en
Feedback
Godwithus biblical truth channe🎤🎤🎤🎤🎤🎤🎤🎤🎤🎤🎤🎤

Godwithus biblical truth channe🎤🎤🎤🎤🎤🎤🎤🎤🎤🎤🎤🎤

Open in Telegram

(ዮሐንስ6፣29፤ ኢየሱስ መልሶ፡— ይህ የእግዚአብሔር ሥራ እርሱ በላከው እንድታምኑ ነው፡ አላቸው።..መጽሐፍ ቅዱሳዊ እውነትን የእለት እንጀራ ለማድረግ፥አብረን እንተጋለን፥ይህም የዚህ (channel) ዋና አላማ ነው።

Show more
228
Subscribers
No data24 hours
-27 days
-530 days
Posts Archive
Part_one(1) የመንፈስ ቅዱስ የጸጋ ስጦታዎችና የቤተክርስቲያን አባቶች በኹለተኛው ክፍለ ዘመን (ከ100-200 ዓ/ም) የነበሩ የቤተክርስቲያን አባቶች የመንፈስ ቅዱስ የጸጋ ስጦታዎች በቤተክርስቲያን ውስጥ በንቃት እንደሚሰሩ ያምኑ ነበር። በዚህ ዘመን የነበረው አመለካከት ዛሬ "ሴሴሽንዝም" (Cessationism) ወይም "ስጦታዎቹ በሐዋርያት ዘመን አብቅተዋል" ከሚለው ትምህርት በተቃራኒ፣ ስጦታዎቹ የቀጠሉ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ ነበር። 1. የጸጋ ስጦታን በተመለከተ በዲድስቅልያ ​ይኽ መጽሐፍ(ዲዲስቅልያ) መጽሐፍ ቅዱስ ተጽፎ ካለቀ በኋላ የነበሩት የመጀመሪያዎቹ ክርስቲያኖች ምን ያምኑ እንደነበር፣ እንዴት ይጸልዩ እንደነበርና ቤተክርስቲያንን እንዴት ያስተዳድሩ እንደነበር ለማወቅ የሚረዳ ታሪካዊ ሰነድ ነው። በሶርያ አካባቢ በ100 ዓ.ም. ገደማ እንደተጻፈ የሚገመተው ዲድስቅልያ፤ የዐሥራ ኹለቱ ሐዋርያት አስተምህሮ በመባል እንደ ቤተ ክርስቲያን ሰነድ ኾኖ ያገለግል ነበር። ይህም የቤተ ክርስቲያን መጽሐፍ ከትንቢት ስጦታ ጋር በተያያዘ በመዘርዘር በተለይ በምዕራፍ 11-13 እውነተኛና ሐሰተኛ ነቢያት እንዴት እንደሚለዩ የተወሰኑ መስፈርቶችን ያቀርባል። “በመንፈስ በሚናገር በማንኛውም ነቢይ ላይ አትፍረድ፤ ኹሉም ኃጢአት ሊሰረይ ይችላል፤ ነገር ግን እንዲህ ዓይነቱ ኃጢአት አይሰረይም። በመንፈስ የሚናገር ኹሉ ነቢይ አይደለም፤ ነቢይ የሚኾነው የጌታን ፍላጎትና የሕይወት ምሳሌ የተከተለ ብቻ ነው። የጌታን ፍላጎትና የሕይወት ምሳሌ በመከተሉና ባለመከተሉ ሐሰተኛ ነቢይና እውነተኛ ነቢይ ሊለይ ይችላል” (ዲድስቅልያ 11፥7-8)። “በመንፈስ ቅዱስ ውስጥ ሆነው” ትንቢትን ስለሚናገሩ ነቢያት ይገልጣል። እንዲሁም “አብ ስጦታዎች ኹሉ ለኹሉም ይሰጥ ዘንድ ይሻል” ይላል። በተጨማሪም “ነቢያት በቁርባን ጊዜ ምስጋና ማቅረብ የሚፈልጉ ከኾነ ይፈቀድላቸዋል...” ይላል (ዲድስቅልያ 10፥7)። 