የሀዋሳ ታቦር ሰባተኛ ቀን አድቬንቲስት አለም አቀፍ ቤተክርስቲያን (Hawassa Tabour 7th day Adventist INternational Church
Open in Telegram
1 070
Subscribers
+124 hours
+177 days
+3830 days
Posts Archive
ብቻውን የቆመ በርበር ብቻውን ትርጉም የለውም ትርጉም የሚያገኘው በግድግዳዊች ሲከበብ ነው፣ እግዚያብሔር ያ የሕይወታችን ግድግዳ ነው።በምድር ላይ ያለ እግዚያብሔር የሚናደርገው ጥረት ሁሉ ልክ እንደ ባዶ በር ነው።በር ብቻውን ትርጉም የለውም። እግዚያብሔር ከሌለ የሕይወታችን በር ወዴት ይከፈታል?? ዛሬ ሁላችን ልክ ቤት እንደሌለው በር ሆነን በአለም ሜዳ ብቻችን ቆመናል። ቃሉ እንደምለው መዝ 5:9 " በአፋቸው እውነት የለምና፥ ልባቸውም ከንቱ ነው፤ ጕሮሮአቸው የተከፈተ መቃብር ነው፤ በምላሳቸው ይሸነግላሉ።" ዛሬ እኮ ፨ መድረኩ ደማቅ ነው መሰዊያው ግን የጨለመ ፨ ቃሉ ይጠቀሳል ነገር ግን አይኖርበትም ፨ ከሰማይ ይልቅ አይኖች ስልኮች ላይ ናቸው ፨ ከድህነት ትምህርት ይልቅ ስለ ራስ ዝና፣ገድል፣ክብር፣ ስለ ገንዘብ ይሰበካል ፨ ከሰው ይልቅ ገንዘብ በለጠ ፨ ክርስትና መለኪያው ብሔር፣ቀለም፣ትውውቅ፣መተጋገዝ ሆነ ፨ ፓስተሮች፣መጋቢዎች መንጋውን ከመጠበቅ ይልቅ ንግዳቸውን ጠባቂ ሆኑ ፨ አገልግሎቾች ትርዒቶች እና ማስመሰያ ሆኑ ፨ ማስመሰል አደገ ጉልበት (መንበርከክ) ግን አጠረ ፨ ክርስቶስ የግርገ ማስታወሻ ሆነ ፨ ወንጌል የራስ ክብር መግለጫ ሆነ ፨ ትኩረት ከክርስቶስ ይልቅ ለራስ ሆነ ፨ መሪዎች ጌታን ከማሳየት ይልቅ እራሳቸውን ማሳየት ሆነ ፨ እልህና በቀል የክርስትና መገለጫ ሆነ ፨ ክርስትና መተመኛው መተጋገዝ ፣ቤተ ክርስቲያን መታየት፣ገንዘብ መስጠት ሆነ ፨ ቤተ ክርስቲያን ክርስቶስን ማሳየት ተሳናት ፨ ቤተሰብ በጋራ መፀለይ እና ቃሉን ማንበብ አቆመ ፨ ክርስቲና የፉክክር መድረክ ሆነ ብቻ ብዙ ብዙ..... ኢሳይያስ 1: 2-6 2፤ እግዚአብሔር ተናግሮአልና ሰማያት ስሙ፥ ምድርም አድምጪ፤ ልጆችን ወለድሁ አሳደግሁም፥ እነርሱም አመጹብኝ። 