en
Feedback
የሀዋሳ ታቦር ሰባተኛ ቀን አድቬንቲስት አለም አቀፍ ቤተክርስቲያን (Hawassa Tabour 7th day Adventist INternational Church

የሀዋሳ ታቦር ሰባተኛ ቀን አድቬንቲስት አለም አቀፍ ቤተክርስቲያን (Hawassa Tabour 7th day Adventist INternational Church

Open in Telegram

እግዚአብሄርን ለመገናኘት ተዘጋጅ

Show more
1 071
Subscribers
+224 hours
+167 days
+3930 days
Posts Archive
መሮዶ
ሰላም ይብዛላችሁ የታቦር ቤ/ያን አባላት የቤ/ያን አባል የሆኑት አቶ ትዕዛዙ አንጁሎ እናቱን አስቀብሮ ዛሬ አርብ ጥቅምንት 21/2018 ዓ.ም ይመለሳል ስለሆነም ከቀኑ 9፡00 ጀምሮ ቤተ ክርስቲያን የማፅናኛ ፕሮግራም ስለምታካህድ የቤ/ያን አባላት በሙሉ በስፍራው እንድትገኙ እናስታውቃለን። አድራሻ፡ አድቬንቲስት መዋለ ህፃናት ትምህርት ቤት አከባቢ

Arise, Go to Zarephath” (Based on 1 Kings 17:7–9; Isaiah 43:19) Elijah teaches us a vital truth: staying where God was is not the same as staying where God is. When the brook dried up, Elijah could have remained, clinging to memories of God’s past provision. But obedience meant moving on—to a new place where God’s presence was still at work. Many of our congregations today stand beside dry brooks—repeating lifeless forms, wondering why our evangelism bears little fruit and our worship lacks power. Yet God’s voice still speaks: “Arise, go to Zarephath.” To move with God is not apostasy—it is obedience. The same Spirit who once blessed us now calls us forward, saying, “Behold, I am doing a new thing; now it springs forth, do you not perceive it?” (Isaiah 43:19). May we have the faith to follow where God leads next. From the book

