cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

ስውር ቁልፎች

ኢትዮጵያን መስራት የሚችሉት ኢትዮጵያውን ብቻ ናቸው። ኢትዮጵያውያን ያልሰሯት ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ አትሆንም። ኢትዮጵያን ሰርተን እናኖራታለን፤ አሊያም ረስተን እናፈርሳታለን! @Siwur_Kulfoch

Show more
Advertising posts
1 146
Subscribers
-124 hours
-127 days
-230 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

Photo unavailableShow in Telegram
ልጅ ደስታ ነው፤ ልጅ ተስፋ ነው። ቤተሰብ በብዙ ናፍቆትና ውጣ ውረድ የአምላክ ሥጦታ የሆነን ልጅ ሲያገኝ እንደገና በልጁ ውስጥ ይወለዳል። ድንገት ይህንን ደስታ የሚያሰናክል ነገር ሲገጥም ህመሙ ለወላጅ ቃላት ከሚገልጹት በላይ ነው። ያውም በከፍተኛ የጤና እንከን መፈተን ምንኛ ከባድ ነው? ሕጻን አሜን ፍቅረአብ ገና በጨቅላ እድሜዋ በልብ ህመም ምክንያት አስቸኳይ የሆነ ከሀገር ውጪ ህክምና አስፈልጓታል። ወዳጆቼ ህመሙ ጊዜ የሚሰጠው አይደለምና ከታች በምስሉ ላይ በምትመለከቱት የባንክ የሒሳብ ቁጥር አቅማችሁ የፈቀደው ሁሉ አድርጉላት! ምንተስኖት መኩሪያ
Show all...
ዛሬ ነገን ከሚሆኑ ታዳጊዎች ጋር መመካከርና እድል አግኝቶ አብሮ መሰንበት ምንኛ ደስ ይላል። ዛሬ ከሀዋሳ የዩኒዬን አካዳሚ የ9ኛ ክፍል ተማሪዎች ጋር የሕይወት ተሞክሮ፣ ስለወጣትነት፣ ስለአቻ ግፊት፣ ስለንባብ እና የቀረቡልንኝን ጥያቄዎች  የመወያያ ጊዜ ነበረኝ። በቆይታዬም በእጅጉ ደስተኛ ነኝ። መምህርትንና ተማሪዎችን ስለሁሉ ነገር ከልብ አመሰግናለሁ። ስላበረከታችሁልኝም የምስጋና ሥጦታ ክብረት ይስጥልኝ! ምንተስኖት መኩሪያ
Show all...
👍 9
Repost from Hasaawu Bare
Show all...
Mintesinot Mekuria | Hasaawu Bare S2E17 | Sidaamu Affi Hasaawa | Sidama | ድንቅ ዉይይት ከምንተስኖት መኩሪያ ጋር

👨🏾‍💻💥 #Season 2 | Gafa Lame 💥 #Episode_17 #Qixaawo_17 Last timesession(Episode 17) live record with Author #Mintesinot_Mekuriya is here! Please help us by inviting your friends to the group! Enjoy our podcast with him! #Episode_17 Sa'u yannata hasaawu bare qixaawo #Mintesinot_Mekuryahu ledo assinoomo hasaawi hinkiilo kuneeti! Jaalla'ne tenne chaanalera kooyisatenni ledonke uurre! #sidama #ethiopia #diaspora #smn #2023 #2024 #mezmur #protestantmezmur #talkshow #podcast #ዘማሪ #መዝሙር #አገልጋይ