3፤ በሬ የገዢውን አህያም የጌታውን ጋጣ አወቀ፤ እስራኤል ግን አላወቀም፥ ሕዝቤም አላስተዋለም። 4፤ ኃጢአተኛ ወገንና በደል የተሞላበት ሕዝብ፥ የክፉዎች ዘር፥ ርኵሰትን የምታደርጉ ልጆች ሆይ፥ ወዮላችሁ! እግዚአብሔርን ትተዋል የእስራኤልንም ቅዱስ አቃልለዋል ወደ ኋላቸውም እየሄዱ ተለይተዋል። 5፤ ደግሞስ ዓመፃ እየጨመራችሁ ለምን ገና ትቀሰፋላችሁ? ራስ ሁሉ ለሕመም ልብም ሁሉ ለድካም ሆኗል። 6፤ ከእግር ጫማ አንስቶ እስከ ራስ ድረስ ጤና የለውም፤ ቍስልና እበጥ የሚመግልም ነው፤ አልፈረጠም፥ አልተጠገነም፥ በዘይትም አልለዘበም። ኢሳይያስ :- 11-18 11፤ የመሥዋዕታችሁ ብዛት ለእኔ ምን ይጠቅመኛል? ይላል እግዚአብሔር፤ የሚቃጠለውን የአውራ በግ መሥዋዕትንና የፍሪዳን ስብ ጠግቤያለሁ፤ የበሬና የበግ ጠቦት የአውራ ፍየልም ደም ደስ አያሰኘኝም። 12፤ በእኔ ፊት ልትታዩ ብትመጡ ይህን የመቅደሴን አደባባይ መርገጣችሁን ከእጃችሁ የሚሻ ማን ነው? 13፤ ምናምንቴውን ቍርባን ጨምራችሁ አታምጡ፤ ዕጣን በእኔ ዘንድ አጸያፊ ነው፤ መባቻችሁንና ሰንበታችሁን በጉባኤ መሰብሰባችሁን አልወድድም፤ በደልንም የተቀደሰውንም ጉባኤ አልታገሥም። 14፤ መባቻችሁንና በዓላቶቻችሁን ነፍሴ ጠልታለች፤ ሸክም ሆነውብኛል፥ ልታገሣቸውም ደክሜያለሁ። 15፤ እጃችሁንም ወደ እኔ ብትዘረጉ ዓይኔን ከእናንተ እሰውራለሁ፥ ልመናንም ብታበዙ አልሰማችሁም፤ እጆቻችሁ ደም ተሞልተዋል። 16፤ ታጠቡ ሰውነታችሁንም አንጹ፤ የሥራችሁን ክፋት ከዓይኔ ፊት አስወግዱ፤ ክፉ ማድረግን ተዉ፥ 17፤ መልካም መሥራትን ተማሩ፥ ፍርድን ፈልጉ፥ የተገፋውን አድኑ፥ ለድሀ አደጉ ፍረዱለት ስለ መበለቲቱም ተምዋገቱ። 18፤ ኑና እንዋቀስ ይላል እግዚአብሔር፤ ኃጢአታችሁ እንደ አለላ ብትሆን እንደ አመዳይ ትነጻለች፤ እንደ ደምም ብትቀላ እንደ ባዘቶ ትጠራለች። ስለዚህ የሕይወታችንን በር ወደ ክርስቶስ ማዞር ይሁንልን። ክርስቶስ የሕይወታችን መሰረት ፣ግድግዳ እና መዳረሻ ይሁን።ያለ እርሱ ሕይወታችን ባዶ ነው፣ጥረታችን ከንቱ ነው፣ማንነታችን ዋጋ የለውም፣ሕይወታችን ትርጉም የሚኖረው በራችን ግድግዳ(ክርስቶስ) ስኖር ነው። ወገኖቼ የሕይወታችን በር ክርስቶስ ይሁን!!!
