Godwithus biblical truth channe🎤🎤🎤🎤🎤🎤🎤🎤🎤🎤🎤🎤
Open in Telegram
(ዮሐንስ6፣29፤ ኢየሱስ መልሶ፡— ይህ የእግዚአብሔር ሥራ እርሱ በላከው እንድታምኑ ነው፡ አላቸው።..መጽሐፍ ቅዱሳዊ እውነትን የእለት እንጀራ ለማድረግ፥አብረን እንተጋለን፥ይህም የዚህ (channel) ዋና አላማ ነው።
Show more228
Subscribers
No data24 hours
-27 days
-530 days
Posts Archive
Repost from 🔥የወንጌል ስርጭት revival🔥🔥
የሐዋርያት ቤተክርስቲያንና ስሁት/የሐሰት ትምህርታቸው_ክፍል_ሁለት(2)
#ክፍል አንድ ላይ የሐዋርያት ቤተክርስቲያን አባላት የሚያነሱት ጥያቄ ለማንሳት ሞክሬ ነበር እርሱም ስለ ስላሴ ስሆን በዚህ ክፍል ደግሞ ስለ ስላሴ ያላቸው አቋም ወይም የቄስ ተክሌ በታሪክ ላይ የፈጸሙት ትልቅ ክህደትና ውሸት ምን እንደሆነ ከእነርሱ መጽሐፍ ጣቅሼ እንዴት ደግሞ ልክ እንደልሆኑ በማስረጃ ለማቅረብ እሞክራለሁ ።
#ቄስ ተክሌ ስለ ስላሴ ትልቅ ውሸት ከዋሹት መጽሐፍ ግምባር ቀደም መጽሐፍ "ትምህርተ መለኮት " የሚለው የገዛ መጽሐፋቸው ገጽ 17 ላይ ስላሴ የሚባለው ትምህርት ወይም እምነት ማለትም አንድነት በሶስትነት የሚለው ሀሳብ ለ ቀድሞ 325 አመታት በቤተክርስቲያን ታሪክ ተሰምቶ የማይታወቅ እናም ከንቅያ ጉባኤ ቧኅላ ማለትም ከ325 አመታት ወዲህ የጀመረ የባእድ አምልኮ ነው አይነት ነገር አስቀምጠዋል ነገር በጣም የሚገርመው ቄስ ተክሌ ወደዚህ ስሁት አስተምሮ ከመግባት በፊት የስላሴ አማኝ መሆናቸውንና በአድስ አበበ የሙሉ ወንጌል ቤተክርስቲያን አባል መሆነቸው ነው፤ነገር ግን በፊት እንደልኩኝም ወደዚህ ስሁት/ኑፈቄ ትምህርት የገቡት 1961 ዓ.ም ነበር፤ይህንን ከላይ የተመለከትናው ጉዳይ ስለሆነ ወደ ዛሬ ሀሳብ እንመልስ፤የዛሬ ትልቁ ሀሳብ ቄስ ተክሌ ውሸተም እንደሆኑ ማስረገጥና ስለ የሚለው ሀሳብ ከ325 ዓ.ም በፊት ቤተክርስቲያን የሚታወቀው ትምህርት እንደሆነ መረጃ ማቅረብና መጽሐፍ ቅዱሳዊ ትምህርት እንጅ የባእድ አምልኮ እንደልሆነ መረጋገጥ ነው። ምን እያልኩ እንደሆነ ግልጽ ለማድረግ ያክል ከንቂያ ጉባኤ በፊት ቤተክርስቲያን ከባጉ ሐዋርያት ተቀብላ አምና ስለ ስላሴ እያስተማረች እንደቆያች ማስረጃ እንመልከት፦
1ኛ..Polycarpየሐዋሪያው ዮሐንስ ደቀመዝሙር የነበረ እንዲሁም የሰምርኔስ ቤተክርስቲያን ሊቀጳጳሳት የነበረሰው ነው።:-በ70ዓ.ም ተወልዶበ155ዓ.ም ወይም በ160ዓ.ም የሞተ አባት ነው ።ይህሰው ትምህርተ ሥላሴን በተመለከተ እንዲህ ብሏል፦
👉“ሁሉን ቻይ እግዚአብሔር ሆይ...ዘላለማዊና ሰማያዊ በሆነ ሊቀካህናት በምትወደውና ባከበርኸው ልጅህ በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል ለአንተና ለእርሱም እንዲሁም ለመንፈ ስቅዱስ አሁንም ሆነለዘላለም ክብርይሁን”
MartyrdomofPolycarp,14.ANF,I:42.