Photo unavailableShow in Telegram
👍 9
ሁሌም ለመልካም ሥራ ደጋግ እጃችሁን ስጠይቅ ስለማትነፍጉኝ ሁላችሁንም ከልብ አመሰግናለሁ። ሌሎችንም በማስተባበር እየተወጣችሁ ስላላችሁት ተግባር ምስጋናዬ ይድረሳችሁ። አሁንም ለዳጊ የጀመርነውን የማሕበራዊ ሚዲያ እንቅስቃሴ እንበርታ!
Show all...
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ሀዋሳ ከሚገኘው የደም ባንክ በተደጋጋሚ የደም እጥረት እንደገጠማቸውና በደም እጦት ምክንያት ከፍተኛ ውጥረት ላይ እንዳሉና ወገኖቻችንም ለጉዳት እየተዳረጉ እንደሚገኙ በስልክ መረጃ ደርሶኛል። እኔም በፍቃደኝነት ደም የሚለግሱ ወዳጆቼን እያነጋገርኩኝ በጎ ምላሽ እያገኘሁ ነው። በደም እጦት ምክንያት የሚከሰትን ሞት እና የጤና ችግር ለመቅረፍ ከእኔ ጋር በፍቃደኝነት ደም በመለገስ የወገንን ድጋፍ ለሚሹ እንድረስላቸው። ከታች ባለው የእጅ ስልኬ ለመለገስ ፍቃደኛ የሆናችሁ ጓደኞቼ ደውሉልኝ! 0916851537 ምንተስኖት መኩሪያ
Show all...
👍 1
Photo unavailableShow in Telegram
ለወንድማችን ዳግማዊ አሰፋ በማሕበራዊ ድረ ገጽ ላይ ከተጀመረ የህክምና ገንዘብ ማሰባሰብ ሥራ ጎን ለጎን በትምህርት ተቋማት ላይ ከተማሪዎች የድጋፍ ገንዘብ ማሰባሰብ ጀምረናል። ዛሬ በሀዮሌ ትምህርት ፕሮጀክት በጀመርነው ሥራ ከ1ኛ እና ከ2ኛ ደረጃ ተማሪዎች ብር 4,125 ተሰብስቧል። ተማሪዎችና አጠቃላይ የትምህርቱን ማሕበረሰብ ለዳጊ ስላሳዩት ፍቅር እናመሰግናለን።
Show all...
👍 6
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
" እጆቼን ማዘዝ ችዬ እኔን ለማገዝ የሚደክሙትን ሁሉ ከድካማቸዉ ባሳርፋቸዉ  ደስ ይለኝ ነበር " - ጠንካራው የይቅርታ ሰዉ ዳግማዊ አሰፋ (ዳጊ) የህግ ባለሞያና ደራሲ ዳግማዊ አሰፋ ከዓመታት በፊት በሀዋሳ ከተማ በእሱ እና በጓደኛው እጅ ላይ ከነበረ የፍትህ ጉዳይ ጋር በተያያዘ " ጉቦ አንቀበልም !! " በማለቱ በአንድ ግለሰብ በጥይት ተመቶ መጎዳቱ ይታወሳል። በዚህ አደጋ ጠንካራ የወጣት እጆቹ አልታዘዝልህ ብለዉታል። በአከርካሪዉ ዙሪያ ያሉ ነርቮች መጎዳትም ቆሞ እንዳይሄድ እንቅፋት ሆነዉበታል። በዚህ ምክኒያት በሰው እጅ መብላቱ መልበሱ እና መንቀሳቀሱ ፈተና ቢሆንበትም ዛሬም ተስፋው ከሱ አልፎ ለሰዎች ይደርሳል። ያልተሰበረው መንፈሱ የተሰበሩትን ይጠግናል ፤ ያልወደቀው ምራሉም የወደቁትን ያነሳል። በዚህ ትጋቱ ያልተገታዉ ዳግማዊ ከህመሙ ጋር እየታገለ ስቃዩን እየተሰቃዬም ቢሆን አርፎ መቀመጥን አልወደደም ሁለት መጽሀፍት ለተደራሲያን አብቅቶ ለብዙዎች ህይዎት መቃናት ምክኒያት ሆኗል። በዚህ ዓመትም ሌላ መጽሀፍ ሊያስመርቅ እየሰራ ነው። የቀደሙ ሁለቱ መጽሀፍትም በአፋን ኦሮሞ ታትመዉ ለመዉጣት ጫፍ መድረሳቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግሯል። ከምንም በላይ ለሰዎች መትረፍ ሲችል የሰዎችን ድጋፍ ይፈልግ ዘንድ ብርቱ ክንዶቹ ዝለው ስራዎቹን መከወን ያቅታቸው ዘንድ ምክኒያት