2. ሰማዕቱ ዮስጢኖስ (Justin Martyr) (100-165 ዓ/ም) ዮስጢኖስ በአይሁድና በክርስትና መካከል ስላለው ልዩነት ሲያስረዳ፣ የትንቢት ስጦታ ከአይሁድ ወደ ክርስቲያኖች መዛወሩን ይገልጻል። "የትንቢት ስጦታ እስከ አኹኑ ሰዓት ድረስ በእኛ ዘንድ ይገኛል። በዚኽም ምክንያት ቀደም ሲል በሕዝባችሁ (በአይሁድ) መካከል የነበሩት ስጦታዎች ወደ እኛ እንደተላለፉ ልትረዱ ይገባል።" (Dialogue with Trypho, Chapter 82.) 3. ቅዱስ ሄሬኒየስ (Irenaeus of Lyons) (125-200 ዓ/ም) ሄሬኒየስ በወቅቱ የነበሩ መናፍቃን (Gnostics) ተአምራት እንደማያደርጉ በመግለጽ፣ እውነተኛዋ ቤተክርስቲያን ግን በተለያዩ ቋንቋዎች (ልሳኖች) እንደምትናገርና ትንቢት እንደምትናገር ይመሰክራል። ስለ ልሳን፦ "በተመሳሳይ ሁኔታ፣ በመንፈስ ቅዱስ አማካኝነት በሁሉም ዓይነት ልሳኖች የሚናገሩ፣ በሰው ውስጥ የተሰወረውን ምስጢር ለጥቅም የሚገልጡና የእግዚአብሔርን ምስጢራት የሚያብራሩ ብዙ ወንድሞችን በቤተክርስቲያን እንሰማለን፤ እነዚህንም ሐዋርያው 'መንፈሳውያን' ብሎ ይጠራቸዋል።" (Against Heresies, Book V, Chapter 6, Section 1.) ስለ ትንቢትና ፈውስ፦ "አንዳንዶች አጋንንትን በእውነትና በእርግጠኝነት ያወጣሉ... ሌሎች ደግሞ ስለ ወደፊቱ ጊዜ አስቀድሞ የማወቅ (Foreknowledge) ስጦታ አላቸው፤ ራእዮችን ያያሉ፣ የትንቢት ቃላትንም ይናገራሉ። ሌሎች ደግሞ በሽተኞችን እጃቸውን በመጫን ይፈውሳሉ..." (Against Heresies, Book II, Chapter 32, Section 4.) 4. ቴርቱሊያን (Tertullian) (160-240 ዓ/ም) ቴርቱሊያን መናፍቃን (በተለይ መርቅያን) የጸጋ ስጦታ ማሳየት እንደማይችሉ ሲሞግት እንዲህ ብሏል፦ "ከእርሱ (ከመርቅያን አምላክ) ዘንድ የኾነ አንድም ነቢይ ያምጣልን፤ እንዲያውም ነቢይ መኾኑን የሚያሳይ፣ የወደፊቱን የሚተነብይ፣ የልብን ምስጢር የሚገልጥ ወይም መንፈሳዊ መነጠቅ (Ecstasy) የሚያሳይ ይኹን... ወይም በልሳን የሚናገር ይኹን።" (Against Marcion, Book V, Chapter 8.) ማጠቃለያ እነዚህ አባቶች የጠቀሷቸው ነጥቦች እንደሚያሳዩት፦ 🔥ተከታታይነት (Continuity)፦ ስጦታዎቹ በሐዋርያት ሞት አላበቁም ብለው ያምኑ ነበር። 👏ማረጋገጫ (Validation)፦ የጸጋ ስጦታዎች መኖራቸው አንዷ እውነተኛ ቤተክርስቲያን ከመናፍቃን ቡድኖች የምትለይበት ምልክት ተደርጎ ይወሰድ ነበር። 🗣 ልሳን (Tongues)፦ ሄሬኒዎስ እንደገለጸው፣ ልሳን በወቅቱ "ምስጢራትን ለመግለጥ" እና "ለቤተክርስቲያን ጥቅም" ይውል ነበር። ✍ አገልጋይ ብርሃኑ ስላሴያዊ ነኝ

