en
Feedback
Theophilus Terefe

Theophilus Terefe

Open in Telegram
441
Subscribers
-124 hours
+17 days
+430 days

Data loading in progress...

Tags Cloud
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Incoming and Outgoing Mentions
---
---
---
---
---
---
Attracting Subscribers
September '24
September '24
+12
in 0 channels
August '24
+16
in 0 channels
Get PRO
July '24
+25
in 0 channels
Get PRO
June '24
+10
in 0 channels
Get PRO
May '24
+19
in 0 channels
Get PRO
April '24
+11
in 0 channels
Get PRO
March '24
+16
in 0 channels
Get PRO
February '24
+9
in 0 channels
Get PRO
January '24
+441
in 0 channels
Date
Subscriber Growth
Mentions
Channels
25 September0
24 September+2
23 September0
22 September0
21 September0
20 September0
19 September+1
18 September0
17 September0
16 September+1
15 September+1
14 September0
13 September+2
12 September+2
11 September0
10 September0
09 September0
08 September0
07 September0
06 September0
05 September+2
04 September0
03 September0
02 September+1
01 September0
Channel Posts
#Christmas 2013 ዓ/ም ከጻፍኩት በልደቱ ምጽአቱን በርካታ ግዜ የክርስቶስ ልደት ብለን በቀይ ቀለም ባሸበረቁ አልባሳት ተውበን በልተን ስንጠጣ የመጣውን መሲሕ መርሳታችን ይደንቀኛል። በርግጥ መልበስና እና መጠጣት ኃጢአት ወይም ክፉት ባይሆንም ትኩረታችንን መውሰዱ ግን ወጣ ብሎ ላዬ ግልጥ ነው። ጌታችን ወደምድር መምጣቱ ትንግርት ኾኖባቸው ለማመን የተቸገሩ፣ መምጣቱን የማይቀበሉ፣ የመጣውን ያላወቁ፣ አምላክ መኾኑን የማይቀበሉ፣... ብዙዎች ሳሉ እኛ ከስራ መስነፋችን ግርምት ውስጥ ይከታል። የዛሬ ሁለት አመት አከባቢ አንድ በትምህርት ቤት የማውቀው ወንድም “ክርስቶስ አምላክ አይደለም የሚል ጠንካራ መከራከሪያ ቀርቧል” ብሎ ተንቀሳቃሽ ምስል (ቪድዮ) ይሰጠኛል፤ ማብራሪያውን ይሰጡ የነበሩት የሃይማኖት መምህር የሚከተለውን ሃሳብ ለማሳመኛነት ያቀርባሉ፦ “አምላክ ሰውን በአራት <4> መንገድ ፈጥሯል። [1ኛ] ካለምንም ከአፈር-(አዳምን)፣ [2ኛ] ያለሴት ከወንድ-(ሔዋንን)፣ [3ኛ] ከወንድና ከሴት-(እኛን)፣ [4ኛ] ሁለተኛውን 'Balance' ለማድረግ ያለወንድ ከሴት -(ኢየሱስን) ፈጥሯል።...” እኚህ መምህር መሠረታዊ ነገር የሳቱት ኢየሱስ ክርስቶስ በውልደት የተፈጠረ ሰው መሆኑን ሲያነሱ ነው።ክርስቶስ ኢየሱስ ፈጣሪ ሰውን የፈጠረበትን መንገድ ለማመጣጠን የተፈጠረ ሰው ሳይሆን፤ ሰውን ለማዳን በስጋ የተገለጠ እግዚአብሔር ነው። (ዮሐ 1፥18፤ 1ኛ ጢሞ 1፥15) ክርስቶስ ኢየሱስ የእግዚአብሔር የመጨረሻ መገለጥ ነው። (ቆላ 1፥25-29) ክርስቶስ ኢየሱስ የተገለጠው የሕይወት ብርሃን ነው። (ዮሐ 1፥4-5፤ 8፥12) ክርስቶስ ኢየሱስ የተገለጠው የእግዚአብሔር ቃል ነው። (ዮሐ 1፥1-2፤ ዕብ 1፥1-4) ይህ ፍጹም አምላክ፣ ፍጹም ሰው ሆኖ የተገለጠው ክርስቶስ ኢየሱስ ሰውን ከኃጢአት ሞቶ ለማዳን ነው። ኢየሱስ ለአንዳንዶች የብዙ ችሎታ ባለቤት (Excellent man) ነው፤ ለሌሎች ደግሞ መልዕክተኛ፤ ለሌሎች ነቢይ፤ ለሌሎች የሮማውያንን ግዛት (Roman Empire) የተቃወመና ንጉስ ሆናለው ብሎ አይሁድን ስያስከትል በአደባባይ የተገደለ ሰው ነው፤ ለሌሎች አንደበተ ርቱዕ ፈላስፋ ነው፤... ለእኛ ግን ክርስቶስ በሥጋ የተገለጠ፣ ተውላጣዊ ሞትን የሞተ፣ ከሞትም በሶስተኛው ቀን <3ኛው> ቀን የተነሳ፣ ወደሰማይ ያረገ፣ በክብር ታጅቦ ልወስደን የሚመጣ የእግዚአብሔር ልጅ፤ እግዚአብሔር ነው። ስለዚህ... የተኛን ነቅተን የመሲሕውን መምጣት እናውጅ፤ እራሳችንን ለበጉ ሠርግ እናዘጋጅ። በውልደቱ መታሰቢያ ብቻ ተደስተን ትምህርቱን፣ ሕይወቱን፣ ሞቱንና ትንሳኤውን፣ ዕርገቱንና ምጽአቱን አንዘንጋ። ማራናታ! መልካም የልደቱ መታሰቢያ ይሁንላቹ!❤ ©ቴዎፍሎስ ተረፈ https://t.me/Theophilus_Terefe https://t.me/Theophilus_Terefe

2
No text...