"አይዞህ"
“በምትሄድበት ሁሉ አምላክህ እግዚአብሔር ከአንተ ጋር ነውና
ጽና፣ አይዞህ አትፍራ፣ አትደንግጥ ብዬ አላዘዝኩህምን?” ኢያሱ1:9
የኢያሱ መጽሐፍ የእግዚአብሔር ሕዝብ ከመቅበዝበዝ ወደ መትረፍረፍ የተሻገረበትን የታሪክ ምእራፍ የሚያሳየን ድንቅ ታሪክ ነው። እኛም በሕይወታችንተመሳሳዩን እንድንለማመድ ለትምህርታችን ተጽፎልናል።
1. እግዚአብሔር ቃሉን የሚጠብቅ አምላክ ነው።
የኢያሱ መጽሐፍ ጅማሬ ላይ ስናነብ ስለ እግዚአብሔር የምናስተውለው ትልቅ እውነታ ቃሉን የሚጠብቅ አምላክ መሆኑን ነው። “ለሙሴ እንደ ነገርሁት የእግራችሁ ጫማ የሚረግጠውን ቦታ ሁሉ ለእናተ ሰጥቻችኋለሁ።” ቁ. 3። እርሱ እንደተናገረው እንደዚያው የሚያደርግ አምላክ ነውና ተስፋ የሰጠው እርሱ የታመነ ነው ብለን እንመሰክራለን።
2. እግዚአብሔር የሚያበረታታ አምላክ ነው።
ይህንን ምእራፍ ስናነብ በሙሴ እግር የተተካው አዲሱ መሪ ኢያሱ ከተጣለበት የሃላፊነት ክብደት የተነሳ ፍርሃት ተሰምቶት እነደነበር መገመት አይከብድም። ይሁን እንጂ፣ እግዚአብሔር ደግሞ እንዲህ በማለት እየደጋገመ ሲያደፋፍረው እንመለከታለን። “ከአንተ ጋር እሆናለሁ፤ አልጥልህም፤ አልተውህም” ቁ.5፣ “ጽና፣ አይዞህ፣” ቁ. 6፣ “ጽና እጅግ በርታ” ቁ. 7፣ “አምላክህ እግዚአብሔር ካንተ ጋር ነውና ጽና፣ አትፍራ፣ አትደንግጥ” ቁ.9። በእርግጥም እግዚአብሔርየሚያበረታታን፣ አቅም ጉልበት የሚሰጠን፣ የሚሸከመን ረድኤታችን ነው።
3. እግዚአብሔር ቃሉንእንድናከብር የሚፈልግ አምላክ ነው።
እግዚአብሔር የራሱን
ቃል የሚያከብር ብቻ ሳይሆን እኛም ደግሞ የእርሱን ቃል እንድናከብር የሚፈልግ አምላክ መሆኑን በዚህ ምእራፍ ለኢያሱ ከተናገረው እንረዳለን። “ባሪያዬ ሙሴ ያዘዘህን ሕግ ሁሉ ጠብቅ፣ አድርገውም በምትሄድበትም ሁሉ እንዲከናወንልህ ወደ ቀኝም ውደ ግራም አትበል።” ቁ. 7. መታዘዛችን ከምናቀርብለት ከየተኛውም መስዋእት ይልቅ ለእርሱ ተመራጭ ነው። “በውኑ የእግዚአብሔርን ቃል በመስማት ደስ እንደሚለው እግዚአብሔር በሚቃጠልና በሚታረድ መስዋእት ደስ ይለዋልን? እነሆ፣ መታዘዝ ከመስዋእት ማዳመጥም የአውራ በግ ስብ ከማቅረብ ይበልጣል። 1 ሳሙ 15:22
ጸሎት
