en
Feedback
የሀዋሳ ታቦር ሰባተኛ ቀን አድቬንቲስት አለም አቀፍ ቤተክርስቲያን (Hawassa Tabour 7th day Adventist INternational Church

የሀዋሳ ታቦር ሰባተኛ ቀን አድቬንቲስት አለም አቀፍ ቤተክርስቲያን (Hawassa Tabour 7th day Adventist INternational Church

Open in Telegram

እግዚአብሄርን ለመገናኘት ተዘጋጅ

Show more
1 071
Subscribers
+224 hours
+167 days
+3930 days
Posts Archive
እግዚያብሔር ዝም ስል
፨ወገኖቼ ሕይወት የተሰመረ መስመር አይደለም፣በሕይወት የተለያዩ ወቅቶች አሉ። ለዚህም ሰለሞን በመጽሐፉ ሲናገር መክብብ 3:-1-8 ለሁሉ ዘመን አለው፥ ከሰማይ በታችም ለሆነ ነገር ሁሉ ጊዜ አለው፤ ለመወለድ ጊዜ አለው፥ ለመሞትም ጊዜ አለው፤ለመትከል ጊዜ አለው፥ የተተከለውንም ለመንቀል ጊዜ አለው፤ ለመግደል ጊዜ አለው፥ ለመፈወስም ጊዜ አለው፤ ለማፍረስ ጊዜ አለው፥ለመሥራትም ጊዜ አለው፤ ለማልቀስ ጊዜ አለው፥ ለመሳቅም ጊዜ አለው፤ ዋይ ለማለት ጊዜ አለው፥ ለመዝፈንም ጊዜ አለው፤ ድንጋይን ለመጣል ጊዜ አለው፥ ድንጋይንም ለመሰብሰብ ጊዜ አለው፤ ለመተቃቀፍ ጊዜ አለው፥ ከመተቃቀፍም ለመራቅ ጊዜ አለው፤ ለመፈለግ ጊዜ አለው፥ ለማጥፋትም ጊዜ አለው፤ ለመጠበቅ ጊዜአለው፥ለመጣልም ጊዜ አለው፤ ለመቅደድ ጊዜ አለው፥ ለመስፋትም ጊዜ አለው፤ ዝም ለማለት ጊዜ አለው፥ ለመናገርም ጊዜ አለው፤ለመውደድ ጊዜ አለው፥ ለመጥላትም ጊዜ አለው፤ ለጦርነት ጊዜ አለው፥ ለሰላምም ጊዜ አለው። ፨እኛ ሰዎች ለእነዚህ ነገሮች ሁሉ እንደሁኔታው ከጊዜው ጋር ነገሮቻችንን እናስማማለን፤ እንደዛው እኛ ክርስቲያኖች አስተሳሰባችንን ከእግዚያብሔር ጊዜ ጋር ማስማማት አለብን። እንዳለመታደል ሆኖ ሁላችን እግዚ/ር ስሰራ እኛ እንቀመጣለን እግዚ/ር ስቀመጥ(ዝም ስል) እኛ እንነሳለን። ፨ ለማይቀረው ወቅት እራሳችንን ማዘጋጀት አለብን(በእግዚ/ር ጊዜ) እግዚያብሔር ዝም ስል ፨ቀኑ አጭር ይሆንብናል፣ምሽቱ ደግሞ ረዥም፣ብቸኝነት ይሰማናል፣በልተን ይርበናል፣ጠጥተን ይጠማናል፣ተስፋ እንቆርጣለን፣መውጫ መግቢያ ይጠፋናል። ፨ዝም ያለን ሰው ሳይሆን የሕይወታችን ምንጭ የማንነታችን መሰረት የሆነ አምላክ ሲሆን ይጨንቃል ያንገበግባል ግራ ያጋባል በዚህም ምክንያት በነገሮቻችን ሁሉ ላይ ተስፋ እንቆርጣለን ሁሉ ነገር ያስጠላናል አልፎም በእግዚያብሔር ላይ እናማራለን፣በእግዚ/ር ላይ ተስፋ እንቆርጣለን፣የተወለድንበትን ቀን እንረግማለን። ፨ የሚገርመው ከዚህ በፊት መገኘቱ እርዳታው ቅርብ እንዳልነበር እስክንረሳ ድረስ፤ስንት ጊዜ የጥያቄዎቻችንን መልስ እንዳላገኘን እስክንረሳ ድረስ በዝምታው ተስፋ እንቆርጣለን። ፨ሁሉን ላንተ ትተን፣ካንተ ጋር ተጣብቀን፣አንተን እያገለገልን፣ዘወትር እየተጋን፣የእንጀራ ልጅ እስክንመስል ለምን ዝም አልክ? የታለህ? እንቅልፍ እስክናጣ የእግ/ር እጅ ከማዳን አላጠረችም ብለን አንተ ግን ለምን ዝም አልክ?? ፨ ወገኖቼ እዮብ እንዲህ አለ በተስፋ መቁረጥ ሆኖ ኢዮብ 23፦8-9 እነሆ፥ ወደ ፊት እሄዳለሁ፥ እርሱም የለም፤ ወደ ኋላም እሄዳለሁ፥ እኔም አላስተውለውም፤ ወደሚሠራበት ወደ ግራ ብሄድ አልመለከተውም፤ በቀኜም ይሰወራል፥ አላየውምም። ፨ ነቢዩ ዕንባቆምም በዙርያው ያለውን ነገር