ዕንባቆም
( ዕንባቆም ምዕራፍ 1 እስከ ምዕራፍ 3) ፨ መጽሐፉ የሚጀምረው በክርክር ነው ፨ እስከ መቼ ነው በይሁዳ መካከል፣ ስምህ በሚጠራበት፣ አንተን በሚያመልኩ መካከል እስከመቼ ነው ማትፈርደው?? ፨ በሌላ አገላለፅ ማውቀው እግዚያብሔር ሌላ ፣እየሰማው ያደኩት እግዚያብሔር ሌላ ፣ የተሰበኩት እግዚያብሔር ሌላ ነገር ግን እውነትን ያለ እየተጎሳቆለ፣ካንተ ጋር ልኑር ያለ እየተሰቃየ፣ ፍርድ እየጎደለበት ..... ፨ ሌላው ግን እንደፈለገ እየሆነ ኋጥያትን ፈልጎና አስቦ እየሰራ ምነው በይሁዳ ዝም አልክ?? የዕንባቆም ክርክር ነበረ ፨ በዚያ ላይ ደግሞ እግዚያብሔር በይሁዳ ላይ ከለዳውያንን አስነሳ ይሄ ደግሞ ዕንባቆምን ይበልጥ ጥያቄ ውስጥ ከተተው ዕን 1:-6 " እነሆ፥ የእነርሱ ያልሆነውን መኖሪያ ይወርሱ ዘንድ በምድር ስፋት ላይ የሚሄዱትን መራሮችንና ፈጣኖችን ሕዝብ ከለዳውያንን አስነሣለሁ። " ፨ የይሁዳ ሕዝብ ምንም እንኳን ኋጥያተኞች ቢሆኑም የአንተ ሕዝቦች ነበሩ ነገር ግን ከለዳውያን የባሱትን ኋጥያትን አስበውና አቅደው የሚሰሩትን እንዴት ይሁዳ ላይ ታስነሳለህ?? የዕንባቆም ጥያቄ ይሄ ነበር ከለዳውያን ፨ ፍርዳቸው እና ክብራቸው ከራሳቸው ይወጣል ፨ ሁሉም ለግፍ ስራ ይወጣሉ ፨ ኋጥያትን አስበውና አቅደው ያደርጋሉ ፨ በነገስታት ላይ ያላግጣሉ ታዲያ እኛን ለምን ?? ይሁዳ ላይ ለምን??? የዕንባቆም ጥያቄ ነበር እኛ አንተን ስናውቅህ ፨ የተቀደስክ አምላክ ፨ እውነተኛ አምላክ ፨ ከዘላለም የነበርክ ፨ ፍርድህ ቅን የሆነ ፨ ዓይኖችህ ክፉ እንዳያዩ ንጹህ ናቸው ፨ ጠማማነትን ትመለከት ዘንድ አትችልም ታዲያ ለምን?? ዕንባቆም ውስጡ አሯል ከስፍራው ለመልቀቅ እየዳዳ ነው ። ፨ ምዕራፍ 1 ላይ ዕንባቆም ስሜቱ ግራ ቢጋባም ለጥያቄ መልስ የምትሰጠኝ አንተ ስለሆንክ አልሄድም ከስፍራሄ አለቅም አለ ዕን 2:1 " በመጠበቂያዬ ላይ እቆማለሁ፥ በአምባ ላይም እወጣለሁ፤ የሚናገረኝንም፥ ስለ ክርክሬም የምመልሰውን አውቅ ዘንድ እመለከታለሁ። " ፨ በመጠበቂያዬ ላይ እቆማለው የትም አልሄድም አለ ፨ አንዳንዴ አይገባም የሰማነው እግ/ር ፣ ያየነው እግ/ር፣የተከተልነው እግዚያብሔር ሌላ በሕይወት የሚሆነው ሌላ ብዙ ጊዜ እንደ ዕንባቆም ግራ እንጋባለን ፨ ትንሽ አይንህን አሻግረህ ስታይ እንዳሻው የሚኖር፣ እንደፈለገ የሚኖር የደላው ፣ እያማረበት የሚሄድ ፨ እንደ ግለሰብ ፣ቤተሰብ፣ ቤተክርስቲያን የሰማነው ሌላ የሚሆነው ሌላ ግራ የሚያጋባ ታዲያ ወዴት