በማጽናናትህ ነፍሳችንን የምታበረታታ ሰማያዊ አባታችን ሆይ፣ አንተ ቃልህን የምትጠብቅና የምታደፋፍረን አምላክ ስለሆንህእናመሰግንሃለን። አሁንም ነፍሳችን ከመቅበዝበዝ አምልጣ ወዳዘጋጀህላት ርስት በሙላት ትገባ ዘንድ በፊትለፊቴ በዘረጋከው የድል ጎድና አብረኸን ስለምትጓዝ፣ አይዞህ ስለምትለን ስምህን ከፍ ከፍ እናደርጋለን። በዚህ መንገድ መሪያችንእንዲሆን ስለሰጠከን ስለ ልጅህ ስለ ኢየሱስ እናመሰግንሃለን። እኛም ወደ ግራና ወደ ቀኝ ሳንል ቃልህን እንድንታዘዘው፣ ቃልህ ከአፋችን እንዳይለይ በሌትና በቀን እንዳናሰላሰለው እርዳን። አሜን።
ፓ/ር መልአክ አለማየሁ
ማስታወሻ
የዓርብ ምሽት እና የቅዳሜ የቤ/ያን ፕሮግራም የወንጌል ጥረት እየተደረገ ባለበት ቦታ ስለሚሆን የቤ/ያናችን አባላት በሙላት በቦታው እንግዶችን በመጋበዝ እንድትገኙ እናስታውቃለን።
አድራሻ......... ከ ጤና ቢሮ ወደ ኢ ቫን በሚወስደው መንገድ ላይ
ማስታወሻ
የዓርብ ምሽት እና የቅዳሜ የቤ/ያን ፕሮግራም የወንጌል ጥረት እየተደረገ ባለበት ቦታ ስለሚሆን የቤ/ያናችን አባላት በሙላት በቦታው እንግዶችን በመጋበዝ እንድትገኙ እናስታውቃለን።
አድራሻ......... ከ ጤና ቢሮ ወደ ኢ ቫን በሚወስደው መንገድ ላይ
Repost from የህይወት ቃል / Word of life
ቀን 37
ያህዌ ሻማ
እግዚአብሔር በዚያ አለ
አምላካችን እግዚአብሔር የፍቅር አምላክ ነውና ከፍጡራኑ ጋር መሆን የሚፈልግ እንዲሁም ከእነርሱ ጋር የጠበቀን ህብረት መመስረት የሚሻ አምላክ ነው። ሰውን በመልኩና በአምሳሉ ከፈጠረው በኋላ በመጀመሪያ የሰጠው ስጦታ ከእርሱ ጋር የተለየ ጊዜ እንዲኖረው የሚያደረገውን የሰንበት እረፍትን ነበር። ከሰራው ስራ ሁሉ በሰባተኛው ቀን እግዚአብሔር ሲያርፍ ለአዳምና ለሔዋን ደግሞ ከእርሱ ከፈጣሪያቸው ጋር ልዩ ህብረት የሚያደርጉበት ቀን ሆነላቸው። ከዚያም ያለ ምንም ከልካይ ከዚህ አፍቃሪ አምላክ ጋር ፊት ለፊት የመገናኘትና ህብረት የማድረግ እድል ነበራቸው።
ይሁን እንጂ፣ በእግዚአብሔር ላይ በማመጽ፣ የተሰጣቸውን የምርጫ ነጻነት ተጠቀመው የራሳቸው አምላክ ለመሆን የትእቢትን ጎዳና በመረጡ ጊዜ ከዚህ የፍቅር አምላክ ሸሹ። ሃጢአትም በሰውና በእግዚአብሔር መካከል የጥል ግድግዳን አቆመ።
ነገር ግን አፍቃሪ አምላካችን እግዚአብሔር ይህንን ሁኔታ ለመቀየርና ለሰብአዊ ዘር ሁለተኛ እድልን በመስጠት እንደገና ወደ እቅፉ ሊመለስን ታላቅ ዋጋን ከፈለ። ከዚም የተነሳ ከሃጢአት የምንድንበትና እንደገና ወደ እግዚአብሔር መገኘት በሙላት ለመግባት የምንችለበት የልጁ የኢየሱስ ክርስቶስ ደም ፈሰሰ። በውጤቱም፣ በመስቀል ላይ ጌታችን ኢየሱስ ህይወቱን በሰጠ ጊዜ በቤተመቅደስ ውስጥ የነበረው መጋረጃ ከላይ እስከታች ተቀደደ። ይህ መጋረጃ ሃጢአት በእኛና በእግዚአብሔር መካከል የፈጠረውን መለያየት ያሳይ የነበረ ሲሆን አሁን ግን በክርስቶስ መስዋእትነት ተወግዶ ወደ ቅድስተ ቅዱሳን የምንገባበት አዲስና ህያው መንገድ ተመርቆ ተከፈተልን።