ባየ ጊዜ ግራ በመጋባት እና ተስፋ በመቁረጥ ውስጥ ሆኖ እግ/ር የታል አለ ዕንባቆም 1:-2-4 አቤቱ፥ እኔ ስጮኽ የማትሰማው እስከ መቼ ነው? ስለ ግፍ ወደ አንተ እጮኻለሁ፥ አንተም አታድንም። ፤ በደልንስ ስለ ምን አሳየኸኝ? ጠማምነትንስ ስለ ምን ትመለከታለህ? ጥፋትና ግፍ በፊቴ ነው፤ ጠብና ክርክር ይነሣሉ፤ ስለዚህ ሕግ ላልቶአል፥ ፍርድም ድል ነሥቶ አይወጣም፤ ኃጢአተኛ ጻድቅን ይከብባልና፤ ስለዚህ ፍርድ ጠማማ ሆኖ ይወጣል። ፨ ነገር ግን እዮብም ዕንባቆምም የእግዚያብሔርን ዝምታ ሲረዱ እንዲህ አሉ ኢዮብ 23፦10 የምሄድበትን መንገድ ያውቃል፤ከፈተነኝም በኋላ እንደ ወርቅ እወጣለሁ። ዕን 2:-20 " እግዚአብሔር ግን በተቀደሰ መቅደሱ አለ፤ ምድርም ሁሉ በፊቱ ዝም ትበል። ፨ እግዚያብሔር ዝም ስል የመጣል የመረሳት ጊዜ ሳይሆን የመሰራት ጊዜ ነው ፨ ዝምታው የዝግጅት ጊዜ ነው ፨ ዝምታው የመማረር ጊዜ ሳይሆን ለእግ/ር ሀሳብ የመማረክ ጊዜ ነው። ፨ወገኖቼ እግዚያብሔር ግን በተቀደሰው መቅደሱ አለ ምንም እንኳ የተመቻቼ ሁኔታ ውስጥ ባንገኝም፣ ነገሮች ባይመቹንም፣ የምናየው የምንሰማው ተስፋ የሚያስቆርጥ ቢሆንም፣ ወዳጅ ዘመድ ጓደኛ ቢሸሸንም፣ የምንይዘው የምንጨብጠው ቢጠፋ ፣ዝምታው ስዳስሰን ባይሰማንም እግ/ር ግን በተቀደሰው መቅደሱ አለ ያየናል፣ይራራልናል፣ይሰማናል። ስለዚህ ልክ እንደ ዕንባቆም የእግዚያብሔር ዝምታው ሲገባን ይህን ልናውጅ ይገባል ዕንባቆም 3፦17-19 ምንም እንኳ በለስም ባታፈራ፥በወይንም ሐረግ ፍሬ ባይገኝ፥የወይራ ሥራ ቢጐድል፥ እርሾችም መብልን ባይሰጡ፥በጎች ከበረቱ ቢጠፉ፥ላሞችም በጋጡ ውስጥ ባይገኙ፥እኔ ግን በእግዚአብሔር ደስ ይለኛል፤በመድኃኒቴ አምላክ ሐሤት አደርጋለሁ፤ ጌታ እግዚአብሔር ኃይሌ ነው፤እግሮቼን እንደ ዋላ እግሮች ያደርጋል፤በከፍታዎችም ላይ ያስሄደኛል። አባቴ ሆይ ዝምታህን እንድንረዳ፣ ሁለም በተቀደሰ መቅደስህ እንዳለክ እንዲሰማን፣እንደ ዕንባቆም በመጠበቂያዬ ላይ እቆማለሁ፥ በአምባ ላይም እወጣለሁ፤ የሚናገረኝንም፥ ስለ ክርክሬም የምመልሰውን አውቅ ዘንድ እመለከታለሁ። "(ዕንባ 2:-1) እንድንል እርዳን አሜን።

Dear My beloved SDA Church fellows, As we celebrate the arrival of the 2018 Ethiopian New Year, I want to share a heartfelt wish for each of you. May this New Year bring you success and fruit in all dimensions of life. Reflecting on the words of (Isaiah 43:19) "See, I am doing a new thing! Now it springs up; do you not perceive it? I am making a way in the wilderness and streams in the wasteland." This verse reminds us that God is always at work, bringing renewal and hope into our lives. May you embrace the new beginnings this year offers, and may God bless you with love, joy, and prosperity. Wishing you a blessed and fulfilling New Year!