215
3
#1st_John #Part_10 ሐ. ለእግዚአብሔር መታዘዝ (1ኛ ዮሐ 2፥1-6)      (1) 1ኛ ዮሐንስ 2፥1-2 ጥቅሱን ለማንበብ ይህን ጽሑፍ ይጫኑ! ዮሐንስ ዝርዝር ሐሳብ በመግለፅ በመደምደሚያ ዓረፍተ ነገር እያጸና ይጽፍላቸዋል። በዚህ ክፍል ውስጥ መጀመሪያ (2፥1-2) ካለፈው ክፍል የቀጠለ ሐሳብ ያነሳል። (ክፍል 9) ይህም አማኝ በኃጢአት ውስጥ ወድቆ ሊገኝ እንደሚችልና ከኃጢአቱም የኢየሱስ ክርስቶስ ደም እንደሚያነጻው ነው። አሁንም እየጻፈላቸው የሚገኘው ኃጢአት እንዳያደርጉ ወይም እንዳይለማመዱ ነው። በዚህ እውቀት ብቻ ኖረው ኋላ ኃጢአትን ሲያደርጉ ከኅብረት እንዳይጠፉም የኃጢአት ማስተሰረያ የሆነ ኢየሱስ አለ ብሎ ያሳውቃቸዋል። እኛ ሰዎች በሕይወት ዘመናችን በኃጢአት ልንወድቅ እንችላለን፤ ነገር ግን ለዚህ ኃጢአት ማስተሰረያም ጠበቃም ሆኖ በአብ ፊት የሚታይልን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። ጠበቃ ሕጉን የሚያውቅ፤ የሙግት አካሄድ የሚያውቅና ከዳኛው ጋር የማውራት አቅም ያለው ነው። ኢየሱስ ክርስቶስ በአብ ፊት መቆም የሚችል ጻድቅና ፍጹም ነው። በአብ ፊት መቆም የሚችል ከኢየሱስ ክርስቶስ በቀር ማንም የለም። እርሱ በአብ ፊት ጽድቃችን ነው። ➝ በዚህ ክፍል በተሳሳተ መልኩ መረዳት የሌለብን ሁለት ሐሳቦች አሉ። 1ኛ. ጠበቃ አለን ማለት እንደፈለግን ኃጢአት እንሰራለን ማለት አይደለም። ለምሣሌ አንድ ድርጅት ወይም ግለሰብ በተለያየ ግዜ ለሚቀርብበት ክስ ወክሎ የሚቀርብ ወይም የሚቆም ጠበቃ ያቆማል። ይህን ጠበቃ ስላቆሙ ግን እንደፈለጉ ወንጀል መፈጸም ይችላሉ ማለት አይደለም። ድንገት ቢፈጽሙና በማያውቁት ከተወነጀሉ ይሟገትላቸዋል ማለት እንጂ። ስለዚህ የኢየሱስ ክርስቶስን ደም ተማምኖ ኃጢአትን መፈጸም እንደሚቻል መጽሐፍ ቅዱስ አያስተምረንም። 2ኛ. ኢየሱስ ጠበቃችን ነው ስንል የሚሟገትልን ኃጢአት የለባቸውም ብሎ ሳይሆን ኃጢአታችንን ገልጦ በእኛ ፈንታ ቅጣቱን ይቀበላል ማለታችን ነው። እግዚአብሔር ጻድቅ ፈራጅ ነው፤ ጠበቃችንም ክርስቶስ ጻድቅ ጠበቃ ነው። ኃጢአታችንን በመደበቅ ሳይሆን ለኃጢአታችን የሚሆነውን ትክክለኛና ፍጹም መስዋዕት በማቅረብ ነው። ከዚህ በፊት ባቀረብኩት ጽሑፍ ላይም እንደገለጽኩት ሰው በሠራው ኃጢአት ለጌታ ሲናዘዝና ወደጌታ ሲቀርብ የኢየሱስ ክርስቶስ ደም ያነጻዋል። እግዚአብሔር ዛሬም በኃጢአት ይቆጣል፤ ከዚህ ቁጣው የምናመልጠው ወደክርስቶስ ተሸሽገን ነው። ይህ መስዋዕት ለጥቂቶች ብቻ የሚሆን ሳይሆን የዓለምን ሁሉ ኃጢአት ማስተሰረይ የሚችል መስዋዕት ነው። https://t.me/Theophilus_Terefe
1 044
4
No text...
277
5
#1st_John #Bible_Verses 1ኛ ዮሐንስ 2፥1-2 ¹ ልጆቼ ሆይ፥ ኃጢአትን እንዳታደርጉ ይህን እጽፍላችኋለሁ። ማንም ኃጢአትን ቢያደርግ ከአብ ዘንድ ጠበቃ አለን እርሱም ጻድቅ የሆነ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። ² እርሱም የኃጢአታችን ማስተስሪያ ነው፥ ለኃጢአታችንም ብቻ አይደለም፥ ነገር ግን ለዓለሙ ሁሉ ኃጢአት እንጂ። https://t.me/Theophilus_Terefe
278
6
#1st_John #Part_9   ለ. በብርሃን መመላለስ (1ኛ ዮሐ 1፥5-10) ጥቅሱን ለማንበብ ይህን ጽሑፍ ይጫኑ! ይህ ሁለተኛው ክፍል ዮሐንስ በመግቢያው ለጠቀሰው ሐሳብ የሚያቀርበው ሐተታ የሚጀምርበት ነው። የሚጀምረውም «እግዚአብሔር ብርሃን ነው» በሚል ገለጻ ነው። ይህ በመጽሐፍ ቅዱሳችን በተደጋጋሚ ከተጠቀሱ የእግዚአብሔር ማንነት አንዱ ነው። ይህን ማንነት ደግሞ ፈፅሞ ጨለማ የማያውቀው ነው። # ብርሃንና ጨለማ ማለት ምን ማለት ነው? መጽሐፍ ቅዱስ የሁለቱንም ቃላት ንፅፅርን በተለይም በአዲስ ኪዳን መልዕክታት ይበልጥ የሚያቀርበው ከኑሮ ወይም ከሕይወት ዘይቤ አንፃር ነው። (2ኛ ቆሮ 6፥14 ፤ ኤፌ 5፥7-14 ፤ 1ኛ ተሰ 5፥4-6 ፤ 1ኛ ዮሐ 