2ኛ..Ignatius of Antioch (የአንፆኪያው)፦የአንጾኪያ ቤተክርስቲያንሽሊቀጳጳሳትችየነበረና በ98ዓ.ም ወይም በ117ዓ.ም እንደሞተ አባት የሚገመት ክርስትናን ከመናፍቃን በመከላከሉ ዙሪያ ብዙ የጻፈ ዐቃቤ ክርስትና ነው።እንዲህም አለ፦
👉“በእምነትና በፍቅር፤በወልድ፣በአብና በመንፈስ ቅዱስ፤በመጀመሪያው እና በመጨረሻው፤ከሚያስደንቅ
ጳጳስችሁ ጋር እናም እንደሽእግዚአብሔር ፈቃድ ካሉ ዲያቆናት ጋር በሚገባ በጠበቀሽመንፈሳዊ አክሊል የምታደርጉትን ሁሉ በስጋና በመንፈስ እንዲከናወን በጌታችንና በሐዋርያት ትምህረት እድትጸኑ አጥኑ።ክርስቶስ ኢየሱስ ለአብ በስጋው እንደተገዛለት እናም ሐዋርያት ለክርስቶስ፣ለአብና ለመንፈስ ቅዱስ
እደሚታዘዙ እናንተም ለጳጳሳችሁ እና እርስ በእርሳችሁ ተገዙ(ታዘዙ)በዚያን ጊዜ በስጋችሁም በመንፈሳችሁም አንድነት ይኖራችኋል።”EpistletotheMagnesians,Chapter13
3ኛ..Tertullian ከ160-215 የነበረ አፍሪካዊ የነገረ መለኮት ሊቅ ነው ።ይህ ሰው ክርስትናን ከመናፍቃንና ከሌሎች ሐያስያን ለመከላከል ብዙ ጽፎአል ፦.
👉“አብና ወልድ ሁለት ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ደግሞ ሦስት መሆናቸውን እንገልጻለን።የቁጥሩንም ቅድመ ተከተል ከድነት አንጻር ነው....ይህም አንድነትና ሦስትነትን መሠረት አድርጎ ሦስቱንም ማዕከል ያደረገ ነው፤እነርሱም አብ፣ወልድና መንፈስ ቅዱስ።[አብ፣ወልድና መንፈስ ቅዱስ]ሦስት ናቸው....ነገር ግን በባሕር ይሳይሆን
በገጽ፣በኀይል ሳይሆን ነገር ግን በዐይነት።በባሕርይና በኀይል አንድ ናቸው፤ምክንያቱም አንድ አምላክ ብቻ
ስላለና ይህም ባሕርይ፣ገጽና ዐይነት በአብ፣በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ዙሪያ ያለ በመሆኑ”Tertullian,
AgainstPraxeas,2.PL2.156–57. እንደውም ስላሴ የሚል የስና መለኮት ቃል ለመጀመርያ ጊዜ የተጠቀመውም ይህ ሰው ነው፥ስለዚህ ቄስ ተክሌ ይህንን የሚያክል ብዙ ምስክር ከ 325 ዓ.ም በፊት እያለ ስላሴ የሚለው ሀሳብ የጀመረው 325 ዓ.ም ላይ ነው ማለታቸው ውሸተም ሊያስብለቻው ይችላል ምክንያቱም በዚህ እውን በሆነ ታሪክ እንኳን የዋሹ ሊቅ ነኝ ባይ ቄስ ተክሌ ትክክለኛውን የሐዋርያትን ትምህርት ሊያስተምሩ በፍጹም አይችሉም ይህ ብቻ አይደለም በዚህ ውሸተም ቄስ መገለጥ ላይ የተመሠረተው ይህም የሀሰት ተቋም መናፍቃን እንደሆኑ ያራገግጣል። ብዙ ማስረጃ ማቅረብ ይቻላል ለዚህ ክፍል ግን ይህ ይባቃናል።