የሆነውን ሰው " ይቅር ብየሀለሁ " ማለቱ ለትንንሽ ጥፋት ይቅርታ ማድረግ ለከበዳቸዉ ሁሉ ታላቅ ትምህርት የሰጠ ሰው ነው። ጠንካራው ዳግማዊ ከሁለት ዓመት በፊት ውጭ ወጥቶ መታከም ከቻለ መዳን እንደሚችል ሀኪሞች ማብሰራቸውን ተከትሎ በርካታ ወዳጆቹ ተደስተዉ ጎ ፈንድሚ ቢያቋቁሙም ወቅቱ ከሰሜኑ ጦርነት ጋር በተያያዘ ሀገራችን ችግር ላይ የነበረችበት ወቅት  በመሆኑ እንዳስቆመው ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ጋር በነበረው ቆይታ ተናግሯል። " አሁን ላይ  ' ጎፈንድሚውን እንጀምር  ዘንድ ፈቃድህን ብቻ ስጠን 'ላሉኝ ጓደኞቼ ፈቃዴን ሰጥቻለሁ "  ብሏል። ድኖ ለብዙዎች መትረፍ ሲችል ' ሀገሬ ችግር ላይ ናት " ብሎ የዘገየዉ ዳግማዊ ምንም እንኳን ብዙ ችግሮቹን " ወዳጆቼን አላስጨንቅም " ብሎ ቢደብቅም በቶሎ መታከም እንዳለበት ግን አሁን ላይ ብዙ ምልክቶችን አሳይቷል። ይህ ተከትሎም ሁሉም ደጋግ ኢትዮጵያውያን እገዛ እንዲያደርግለት ወዳጆቹ እየተረባረቡ ይገኛሉ። ዳግማዊ ፥ " ' 2 ሺህ የፌስቡክ ጓደኞቻችን ሁለት ሁለት መቶ ሰው ይዘዉ የአንድ ማኪያቶ የሚሆን 57 ብር በማዉጣት ያሳክሙሀል ' ብሎ ወዳጄ መምህር ወሌ ሀሳቡን ጀምሮታል " ብሏል። " ዳግማዊ ገንዘቡ ተሰብስቦልህ ታክመህ ስትድን በእጆችህ ቀድመህ ልትሰራ የምታስበዉ ምንድን ነው ? " በማለት የቲክቫህ ሀዋሳ ቤተሰብ አባል ጥያቄ አቅርቧል። ከረዥም ዝምታ በኋላ ፦ " አይገርምህም አስቤዉ አላዉቅም ... ግን እጆቼን ማዘዝ ችዬ እኔን ለማገዝ የሚደክሙትን ሁሉ ከድካማቸዉ ባሳርፋቸዉ  ደስ ይለኝ ነበር። " ዳግማዊ አሰፋን ማገዝ የምትፈልጉ በሀገር ውስጥ ሆነ በውጭ ያላችሁ ደጋግ ኢትዮጵያዉያን ፦ በጎፈንድሚ 👉 https://gofund.me/d93d0840 በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 👉1000310977938 በዳሽን ባንክ 👉 5016527877077 በአቢሲንያ ባንክ 👉 39796821 በኩል ድጋፍ ማድረግ ትችላላችሁ። ስልክ እንፈልጋለን ለምትሉም ፦ 0909888857 ላይ መደወል ትችላላችሁ። #TikvahEthiopiaFamilyHawassa @tikvahethiopia
Show all...
ትናንትና በአለታ ጩኮ ከተማ የ"ዲኪሲሴሞኤ" የመዝሙር አልበም ምረቃ ምክንያት በማድረግ ከከተማ አስተዳደሩ ጋር በመቀናጀት በተዘጋጀ የችግኝ ተከላ፣ የከተማ ጽዳት ስራና የሩጫ መሰናዶ የከተማ አስተዳደሩ ሰራተኞች፣ በርካታ ወጣቶችና የተለያዩ የማሕበረሰቡ አባላት የተሳተፉበት እና በእጅጉ የሚያስደስት ነበር። እኔም የዚሁ ሁነት ተሳታፊ በመሆኔ ደስ ብሎኛል። ዛሬ በብዙ ናፍቀን የነበርነው የወንድሜ መዳን ታየ የመዝሙር አልበም ምረቃ ይካሄዳል። መዝሙሮቹን ቀደም ብሎ የመስማት እድል አግቼ ሰምቼአቸዋለሁ። በአጭሩ የእግዚአብሔር ቃል እርሱም ኢየሱስ ክርስቶስ ተዘምሯል። ዛሬ በአለታ ጩኮ የወረዳው አስተዳደር  አዳራሽ ላይ ከቀኑ 07:00 ጀምሮ በመገኘት እንድንመርቅለት ሁላችንም ተጋብዘናል። ምንተስኖት መኩሪያ ግንቦት 04/2016 ዓ.ም
Show all...
👍 1