2፥9-10) በዚህ መልዕክት መሠረት «ብርሃን» የጽድቅ፣ የቅድስናና የንፅህና ሕይወት ሲሆን፤ «ጨለማ» ቅድስና የሌለው የኃጢአት፣ የአመጽና የክፋት ሕይወት ነው። ስለዚህ ዮሐንስ የሚጽፈው እግዚአብሔር ዘንድ አመጽና ክፋት ፈፅሞ የለም፤ በእርሱ ዘንድ ያለው ቅድስና ነው የሚል መልዕክት ነው። ይሄንን መልዕክት ደግሞ የሰማነው ከራሱ ሰው ሆኖ ከተገለጠው አምላክ ከኢየሱስ ክርስቶስ ነው በማለት ታዕማንነቱን ያረጋግጣል። (ዮሐ 8፥12 ፤ 12፥35-36 ፣ 42) መጽሐፍ ቅዱስ እግዚአብሔር ብርሃን መሆኑን በተለያየ ክፍል በአጽንኦት ይናገራል። (መዝ 104፥2 ፤ 1ኛ ጢሞ 6፥16) ኢየሱስ ጨለማ በእርሱ ዘንድ የማይታወቅ እውነተኛ የሕይወት ብርሃን ነው። (ዮሐ 1፥4-5 ፣ 9 ፤ ራዕይ 22፥5) ዮሐንስ እያብራራልን ያለው በመግቢያው ላይ (ምዕራፍ 1፥1-4) የተናገረውን የሚደግፍ ሐተታ ነው። እግዚአብሔር ወልድ ሥጋን ለብሶ ወደ ምድር የመጣ የዘላለምን ሕይወት የሚሰጥ ቃል ነው፤ በእርሱ ያመንን ደግሞ ከእርሱ ከመለኮት (ከእግዚአብሔር) ጋር ኅብረት አለን። ኅብረት እያደረግን ያለነው የሕይወት ብርሃን ከሆነው ከኢየሱስ ጋር ነው። ኢየሱስ ብርሃን ማንነቱ ከሆነ፤ ጨለማ በእርሱ ዘንድ ከሌለ እኛም ከእርሱ ጋር ኅብረት ያለን ምልልሳችን እንደ እርሱ ሊሆን ይገባል። ነገር ግን ከእርሱ ጋር ኅብረት አለን እያልን ምልልሳችንን ያለቅድስናና ጽድቅ ከሆነ እውነትን የማናወቅ ሐሰተኛ አማኞች ነን። የዚህ ክፍል ዋናው ትኩረት ዕለት ዕለት በሚገጥሙት ፈተናዎች እየወደቀ የሚነሳውን ሰው ማለትም በየቀኑ በሚቀርቡለት የኃጢአት ግብዣ እየተሰናከለ ዳግም ጌታ ፊት በምሕረት የሚቆመውን ሳይሆን በአንደበቱና በትምሕርቱ በጽድቅና በቅድስና እየኖርኩ ነው እያለ በግል ሕይወቱ ግን በኃጢአት ውስጥ የሚመላለሰውን ሰው ነው። በየቀኑ በሚቀርቡ የኃጢአት ግብዣዎች ተደናቅፈን ልንወድቅ እንችላለን፤ በምሕረት ጌታ ፊት ስንቀርብ ደሙ ከኃጢአት ሁሉ ያነጻናል። ነገር ግን በአንደበታችን «እኔ በክርስቶስ ድኛለሁ፤ ከእርሱም ጋር ኅብረት አለኝ!» እያልን በኑሮአችን ግን የድፍረት ኃጢአቶችን የምንለማመድ ከሆነ ኅብረታችን ጤናማ አይደለም፤ እኛም ኅብረት ሳይኖረን የምንናገር ውሸተኞች ነን። # በክርስቶስ ያመነ በኃጢአት ሊወድቅ አይችልም? በክርስቶስ ያመነ በኃጢአት ሊወድቅ ይችላል! ይህ ማለት ግን እያወቀ ኅጢአትን እየተለማመደ መኖር አለበት ለሚለው ድምዳሜ ምንም ዋስትናና መሠረት ሊሆን አይችልም። ሰው በሕይወቱ ከፈተናዎች ብዛት ኃጢአትን ሊፈፅም ይችላል። ነገር ግን በዛው ኃጢአት ስር በየቀኑ እየተመላለሰ «የምኖረው በጽድቅና በቅድስና (በብርሃን) ነው፤ ኃጢአት (ጨለማ) የለብኝም!» የሚል ከሆነ እርሱ እውነትና ቃሉ (ሎጎስ) በውስጡ የለሌ፣ ራሱን የሚያታልልና ውሸተኛ ነው። (1ኛ ዮሐ 1፥8 ፤ 9) # ኃጢአት ከሰራን ምን ማድረግ አለብን? ዮሐንስ ግልጽ ነገር አስቀምጧል። ኃጢአትን ከሰራን የመጀመሪያው ማድረግ ያለብን ነገር በጌታ ፊት የሰራነውን ኃጢአት በሙሉ መናዘዝ ነው። የምንናዘዘው ወይም የምንነግረው ስለማያውቀው ሳይሆን ለመንጻትና በምሕረት ለመቅረብ ያለንን ፍላጎትና ፈቃደኝነታችንን ለማሳየት ነው። ይህን ስናደርግ እርሱ ከሰራነው ኃጢአትና ከሳየነው አመጻ ሁሉ ይቅር ብሎንና በደሙ አንጽቶን ኅብረታችንን እንድንቀጥል ጸጋውን ያበዛልናል። በዚህም ከብርሃን ጋር ኅብረት እንዳለው ሰው በብርሃን እንመላለሳለን። https://t.me/Theophilus_Terefe
1 090
7
No text...
293
8
#1st_John #Bible_Verses 1ኛ ዮሐንስ 1፥5-10 ⁵ ከእርሱም የሰማናት ለእናንተም የምናወራላችሁ መልእክት፦ እግዚአብሔር ብርሃን ነው ጨለማም በእርሱ ዘንድ ከቶ የለም የምትል ይህች ናት። ⁶ ከእርሱ ጋር ኅብረት አለን ብንል በጨለማም ብንመላለስ እንዋሻለን እውነትንም አናደርግም፤ ⁷ ነገር ግን እርሱ በብርሃን እንዳለ በብርሃን ብንመላለስ ለእያንዳንዳችን ኅብረት አለን፥ የልጁም የኢየሱስ ክርስቶስ ደም ከኃጢአት ሁሉ ያነጻናል። ⁸ ኃጢአት የለብንም ብንል ራሳችንን እናስታለን፥ እውነትም በእኛ ውስጥ የለም። ⁹ በኃጢአታችን ብንናዘዝ ኃጢአታችንን ይቅር ሊለን ከዓመፃም ሁሉ ሊያነጻን የታመነና ጻድቅ ነው። ¹⁰ ኃጢአትን አላደረግንም ብንል ሐሰተኛ እናደርገዋለን ቃሉም በእኛ ውስጥ የለም። https://t.me/Theophilus_Terefe