♦መልካም ፈቃደችሁ ከሆነ ደግሞ ወደዚህ ቤት የዚህ የስሁት አስተምሮ ተጠቅ የሆኑትንና ሌሎች ጓደኞቻችሁን ጋብዙ ተባረኩልኝ🥰
https://t.me/onegodtruth
ሰው ከሆንክ መድከም የሕይወትህ አንዱ_ክፍል ነው፤ነገር ግን ተዳክመህ ፈጽማህ ወድቀህ እንደትቀር፣ደግሞ መቼ እወድቃለሁ በሚል ስጋትና ፍርሃት ቀኖችህ የተሞሉ እንደይሆኑ መጽሐፍ እንዲህ_ይላል፦
እንዴት ነችሁልኝ ቅዱሳን የእግዜር ልጆች ሰላም ይብዛለችሁ፥ዛሬ አንድ ነገር ከትዝብቶቼ መከከል ሊነገር፤እርሱም ከሰምንት በፊት ነበር ከጓደኞቼ ጋር እድል አግንቼ በይርጋላም ሆስፒታል ህክምና ላይ ያሉ ሰዎች እንዴት ነችሁ ልንለቻውና ሊንጻልይ ብቅ አልን እናም ተከፋፈልንና ጥያቃ ጀመርን እኔ እንደ እድል የደረሳልኝ የሳንባ በሽታ ህክምና ክፍል ነበር #እናም በጣም ብዙ ሰዎች ነበር ተኝቶ ታከሚ ክፍል ህክምና እየተደረገላቸው የነባሩት ከነዚያ መከከል አንደንዶቹ በጣም በምያሳዝን ሁኔታ ውስጥ ያሉ ነቸው #እናም ጸሎት ለመረግ ፈቃደኝነተቻውን ስንጠይቅ ብዙዎች በሕይወት የመቀጣል ጉዳይ አሳሰብ ብሆንም ግን ክርስቶስን የተቀባሉ በሥጋ ሞት ብሄዱ እንኳን ወደት እንደሚሄዱ የሚያውቁ መሆነቸው በጣም አስደሳች ነበር #ነገር ግን በዛው ልክ ደግሞ ሁለት ሞት ለመሞት የተዛገጁ እንደሉ ማዬት ለእኔ በጣም ሊብ ሳበር ነበር ምክንያቱም ሰው ክርስቶስን በእምነት ከተቀበለ ብሞት እንኳን ሕያው አደርገዋል ብሏል እየሱስ ስለዚህ ምን ለማለት መሰላችሁ ትልቁ ጉደት የሥጋ ሞት ሳይሆን በአለማመን ምክንያት የሚመጠው ሞት ነው #ስለዚህ በአጭሩ በክርስቶስ እየሱስ አምኖ መዳን ለዛሬ ብቻ ሳይሆን ለዘለላም ሕይወት ዋስትና ነው ምክንያቱም የእየሱስ ከሞት መነሳት እኛም በሥጋ ብንሞት እንኳን በትንሳኤ እንደምንነሳ እርግጠኛ የሚያረገን ነገር ነው በእምነት መሞቱንና መነሳቱን ከማንን ስለዚህ ወደጄ ብዙ ድካም ሰይዝህ ወደ እየሱስ ናናናናናናናናና!!
#please share it, at least three unbeliever frends🥰🥰
+6
ቅዳሜ ቀን በይርጋዓለም እግዚአብሔር ድንቅ ጊዜ ሰጥቶን JEMA እና ONE TO ONE ምስክርነት ጊዜ ነበረን። ምስክሮች እንድንሆን የረዳን እግዚአብሔር ይባረክ።🙏
2ኛ ቆሮ 2:14-17
ነገር ግን በክርስቶስ ሁልጊዜ ድል በመንሣቱ ለሚያዞረን በእኛም በየስፍራው ሁሉ የእውቀቱን ሽታ ለሚገልጥ ለአምላክ ምስጋና ይሁን፤ በሚድኑቱና በሚጠፉቱ ዘንድ ለእግዚአብሔር የክርስቶስ መዓዛ ነንና፤ ለእነዚህ ለሞት የሚሆን የሞት ሽታ ለእነዚያም ለሕይወት የሚሆን የሕይወት ሽታ ነን። ለዚህም ነገር የሚበቃ ማን ነው?