ልዩ ኘሮግራም በያህዌህ - ንሲ መዘመራን ከፊታችን አርብ ጀምሮ ቅዳሜ ሙሉ ቀን በአይነቱ ለየት ያለ ኘሮግራም ስላለ ሁላችሁም ተጋብዛችኋል። ቀኑ - ነሐሴ 23-24/2017 ዓ.ም
ልዩ ኘሮግራም በያህዌህ - ንሲ መዘመራን
ከፊታችን አርብ  ጀምሮ ቅዳሜ ሙሉ ቀን በአይነቱ ለየት ያለ ኘሮግራም ስላለ ሁላችሁም ተጋብዛችኋል።    ቀኑ -  ነሐሴ 23-24/2017 ዓ.ም

ልዩ ኘሮግራም በያህዌህ - ንሲ መዘመራን
ከፊታችን አርብ ጀምሮ ቅዳሜ ሙሉ ቀን በአይነቱ ለየት ያለ ኘሮግራም ስላለ ሁላችሁም ተጋብዛችኋል። ቀኑ - ነሐሴ 23-24/2017 ዓ.ም

ከውድቀት መነሳት
የዕለቱ ጥቅስ: “እግዚአብሔርም ኢያሱን:- አትፍራ፥ አትደንግጥ ሰልፈኞችን ሁሉ ከአንተ ጋር ውሰድ፡ ተነሥተህም ወደ ጋይ ውጣ እይ፣ የጋይን ንጉሥ ሕዝቡንም ከተማውንም ምድሩንም በእጅህ ሰጥቼሃለሁ። » ኢያሱ 8:1 ኢያሱ ምእራፍ ስምንት ከሽንፈት በኋላ ስለተገኘ ድል ይነግረናል። እስራኤላውያን እንዴት ከወደቁበት ተነስተው እንደገና ጉዟቸውን መቀጠል እንደቻሉ ከዚህ ምእራፍ እንማራለን። በተለይም ስለ እግዚአብሔር ማንነት  የሚከተሉትን ሦስት ቁልፍ እውነታዎች ልብ እንበል። 1. እግዚአብሔር በሽንፈት ውስጥ ወድቀን ሳለ የሚያጽናናን አምላክ ነው፡፡ ይህንን ምዕራፍ ማንበብ ስንጀምር የእግዚአብሔር የመጀመሪያ ቃል ለኢያሱ “አትፍራ፥ አትደንግጥ" የሚል ሆኖ እናገኘዋለን፡፡ በእርግጥም ኢያሱ ከደረሰባቸው ሽንፈት የተነሳ ግራ በመጋባት ውስጥ በወደቀበት ጊዜ እነዚህን ነፍስ የሚዘሩ የማጽናኛ ቃላት መስማቱ ምን ያህል አጽናንቶት እንደነበረ መገመት አይከብድም፡፡ 2. እግዚአብሔር ከወደቅንበትም የሚያነሳን የእንደገና አምላከ ነው። እግዚኣብሔር በውድቀታችን ደርሶ “አይዞአችሁ” የሚል ብቻ ሳይሆን፣ እንደገና የሚያነሳንና ድልንም የሚያቀዳጀን አምላከ ነው፡፡ እግዚአብሔር ኢያሱን ጥበብ በተሞላ የጦር ስልት አሰለጠነውና በውድቀታቸው ማግስት እጅግ አንጸባራቂ የሆነን ድል ለማስመዝገብ ቻሉ። በእርግጥም እግዚአብሔር የእንደገና አምላከ ነው፡፡ ምህረቱ ማለዳ ማለዳ አዲስ ነው፡፡ ከወደቅንበት ያነሳናል፡፡ ድልን ዳግም ያጎናጽፈናል፡፡ 3. እግዚአብሔር ከውድቀት ልምምዳችን ያልተጠበቀን በረከት ያወጣል። ከዚህ ቀደም ባደረጉት ውጊያ እስካሁን ለራሳቸው የሚሆንን ነገር ከጦር ምርኮአቸው አልወሰዱም ነበር፡፡ አሁን ግን በውድቀታቸው ማግስት እግዚአብሔር ከማጽናናት ባለፈ በሰጣቸው ድል የሚዘርፉትን በረከት ጭምርም ሰጥቶአቸው ነበር። እንደገና ድል ማድረጋቸው ብቻ እንኳን ትልቅ ነገር ሆኖ ሳለ፣ እግዚአብሔር ግን በተጨማሪ የሚበዘብዙትን ምርኮ ሰጣቸው፡፡ እግዚአብሔር ከውድቀታቸን ሲያነሳንና እንደገና ድልን ሲያለማምደን ከጸጋው ባለጠግነት የተነሳ ከውድቀት ልምምዳችን ውስጥ ያልተጠበቀና የላቀ በረከትን ሊሰጠን ይችላል። ጸሎት ከወደቅሁበት የምታነሳኝና እንደገና በድል ጎዳና እግሮቼን የምታቆም የተወደድህ የሰማይ አባት፣ ወድቄ ሳለ የምትገስጸኝ ብቻ ሳይሆን የምታጽናናኝ፣ የምታነሳኝና የምትባርከኝ አባት ስለሆንህ እመሰግንሃለሁ፡፡ በልጅህ በኢየሱስ ክርስቶስ መስዋዕትነት በዘረረኝ ነገር ሁሉ ላይ ድል ስለምታጫማኝ አከብርሃለሁ፡፡ እኔም በነገር ሁሉ የአንተን አመራር እንድፈልግ አመራርህንም በጥንቃቄ እንድከተል፣ ለዚህም በቃልህ ዘወትር እንድትናገረኝ እጸልያለሁ፡፡ አሜን! ፓስተር መልዓክ አለማየሁ እንደፃፈው