300
9
#1st_John #Part_8   ሀ. የሕይወት ቃል (1ኛ ዮሐ 1፥1-4) ጥቅሱን ለማንበብ ይህን ጽሑፍ ይጫኑ! ምዕራፍ 1፥2-4 በዚህ ቅድመ ቃል ውስጥ ከሚገኙ ቁልፍ ሐረጋትና ቃላት መካከል በተደጋጋሚ የሚመጣው ሕይወት የሚለው ቃል ነው። ከዚህ ቀደም ስለ«ሕይወት» እንደጻፍኹትም ክርስቶስን አመልካች ቃል ነው። (ይህን ጽሑፍ ተጭነው ማብራሪያውን ይመልከቱ) ዮሐንስ አሁን ደግሞ የሚነግራቸው ይህ ሕይወት በአካል (ቁሳዊ አካል ይዞ) መገለጡን ነው። ይህ «ተገለጠ» የሚለው አባባል የተገለጠው አካል ቀድሞ እንደነበረና አሁን ግን ላላዩት መታየቱን ያሳያል። ዮሐንስ በዚህ ብቻ ግራ አጋብቶ አይተውም። የእርሱን ቀዳሚ መኖሪያውንና ማንነቱን «ከአብ ዘንድ የነበረውንም» በማለት ይገልፃል። ይህ አገላለጽ ደግሞ አምላክ ሥጋን ለብሶ ሰው ሆኖ እንደመጣ ይገልፃል። የዮሐንስ አፃፃፍ የሚያውቅ ሰው የሚያውቀውን ነገር ለማስረዳት የሚጣደፍበትን በእውቀት የተሞላ ድፍረትን ያሳያል። ይህንን የምናረጋግጠው «...እንመሰክርማለን...እናወራላችኋለን» በሚለው አገላለጹ ነው። የሚመሰክሩትም ደግሞ ይህ የተገለጠው የሕይወት ቃል የዘላለም ሕይወት እና አዳኝ መሆኑን ነው። # ይህን የሚመሰክሩት ለምንድር ነው? ዮሐንስ የሚመሰክሩበትን ዓላማ በገልጽ ያስቀምጣል። 1ኛ. ከአባትና ከልጅ (ከመለኮት) እና ከአማኞች ጋር ኅብረት እንዲኖራቸው ነው። አንድ ሰው በተገለጠው የሕይወት ቃል (በኢየሱስ ክርስቶስ) ሲያምን ከመለኮት ጋር ኅብረት ይኖረዋል። ከዚህ ጋር ተመሳሳይ ሐሳብ ኢየሱስም በዮሐንስ ወንጌል 14፥23 ላይ ሲናገር እንመለከታለን። “ኢየሱስም መለሰ አለውም፦ የሚወደኝ ቢኖር ቃሌን ይጠብቃል፤ አባቴም ይወደዋል ወደ እርሱም እንመጣለን በእርሱም ዘንድ መኖሪያ እናደርጋለን።” ከመለኮት ጋር ጤናማ ኅብረት ያለው ሰው ከአማኞች ጋርም ጤናማ ኅብረት ይኖረዋል። 2ኛ. ፍጹም ደስታን እንዲያገኙ ዘንድ ነው። በክርስቶስ አምኖ ደህንነት ያገኘና በእውነተኛው መንገድ በመሄድ ከቅዱሳን ጋር ኅብረት የሚያደርግ ፍጹም ደስታን ያገኛል። ዮሐንስ ደስተኛ ይሆን የነበረው በክርስቶስ በማመኑና ከቅዱሳን ጋር ባለው ኅብረት ብቻ ሳይሆን መንፈሳዊ ልጆቹም በዚህ መንገድ በመሄዳቸውም ጭምር ነው። “ልጆቼ በእውነት የሚመላለሱ መሆናቸውን ከመስማት የሚበልጥ ደስታ የለኝም።” (3 ዮሐ 1፥4) ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዮሐንስ ወንጌል 15፥9-14 ላይ የእርሱን ትዕዛዝ በመጠበቅ በመለኮት ዘንድ ያለውን ደስታ እንዲያገኙ ያስተምራቸዋል። “አብ እንደ ወደደኝ እኔ ደግሞ ወደድኋችሁ፤ በፍቅሬ ኑሩ። እኔ የአባቴን ትእዛዝ እንደ ጠበቅሁ በፍቅሩም እንደምኖር፥ ትእዛዜን ብትጠብቁ በፍቅሬ ትኖራላችሁ። ደስታዬም በእናንተ እንዲሆን ደስታችሁም እንዲፈጸም ይህን ነግሬአችኋለሁ። እኔ እንደ ወደድኋችሁ እርስ በርሳችሁ ትዋደዱ ዘንድ ትእዛዜ ይህች ናት። ነፍሱን ስለ ወዳጆቹ ከመስጠት ይልቅ ከዚህ የሚበልጥ ፍቅር ለማንም የለውም። እኔ ያዘዝኋችሁን ሁሉ ብታደርጉ እናንተ ወዳጆቼ ናችሁ።” ማጠቃለያ - ምዕራፍ 1፥1፦ አምላክ ሰው ሆኖ መገለጡን እናወራለን። - ምዕራፍ 1፥2፦ የተገለጠው የዘላለም ሕይወት ነው። - ምዕራፍ 1፥3፦ በእርሱ የሚያምን ከአባትና ከልጅ (ከመለኮት) እንዲሁም ከቅዱሳን ጋር ኅብረት አለው። - ምዕራፍ 1፥4፦ ኅብረትን የሚያደርግ ሁሉ ደስታው ፍጹም ነው። ➝ በክርስቶስ ኢየሱስ ማመን + የዘላለም ሕይወት + ኅብረት = ፍጹም ደስታ https://t.me/Theophilus_Terefe
1 450
10
No text...