የእግዚአብሔርን ቃል ቀላቅለው እንደሚሸቃቅጡት እንደ ብዙዎቹ አይደለንምና፤ በቅንነት ግን ከእግዚአብሔር እንደ ተላክን በእግዚአብሔር ፊት በክርስቶስ ሆነን እንናገራለን።
በአጠቃላይ ከተመሰከረላቸው ውስጥ
ተስፋ የሰጡ= 8
በንስሐ የተመለሰ=1
ጌታን አምነው የዳኑ=13
ለሁሉም በጌታ ሥር መስደድ እንድሆንላቸው እንጸልይ🙏🙏🙏🙏
#ወንጌል_ለሁሉም_ሁሉም_ለወንጌል!!
#ወንጌል_ለሁሉም_ሁሉም_ለወንጌል!
#ወንጌል_ለሁሉም_ሁሉም_ለወንጌል!!
#ወንጌል_ለሁሉም_ሁሉም_ለወንጌል!!
HU Af Gospel Mobilizers Team.
#እግዚአብሔር ይማስጌን🙏🙏🙏
https://t.me/xlmau
✍@godwithusbibletruthchannel
እንዴት ነችሁ የጌታ ብሩከን ሰላም ይብዛለችሁ🙌🙌 ከላይ እንደምታዩት ዘማሪ አዚ እግዚአብሔር ረድቶት አድስ መዝሙር እነሆ እያለን ነው፤እናም የዩቱብ አካውንት subscribe አድርጉ እናም ሼር አድርጉላት።
እንግዲህ ብዙ ሰዎች ለመመለስ ቀን ይቀጥራሉ፤ነገ ወደ እግዜር እመለሳለሁ እየሱስን እንዴ ግል አደኜ እቀበልና ከዛሬ የተሻለ መንፈሳዊ ሕይወት እኖራለሁ ብለው ብዙ እቅድና ፕሮግራም ያወጠሉ #እቅድ ማውጣቱ በጣም ጥሩ እኮ ነው #ነገር ግን በጣም መታሰብ የለባት ነገር ደግሞ ስትሳሩ ለዘለዓለም እንዴምኖር ሰው #የእየሱስን መምጣት ግን ዛሬ እንደልሆነ አስቡት ብሎ የሄደው እየሱስ ብመጣ የሚለውና #ማን ያውቃል ደግሞ በአገጣም ወደ ጌታ የምንሄድበት ሰዓት አሁን ብሆን ብለን መሳብና በፍጥነት በደሙ በኩል ማለት በእየሱስ በኩል ወደ እግዜር መመለስና ንስሃ ገብተን ከእግዜር ጋር መተረቅና በዘለለም ሕይወት እርግጠኞች ልንሆን ይገባል #እየሱስ ሰውን ሁሉ ይወደል #በእርሱ በኩሉ ደግሞ ወደ አብ የሚመጡትን ሁሉ ፈጽሞ ሊያድን ይችላል።
“ወንድሞች ሆይ፥ መጠራታችሁን ተመልከቱ፤ እንደ ሰው ጥበብ ጥበበኞች የሆኑ ብዙዎች፥ ኀያላን የሆኑ ብዙዎች፥ ባላባቶች የሆኑ ብዙዎች አልተጠሩም።”
— 1ኛ ቆሮንቶስ 1፥26
#ውዶቼ አዎ መጠራታችንን እንመልከት፤እግዚአብሔር እንዴት እንደጠራንና ከምን አይነት ነገር ውስጥ ጠርቶ እንደወጣና፤እንዴት ወደ እራሱ እንደቀረበን በትኩረት እንመልከት ምክንያቱም እግዚአብሔር ጠርቶ ስያወጣን ብዙ የእኛን የኃላ ታሪካችንን፣ብዙ ጉድለታችንን፣ወገን አለመሆናችንን፣ከመሳፍንት ዛር፣እንደ ሰው ወግና ሰርዐት እናም አስተሳሰብ ከትልልቅ ቤተሰብ መሆናችንን እናም በጣም ጥሩ፣ዝናችን የገነነ፣ጥሩ እውቀት በእኔና በእናንተ ተገኝቶብን ሳይሆን፤ከእኛ ብንጠያቅ የሚነሳይ ምንም መልካምነት ሳይኖረን፤እንደው የአላም ሞኞች ሆነን ክርስቶስን በለማወቅ ድንቊርና ውስጥ እያለን እግዚአብሔር አብ የገዛ ልጁን ስለ እኔና እናንተ ለመስቀል ሞት አሳልፎ ሰጥቶ ለዛሬ ብቻ ሳይሆን እስካ መጨረሻው ወደደን፤ይህንን ሁሉ ደግሞ ያደረገው እኛ የነበርንባትን ሁኔታ ማለት ድካም፣ ጥንካሬአችንን አይቶ ሳይሆን በእኛ ሊገለጥ የነበረውን የልጁን መልክ አይቶ ነው።