መርዶ ሰላም ይብዛላችሁ የታቦር ቤ/ያን የቤ/ያን አባል የሆኑት አቶ ዘውዴ ለማ እናቱን አስቀብሮ ነገ ረቡዕ ነሃሴ 15/2017 ዓ.ም ይመለሳል ስለሆነም ከቀኑ 8፡00 ጀምሮ የማፅናኛ ፕሮግራም ስለምኖር የቤ/ያን አባላት በሙሉ እንድትገኙ እናስታውቃለን። አድራሻ፡ ከዳኢቴ ወደ ዲያስፓራ በሚወስደው መንገድ ላይ

ተሸሽጎ ነበረና ተረፈ
መሳ 9:-5 " ወደ አባቱም ቤት ወደ ዖፍራ ሄደ፤ ሰባ የሆኑትን የይሩበኣልን ልጆች ወንድሞቹን በአንድ ድንጋይ ላይ አረዳቸው፤ ትንሹ የይሩበኣል ልጅ ኢዮአታም ግን ተሸሽጎ ነበርና ተረፈ።" © ወገኖቼ ይህ ክፉ ዘመን ተሸሽገን የምናልፈው ዘመን ነው፤አለም የዘራችብን(ሰይጣን የዘራብን) መርዝ እንክርዳድ ብዙ ነው *ብሔር ጎሳና ዘር ሳንቆጥር ይሄን ዘመን ተሸሽገን እንለፍ * ከአፋችን ክፉ ሳይወጣ ይሄን ዘመን ተሸሽገን እንለፍ * ቅምና ተንኮል ቅንዓትና ቁጣ ትተን ይሄን ዘመን ተሸሽገን እንለፍ * የወንድሞች ጠላት ሳንሆን ይሄን ዘመን ተሸሽገን እንለፍ እስኪ ይህን የመጽሐፍ ቅዱስ ሀሳብ ከማየታችን በፊት እስኪ የመሳፍንትን ዘመን ጠቅለል ያለ ታርክ እንይ ፨ መሳፍንት በንግስና ሳይሆን በጦርነትና በኋይል ሕዝቡን የሚመራበት ዘመን ነው ፨ መሳፍንት ዘመን አብዛኛው ወንጀል ይበዛዋል፣መጠቃት ይበዛዋል ፨ መሳፍንቶቹ ለሕዝቡ ክፉ ናቸው፣ጭካነያቸው በጣም ከባድ ነው ፨ መሳፍንቶች የሕዝቡ የብዙ ችግር መነሻ(መንስኤ) ናቸው ፨ የረሀቡ መነሻ ነበሩ (ሩት 1:1) ፨ የኑኋሚንና ባሏ እና ልጆቿ ስደት ምክንያት ነበሩ ፨ መሳፍንቶች እግዚያብሔርን ያስረሳሉ © መሳፍንት ዘመን ከባድ ዘመን ቢሆንም እግ/ር በየመሀሉ ጣልቃ እየገባ የሚያስነሳቸው ሰዎች ሕዝቡን በፍቅር ያስተዳድሩ ነበር፣ በዚያ ዘመን ከተነሱት ውስጥ ጌድዮን የሚባል ሰው ነበር እግ/ርን የሚፈራ ለእስራኤላዊያን የሚያዝን የሚቆረቆር © እስራኤላዊያን በክፉ ስራቸው እግ/ርን ባለመታዘዝ ለ 7 ዓመት በምድያዊያን ተይዘው በስራቸው እግ/ር አሳልፎ ሲሰጣቸው ተደብቆ ከሚኖሩ ሰዎች መካከል አንዱ ነበር ጌድዮን፣ ታዲያ በዚያ ዘመነ መሳፍንት መከራ የበዛባቸው እስራኤላዊያን በምድያዊያን * ገና ከብቶቻቸውን ሲያሰማሩ መተው ይዘርፏቸዋል * በማሳ ላይ የዘሩትን እህል ይዘርፏቸዋል * በማሳ የዘሩትን ያልደረሰ ዘር ያቃጥሉባቸዋል * መጥተው አደጋ ይጥሉባቸዋል በዚህ ምክንያት ከእግ/ር ስለራቁ እየደረሰባቸው ባሉ ከባድ ፈተናዎች ቀስማቸው ተሰባብሮ ነበር። አሁን በዚህ ዘመን ያለን ክርስቲያኖች ከእግ/ር በብዙ ነገር የራቅን አሁን በሕይወታችን እየሆነ ባለው ነገር ቅስማችን የተሰባበረ ሰዎች ነን፣ የሚሆነው የሚንሰማው የሚናየው ነገር በጣም የከፋ ነው በዚያ ላይ በጣም ከባድ የሚያደርግብን እግ/ርን ከኛ ያራቅን መሆኑ ነው።እኛ ክርስቲያኖች ከእግ/ር ስለራቅን ከአምላክ ይልቅ ለክብራችን ለብሔራችን ለሀብታችን ለማንነታችን ቅድሚያ የምንሰጥ ነን፣ የሚያሳዝነው ግን የተመካናቸው ከእግ/ር ያስበለጥናቸው ነገሮች አብረውን አይቆሙም፣ልክ መኪና የያዘ ሹፌር ወደ ገደል መኪና ልገባ ቢቃረብ ብሔሬ ነው ብሎ አብሮ አይገባም ዘሎ ይወርዳል ወደ ታርኩ ስመለስ በዚያ አስቸጋሪ ጊዜ እስራኤላዊያን ቀስማቸው በተሰበረ ጊዜ ጌድዮን ነገሰ፣ ካሉበት ስቃይ አወጣቸው ለ40 ዓመታት