268
11
#Quote «ነገሮች ውድ ስለሆኑ አይደለም የሚያምሩት፤ እንዴት ማስተካከል እንዳለብህ ስላወክ ነው።» ኤስ ኤ ቲያ https://t.me/Theophilus_Terefe
#Quote «ነገሮች ውድ ስለሆኑ አይደለም የሚያምሩት፤ እንዴት ማስተካከል እንዳለብህ ስላወክ ነው።» ኤስ ኤ ቲያ https://t.me/Theophilus_Terefe
331
12
#1st_John #Part_7   ሀ. የሕይወት ቃል (1ኛ ዮሐ 1፥1-4) ጥቅሱን ለማንበብ ይህን ጽሑፍ ይጫኑ! 1.3. «እጆቻችንም የዳሰሱትን» የኢየሱስ ክርስቶስን በሥጋ መምጣትና አካላዊ ትንሣኤውን የሚቃወሙ ሰዎችን ይበልጥ ለመሞገትና ለማሳመን ዮሐንስና ደቀ መዛሙርት ብቁ መሆናቸውን በዚህ አገላለጹ እናረጋግጣለን። በተለይም ዮሐንስ ከኢየሱስ ጋር የሥጋ ዝምድና ስለነበረውና (የኢየሱስ እናት ማሪያምና የዮሐንስና የያዕቆብ እናት ሰሎሜ እህትማማቾች ነበሩ።) ከሌሎች ደቀ መዛሙርት ይልቅ ደረቱ ጋር ቀርቦ ነገሮችን ጠይቆ ያረጋገጠም ስለነበረ ኢየሱስን ዳስሶ በሥጋ እንደነበረ ያውቀዋል። ይህ «የዳሰስነውን» (ψηλαφάω) የሚለው ቃል አካላዊ የሆነውን መነካካት ወይም መንካትን የሚያሳይ ቃል ነው። # እነዮሐንስ ዳስሰው ያወቁት ምንድር ነው? 1. ሰው መሆኑን (ቁሳዊ አካል እንደነበረው) “ኢየሱስም ይወደው የነበረ ከደቀ መዛሙርቱ አንዱ በኢየሱስ ደረት ላይ ተጠጋ፤”   — ዮሐንስ 13፥23 2. ሞቱን “ከዚህም በኋላ አይሁድን ስለ ፈራ በስውር የኢየሱስ ደቀ መዝሙር የነበረ የአርማትያስ ዮሴፍ የኢየሱስን ሥጋ ሊወስድ ጲላጦስን ለመነ፤ ጲላጦስም ፈቀደለት። ስለዚህም መጥቶ የኢየሱስን ሥጋ ወሰደ። የኢየሱስንም ሥጋ ወስደው እንደ አይሁድ አገናነዝ ልማድ ከሽቱ ጋር በተልባ እግር ልብስ ከፈኑት።” (ዮሐ 19፥38፤ 40) 3. ትንሣኤውን “ከዚያም በኋላ ቶማስን፦ ጣትህን ወደዚህ አምጣና እጆቼን እይ፤ እጅህንም አምጣና በጎኔ አግባው፤ ያመንህ እንጂ ያላመንህ አትሁን አለው።”   — ዮሐንስ 20፥27 # በዚህ ዘመን ያለን ምስክሮች እንዴት እንዳስሳለን? ከዚህ በፊት በሌሎችም እንዳነሳሁት ኢየሱስን ፍጹም አምላክ ፍጹም ሰው ሆኖ መገለጡን በአሁኑ ዘመን የዓይን እማኝ ሆነን ልንመሰክር አንችልም። ነገር ግን ከእርሱ ጋር ባለን መንፈሳዊ ግንኙነት ልንዳስሰው እንችላለን። ለዚህም ትክክለኛው መንገድ ቃሉን መረዳትና በቃሉ መሠረት ኅብረት ከጌታ ጋር ማድረግ ነው። https://t.me/Theophilus_Terefe
832
13
No text...
294
14
የቀጠለ... ኢየሱስ መሲሕ (ክርስቶስ) ነውን? ስለ መሲሑ የተነገሩ ትንቢቶች በተለያዩ ሰዎች ላይ ሊፈጸሙ ይችላሉ? አይችሉም! የጣት አሻራ አንድን ግለሰብ ብቻ ለይቶ እንደሚያሳውቅ ሁሉ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የተነገሩት ትንቢቶችም ፍጻሜያቸውን የሚያገኙት በአንድ መሲሕ ወይም ክርስቶስ ላይ ብቻ ነው። ያም ቢሆን መጽሐፍ ቅዱስ የሚከተለውን ማስጠንቀቂያ ይዟል፦ “ሐሰተኛ ክርስቶሶችና ሐሰተኛ ነቢያት ይነሳሉ፤ ቢቻላቸው የተመረጡትን እንኳ እስኪያስቱ ድረስ ታላላቅ ምልክቶችና አስደናቂ ነገሮች ያደርጋሉ።” ማቴዎስ 24:24 ወደፊት የሚመጣ መሲሕ ሊኖር ይችላል? በፍጹም!! መጽሐፍ ቅዱስ መሲሑ የእስራኤል ንጉሥ የነበረው የዳዊት ዘር እንደሚሆን አስቀድሞ ተናግሯል። (መዝሙር 89:3-4) ይሁንና የዳዊትን የዘር ሐረግ የያዙ ጥንታዊ የአይሁዳውያን መዝገቦች በአሁኑ ጊዜ አይገኙም፤ ምናልባትም እነዚህ መዝገቦች የጠፉት ሮማውያን በ70 ዓ.ም ኢየሩሳሌምን ድል ባደረጉበት ወቅት ሊሆን ይችላል። ከዚያ ጊዜ አንስቶ፣ ማንም ሰው የዳዊት ንጉሣዊ ቤተሰብ አባል መሆኑን በማስረጃ ማረጋገጥ አልቻለም። በኢየሱስ ዘመን ግን እነዚህ መዝገቦች ስለነበሩ ጠላቶቹ እንኳ ኢየሱስ የዳዊት ዘር ስለመሆኑ ጥያቄ አላነሱም። (ማቴዎስ 22:41-46) ስለዚህ የመጣ እንጂ የሚመጣ መሲሕ የለም!! በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ስለ መሲሑ የሚናገሩ ምን ያህል ትንቢቶች ይገኛሉ? ስለ መሲሑ የሚገልጹ ምን ያህል ትንቢቶች እንደሚገኙ በትክክል መናገር አይቻልም። ስለ መሲሑ የሚናገሩ መሆናቸው በእርግጠኝነት የሚታወቁ ትንቢቶች እንኳ የሚቆጠሩበት መንገድ የተለያየ ነው። ለምሳሌ በኢሳይያስ 53:2-7 ላይ ስለ መሲሑ የሚናገሩ በርካታ ትንቢታዊ መግለጫዎችን እናገኛለን። አንዳንዶች ሙሉውን ሐሳብ እንደ አንድ ትንቢት ይቆጥሩታል፤ ሌሎች ደግሞ እያንዳንዱ መግለጫ እንደ አንድ ትንቢት መቆጠር እንዳለበት ያስባሉ። በመጨረሻም ብሉይ ኪዳን በሙሉ በቀጥታ ቃል በቃል እንዲሁም አገልጋዮችን እንደ ምሣሌነት በመጠቀም ስለሚመጣው መሲሕ ይነግረናል። https://t.me/Theophilus_Terefe