#Story of Evangelist አባ ጎሌ #Part_3 #ስላሴያዊ ነኝ

Story of Evangelist ዋንዳሮ #Part_2

Libamen Set Man Liyagegate Yichlal · Getayawkal Girmay Hadgo & Biruktawit Assefa Birke Special Wedding Song ℗ 2016 Getayawkal Girmay Hadgo & Biruktawit Assefa Birke

የመከተል መንገድ ክርስትና በመከተል የሚጀምር በመከተል ደግሞ የምያልቅ ወይም የሚፈጸም ሕይወት ነው። እየሱስ ለዚህም ነው ደቀሙዝሙርቱን ኑና ተከተሉኝ ያለው፤ስለዚህ ደቀመዝሙር የመሆን ቅድመ ሁኔታ መከተል መረዳት እንችላለን ። መከተል ደግሞ ፈጽሞ የመሪውን ሀሰብ

Ojች_የት ነችሁ?
መስቀሉ ስላሴያዊ ከሆነ፥ማለትም በመስቀል የተሰራው ሥራ የስላሴ አካላት የተባበሩት ከሆነ ስላሴን አልቀበልም ብሎ መዳን አይቻልም ምክንያቱም መዳነችን ስላሴያዊ ነውና። ምናልባትም እንዴት የሚል ጥያቄ ብኖር በመስቀሉ ሥራ እግዚአብሔር አብ፣እግዚአብሔር ወልድ እና እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ተስማምተዋል ስለዚህ መዳናችን ስላሴያዊ ነው።
ስላሴን አልቀበልም የሚል ሰው የመዳን ሥራ በሰራው አምላክ ማንነት ላይ ትልቅ ስህታት የሳተ ሰው ነው። From የተሰቀለው መጽሐፍ perspective

ጸሎት......ማት 17፣1-21 #ጸሎት በልጅነ በ አባት መካከል የምዳረግ ግንኙነት ነው። #ጸሎት ለምን የስፈልገል? ♦ለለውጥ ነው።(for rivaival) ♦የእግዜር ጉብኝት እንዲሆን ጸሎት ወሳኝነት አላው። ♦የሰይጣንን እቅድና ሥራ ለመፍረስ ነው። ♦ስንጸልይ የበረታች የእግዜር ክንድ ትሰራለች ። ♦ከሰማይ አምላክ የምያስደንቅ ነገር እንዲሆን ነው። ♦ወደ እግዜር በይበልጥ እንድንጠገ የደርገል። ♦ነፍሰችን አብዝተ እግዜርን እንትፈልግ የደርገል። ♦ለእግዜር ሀሳብ መንፈሳችን ንቁ እንዲሆን ። (ለእግዜር ሀሳብ ፈጣን ምለሽ እንድንሰጥ የደርገል)።1ኛ ጴጥ 5፣5 ♦በችግረችን ውስጥ የእግዜርን እጅ እነያሌን።1ኛ ሰሙ 13፣... ♦ጸሎት የሽግግር ቦታችን ነው።

ትላንት በይርጋለም One to One + Jema ድንቅ ጊዜ ነበረን። በነገር ሁሉ ይረዳ እግዚአብሔር ይባረክ:: ስለ ሐዋርያት ቤተክርስቲያን ኑፈቄም የተወሰና ነገር ለመንሳትና ስሁትናቱን ግንዛቤ ለመፍ
+9
ትላንት በይርጋለም One to One + Jema ድንቅ ጊዜ ነበረን። በነገር ሁሉ ይረዳ እግዚአብሔር ይባረክ:: ስለ ሐዋርያት ቤተክርስቲያን ኑፈቄም የተወሰና ነገር ለመንሳትና ስሁትናቱን ግንዛቤ ለመፍጣር የሞካርንባት ጊዜ ነበር ክብር ለአብ፣ለወልድና ለመንፈስ ቅዱስ ለአንድ አምላክ ይሁን! ሙሉ Report በቅርቡ ይለቀቃል....
1ኛ ዮሐንስ 1 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹ ስለ ሕይወት ቃል ከመጀመሪያው የነበረውንና የሰማነውን በዓይኖቻችንም ያየነውን የተመለከትነውንም እጆቻችንም የዳሰሱትን እናወራለን፤ ² ሕይወትም ተገለጠ አይተንማል እንመሰክርማለን፥ ከአብ ዘንድ የነበረውንም ለእኛም የተገለጠውን የዘላለምን ሕይወት እናወራላችኋለን፤ ³ እናንተ ደግሞ ከእኛ ጋር ኅብረት እንዲኖራችሁ ያየነውንና የሰማነውን ለእናንተ ደግሞ እናወራላችኋለን። ኅብረታችንም ከአባት ጋር ከልጁም ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር ነው። ⁴ ደስታችሁም እንዲፈጸም ይህን እንጽፍላችኋለን
#ወንጌል_ለሁሉም_ሁሉም_ለወንጌል #ወንጌል_ለሁሉም_ሁሉም_ለወንጌል #ወንጌል_ለሁሉም_ሁሉም_ለወንጌል #ወንጌል_ለሁሉም_ሁሉም_ለወንጌል