ገዛቸው ሕዝቡም እግ/ር የሚፈራ ሆነ 40 ዓመታት መልካም ጊዜ ነበራቸው፣ ከዚያ ጌድዮን ሞተ ነገር ግን ሕዝቡ በድጋሚ እግ/ርን ረሳ ጣኦት ማምለክ ጀመረ። መሳ 9:- 1 ጀምሮ ስታነቡ ሕዝቡ ከጌድዮን 70 ልጆች መካከል ጨካኝ የሆነውን አቤሜሌክ የሚባል ሰዉ ሾመ፣ ሁሉንም ወንድሞቹን ገደለ(69 ወንድሞቹን ገደለ) ነገር ግን ትንሹ የጌድዮን ልጅ ኢዮአታም ግን ተሸሽጎ ነበርና ተረፈ(መሳ 9:-5) ፨ ወገኖቼ ክፉ ጊዜን ለማለፍ መሸሸግ ያስፈልገናል የዓለም እሳቷ ሰይፏ ብዙ ነው፣ ከቅመኝነት ሰይፊ ከዘረኝነት ሰይፊ ከፍርደ ገምደልነት ሰይፊ ከረሀብ ሰይፊ ከበሽታ ሰይፊ ከክፋት ሰይፊ ከእግ/ር ጋር መውጣት ይሁንልን አቤሜሌክ እንደነገሰ የሰኬም ሰዎች ለትንሹ ኢዮአታም ነገሩት፣እርሱም እንዲህ አላቸው (መጽሐፈ መሳፍንት ምዕራፍ 9) ---------- 8፤ አንድ ጊዜ ዛፎች በላያቸው ንጉሥ ሊያነግሡ ጌዱ፤ ወይራውንም። በእኛ ላይ ንገሥ አሉት። 9፤ ወይራው ግን። እግዚአብሔርና ሰዎች በእኔ የሚከበሩበትን ቅባቴን ትቼ በዛፎች ላይ እንድሰፍፍ ልሂድ? አላቸው። 10፤ ዛፎችም በለሱን። መጥተህ በላያችን ንገሥ አሉት። 11፤ በለሱ ግን። ጣፋጭነቴንና መልካሙን ፍሬዬን ትቼ በዛፎች ላይ እንድሰፍፍ ልሂድ? አላቸው። 12፤ ዛፎችም ውይኑን። መጥተህ በላያችን ንገሥ አሉት። 13፤ ወይኑም። እግዚአብሔርንና ሰውን ደስ የሚያሰኘውን የወይን ጠጄን ትቼ በዛፎች ላይ እንድሰፍፍ ልሂድ? አላቸው። 14፤ ዛፎችም ሁሉ እሾህን። መጥተህ በላያችን ንገሥ አሉት። 15፤ እሾሁም ዛፎችን። በእውነት እኔን በእናንተ ላይ ታነግሡኝ እንደ ሆነ ኑ ከጥላዬ በታች ተጠጉ። እንዲሁም ባይሆን እሳት ከእሾህ ይውጣ፥ የሊባኖስንም ዝግባ ያቃጥል አላቸው። 16፤ አሁን እንግዲህ አቤሜሌክን በማንገሣችሁ እውነትንና ቅንነትን አድርጋችሁ እንደ ሆነ፥ ለይሩበኣልም ለቤቱም በጎ አድርጋችሁ እንደ ሆነ፥ እንዳደረገውም መጠን ለእርሱ የተገባውን አድርጋችሁ እንደ ሆነ፥ 17፤ አባቴ ስለ እናንተ ተጋድሎ ነበርና፥ ከምድያምም እጅ ሊያድናችሁ ነፍሱን ለሞት አሳልፎ ሰጥቶ ነበርና፥ 18፤ እናንተም ዛሬ በአባቴ ቤት ተነሥታችኋልና፥ ሰባ የሆኑትን ልጆቹንም በአንድ ድንጋይ ላይ አርዳችኋልና፥ ወንድማችሁም ስለ ሆነ የባሪያይቱን ልጅ አቤሜሌክን በሴኬም ሰዎች ላይ አንግሣችኋልና፥ 19፤ እንግዲህ ለይሩበኣልና ለቤቱ እውነትንና ቅንነትን ዛሬ አድርጋችሁ እንደ ሆነ፥ በአቤሜሌክ ደስ ይበላችሁ፥ እርሱ ደግሞ በእናንተ ደስ ይበለው፤ 20፤ እንዲህ ባይሆን ግን ከአቤሜሌክ እሳት ይውጣ፥ የሴኬምንም ሰዎች ቤትሚሎንም ይብላ፤ ከሴኬምም ሰዎች ከቤትሚሎም እሳት ይውጣ፥ አቤሜሌክንም ይብላ። ወገኖቼ እንደኛ እግ/ርን የከበደው ነገር አለ? ችሎን እንጂ ወየሁልኝ ልንል ይገባል እንደ ኢዮአታም ከክፊ ተሸሽገው ነበረና ተረፉ ልንባል ያስፈልጋል " የፊታቸውም እፍረት ይመሰክርባቸዋል፤ እንደ ሰዶምም ኃጢአታቸውን ያወራሉ፥ አይሠውሩአትም። በራሳቸው ላይ ክፉ ነገርን ሠርተዋልና ለነፍሳቸው ወዮ! " ኢሳይያስ 3:9 " ምክራቸውን ጥልቅ አድርገው ከእግዚአብሔር ለሚሰውሩ፥ ሥራቸውንም በጨለማ ውስጥ አድርገው። ማን ያየናል? ወይስ ማን ያውቀናል? ለሚሉ ወዮላቸው! " ኢሳይያስ 29:15 እንደ ኢዮአታም ወደ እግ/ር ጉያ ገብተን እንሸሸግ እናምልጥ እንትረፍ

እናንተስ እነማን ናችሁ?