428
15
#1st_John #Part_6   ሀ. የሕይወት ቃል (1ኛ ዮሐ 1፥1-4) ጥቅሱን ለማንበብ ይህን ጽሑፍ ይጫኑ! 1.2. «ያየነውን፥ የተመለከትነውንም» ሐዋርያው ቅዱስ ዮሐንስ ኢየሱስን ፍፁም አምላክና ፍፁም ሰው መሆኑን ሰምተን ብቻ አይደለም የምናወራው፤ አይተነዋል፣ ተመልክተነዋልም በማለት ቅድመ ቃሉን ይቀጥላል። በዚህ ክፍል የተጠቀሱት ሁለቱም ቃላት ደቀ መዛሙርቱ ከክርስቶስ ጋር የነበራቸውን ቅርበት አጉልተው የሚያሳዩ ናቸው። «ያየነውን» (ὁράω) የሚለው ገላጭ ቃል ከኢየሱስ ጋር ባሳለፉት ቆይታ በእርሱ ሲደረግ ያዩትንና ፍፁም ሰው መሆኑን በዓይነ ሥጋ መለየታቸውን የሚገልጽ ሲሆን፤ የተመለከትነው (θεάομαι) የሚለው ደግሞ የእርሱ ማንነት በአትኩሮት ቀርበው የለዩበትን የሚገልጽ ቃል ነው። ሲጠቀለል ዮሐንስ እየጻፈላቸው ያለው፦ ከመጀመሪያው የነበረው ቃል ሕይወት ሆኖ ተገልጦ በዓይነ ሥጋችን አይተን በጥልቀትና በአትኩሮት ማንነቱን አጢነን አውቀናል፤ ስለዚህ ይህንን እናወራለን ነው። # እነዮሐንስ ያዩትና የተመለከቱት ምንድርነው? ሀ. «ያየነውን» ፦ 1. በግርማው በፊታቸው ሲለወጥ አይተዋል። “በፊታቸውም ተለወጠ፥ ፊቱም እንደ ፀሐይ በራ፥ ልብሱም እንደ ብርሃን ነጭ ሆነ።” (ማቴ 17፥2) 2. ተዓምራትን ሲያደርግ አይተዋል። “እጁንም ዘርግቶ ዳሰሰውና፦ እወዳለሁ፥ ንጻ አለው፤ ወዲያውም ለምጹ ለቀቀው።” (ሉቃስ 5፥13) “ቀርቦም ቃሬዛውን ነካ፥ የተሸከሙትም ቆሙ፤ አለውም፦ አንተ ጐበዝ፥ እልሃለሁ፥ ተነሣ። የሞተውም ቀና ብሎ ተቀመጠ ሊናገርም ጀመረ፥ ለእናቱም ሰጣት።” (ሉቃስ 7፥14-15) 3. ለሰዎች በደል ስቃይ መቀበሉን አይተዋል። “ኢየሱስንም ይዘው ወሰዱት፤ መስቀሉንም ተሸክሞ በዕብራይስጥ ጎልጎታ ወደ ተባለው የራስ ቅል ስፍራ ወደሚሉት ወጣ። በዚያም ሰቀሉት፥ ከእርሱም ጋር ሌሎች ሁለት፥ አንዱን በዚህ አንዱን በዚያ ኢየሱስንም በመካከላቸው ሰቀሉ።” (ዮሐ 19፥17) 4. ከሞት ተነስቶ በዓይነ ሥጋቸው አይተዋል። “ደግሞ አርባ ቀን እየታያቸው ስለ እግዚአብሔርም መንግሥት ነገር እየነገራቸው፥ በብዙ ማስረጃ ከሕማማቱ በኋላ ሕያው ሆኖ ለእነርሱ ራሱን አሳያቸው።” (ሐዋ 1፥3) 5. ወደሰማይ ሲያርግ (ዕርገቱን) አይተዋል። “ይህንም ከተናገረ በኋላ እነርሱ እያዩት ከፍ ከፍ አለ፤ ደመናም ከዓይናቸው ሰውራ ተቀበለችው።” (ሐዋ 1፥9) ለ. «የተመለከትነውንም» ፦ 6. ኃጢአትን የሚያስወግድ መሥዋዕት (በግ) እንደሆነ ተመልክተዋል። “በነገው ዮሐንስ ኢየሱስን ወደ እርሱ ሲመጣ አይቶ እንዲህ አለ፦ እነሆ የዓለምን ኃጢአት የሚያስወግድ የእግዚአብሔር በግ። ...ኢየሱስም ሲሄድ ተመልክቶ፦ እነሆ የእግዚአብሔር በግ አለ።” (ዮሐ 1፥29፤36) 7. መሢሕ (ክርስቶስ/ አዳኝ) መሆኑን ተመልክተዋል። “እርሱ አስቀድሞ የራሱን ወንድም ስምዖንን አገኘውና፦ መሢሕን አግኝተናል አለው፤ ትርጓሜውም ክርስቶስ ማለት ነው።” (ዮሐ 1፥42) “ፊልጶስ ናትናኤልን አግኝቶ፦ ሙሴ በሕግ ነቢያትም ስለ እርሱ የጻፉትን የዮሴፍን ልጅ የናዝሬቱን ኢየሱስን አግኝተነዋል አለው።” (ዮሐ 1፥46) 8. የእግዚአብሔር ልጅ መሆኑን ተመልክተዋል። “ናትናኤልም መልሶ፦ መምህር ሆይ፥ አንተ የእግዚአብሔር ልጅ ነህ፤ አንተ የእስራኤል ንጉሥ ነህ አለው።” (ዮሐ 1፥50) 9. አምላክ መሆኑን ተመልክተዋል። “ቶማስም፦ ጌታዬ አምላኬም ብሎ መለሰለት።” (ዮሐ 20፥28) # በዚህ ዘመን ያለን ምስክሮች እንዴት እናያለን፣ እንመለከትማለን? በዚህ ዘመን ክርስቶስን በዓይነ ሥጋ እያየነውና እየተመለከትነው ማንነቱን አንረዳም። ሆኖም ግን ለአማኞች ዛሬም ማንነቱን ይገልጣል። እርሱን ማየትና መመልከት የምንችለውም ቃሉን መንፈስ ቅዱስ በገለጠልን ልክና በጸሎት ከእርሱ ጋር በማውራትና ኅብረት በማድረግ ነው። ➝ በዚህ አጋጣሚ መንግሥተ ሰማይ ሄደን ክርስቶስን፣ ጳውሎስን፣ ስልዋኖስን፣ ጴጥሮስን ወዘተ አይተን፤ ሲኦልን ጎብኝተን መጣን ከሚሉ ግለሰቦች አስፈላጊውን ጥንቃቄ በማድረግ ነገሩን እንድትመረምሩት እላለሁ። https://t.me/Theophilus_Terefe
895
16
No text...