#ውዶቼ ተድያ አምላክ ሰው በመሆን የተከናወነው የእኔና የእናንተ መዳን እንዴት ትልቅ ነው!🤔🤔 ይህንን መመልከቱ ክርስትናን በአገባብ እንድንኖር ክርስቶስ በእኛ እንድገለጥ ትልቅ ጥቅም አላው። እውነት መጠራታንን እንዴት ድንቅ ነው!!!!
#ዛሬ ማታ እንደዚህ ይሁንላችሁ እግዚአብሔርን ወደ ፈቀዳችሁ መጥራት ሰይሆን እናንተ ወደ እግዚአብሔር ፈቃድ መጠጋት ወይም መቅረብ፣መስማማት ይሁንላችሁ ውዶቼ!!!
@godwithusbibletruthchannel
#የዛሬዋ ቤተክርስቲያን
#እንዴት ነችሁ ውዶቼ ሰላምና ፀጋ ይብዛለችሁ 🙌🙌 ዛሬ አንድ ነገር ለማለት ነው የመጠሁት ስለ ዛሬይቱ ቤተክርስቲያን፥እኔ የእኔን ሀሳብ ከማለቴ በፊት አንድ ጥያቄ ሊጠይቃችሁ እወዳለሁ፥ጥያቄውም የዛሬ ቤተክርስቲያን ምንን ትመስላለች? ? #የጥንቱን የሐዋርያት፣ክርስቶስን አድምቃ የገለጣችሁን፣ክርስቶስ ላይ የተመሠረተችሁን ወይም ምን ወይም ማን ትመስላለች? ? #ሌላው ደግሞ ማንን ወይም ምን ትሸተላች?? #መጽሐፍ ቅዱስ ስለ ቤተክርስቲያ ማንናት ግልጽ የሆና ትምህርት አለው፥ማን እንደሆነች፣ከዬት እንደመጣች እናም ወዴት እንዴሚትሄድ ፍንቱዊ አድርጎ ያስቀምጣል፥ከዚህ መጽሐፍ ቅዱስ ስለ ቤተክርስቲያን ከሚናገረው ነገር አንፃር የዛሬዋን ቤተክርስቲያን ስንመለከት እውነትም መልኳ እንደጠፋ፣ጠራኗ እንዳካራፈ በቤቷ ውስጥ ሊገለጥ የሚገባው የተረደው በግ ክብር፣ምስጋና፣አምልኮ የሚገባው እርሱ በብዙ ነገር ተሻፍኖና ደብዝዞ ማዬት በጣም አሳዘኝና የሞት ያክል ሊብ ሰባር ነው። #እስክ አስቡት በዬሰምንቱ ፕሮግራማችን ማን ይሁን ድምቅ ብሎ የሚተያው? #የሚሳበከውስ ማን ነው? #ብዙ ጊዜ ቤተክርስቲያን ውስጥ የሚደረጉ ሳበከዎችንና ትምህርቶችን ሳይ በጣም አዝናለው ምክንያቱም መጽሐፍ ቅዱስ ክፍሉን ነግረውን፣ርዕስ ተቀብለን እንማራለን ብለን ስንጠብቅ የከፈትናው መጽሐፍ እዛው ይቆይና መንገድ የተመለከቱትን ቅረቅንቦና የሰውን ባህርይ፣ከእግዝአብሔር የተቀባሉትን ሳይሆን እነርሱ አይታው ለእነርሱ ትክክል የልመሳላቻውን ነገር በጆሮ ስካቱ መድረኩ ክርስቶስ የሌላባት ኦና ቤት የመስላል፣ደግሞ የትኛውንም የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል የንብቡ መገላጥ እናገለግለላን የሚሉ ሰዎችን ይተቻሉ፤እነዚህ ስዎች