የተወደዳችሁ የፌሏችን ልጆች ፡ ሰላም ለእናንተ ይሁን🤗 🔑እግዚአብሔርን መፈለግ #SUBTITLE_1 በመመለስ #SUB-SUBTITLE_3 በመተውና በእምነት በመቅረብ ጌታ ረድቶን ባለፈው ሳምንት የቢግ
የተወደዳችሁ የፌሏችን ልጆች ፡ ሰላም ለእናንተ ይሁን🤗              🔑እግዚአብሔርን መፈለግ                     #SUBTITLE_1                        በመመለስ                     #SUB-SUBTITLE_3 በመተውና በእምነት በመቅረብ                         ጌታ ረድቶን ባለፈው ሳምንት የቢግ ፒክቸራችንን እግዚአብሔርን መፈለግን #SUBTITLE_1 በመመለስን #SUB-SUBTITLE_2 መናዘዝ ከአገልጋይ ፍቃዱ ጋር አይተን ነበር :: የእግዚአብሔር ፍቃድ ከሆነ ነገ #አርብ ደግሞ ከአገልጋይ ተመስገን ተሰማ ጋር #SUB-SUBTITLE_3 #በመተውና በእምነት በመቅረብ በሚል ርዕስ   የእግዚአብሔርን ቃል የምንከፋፈል ይሆናል :: 📔ስትመጡ ማስታወሻ መያዝ እንዳትረሱ : 👫ጓደኞቻችሁን ጋብዙ ::        #በመመለስ እግዚአብሔርን መፈለግ            #FRIDAYSERVICE ⏰️ 11:30 📍መካነ-ኢየሱስ 🚫መቅረትም ማርፈድም ፈፅሞ አይቻልም! #SUBTITLE_1 #በመመለስ #በመተውና በእምነት በመቅረብ #seekingGod #HUAWADAFELLOW #SHOFAR

✍እግዚአብሔርም ልጁን ወደ ዓለም የለከው ስጋ የለበሰ ሁሉ በእምነት እንድጸድቅ ነው ምክንያቱም፦ኤፌሶን 2⁸ ጸጋው በእምነት አድኖአችኋልና፤ ይህም የእግዚአብሔር ስጦታ ነው እንጂ ከእናንተ አይደለም፤⁹ ማንም እንዳይመካ ከሥራ አይደለም። ስለዚህ ዛሬ ፍጹም ኃጢአትህን ሁሉ ሊያስወግድ ወደሚችል ቅዱስ ወደ ሆነው በግ ና ወንድም ምክንያቱም እርሱ የሞተው፣የአምላክነት ክብሩ ግድ ሰይለው ወደ ምድር የወረዳው ምንም ሌላ ምክንያት የለም የአንተ ፍቅር በልጦባት ነው።ዛሬም ከና ኃጢአት ብትመጣ ፈጽሞ ይቅር ሊልህ፣የዘላለም ሕይወት ሊሰጥህና ከአብ ጋር ሊያስተርቅህ የሚችል አምላክ ነው፤ስለዚህ የራስህን ጥረት ዛሬ እርግፍ አድርግና ከእግሩ ስር እንድትደፈ አባቴ ሆይ ይቅር በለኝ እንድትለው በእምነት ብቻ የሚሆነውን የዘለዓለምን ሕይወት እንድታገኝ አበረታታሃለው ምክንያቱም እግዚአብሔር እርሱን ወደ አላም የላከው አላም በእርሱ እንዲድን እንጅ በአላም እንዲፈርድ አይደለምና ስለዚህ ወደ ፊት በለመማንህ ምክንያት ከሚፈረድብህ ፍርድ አሁን በደሙ በኩል ወደሚጣረህ አምላክ ና የክርስቶስ ደም ከኃጢአት ሁሉ ያነጻልና።