326
17
#1st_John #Part_5   ሀ. የሕይወት ቃል (1ኛ ዮሐ 1፥1-4) ጥቅሱን ለማንበብ ይህን ጽሑፍ ይጫኑ! “ስለ ሕይወት ቃል ከመጀመሪያው የነበረውንና የሰማነውን በዓይኖቻችንም ያየነውን የተመለከትነውንም እጆቻችንም የዳሰሱትን እናወራለን”        1ኛ ዮሐንስ 1፥1 1. «እናወራለን» ዮሐንስ አንድ ሰው የዓይን ምስክር ነው ይባል ዘንድ የሚያስፈልጉትን መስፈርቶች እርሱና የክርስቶስ ቀደምት ደቀ መዛሙርት እንዳሟሉ ያረጋግጣል። ይህም መግቢያ በዘመኑ የክርስቶስን በሥጋ መምጣት (ትሥጉት/ Incarnation) ከማያምኑ ሰዎች አማኞችን ለመታደግ የሚያደርገውን ሙግት ይበልጥ ደጋፊ ነው። ባለፈው ጽሑፌ እንዳቀረብኩት ዮሐንስ የክርስቶስን ዘላለማዊ አምላክነት «በመጀመሪያው የነበረውንና» ብሎ ገልጾታል። «እና» የሚለው አያያዥ ቃል ቀጥሎ ከአምላክነቱ በተጨማሪ ሌላ አካል እንደሆነ ለማስረዳት የገባ ነው። ማለትም አምላክ የሆነው እግዚአብሔር ቁሳዊ አካል (ሥጋን) ለብሶ በሰው ታሪክ ውስጥ መገለጡን ለማስረዳት ነው። ይህን አምላክ በሰው ታሪክ መገለጡን በአፈታሪክ ሳይሆን እኛ ከእርሱ ጋር በመቆየት አውቀናል፤ ስለዚህ በሦስት የስሜት ሕዋሳት (በጆሮ፣ በዓይንና በእጅ) ያወቁትን እናወራለን በማለት ነው የሚጀምረው። # እነዮሐንስ የሚያወሩት ምንድርነው? 1.1. «የሰማነውን» ይህ አባባል በተለያየ ጊዜ መጽሐፍ ቅዱስን ለመፍታትና ለማጥናት በተጉ ሰዎች መካከል ክርክርን አስነስቶም ነበረ። የመጀመሪያው ሐሳብ «የሰማነውን» ብሎ የገለጸው ክርስቶስ ከመገለጡ በፊት ስለተነገሩ ትንቢቶችና ስለመሢሁ የተሰጠውን ተስፋ ነው የሚል ሲሆን፤ ሁለተኛው ደግሞ በምድር ሲመላለስ ያስተማራቸውን ትምህርት ነው የሚል ነው። በርግጥ አስቀድሞ ስለክርስቶስ የተሰጠውን ተስፋ ሐዋሪያቱ ሰምተዋል፤ ይህ ማለት ግን ተስፋውን ብቻ ነው «የሰማነውን» ብሎ የገለጸው ማለት አይደለም። ምክንያቱም ቀጥሎ “ከእርሱም የሰማናት ለእናንተም የምናወራላችሁ መልእክት...” (1፥5) ብሎ መግለጹ ቀድሞ በነቢያት በኩል የሰሙትን ከራሱ ከኢየሱስ ክርስቶስ እንደሰሙ ስለሚነግረን ነው። እንዲሁም ቀጥሎ ስለሚነግራቸው ነገር የዓይን ምስክር መሆናቸውን የሚያስረግጥባቸው «በዓይኖቻችንም ያየነውን የተመለከትነውንም እጆቻችንም የዳሰሱትን» (1፥1) የሚሉ አገላለጾች ተከታታይነታቸው ከእርሱ ጋር ሳሉ የሰሙት መሆኑን እንድረዳ ያደርገናል። ከእርሱ ካልሰማ ደግሞ ትዕዛዛቱንም እርሱን አውቄዋለሁ እያለ ለማስተማር ባልተነሳ ነበረ። ስለዚህ «የሰማነውን» የሚለው አገላለጽ ቀድሞ ስለመሢሑ (ስለክርስቶስ) የሰሙት ተስፋ ቢኖርም ዮሐንስ በመልዕክቱ የክርስቶስን ትሥጉት ከማጉላቱና በሥጋ ተገልጦ ስለማወቃቸው ከመመስከሩ አንፃር ስንመለከተው ከእርሱ ስለሰሙት ትምህርት ነው። # እነዮሐንስ የሰሙት ምንድርነው? ከክርስቶስ ደቀመዛሙርት በርካታ ትምህርቶችን ሰምተዋል። በዚህ መልዕክት ዮሐንስ ከጻፋቸው አንፃር ጥቂቶቹን እንመልከት፦ 1. ኢየሱስ ሕይወት (የዘላለም ሕይወት) መሆኑን ሰምተዋል። “እኔም የዘላለም ሕይወትን እሰጣቸዋለሁ...” (ዮሐ 10፥28) “ትንሣኤና ሕይወት እኔ ነኝ...” (ዮሐንስ 11፥25) 2. በአምላክነት ሥልጣን ስያዝ ሰምተዋል። “ነቅቶም ነፋሱን ገሠጸው ባሕሩንም፦ ዝም በል፥ ፀጥ በል አለው። ነፋሱም ተወ ታላቅ ፀጥታም ሆነ።” (ማር 4፥39) “ይህንም ብሎ በታላቅ ድምፅ፦ አልዓዛር ሆይ፥ ወደ ውጭ ና ብሎ ጮኸ። የሞተውም እጆቹና እግሮቹ በመግነዝ እንደ ተገነዙ ወጣ፤ ፊቱም በጨርቅ እንደ ተጠመጠመ ነበር። ኢየሱስም፦ ፍቱትና ይሂድ ተዉት አላቸው።” (ዮሐ 11፥43-44) 3. ይቅር ሲል ሰምተዋል። “ኢየሱስም፦ አባት ሆይ፥ የሚያደርጉትን አያውቁምና ይቅር በላቸው አለ።” (ሉቃስ 23፥34) 4. በፍቅር እንዲመላለሱ ስያዝ ሰምተዋል። “እርሱም መልሶ፦ ጌታ አምላክህን በፍጹም ልብህ በፍጹም ነፍስህም በፍጹም ኃይልህም በፍጹም አሳብህም ውደድ፥ ባልንጀራህንም እንደ ራስህ ውደድ አለው።” (ሉቃስ 10፥27) # በዚህ ዘመን ያለን ምስክሮች ከየት ነው የምንሰማው? በዚህ ዘመን ያለን ምስክሮች እንደ ቀደሙት ደቀ መዛሙርት ከኢየሱስ እግር ስር ቁጭ ብለን ኢየሱስን በዓይነ ሥጋችን እያየነው አሁን መማር አንችልም። ሆኖም ግን ከእርሱ ዘንድ መማርን ለሚሻ ክርስቶስ ዛሬም ራሱን ያሳያል። ይህን ትምህርት የምናገኘው በመንፈስ ቅዱስ አብርኆት ከቃሉ ዘንድ ነው። እግዚአብሔር በልጁ ለዓለም ተናግሯል፤ ይህም እውነት በሕያው ቃሉ ተጽፎ እስካሁን ይሰራል፤ ቃሉን መንፈሱ ያበራልናል። ቅዱስ ቃሉን በቅዱስ መንፈስ ስንረዳ ያን ግዜ የኢየሱስ ክርስቶስ ምስክሮች ነን። https://t.me/Theophilus_Terefe
990
18
No text...