" ክፉው መንፈስ ግን መልሶ። ኢየሱስንስ አውቀዋለሁ ጳውሎስንም አውቀዋለሁ፤ እናንተስ እነማን ናችሁ? አላቸው።" "ሐዋ 19:15" የካህናት አለቃ ለሆነ አስቄዋ ለሚሉት ሰባት ልጆች ነበሩት(ሐዋ 19:-14) ጳዉሎስ በሚሰብከው በኢየሱስ ስም እናምላችኋለን እያሉ ክፉዎች መናፍስት ባሉባቸው ላይ የጌታን የኢየሱስን ስም ይጠሩባቸው ዘንድ ሞከሩ(ሐዋ 19:-13) ነገር ግን ክፉ መንፈስ ያለበት ሰው ዘለለባቸው ቆስለውም ከዚህ ቤት ዕራቁታቸውን እስኪሸሹ ድረስ በረታባቸው አሸነፋቸውም። ዛሬ እኛ ሁላችን እነዚህን የአስቄዋ ልጆችን የምንወክል አስመሳይ ሀይሉን ያጣን ክርስቲያኖች ነን፣ በሚያሳዝን ሁኔታ ሰይጣን እንኳ የሚንቀን ክርስቲያኖች ነን። ሰይጣን ፨ ማንነታችንን ያውቀዋል ፨ በኢየሱስ ስም ምንም ማድረግ የማንችል መሆናችንን ያውቀዋል ፨ በማስመሰል ሕይወት ውስጥ እንዳለን ያውቃል ፨ ሀሳባችን ምድራዊ መሆኑን ያውቃል ለዚህም ነው ኢየሱስን ከልብ ማወቅ ከልብ መገናኘት በእውነት መኖር ያለብን ዛሬ እኮ ፀሎታችን፣ስብከታችን፣መዝሙራችን፣ክርስትናችን፣አረማመዳችን፣ተግባራችን ብቻ ሁሉ ነገራችን እውነተኛ አይደለም ልክ እንደ አስቄዋ ልጆች ሰይጣን እንኳን ሳይቀር ክርስቶስንም ጳውሎስንም አውቀዋለው እናንተ እነማንናችሁ የሚለን በእውነት ከእንደዚህ ዓይነት ውርደት ይጠብቀን። ዛሬ እኛ ክርስቲያኖች በእውነት የጌታን ኋይል የምናውቅ፣ይቅር የምንል፣በፍቅር የምንመላለስ፣የምንተሳሰብ፣በጌታ አንድ የሆንን፣ከክፋት የራቅን፣በቅን የምንፈርድ፣የምናዝን መሆን አለብን። እንደዚህ ካልሆንን በሰይጣን የምንታወቅ እንሆናለን። ንጉስ ኢዮሳፍጥን በወቅቱ የነበሩት ሦስቱ ሀያላን መንግስታት ሞዓባዊያን፣አሞናዊያን እና ምድያማዊያን ግንባር ፈጥረው ሊወጉት በመጡ ጊዜ ፈራ ነገር ግን ከእግ/ር መልዕክተኛ የተሰጠው ትዕዛዝ በመስማት በአምላክ ላይ በመደገፍ መዘመራንን ከፊቱ አስቀድሞ ወጣ። ይህን ባደረገ ጊዜ ያሸበረቀ ድል አገኘ፣ በእርግጥ መዝሙርን ሳይሆን እውነተኛ መዝሙርን ሲያዘሙ እግ/ር ድብቅ ጦርን አዘጋጅቶ ረታቸው። እውነተኛ ክርስቲያን ስንሆን ሰይጣን እንኳ የሚታዘዝልን እንሆናለን። ማር 1:- 21-24 21፤ ወደ ቅፍርናሆምም ገቡ፤ ወዲያውም በሰንበት ወደ ምኵራብ ገብቶ አስተማረ። 22፤ እንደ ባለ ሥልጣን ያስተምራቸው ነበር እንጂ እንደ ጻፎች አይደለምና በትምህርቱ ተገረሙ። 23፤ በዚያን ጊዜም በምኩራባቸው ርኵስ መንፈስ ያለው ሰው ነበረ፤ 24፤ እርሱም። የናዝሬቱ ኢየሱስ ሆይ፥ ከአንተ ጋር ምን አለን? ልታጠፋን መጣህን? ማን እንደ ሆንህ አውቄአለሁ፥ የእግዚአብሔር ቅዱሱ ብሎ ጮኸ። ዛሬስ ሰይጣን እኛን ማን ብሎ ነው የሚጠራን ፨ ልክ እንደ ጳውሎስና ኢየሱስ ''የእግ/ር ቅዱስ'' ይለናል ወይስ ፨ ልክ እንደ አስቄዋ ልጆች ስለዚህ ወገኞቼ በእውነት ክርስቲያን መሆን ይሁንልን ያዕ 4:- 7-10 7፤ እንግዲህ ለእግዚአብሔር ተገዙ፤ ዲያብሎስን ግን ተቃወሙ ከእናንተም ይሸሻል፤ 8፤ ወደ እግዚአብሔር ቅረቡ ወደ እናንተም ይቀርባል። እናንተ ኃጢአተኞች፥ እጆቻችሁን አንጹ፤ ሁለት አሳብም ያላችሁ እናንተ፥ ልባችሁን አጥሩ። 9፤ ተጨነቁና እዘኑ አልቅሱም፤ ሳቃችሁ ወደ ኀዘን ደስታችሁም ወደ ትካዜ ይለወጥ። 10፤ በጌታ ፊት ራሳችሁን አዋርዱ ከፍ ከፍም ያደርጋችኋል። ጌታ በነገር ሁሉ ይርዳን።

ብቻውን የቆመ በር