እነሆ የዓለምን ኃጢአት የሚያስወግድ የእግዚአብሔር በግ፦ ✍መጽሐፍ ቅዱሳችን በዘፍጥረት መጽሐፍ እንዲህ ይላል፦ “እግዚአብሔርም አለ፦ ሰውን በመልካችን እንደ ምሳሌአችን እንፍጠር፤ የባሕር ዓሦችንና የሰማይ ወፎችን፥ እንስሳትንና ምድርን ሁሉ፥ በምድር ላይ የሚንቀሳቀሱትንም ሁሉ ይግዙ።”  — ዘፍጥረት 1፥26 በዚህ ክፍል የእግዚአብሔርን ፍቅር እንመለከታለን ምክንያቱም እግዚአብሔር አምላክ ሰው ከመውደዱ የተነሣ በራሱ መልክ ማለት በእግዚአብሔር መልክ እንፍጠር በማለት ሰውን ምን ያክል እንደሚወድና እግዚአብሔር ከፈጠረቸው ፍጥረት ሁሉ ልዩ እንደሆነ በማስመልከት ሰው በእግዚአብሔር መልክ የመፈጠሩን አላማ ጭምር ያስቀምጣል፤ነገር ግን ምዕራፍ ሁለት ላይ እግዚአብሔር የፈጠረውን ሰው ከመውደዱ የተነሳ ማድረግ ያለበትንና የሌለበትን ለይቶ ነገረው። ✍ እግዚአብሔር ከፈጠረውም ፍጥረት ሁሉ አዳምን ብላ ካለው በኋላ በመቀጠልም መብላት የሌለበትንም ጭምር ከሚመጣው ውጤት ጋር ነገረው፤ አትብላ ያልኩህን ከበላህ ሞትን ትሞታለህ አለው ምክንያቱም እግዚአብሔር ሰውን የፈጠረው ለሞት አይደለምና ነገር ግን በጣም አሳዛኙ ጉዳይ አዳም የፈጠርውን፣በእጁ የሰራውን አምላክ ትዕዛዝ ለመጣስ በቀለሉ በሰይጣን ተታለለ። ✍ አዳም አትብላ የተባለውን ፍሬ በመብላት እግዚአብሔር ተናግሮት የነበረውን ሞት እርሱም ሞተ ደግሞም ሞት በአንድ ሰው ወደ ዓለም ገባ ምክንያቱም የኃጢአት ደሞዝ ሞት ነውና፤ከዚህ አዳም ከሰራው ኃጢአት የተነሳ ምድር ተረገመች በጣም የሚገርመው ነገር ግን እግዚአብሔር እስከ አሁን አዳምን ችላ አለማለቱ ነው፤ምንም ከኃጢአቱ የተነሳ አዳም መሸሸግን ቢመርጥም እግዚአብሔር ግን ለአዳምና ለሔዋን የቁርበትን ልብስ አደረገላቸው፥ አለበሳቸውም።”ዘፍጥረት 3፥21 ፤ይህም እግዚአብሔር ለሰው የነበረውን ትልቅ ፍቅር አመልካች ብሎም ደግሞ መሲሑን ጠቋሚ ነበር። ✍ሌላው እኛ ሁላችንም ከኃጢአት የተነሳ ተቅበዝባዥ ሆነን ልዩነት ሳይኖር አይሁድን ጨምሮ ይህንን ከኃጢአት የተነሳ መቅባዝበዝ መጽሐፍ እንድህ ብሎታል ፦“ገና ደካሞች ሳለን ክርስቶስ ዘመኑ ሲደርስ ስለ ኃጢአተኞች ሞቶአልና።”ሮሜ 5፥6 ✍ይህ ከአዳም የወረስነውን ወይም በአንዱ መተላለፍ ምክንያት ሁሉም ተጠያቂ እንደሆነ የሚያስረግጥ የእግዚአብሔር ቃል ክፍል ነው። ከዚህም የተነሳ እግዚአብሔር በሙሴ በኩል የመስዋዕት ሰርዓት ሰጥቷቸው ነበር ነገር ግን የዕብራውያን ጸሐፊ አስረግጦ ይህ መስዋዕት ፈጽሞ ኃጢአት ሊያስወግድ እንደማይችል ይናገራል ብሎም እኛ ደግሞ አህዛብ የተባልን ተስፋ ያልነበረን እንግዶች እያለ ጴጥሮስ እንዲህ ይገልጻል፦ “እናንተ ቀድሞ ወገን አልነበራችሁም አሁን ግን የእግዚአብሔር ወገን ናችሁ፤ እናንተ ምሕረት ያገኛችሁ አልነበራችሁም አሁን ግን ምሕረትን አግኝታችኋል።”  — 1ኛ ጴጥሮስ 2፥10 ✍ ምንም  እንኳ ታሪካችን እንዲህ ቢሆንም በመጥምቁ ዮሐንስ በኩል እንደገና እነሆ የዓለምን ኃጢአት የሚያስወግድ የእግዚአብሔር በግ የሚል አስደሳች ዜና ተሰማ ይህ ቅዱስ በግ እግዚአብሔር የቃልኪዳን አክባሪና ሰው ሁሉ ወዳድ አምላክ ስለሆነ ለአብርሃም ቃል ኪዳን እንደገባለት መሠረት፣ኢሳያስም እንደተነበየው ወደ ምድር ቅዱስ የእግዚአብሔር በግ ሆኖ መጣ፤እርሱ አሁን እንከን ወይም ነውር የለሽ መስዋዕት ነው። ✍እንደ አይሁድ ሰርዓትም አይደለም ክህነቱ ማለትም መካከለኛነቱ ፍጹም ፈጽሞ ሰውንና እግዚአብሔርን ለማስታረቅ የሚችል ፍጹም በግ፤ለራሱ ማቅረብ ሳያስፈልገው የራሱን ደም