ አንተም ስለ ሚስትህ ስትል መሞት ቢያስፈልግህ እንኳ ወደኋላ አትበል። ስድብን፣ መገፋትንና መከራን ሁሉ ስለ እርሷ ታገሥ። ክርስቶስ ቤተክርስቲያንን ወደ እርሱ የቀረባት በዛቻና በማስፈራራት ሳይሆን በፍቅርና በቸርነት ነው። አንተም ሚስትህን በፍቅር እንጂ በኃይል አታስገዛት። በፍርሃት የምትገዛ ሚስት ከጥቂት ጊዜ በኋላ ትሰለችሃለች፤ በፍቅር የምትገዛ ግን እስከመቃብር ታምንሃለች። 🍁🌹✨✨ ሚስት ሆይ! አንቺም ለባልሽ ተገዢ፤ መገዛት ሲባል ግን እንደ ባሪያ መሆን ሳይሆን እንደ አካል መሆን ነው። አካል ለራስ እንደሚታዘዝ አንቺም ለባልሽ ታዘዢ። እርሱ ራስሽ ነውና። ባልሽ ባልደረባሽ እንጂ አገልጋይሽ አይደለምና ክብሩን ጠብቂ። በቤታችሁ ውስጥ 'የእኔ' እና 'የአንተ' የሚሉ ቃላትን አጥፉ። እነዚህ ቃላት የጠብ ምንጮች ናቸው። ይልቁንም 'የእኛ' በሉ። ሀብቱ የእኛ፣ ልጆቹ የእኛ፣ ሕይወቱ የእኛ ነው በሉ። ባል ለሚስቱ እንዲህ ይበላት፦
'እኔ አንቺን ከመውደዴ የተነሳ ዓለምንና መንግሥትን ሁሉ ብታጣ እንኳ ግድ የለኝም፤ አንቺ ከእኔ ጋር ከሆንሽ ብቻ ይበቃኛል።'ሚስት ለባሏ እንዲህ ትበለው፦
'የአንተ መኖር ለእኔ ከወርቅና ከብር ይበልጥብኛል።'እንዲህ ዓይነት ንግግር ባለበት ቤት ውስጥ ሰይጣን መግቢያ ቀዳዳ አያገኝም። ጸሎታችሁም አይሰናከልም። ልጆችን በምግባርና በሃይማኖት አሳድጉ። ቤታችሁን ቤተክርስቲያን አድርጉት። መዝሙር ዘምሩ፣ መጽሐፍ ቅዱስን አብራችሁ አንብቡ። ባል ለሚስቱ፣ ሚስት ለባሏ በመንፈሳዊ ሕይወት መበርታት ምክንያት ይሁኑ። አንዱ ሲደክም አንዱ ያንሳው። በምድር ላይ በፍቅር የኖራችሁ እንደሆነ፣ በሰማያዊው መንግሥትም ለዘላለም አብራችሁ ትኖራላችሁ።" ✨ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅን 📝በኤፌሶን መልእክት ምዕራፍ ፭ (5) በተረጎመበት ድርሳኑ 🍁🌹✨✨✨🍁🌹✨✨✨
293
🕊 ከዕለተ ትንሣኤ እስከ ዳግም ትንሣኤ 🕊
በቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ከትንሣኤ እሑድ እስከ ሳምንቱ እሑድ ያሉት ዕለታት ‹ሰሙነ ፋሲካ› ወይም ‹ትንሣኤ› በመባል ይታወቃሉ። በእነዚህ ዕለታት የሚከናወነው መንፈሳዊ ሥርዓት እንደ መጀመሪያው የትንሣኤ ዕለት በደመቀ ሁኔታ ይፈጸማል።
የዕለታቱን ምሥጢራዊ ስያሜዎች እንደሚከተለው እንመልከት፦
🌅 ሰኞ | ፀአተ ሲኦል (ማዕዶት)
ጌታችን በትንሣኤው ነፍሳትን ከሲኦል አውጥቶ ወደ ገነት አሻግሮ የማስገባቱ መታሰቢያ ናት።
📖 (ዮሐ. ፲፱፥፲፰፤ ሮሜ. ፭፥፲-፲፯)
👣 ማክሰኞ | ቶማስ
ሐዋርያው ቶማስ "ካላየሁ አላምንም" ባለበት ወቅት ጌታችን በድጋሜ ተገልጦ ለቶማስ የታየበትና ያመነበት ዕለት መታሰቢያ ነው።
📖 (ዮሐ. ፳፥፳፬-፴)
🕯 ረቡዕ | አልዓዛር
ጌታችን ከአራት ቀን በኋላ ከመቃብር ጠርቶ ላስነሣው ለወዳጁ ለአልዓዛር መታሰቢያ የተሰየመ ዕለት ነው።
📖 (ዮሐ. ፲፩፥፴፰-፵፮)
🍎 ሐሙስ | የአዳም ሐሙስ
ከልጅ ልጅህ ተወልጄ አድንሃለሁ" ተብሎ የተገባለት የተስፋ ቃል ተፈጽሞ አዳም ወደ ቀደመ ክብሩ የተመለሰበት ዕለት መታሰቢያ ነው።
📖 (ሉቃ. ፳፬፥፳፭-፵፱)
⛪️ ዐርብ | ቤተ ክርስቲያን
ይህቺ ዕለት በክርስቶስ ክቡር ደም ለተመሠረተችው ቅድስት ቤተ ክርስቲያን መታሰቢያ ትሆን ዘንድ ተሰይማለች።
📖 (ማቴ. ፳፮፥፳፮-፵፱፤ ሐዋ. ፳፥፳፰)
💐 ቀዳሚት ሰንበት | ቅዱሳት አንስት
ጌታን በሽቱና በአበባ ላገለገሉት፣ እስከ ቀራንዮ ለተከተሉትና ትንሣኤውን ቀድመው ለማየት ለበቁት ቅዱሳት አንስት መታሰቢያ ናት።
🌟 እሑድ | ዳግም ትንሣኤ
ጌታችን በዝግ በር ገብቶ ለሐዋርያት ለሁለተኛ ጊዜ የታየበት፣ ቶማስም "ጌታዬ አምላኬ" ብሎ የመሰከረበት ታላቅ ዕለት ነው።
📖 *(ዮሐ. ፳፥፳፬-፴)
✨ "ብርሃነ ትንሣኤውን የገለጸልን አምላካችን ለብርሃነ ዕርገቱም በሰላም ያድርሰን!" ✨
🙏 ወስብሐት ለእግዚአብሔር
Уже доступно! Исследование Telegram 2025 — ключевые инсайты года 