በር ብቻውን ትርጉም የለውም ትርጉም የሚያገኘው በግድግዳዊች ሲከበብ ነው፣ እግዚያብሔር ያ የሕይወታችን ግድግዳ ነው።በምድር ላይ ያለ እግዚያብሔር የሚናደርገው ጥረት ሁሉ ልክ እንደ ባዶ በር ነው።በር ብቻውን ትርጉም የለውም። እግዚያብሔር ከሌለ የሕይወታችን በር ወዴት ይከፈታል?? ዛሬ ሁላችን ልክ ቤት እንደሌለው በር ሆነን በአለም ሜዳ ብቻችን ቆመናል። ቃሉ እንደምለው መዝ 5:9 " በአፋቸው እውነት የለምና፥ ልባቸውም ከንቱ ነው፤ ጕሮሮአቸው የተከፈተ መቃብር ነው፤ በምላሳቸው ይሸነግላሉ።" ዛሬ እኮ ፨ መድረኩ ደማቅ ነው መሰዊያው ግን የጨለመ ፨ ቃሉ ይጠቀሳል ነገር ግን አይኖርበትም ፨ ከሰማይ ይልቅ አይኖች ስልኮች ላይ ናቸው ፨ ከድህነት ትምህርት ይልቅ ስለ ራስ ዝና፣ገድል፣ክብር፣ ስለ ገንዘብ ይሰበካል ፨ ከሰው ይልቅ ገንዘብ በለጠ ፨ ክርስትና መለኪያው ብሔር፣ቀለም፣ትውውቅ፣መተጋገዝ ሆነ ፨ ፓስተሮች፣መጋቢዎች መንጋውን ከመጠበቅ ይልቅ ንግዳቸውን ጠባቂ ሆኑ ፨ አገልግሎቾች ትርዒቶች እና ማስመሰያ ሆኑ ፨ ማስመሰል አደገ ጉልበት (መንበርከክ) ግን አጠረ ፨ ክርስቶስ የግርገ ማስታወሻ ሆነ ፨ ወንጌል የራስ ክብር መግለጫ ሆነ ፨ ትኩረት ከክርስቶስ ይልቅ ለራስ ሆነ ፨ መሪዎች ጌታን ከማሳየት ይልቅ እራሳቸውን ማሳየት ሆነ ፨ እልህና በቀል የክርስትና መገለጫ ሆነ ፨ ክርስትና መተመኛው መተጋገዝ ፣ቤተ ክርስቲያን መታየት፣ገንዘብ መስጠት ሆነ ፨ ቤተ ክርስቲያን ክርስቶስን ማሳየት ተሳናት ፨ ቤተሰብ በጋራ መፀለይ እና ቃሉን ማንበብ አቆመ ፨ ክርስቲና የፉክክር መድረክ ሆነ ብቻ ብዙ ብዙ..... ኢሳይያስ 1: 2-6 2፤ እግዚአብሔር ተናግሮአልና ሰማያት ስሙ፥ ምድርም አድምጪ፤ ልጆችን ወለድሁ አሳደግሁም፥ እነርሱም አመጹብኝ። 3፤ በሬ የገዢውን አህያም የጌታውን ጋጣ አወቀ፤ እስራኤል ግን አላወቀም፥ ሕዝቤም አላስተዋለም። 4፤ ኃጢአተኛ ወገንና በደል የተሞላበት ሕዝብ፥ የክፉዎች ዘር፥ ርኵሰትን የምታደርጉ ልጆች ሆይ፥ ወዮላችሁ! እግዚአብሔርን ትተዋል የእስራኤልንም ቅዱስ አቃልለዋል ወደ ኋላቸውም እየሄዱ ተለይተዋል። 5፤ ደግሞስ ዓመፃ እየጨመራችሁ ለምን ገና ትቀሰፋላችሁ? ራስ ሁሉ ለሕመም ልብም ሁሉ ለድካም ሆኗል። 6፤ ከእግር ጫማ አንስቶ እስከ ራስ ድረስ ጤና የለውም፤ ቍስልና እበጥ የሚመግልም ነው፤ አልፈረጠም፥ አልተጠገነም፥ በዘይትም አልለዘበም። ኢሳይያስ :- 11-18 11፤ የመሥዋዕታችሁ ብዛት ለእኔ ምን ይጠቅመኛል? ይላል እግዚአብሔር፤ የሚቃጠለውን የአውራ በግ መሥዋዕትንና የፍሪዳን ስብ ጠግቤያለሁ፤ የበሬና የበግ ጠቦት የአውራ ፍየልም ደም ደስ አያሰኘኝም። 12፤ በእኔ ፊት ልትታዩ ብትመጡ ይህን የመቅደሴን አደባባይ መርገጣችሁን ከእጃችሁ የሚሻ ማን ነው? 13፤ ምናምንቴውን ቍርባን ጨምራችሁ አታምጡ፤ ዕጣን በእኔ ዘንድ አጸያፊ ነው፤ መባቻችሁንና ሰንበታችሁን በጉባኤ መሰብሰባችሁን አልወድድም፤ በደልንም የተቀደሰውንም ጉባኤ አልታገሥም። 14፤ መባቻችሁንና በዓላቶቻችሁን ነፍሴ ጠልታለች፤ ሸክም ሆነውብኛል፥ ልታገሣቸውም ደክሜያለሁ። 15፤ እጃችሁንም ወደ እኔ ብትዘረጉ ዓይኔን ከእናንተ እሰውራለሁ፥ ልመናንም ብታበዙ አልሰማችሁም፤ እጆቻችሁ ደም ተሞልተዋል። 16፤ ታጠቡ ሰውነታችሁንም አንጹ፤ የሥራችሁን ክፋት ከዓይኔ ፊት አስወግዱ፤ ክፉ ማድረግን ተዉ፥ 17፤ መልካም መሥራትን ተማሩ፥ ፍርድን ፈልጉ፥ የተገፋውን አድኑ፥ ለድሀ አደጉ ፍረዱለት ስለ መበለቲቱም ተምዋገቱ። 18፤ ኑና እንዋቀስ ይላል እግዚአብሔር፤ ኃጢአታችሁ እንደ አለላ ብትሆን እንደ አመዳይ ትነጻለች፤ እንደ ደምም ብትቀላ እንደ ባዘቶ ትጠራለች። ስለዚህ የሕይወታችንን በር ወደ ክርስቶስ ማዞር ይሁንልን። ክርስቶስ የሕይወታችን መሰረት ፣ግድግዳ እና መዳረሻ ይሁን።ያለ እርሱ ሕይወታችን ባዶ ነው፣ጥረታችን ከንቱ ነው፣ማንነታችን ዋጋ የለውም፣ሕይወታችን ትርጉም የሚኖረው በራችን ግድግዳ(ክርስቶስ) ስኖር ነው። ወገኖቼ የሕይወታችን በር ክርስቶስ ይሁን!!!