378
19
#1st_John #Part_4   ሀ. የሕይወት ቃል (1ኛ ዮሐ 1፥1-4) ጥቅሱን ለማንበብ ይህን ጽሑፍ ይጫኑ! “ስለ ሕይወት ቃል ከመጀመሪያው የነበረውንና የሰማነውን በዓይኖቻችንም ያየነውን የተመለከትነውንም እጆቻችንም የዳሰሱትን እናወራለን”        1ኛ ዮሐንስ 1፥1 ዮሐንስ ይህንን መልእክት የሚጀመረው ለምን እንደጻፈ ለአንባቢያኑ በሚያብራራ መቅድም ወይም ቅድመ ቃል (Prologue) ነው። (1ኛ ዮሐ 1፥3) ከእግዚአብሔር ጋር ኅብረት ማድረግ የሚችሉት ኢየሱስን ያወቁት ብቻ እንደሆኑና አንባቢዎቹም ኢየሱስን በማወቅ ከእግዚአብሔር ጋር ባለው ኅብረት እንዲደሰቱ ሲል ጽፏል። ይህ ኅብረት፣ በኢየሱስ ክርስቶስ በሥጋ የመገለጥ (Incarnation) እውነታ ላይ ያረፈ ነው፤ ይህን ለተረዱት ሙሉ ደስታን ይሰጣል። «ስለ» የሚለውን ስመ ምትክ የተጠቀመውም ቀጥሎ የሚጽፍላቸውን አካል (Person) ማንነት ለማብራራት በመንደርደር ነው። በነገረ ክርስቶስ (Christology) ጥናት የሚታወቁትን ሁለት ዘርፎችን ማለትም የክርስቶስን ማንነት እና የክርስቶስን ሥራ በማጣመር የያዘ መልዕክት ቢሆንም፤ ዮሐንስ ትኩረቱን ግን ማንነቱ ላይ በማድረግ ማብራራት ይጀምራል። ይህ ቀጥዬ የማወራላችሁ ነገር ከመጀመሪያው የነበረ ነው ይላል። «ከመጀመሪያው» መቼ ነው? ይህ በመጽሐፍ ቅዱስ በተለያየ ስፍራ ተጠቅሶ የሚገኝ ቃል ሲሆን፤ በግሪክ አርኬ (ἀρχή) ተብሎ ከተጻፈው የተተረጎመ ቃል ነው። ይህ ቃል የተለያዩ ግዜያትን የሚያመለክት ሆኖ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ተጠቅሶ እናገኛለን፦ 1. የሁሉንም ነገር መጀመሪያ ሊያመለክት ይችላል። (1ኛ ዮሐ 2፥13-14፤ ዮሐንስ 1፥1) 2. የፍጥረትን መጀመሪያ ሊያመለክት ይችላል። (1ኛ ዮሐ 3፥8፤ ዘፍ 1፥1) 3. የኢየሱስን በሥጋ መገለጥ (ትሥጉት/ Incarnation) (1ኛ ዮሐ1፥2፤ ዮሐ 1፥14) እሱም የኢየሱስን ምድራዊ አገልግሎት መጀመሪያ (ሐዋ. 1፥22-24) የወንጌል መጀመሪያ (ማርቆስ 1፥1-4) ሊያመለክት ይችላል። 4. የአንባቢያን ክርስቲያኖችን ልምድ መጀመሪያ ሊያመለክት ይችላል (1ኛ ዮሐ 2፥7፣ 24፤ 3፥11 ) በዚህ መልዕክት ጅማሬ ላይ የተጠቀሰው «ከመጀመሪያው» የሚለውም ቃል የሚገልጠው የነገርን ሁሉ ጅማሬ ነው። «ከመጀመሪያው የነበረውንና...» ይህ የሕይወት ቃል (Logos) ከመጀመሪያው የነበረ ነው። ዮሐንስ ለመልዕክቱ ተቀባዮች የሚነግራቸው ቃል (Logos) ከፍጥረት በፊት የነበረውን የሕይወትን ቃል ነው። ይህ ቃል (Logos) ከመጀመሪያው ነበረ እንጂ ከፍጥረት ጋር አልተፈጠረም። ፍጥረት እንኳን የተፈጠሩት በርሱ ነው። (ዕብ 1፥2) ይህ ቃል አስቀድሞም ከአብ ዘንድ የነበረ ነው። “...ከአብ ዘንድ የነበረውንም...” (1ኛ ዮሐ 1፥2) በዮሐንስ ወንጌል መሠረት ይህ ከአብ ዘንድ የነበረው እግዚአብሔር ወልድ (ኢየሱስ ክርስቶስ) ነው። «...የነበረውንና...» ይህ ቃል «የነበረውን» እና «እና» ከሚሉ ሁለት ቃላት የተጣመረ ነው። ከላይ እንደገለጽኩት «የነበረውን» የሚለው ቃል ከነገሮች ሁሉ፣ ከፍጥረት ጅማሬም አስቀድሞ መኖሩን እና መነሻ ግዜው የማይታወቅ ዘላለማዊ አምላክ መሆኑን የሚያመለክት ሲሆን፤ «እና» የሚለው አያያዥ ቃል ቀድሞ ከተገለጸው ውጪ ያለውን ሌላ ማንነቱን ለማመልከት የገባ ነው፤ እርሱም ከመጀመሪያው የነበረ አምላክ ሥጋ መልበሱን (ሰው ሆኖ መገለጡን) ለማመልከት ነው። ይህንንም ዮሐንስ አጽንኦት ሰጥቶ መንደርደሪያ አድርጎ የጀመረው በአማኞች መካከል ሰርገው የገቡ ሐሰተኛ ትምህርቶች በመኖራቸው ነው። ያመኑትንም ክርስቶስ የመጣው በሥጋ አይደለም፤ እርሱ መንፈስ ነበረ በማለት ያስቱ ነበረ። ዮሐንስ ይህን ትምህርታቸውን የሚቃወመው ኢየሱስ ከመጀመሪያው የነበረ ፍጹም አምላክና በሥጋ የተገለጠ ፍጹም ሰው ነው በሚል ማስረጃ ነው። እግዚአብሔር ወደዓለም ሰው ሆኖ መጥቷል ለዚህም ዮሐንስ የዓይን ምስክር ነው። ለምስክርነቱም መስፈርቱ በቂ ነው። ሰምተነዋል፣ አይተነዋል፣ ተመልክተነዋል፣ ዳሰነዋል በማለት ትክክለኛ እማኝ መሆኑን ያረጋግጣል። https://t.me/Theophilus_Terefe
2 212
20
No text...
368