ይኬድ?? አንተን እጠብቃለው የትም አልሄድም አለ ዕንባቆም ፨ ወገኖቼ ጥያቄዎቻችን ላይመለሱ ይችላሉ፣ ተጎሳቁለን ሊሆን ይችላል፣ በሕይወታችን ግራ የሚያጋባ ነገር እየሆነ ይሆናል፣ ፍርድ ጎሎብን ይሆናል፣ ፊትህ አተን ይሆናል፣ ሰው ሸሽቶን ሊሆን ይችላል፣ ቤተሰብ ቤተክርስቲያን አሳዝኖን ይሆናል፣ በብዙ ሀዘን መከራ ውስጥ ሆነን ይሆናል ነገር ግን በስፍራችንን ሆነን እንጠብቀው ፨ እያገለገልን፣ እየፀለይን እንጠብቀው ፨ በስፍራው ብቻ እንጠብቅ የትም ብንሄድ መልስ አናገኝም መልሱ ያለው እርሱ ጋር ነው ፨ ወገኖቼ እግዚያብሔር በተቀደሰው መቅደሱ አለ ያየናል፣ ይሰማናል ፣ ችግራችን ይገባዋል ነገር ግን ዝም እንበል እንጠብቀው ዕን 2:-20 " እግዚአብሔር ግን በተቀደሰ መቅደሱ አለ፤ ምድርም ሁሉ በፊቱ ዝም ትበል። ፨ ሁኔታ ተስፋ ያስቆርጣል ግን እርሱ አለ፣ ሰው የለን ይሆናል ግን እርሱ አለ፣ ጤና ላይኖረን ይችላል ግን እርሱ አለ፣ ነገሮች እንዳሰብናቸው ላይሆኑ ይችላሉ ግን እርሱ አለ፣አንሰን ታይተን ሊሆን ይችላል ግን እርሱ አለ ፨ ሰይጣን ግን ስፍራ ሊያስለቅቀን ሁሌም ይተጋል ፨ ኢዮብን ተመልከቱ ልጆቹ አለቁ፣ ሀብቱ አለቀ፣ አገልጋዮቹ አለቁ፣ ሰውነቱ አለቀ ተላ በዚህ ምክንያት ከስፍራው ሊያስለቅቁት ሚስቱ እና ጓደኞቹ ብዙ ጣሩ ነገር ግን ኢዮብ እንዲህ አለ ኢዮብ 23:10-12 የምሄድበትን መንገድ ያውቃል፤ ከፈተነኝም በኋላ እንደ ወርቅ እወጣለው፤ እግሬ ወደ እርምጃው ተጣብቆአል፤ መንገዱንም ጠብቄአለሁ፥ ፈቀቅም አላልሁም፤ ከከንፈሩ ትእዛዝ አልተመለስሁም፤ የአፉን ቃል በልቤ ሰውሬአለሁ። ፨ ነገር ግን ይሄ ሁሉ መከራ ይሄ ሁሉ ጨለማ ኢዮብን ስፍራውን አላስለቀቀውም ፨ በመጨረሻም ዕንባቆም የእግዚያብሔርን ዝምታ በስፍራው ሆኖ የጠበቀውን አምላክ ሲረዳ እንዲህ አለ ዕንባ 3፡17-19 1ምንም እንኳ በለስም ባታፈራ፥በወይንም ሐረግ ፍሬ ባይገኝ፥የወይራ ሥራ ቢጐድል፥ እርሾችም መብልን ባይሰጡ፥በጎች ከበረቱ ቢጠፉ፥ላሞችም በጋጡ ውስጥ ባይገኙ፤ እኔ ግን በእግዚአብሔር ደስ ይለኛል፤በመድኃኒቴ አምላክ ሐሤት አደርጋለሁ፤ ጌታ እግዚአብሔር ኃይሌ ነው፤እግሮቼን እንደ ዋላ እግሮች ያደርጋል፤በከፍታዎችም ላይ ያስሄደኛል። ፨ የእግዚያብሔር ውዶች እኛም በየትኛውም አስቸጋሪ ሁኔታ እያለፍን ቢሆን እንኳ እግዚያብሔርን እንጠብቀው እርሱ አዋቂ ነው፣ያስብልና፣ይራራልናል፣ይረዳናል፣ይጠብቀናል ፨ እርሱን ዝምታውን መጠበቅ እንድንችል እርሱ ራሱ ይርዳን ዮሐንስ ዲላ