"አይዞህ" “በምትሄድበት ሁሉ አምላክህ እግዚአብሔር ከአንተ ጋር ነውና ጽና፣ አይዞህ አትፍራ፣ አትደንግጥ ብዬ አላዘዝኩህምን?” ኢያሱ1:9 የኢያሱ መጽሐፍ የእግዚአብሔር ሕዝብ ከመቅበዝበዝ ወደ መትረፍረፍ የተሻገረበትን የታሪክ ምእራፍ የሚያሳየን ድንቅ ታሪክ ነው። እኛም በሕይወታችንተመሳሳዩን እንድንለማመድ ለትምህርታችን ተጽፎልናል። 1. እግዚአብሔር ቃሉን የሚጠብቅ አምላክ ነው። የኢያሱ መጽሐፍ ጅማሬ ላይ ስናነብ ስለ እግዚአብሔር የምናስተውለው ትልቅ እውነታ ቃሉን የሚጠብቅ አምላክ መሆኑን ነው። “ለሙሴ እንደ ነገርሁት የእግራችሁ ጫማ የሚረግጠውን ቦታ ሁሉ ለእናተ ሰጥቻችኋለሁ።” ቁ. 3። እርሱ እንደተናገረው እንደዚያው የሚያደርግ አምላክ ነውና ተስፋ የሰጠው እርሱ የታመነ ነው ብለን እንመሰክራለን። 2. እግዚአብሔር የሚያበረታታ አምላክ ነው። ይህንን ምእራፍ ስናነብ በሙሴ እግር የተተካው አዲሱ መሪ ኢያሱ ከተጣለበት የሃላፊነት ክብደት የተነሳ ፍርሃት ተሰምቶት እነደነበር መገመት አይከብድም። ይሁን እንጂ፣ እግዚአብሔር ደግሞ እንዲህ በማለት እየደጋገመ ሲያደፋፍረው እንመለከታለን። “ከአንተ ጋር እሆናለሁ፤ አልጥልህም፤ አልተውህም” ቁ.5፣ “ጽና፣ አይዞህ፣” ቁ. 6፣ “ጽና እጅግ በርታ” ቁ. 7፣ “አምላክህ እግዚአብሔር ካንተ ጋር ነውና ጽና፣ አትፍራ፣ አትደንግጥ” ቁ.9። በእርግጥም እግዚአብሔርየሚያበረታታን፣ አቅም ጉልበት የሚሰጠን፣ የሚሸከመን ረድኤታችን ነው። 3. እግዚአብሔር ቃሉንእንድናከብር የሚፈልግ አምላክ ነው። እግዚአብሔር የራሱን ቃል የሚያከብር ብቻ ሳይሆን እኛም ደግሞ የእርሱን ቃል እንድናከብር የሚፈልግ አምላክ መሆኑን በዚህ ምእራፍ ለኢያሱ ከተናገረው እንረዳለን። “ባሪያዬ ሙሴ ያዘዘህን ሕግ ሁሉ ጠብቅ፣ አድርገውም በምትሄድበትም ሁሉ እንዲከናወንልህ ወደ ቀኝም ውደ ግራም አትበል።” ቁ. 7. መታዘዛችን ከምናቀርብለት ከየተኛውም መስዋእት ይልቅ ለእርሱ ተመራጭ ነው። “በውኑ የእግዚአብሔርን ቃል በመስማት ደስ እንደሚለው እግዚአብሔር በሚቃጠልና በሚታረድ መስዋእት ደስ ይለዋልን? እነሆ፣ መታዘዝ ከመስዋእት ማዳመጥም የአውራ በግ ስብ ከማቅረብ ይበልጣል። 1 ሳሙ 15:22 ጸሎት በማጽናናትህ ነፍሳችንን የምታበረታታ ሰማያዊ አባታችን ሆይ፣ አንተ ቃልህን የምትጠብቅና የምታደፋፍረን አምላክ ስለሆንህእናመሰግንሃለን። አሁንም ነፍሳችን ከመቅበዝበዝ አምልጣ ወዳዘጋጀህላት ርስት በሙላት ትገባ ዘንድ በፊትለፊቴ በዘረጋከው የድል ጎድና አብረኸን ስለምትጓዝ፣ አይዞህ ስለምትለን ስምህን ከፍ ከፍ እናደርጋለን። በዚህ መንገድ መሪያችንእንዲሆን ስለሰጠከን ስለ ልጅህ ስለ ኢየሱስ እናመሰግንሃለን። እኛም ወደ ግራና ወደ ቀኝ ሳንል ቃልህን እንድንታዘዘው፣ ቃልህ ከአፋችን እንዳይለይ በሌትና በቀን እንዳናሰላሰለው እርዳን። አሜን። ፓ/ር መልአክ አለማየሁ