"እኔ መንገድ እውነትና ህይወት ነኝ" ባለው በክርስቶስ ኢየሱስ ያመኑና እርሱንም ወደ ሚሄድበት ሁሉ የተከተሉ ሁሉ በቅርብ የእግዚአብሔር ዘላለማዊ የክብር መንግስት ስትመሰረት በዚያ ከአፍቃሪ አምላካቸው ጋር ለዘላለም ይኖራሉ። ሃጢአት ከዩንቨርስ ተወግዶ አዲስ ሰማይና ምድርን እግዚአብሔር ሲፈጥር፣ ይህ አፍቃሪ አምላክ መኖሪያውን እንደገና ከሰዎች መካከል ያደርጋል።
“ከዚህ በኋላ አዲስ ሰማይና አዲስ ምድር አየሁ፤ የመጀመሪያው ሰማይና የመጀመሪያዪቱ ምድር ዐልፈዋልና፤ ባሕርም ከእንግዲህ ወዲህ አይኖርም። ቅድስቲቱ ከተማ፣ አዲሲቱ ኢየሩሳሌም ለባሏ እንደ ተዋበች ሙሽራ ተዘጋጅታ ከሰማይ ከእግዚአብሔር ዘንድ ስትወርድ አየሁ። ደግሞም እንዲህ የሚል ታላቅ ድምፅ ከዙፋኑ ሲወጣ ሰማሁ፤ “እነሆ፤ የእግዚአብሔር ማደሪያ በሰዎች መካከል ነው፤ እርሱ ከእነርሱ ጋር ይኖራል፤ እነርሱም ሕዝቡ ይሆናሉ፤ እግዚአብሔር ራሱም ከእነርሱ ጋር ይኖራል፤ አምላካቸውም ይሆናል። እንባን ሁሉ ከዐይናቸው ያብሳል፤ ከእንግዲህ ወዲህ ሞት ወይም ሐዘን ወይም ልቅሶ ወይም ሥቃይ አይኖርም፤ የቀድሞው ሥርዐት ዐልፎአልና።” ራእ 21:1-4
ይሄን ጊዜ ነብዩ ህዝቅኤል አስቀድሞ የተናገረው ትንቢት ይፈጸምና በእርግጥም የከተማይቱ ስም “ያህዌ ሻማ” ትርጉሙም "እግዚአብሔር በዚያ አለ" ይሆናል። ከዚያም ከእርሱ ጋር ፍጹም በሆነ የፍቅር ህብረት እርሱ አምላካችን እኛም ህዝቡ ሆነን ለዘላለም የተትረፈረፈ ህይወትን እንኖራለን። ይሄ ነው የተባረከው ተስፋችን!
አባት ሆይ፣ መልሰህ ወደ እቅፍህ ልታስገባን፣ መኖርያህንም ከእኛ መካከል ልታደርግ በቅርቡ ይህንን ተስፋ ስለምትፈጽምልን እያመሰገንህ፣ እኛም "በጉን በሄደበት ሁሉ በመከተል" የህወታችን ምንጭ ከሆነው ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር ተጣብቀን እስከ መጨረሻ እንድንጸናና የዚህ ርስት ወራሾች እንድንሆን እርዳን። አሜን።
እሁድ ማታ ከ ፓር መልአክ አለማየሁ ጋር የነበረ ቆይታ በጌታ ፍቃድ ሳምንት እሁድም ይቀጥላል።
እሁድ ማታ ከ ፓር መልአክ አለማየሁ ጋር የነበረ ቆይታ በጌታ ፍቃድ ሳምንት እሁድም ይቀጥላል።