ይዞ እውነተኛ ወደ ሆነችሁ ወደ ቅድስቲቱ የገባ ታመኝ በግ ነው እግዚአብሔርም ይህን በግ በማቅረቡ እጅግ በጣም ደስታኛ ሆኗል ምክንያቱም ይህ በግ የእግዚአብሔርን ጽድቅ የሚመጥን ብቸኛ እግዚአብሔር ሰውን ከመውደዱ የተነሳ ለዓለም የሰጠው በግ ነው ይህ በግ እራሱ መስዋዕት፣እራሱ አቅራቢ ነው ይህም ፍጹምናውን የሚያመለክት ነው። ✍እግዚአብሔር ይህንን በግ ወደ ዓለም የላከበትን ምክንያት መጽሐፍ ቅዱስ በግልጽ ይነግራናል በብሉይም በአዲሱ ኪዳንም እንመልከት ፦“ሰውም እንደሌለ አየ፥ ወደ እርሱ የሚማልድ እንደሌለ ተረዳ ተደነቀም፤ ስለዚህ የገዛ ክንዱ መድኃኒት አመጣለት፥ ጽድቁም አገዘው።” — ኢሳይያስ 59፥16 ✍ዕብራውያን 10፥3 ነገር ግን በዚያ መሥዋዕት በየዓመቱ የኃጢአት መታሰቢያ አለ፤ ⁴ የኮርማዎችና የፍየሎች ደም ኃጢአትን እንዲያስወግድ የማይቻል ነውና። ✍“ነገር ግን ሰው በኢየሱስ ክርስቶስ በማመን እንዲጸድቅ እንጂ በሕግ ሥራ እንዳይሆን አውቀን፥ ሥጋን የለበሰ ሁሉ በሕግ ሥራ  ስለማይጸድቅ፥ እኛ ራሳችን በሕግ ሥራ ሳይሆን በክርስቶስ እምነት እንጸድቅ ዘንድ በክርስቶስ ኢየሱስ አምነናል።”  — ገላትያ 2፥16 ✍ እግዚአብሔር መጀመርያ በሙሴ በኩል ሕግ ለአይሁዶች ሰጥቶ ነበር፤ስለዚህ አይሁዶች ማለትም ሕጉ የተሰጣቸው ሁሉ በእግዚአብሔር ፊት ለመጽደቅ ቅንጣት እንኳን ሳትቀር መፈጸም ነበረባቸው ነገር ግን ይህ በአዳም መተላለፍ ምክንያት ጽድቁ ለተባለሸ ሰው ወይም ያንን የወደቀውን አዳማዊ ማንነት ለተካፈለ ሰው ፈጽሞ የሚቻል አልነበረም ምክንያቱም((“ከሕግ ሥራ የሆኑት ሁሉ በእርግማን በታች ናቸውና፤ በሕግ መጽሐፍ በተጻፉት ሁሉ ጸንቶ የማይኖር የማያደርግም ሁሉ የተረገመ ነው ተብሎ ተጽፎአልና።”))  ገላትያ 3፥10 ✍ይህን የወደቀውን ስጋ እግዚአብሔር በመስቀል በክርስቶስ እየሱስ ማስወገድ ነበረበት ማለትም አዲሱን ሰው መልበስ የግዴታ ሆኖ ተገኘ። ✍ስለዚህ እግዚአብሔር የእራሱን ጽድቅ ልኮ ዓለምን ከራሱ ጋር ማስታረቅ ነበረበት ስለዚህም እግዚአብሔር አምላክ የመረጠው መንገድ የአንዱን አለመታዘዝ በአንዱ መታዘዝ ምክንያት ማስተካከል ፈለገ ፦“በአንዱ ሰው አለመታዘዝ ብዙዎች ኃጢአተኞች እንደ ሆኑ፥ እንዲሁ ደግሞ በአንዱ መታዘዝ ብዙዎች ጻድቃን ይሆናሉ።”— ሮሜ 5፥19 ✍በአዳም አለመታዘዝ ምክንያት የሞቱ ሰዎችን እግዚአብሔር በአንዱ መታዘዝ ሊያጸድቅ ወደደ እዚህ ጋር በጣም ትኩረት መስጠት ያለብን የአንዱ ለሁሉም የሚሰራ መሆኑን ነው! ምክንያቱም እግዚአብሔር እንዲህ እንዲሆን ፈቅዷልና። ✍ስለዚህ ዛሬ ምናልባትም ኢየሱስ በመስቀል ላይ የሰራው ሥራ እንዴት በእኔ ላይ ወይም ለእኔ ይሰራል የሚል ሰው ቢኖር መጽሐፍ ቅዱስ ምስጢሩን ግልጽ አድርጎ ይናገራል እርሱም ምንድነው ካልን እየሱስ በመስቀል ላይ የሰራውን ሥራ አዎ ብሎ በልብ በሚሆን እውነተኛ እምነት እርሱ የሰራው ጽድቅ ለእኛ ይቆጠራል ፦“ሰው ያለ ሕግ ሥራ በእምነትህ እንዲጸድቅ እንቆጥራለንና።”— ሮሜ 3፥28 ✍“እንግዲህ ምን እንላለን? ጽድቅን ያልተከተሉት አሕዛብ ጽድቅን አገኙ፥ እርሱ ግን ከእምነት የሆነ ጽድቅ ነው፤”— ሮሜ 9፥30 በዚህ ክፍል ጰውሎስ ጽድቅን ያልተከተሉ አህዛብ እንዴት እንደጸዳቁ ሲናገር ከእምነት የሆነ እንደሆነ ግልጽ አድርጎ ይገልጻል ስለዚህ ማንም የራሱን ጽድቅ ይዞ ወደ እግዚአብሔር ፊት ሊመጣ ቢሞክር ከንቱ ልፋት እንጂ ትርጉም የለሽ ድካም ነው ምክንያቱም መጽሐፍ ሲናገር ጽድቃችን የመርገም ጨርቅ እንደነበር ይናግራልና።