ትክክል ነቸው ማለቴ አይደላም ግን በማድረካችን ላይ እየሱስ ከሚጣረው በላይ እነርሱ ስብከት ሆናዋል ማለቴ እንጂ፤ለምን እንዲህ አልክ ስህታት መሆናቻው ማወራት አለባት የሚል ሰው ብኖር እኔ አንድ ነገር አምናለው እርሱም ስህታትን ደገግማን ከማውራት ፍጣረት ሁሉ የሚሻናፈውን ጉልባት ሁሉ በፈቃዱ የምንባረከካለትን እየስስንና የመስቀል ፍቅሩን በጥልቃትና በመንፈስ ኃይል እግዚአብሔርን በማወቅ ማስተማሩና በትውልድ አዕምሮ ደገግሞ መጨመሩ ትልቅ ተፅዕኖ ያመጣል ብዬ አምናለው፤ማደረግ የለበትም እንደዛው ነው ብዬ አስባለው። #ይህንን ሀሳቤ የሚደግፈውን አንድ ታሪክ ለጫውታችሁ አንድ ብር የሚያመርት ድርጅት ሠራተኞቹ ከትክክለኛው ብር ፌኩን እንድላዩ የሚያደርገው ወይም ለማስተማር የሚጠቃመውን መርሆ በጣም እወደዋለሁ፤ እርሱም ድርጅቱ ሠራተኞቹ ደገግመው ትክክለኛውን ብር እንድቀጥሩ የረገቻዋል ከዚያም ሠራተኞቹ በቀለሉ የብር ቀላም አይናቱን እንኳን ማዬት ሰይጠባቅባቻው በቃላሉ ፌኩን በእጅ ብቻ ማለዬት ይችላሉ፤ስህታትን ሁልግዜ በግናት ከመናገር ይልቅ ትክክለኛውን ነገር አጉልቶ ማሰዬት ለዛሬዋ ቤተክርስቲያን ወደ ትክክለኛው እግዚአብሔር ፕሮግራምና እቅድ እንድትመለስ ምርጫ የሌላው መብቴ ነው በዬ አስባለውም እምነቴም ነው። ተባረኩልኝ ውዶቼ 🥰🥰
✍@godwithusbibletruthchannel
እርዳኝ_erdagn_ርኆቦት_መዘምራን_Rehoboth_Choir_ዳምቦያ_ኡሩልቾ.m4a7.40 MB
እርዳኝ |erdagn |ርኆቦት መዘምራን|Rehoboth Choir(ዳምቦያ-ኡሩልቾ)
👁 2.3K 👍 88
📥 09.05.2025
👤 Rehoboth Choir-Urulecho
🕒 07:59
Isaiah 6:1-3
[1]IN THE year that King Uzziah died, [in a vision] I saw the Lord sitting upon a throne, high and lifted up, and the skirts of His train filled the [most holy part of the] temple. [John 12:41.]
[2]Above Him stood the seraphim; each had six wings: with two [each] covered his [own] face, and with two [each] covered his feet, and with two [each] flew.
[3]And one cried to another and said, Holy, holy, holy is the Lord of hosts; the whole earth is full of His glory!
Devotional verse
@godwithusbibletruthchannel