ኤል ካቢርእግዚአብሔር ኀያል (ኤል ካቢር) ነው፤ ግን ማንንም አይንቅም፤ ኀያል፣ በዐላማውም ጽኑ ነው። በሃብት ወይም በስልጣን አድገው “ከተራነት” ወደ “ኀያልነት” ከፍ ሲሉ ዝቅ ባለው ስፍራ አብረዋቸው የነበሩትን የሚያስቡ ስንቶች ይሆኑ? በአብዛኛው የሚታየው ግን ከፍ ባልን ቁጥር ዝቅ ያሉትን ስንረሳ፣ ስንንቅ አልፎም ጉልበታችንን አላግባብ በመጠቀም ስንረግጥ ነው። በእግዚአብሔር ዘንድ የምናየው ግን የዚህን ፍጹም ተቃራኒ ነው። አምላካችን እግዚአብሔር የኀያላን ሁሉ ኀያል፣ ዙፋኑም ከዙፋናት ሁሉ በላይ ነው። ንጉስ ሰለሞን የዚህን አምላክ ታላቅነት ሲገልጽ እንዲህ ነበር ያለው:- “ እነሆ፤ ሰማይ፣ ከሰማያትም በላይ ያለው ሰማይ እንኳ ይይዝህ ዘንድ አይችልም፤” (1 ነገ 8:27) ምንም እንኳን እርሱ እንዲህ ከአእምሮችን በላይ ታላቅ የሆነ አምላክ ቢሆንም ግን ማንንም አይንቅም። “ ውሆችን በዕፍኙ የሰፈረ፣ ሰማያትን በስንዝሩ የለካ፣ የምድርን ዐፈር በመስፈሪያ ሰብስቦ የያዘ፣ ተራሮችን በሚዛን፣ ኰረብቶችንም በመድሎት የመዘነ” ይሄ ኀያል አምላክ ከእርሱ ግዙፍነት ጋር ስንነጻጸር ፈጽሞ ኢምንት የሆነውን እኛን ለመፈለግ ዝቅ አለ። ከዙፋኑ ወርዶ በእኛ ሥጋ ውስጥ አደረ። በመካከላችን ተመላለሰ። ይህም በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ምድር መምጣት ተፈጸመ። ከዙፋኑ ወርዶ፣ የሰውን ተፈጥሮ ወስዶ ወደ ምድር መምጣቱ ሳያንስ በክብር ስፍራ በቤተመንግስት ሳይሆን በበረት ተወለደ። በምቾት ተንደላቆ ማደግ ሲችል፣ መልካም አይወጣባትም በተባለች በናዝሬት ከተማ፣ በአናጺነት ሙያ ተሰማርቶ አደገ። የመጣበትንም ተልእኮ ለመፈጸም ወደ አደባባይ ሲወጣ ውሎው ከተናቁትና ከተጠሉት በሰው ዘንድ ስፍራ ከማይሰጣቸው ጋር ነበር። በመጨረሻም በሁለት ወንበዴዎች መካከል በመስቀል ላይ የሁላችንን ሃጢአት ተሸክሞ ህይወቱን ሰጠ። ይህን ሁሉ ያደረገው ደግሞ በሃጢአት ውስጥ የወደቀውን ሰብአዊ ዘር ለመታደግ ነበር። በእርግጥም እግዚአብሔር ትልቅ ነው፤ ግን ማንንም አይንቅም። በዚህ እውነት ላይ እምነታችንን አድርገን በቸርነቱና በምህረቱ ወደ ሚከተለን ጌታ ፊታችንን እንመልስ። ህይወታችንን ለእርሱ እንስጠው። እርሱም “ወደ እኔ የመጣውን ወደ ሜዳ አልሰደውም” ያለ ጌታ፣ እጆቹን ዘርግቶ ይቀበለናል። በብርቱ ክንዱም ደግፎ ይይዘናል። እኛም በሃያሉ አምላክ ትከሻ ላይ ሆነን፣ “ኃይልን በሚሰጠኝ በክርስቶስ ሁሉን ማድረግ እችላለሁ” ብለን በእምነት ማወጅ ይሆንልናል። አባት ሆይ፣ በእርግጥም ለታላቅነትህ ተወዳዳሪ የሌለህ ብትሆንም፣ ትንሾቹን እኛን፣ በሃጢአት ከወደቅንበት ልታነሳን ዝቅ ብለህ ስለፈለግኸን እያመሰገንህ፣ ወደ እቅፍ ውስጥ ለመግባት እንድንፈጥን፣ ህይወታችን ሁልጊዜ ባንተ በታላቁ አምላካችን ውስጥ እንዲሰወርና በእምነት ያንተን ሃያል ክንዶች ጨብጠን እንደፈቃድህ እንድንኖር እርዳን። አሜን። ምንጭ :-ፓስተር መልዓክ አለማየው