ይህ channel እራሳቸውን ሐዋርያት ቤተክርስቲያን ነንብለው የምትጠሩትን የኢትዮጵያ ሐዋርያዊት ቤተክርስቲያንና እየሱስ አብ ነው የሚለውን ትምህርቷን በቀለ እግዚአብሔር መመዘንና ስለ ኑፈቄው በchannel በቤተሰቦች ዘንድ ግንዛቤ መፍጠር ነው፤ምክንያቱም እራሳቸውን ፕሮቴስታንት ጋር አንድ ነን በማለት ብዙዎችን ወደ ጨለማ እንዳይወስዱ ግንዛቤ መስጠትና ከጨለማ ነፍሳትን ወደ ብርሃን መጥራት ዋናው አላማ ነው ስለዚህ channelን ተቀላቀሉ 👆👆

OJ_የት ነችሁ? ሰሞኑን በአንድ ጽሑፌ አንድ ነገር ስለ OJ ቤተ_እምነት የእርስ በእርስ መጣራስ ለመመልከት ሞክራን ነበር እርሱም የቤተ_እምነቱ መስራች የሆኑት/የመጋለጡ ተቀባይ ቄስ ተክሌ በአንድ መጽሐፋቸው የተወለደው እግዚአብሔር እራሱን ነው ማለትም እንደ እነርሱ እምነት እግዚአብሔር የሚበላው እግዚአብሔር አብ ብቻ ስለሆነ ይህም ቄስ የተወለደው ይሁ እግዚአብሔር ነው ብለዋል በዚህ ቭድዮ ደግሞ ዳጉ ምን እንደሚሉ ተመልከቱ ምክንያቱም የOJ እምነት በቄስ ተክሌ መገለጥ ላይ የተመሰረተ ከሆነ እንደ ቄስ ዳጉ ንግግር የቄስ ተክሌ ትምህርት መጽሐፍ ቅዱሳዊ ወይስ አይደለም? ፍርዱን ለእናንተ 🤷‍♂ ✍@godwithusbibletruthchannel https://t.me/onegodtruth

እንዴት አላችሁ ውዶቼ ሰላምና ፀጋ ይብዛለችሁ፥እያልኩ ትንሽዬ ነገር ለማለት እወደለሁ፥እርሱም በዚህ ምድር በሚትኖሩባት ግዜ የሁልጊዜ ተግባር ማድረግና የሁልጊዜ ተግባር ማድረግ የሌለባችሁ ነገር ነው፥እርሱም በጣም ግልጽ መሆን ከለባችሁ፥በጣም ግልጽ መሆን ያለባችሁ በእግዚአብሔር የፀጋ ዙፋን ፊት ብቻ ነው፤ምክንያቱም እግዚአብሔር ስታወሩት ትኩረቱ ከእናንተ አፍ በሚወጣው ቃል ላይ ብቻ አይደለም፤ይልቅ በምን intention ነው የሚታወሩት በሚለው ላይ ነው፥ይህን ደግሞ የሚሆነው እርሱ አምላካችን መንፈስን የሚመዝን፣የልብን ሀሳብ የሚያውቅ ስለሆነ ደግሞም እርሱ አባት ስለሆነ ነው፤ይህ መርሆ ግን በሰው ፊት የማይሰራ ሆኖ በትንሹ እድሜዬ ለመመልከትና ለመረዳት ችያለው ስለዚህ በጣም ግልጽ መሆኑን በእግዚአብሔር ፈት ልናደርግ ይገባል፤ይህንን ግን የእውነት face እንደዳረገ ሰው ነው የሚላችሁ ስለዚህ ግልጽ መሆኑን በእግዚአብሔር ፊት ብቻ አድርጉት ማመንም እግዚአብሔርን ብቻ መሆን ነው ያለባት ምክንያቱም ፈጽሞ ሊታመን የሚችልና የሚገባው አምላክ ደግሞም ፍጹም ተመኝ አምላክ እርሱ ብቻ ነው፤ደግሞ ፍጹም ተመኝ ሰውም የእግዚአብሔር ልጅ የሆነው ስለ ሐጥያታችን በመስቀል የሞተው ፍጹም ሰው እናም ፍጹም አምላክ እርሱ ብቻ ነው፤ይህንን መጽሐፍ ቅዱስ በግልጽ የሚናገር ጉዳይ ነው፥የዮሐንስ ወንጌል ምእራፍ አራት ላይ እየሱስ ወደ ሰማረዊቷ ሴት ሊያወራት ስሄድ ደቀ_መዝሙርትን ወድ ከተማ ሊኮ ለብቻው ነበር ያንን ሁሉ ምስጥሩዋን የሰማው እንዴት አይነት ሰው፣እንዴት አይነት ምስጢር የሚጣብቅ አምላክ ነው እየሱስ፤ስለዚህ ብዙ ምስጢራችሁን መነገር ያለባችሁ ለእርሱ ብቻ ነው። ብዙ ጊዜ እኔ አንዳንድ ነገር የከባዳኝ ወቅት ለማን ለውራ ብዬ አውቃለሁ ነገር ግን ይህ በፍጹም ስህታት እንደሆነ መንፈስ ቅዱስ አስተምሮኛል እናም ከዚህ መረዳት ቧኀላ ምንም ልሁን ምን ለማን ለውራ የሚለውን ጥያቄ መጠየቅ እጅግ በሕይወቴ እየቀነሰ መጥቶአል፤ምክንያቱም በግልጽ የማወረው ድንቅ፣ከወዳጅ ይልቅ የሚቀርብ አባት ደግሞ ሁሌም እኔ እርሱን ከሚፈልገው በላይ እኔ እርሱ ፈት እንዲሆን የምነፍቅ አባት ከነ ድካሜ የወደደኝ፣ከነ ድካሜ የሚወደኝ እንደለ ነፍሴም መንፈሴም እርግጠኛ ሆናዋል፤ምንድነው ምን አይነት መንፈስ እድገት ደረጃ ላይ ደርሳህ ነው የሚለኝ ሰው ብኖር ምንም ላይ አልደረስኩም ነገር ግን አንድ ወዳጄ ላይ እርግጠኛ ነኝ ስለዚህ ዛሬ ውዶቼ በጣም ግልጽ ብትሆኑ በእግዚአብሔር ፈት እናም በጣም ብታምኑ እግዚአብሔርን አመኑ፤ይህንን በሕይወታችሁ የዘወትር ተግባር አድርጉ እናም እናድርግ በጣም የሚፈታንባትንና ደካመ ጎኔን ነው የነገርኳችሁ እወዳቹዋለሁ🥰🥰በተላለያዩ በሕይወት ፈተና ውስጥ የሚተልፉ ሰዎች ብትኖሩ ደግሞ በውስጥ አውሩን ያው ምን በልራዳችሁ በእግዚአብሔር ቃል እርስ በእርሳችን እንደገጋፈለን።🙌🙌 ✍@godwithusbibletruthchannel https://t.me/onegodtruth