የታቦር ሰባተኛ ቀን አድቬንቲስት ቤተ ክርስቲያን የልማት ኮሚቴ አጭር መልዕክት ለምዕመናኖቻችን!!የቤተ ክርስቲያኒቱን ምዕመናን ለብዙ ዓመታት እያስተባበረ በርካታ ዘመን ተሻጋሪ የልማት ሥራዎችን ይሰራ የነበረው የልማት ኮሚቴ በመጋቢት 2017 ዓ.ም በተመረጠው አዲስ ቦርድ መበተኑን እየገለፅን ይህ ኮሚቴ ሥራውን ጌታ በረዳው መጠን ከምዕመናን ጋር በሰራባቸው ዓመታት ያከናወነውን ሥራ በቤ/ያኒቱ የሂሳብ ባለሙያዎች የተረጋገጠውን አጠቃላይ የሥራ ሂደት ከዚህ በታች በተገለፀው መሰረት የሥራ ማሰናበቻ (clearance) ወስዶ እና ሙሉ ዶክመንት አስረክቦ መሰናበቱን የተከበረው የቤተ ክርስቲያኒቱ ምዕመናን እንድያውቅ በአክብሮት እንገላፃለን!! ጌታ ይባርካችሁ!!! ኮሚቴው!! ግንቦት 2017 ዓ.ም
አስቸኳይ ማስታወቂያነገ ማክሰኞ 22/11/2017 ዓ.ም ልክ 11.00 ላይ የታቦር ቤተ ክርስቲያን ቦርድ፣ አስቸኳይ ስብሰባ ስላለ ቤተ ክርስቲያን ቅጥር ጊቢ መሰብሰቢያ ቦታ እንድትገኙ ቤተ ክርስቲያን ታሳስባለች። ተባረኩ!!
መርዶየቤተ ክርስቲያናችንአባል የሆኑት አቶ ታፈሰ ሻሜቦ አባቱን አስቀብሮ የፊታችን አርብ ሐምሌ 18/2017 ዓ.ም ወደ ሀዋሳ ይመለሳል። ቤተክርስቲያናችን በአባቱ ሞት የተሰማትን ጥልቅ ሀዘን እየገለፀች ለቤተሰቡና ወዳጅ ዘመዶቹ መጽናናትን ትመኛለች። የቤተክርስቲያናችን ምዕመናንና ወዳጆች በሙሉ ሐምሌ 18/2017 ዓ.ም አርብ ከቀኑ 9፡00 ጀምሮ የማፅናኛ ፕሮግራም ስለምኖር የቤ/ያን አባላት በሙሉ እንድትገኙ እናስታውቃለን። አድራሻ:- 01 ደቡብ ኮንዶሚንየም
መርዶየቤ/ያን አባል የሆኑት አቶ በየነ ባፋ ወንድሙን አስቀብሮ ዛሬ ማክሰኞ ሐምሌ 15/2017 ዓ.ም ወደ ሀዋሳ ይመለሳል ቤተ ክርስቲያናችን በወንድሙ ሞት የተሰማትን ጥልቅ ሀዘን እየገለፀች ለቤተሰቡና ወዳጅ ዘመዶቹ መጽናናትን ትመኛለች የቤተ ክርስቲያናችን ምዕመናንና ወዳጆቹ በሙሉ ከዛሬ ማክሰኞ ከቀኑ 9፡00 ጀምሮ የማፅናኛ ፕሮግራም ስለምኖረን በስፍራው እንድትገኙ እናስታውቃለን። አድራሻ፦ ታቦር የመጀመርያ ደረጃ ት/ቤት ጀርባ ወይም ከነ ጋሽ አድማሱ ጆፌ ቤት ጀርባ