አሳፍ
፨ በዳዊት ንግስና ዘመን የአምልኮ መሪ የነበረ፣ የመዘመራን አለቃ፣ የመዝሙር ፀሐፊ፣ ትውልዱ ሁሉ በመዝሙር እና አምልኮ የሚታወቅ፣ ዕድመውን ሁሉ በእግዚያብሔር ቤት ያሳለፈ፣ ከመዝሙረ ዳዊት መጽሐፍ ውስጥ መዝ 50፣መዝ 73 እስከ መዝ 83 ያሉትን ምዕራፎች የፃፈ ሰው ነው ነው ፨ ነገር ግን የዛሬ ትኩረቴ ይሄ ዘማሪ በመዝሙር 73 ስለዘመረው መዝሙር ነው ፨ መዝሙር 73:-1-14 ስናነብ በዚህ ክፍል ላይ አሳፍ ቀንቼ ነበር ይላል     የቀናውም 💀 "የኃጢአተኞችን ሰላም አይቼ በዓመፀኞች ቀንቼ ነበርና። 💀 ለሞታቸው መጣጣር የለውምና፤ ኃይላቸውም ጠንካራ ነውና። 💀 እንደ ሰው በድካም አልሆኑም፥ ከሰው ጋርም አልተገረፉም። 💀  እንደ ሰው በድካም አልሆኑም፥ ከሰው ጋርም አልተገረፉም። 💀  ዓይናቸው ስብ ስለ ሆነ ወጣ፤ ልባቸውም ከምኞታቸው ይልቅ አገኘ። 💀  አስበው ክፉ ነገርን ተናገሩ ከፍ ከፍ ብለውም በዓመፃ ተናገሩ። 💀  እግዚአብሔር እንዴት ያውቃል? በልዑልስ ዘንድ በውኑ እውቀት አለ? ይላሉ። 💀  እነሆ፥ እነዚህ ኃጢአተኞች ይደሰታሉ፥ ሁልጊዜም ባለጠግነታቸውን ያበዛሉ። ፨ ወገኖቼ አሳፍ ይህን አይቶ ቀና መቅናት ብቻ አይደለም በእግዚያብሔር ማመኑ፣ በቤቱ ማገልገሉ ከንቱ እና ዋጋ ቢስ እንደሆነ አሰበ እንዲህም አለ           መዝ 73:13  " እንዲህም አልሁ። በውኑ ልቤን በከንቱ አጸደቅሁ፥ እጆቼንም በንጽሕና በከንቱ አጠብሁ።" ፨ በእግዚያብሔር ተስፍ ቆረጠ ልቡን ማጽደቁ ከንቱ እንደ ሆነ አሰበ ንጹ ሆኖ መገኘቱ ቆጨው እንደ ኋጥያተኞች መሆንን ተመኘ ፨ ወዳጆቼ እንዲህ ተሰምቷቹ አያቅም??? ፨ በተመሳሳይ በ ሚልክያስ መጽሐፎ ውስጥ ሕዝቡ በእግዚያብሔር ሲያማር እናያለን እንዲህ ይላል ሚል 3:-13-15 13፤ ቃላችሁ በእኔ ላይ ድፍረት ሆኖአል፥ ይላል እግዚአብሔር። እናንተ ግን። በአንተ ላይ ደፍረን የተናገርነው በምንድር ነው? ብላችኋል። 14፤ እናንተም። እግዚአብሔርን ማገልገል ከንቱ ነው፤ ትእዛዙንስ በመጠበቅ፥ በሠራዊት ጌታ በእግዚአብሔር ፊት ኀዘንተኞች ሆነን በመሄድ ምን ይረባናል? 15፤ አሁንም የሚታበዩትን ሰዎች ብፁዓን ብለን እንጠራቸዋለን፤ ክፉንም የሚሠሩ ጸንተዋል እግዚአብሔርንም ይፈታተናሉ፥ ያመልጣሉም ብላችኋል። ፨ በተጨማሪም ጰጥሮስ ኢየሱስን እንዲህ አለው ማቴ 19:- 27 " በዚያን ጊዜ ጴጥሮስ መልሶ። እነሆ፥ እኛ ሁሉን ትተን ተከተልንህ፤ እንኪያስ ምን እናገኝ ይሆን? አለው።" 💀 ኦ ወየሁልን! ማመናችን በእግዚያብሔር ተስፋ ማድረጋችን ለምን ይሁን?? 1ኛ  ቆሮ15:19 " በዚች ሕይወት ብቻ ክርስቶስን ተስፋ ያደረግን ከሆነ፥ ከሰው ሁሉ ይልቅ ምስኪኖች ነን።" ፨ ስለዚህ የእኛ ግብ ተስፋችን ማመናችን ለዚህ ምድር መሆን የለበትም ለዚህም ማቴዎስ ሲናገር ማቴ 16:26 " ሰው ዓለሙን ሁሉ ቢያተርፍ ነፍሱንም ቢያጐድል ምን ይጠቅመዋል? ወይስ ሰው ስለ ነፍሱ ቤዛ ምን ይሰጣል?" ፨ ለዚህም ነው እግዚያብሔርን መጠበቅ እርሱን መፈለግ ለከንቱ አይደለም ያይደለው ፨ አሳፍ ሲገባው እያሰበ የነበረው ሀሳብ ከንቱ እንደሆነ ሲረዳ እንዲህ አለ መዝ 73:17-28 17፤ ወደ እግዚአብሔር መቅደስ እስክገባ ድረስ፥ ፍጻሜአቸውንም እስካስተውል ድረስ። 18፤ በድጥ ስፍራ አስቀመጥኻቸው፥ ወደ ጥፋትም ጣልኻቸው። 19፤ እንዴት ለጥፋት ሆኑ! በድንገት አለቁ ስለ ኃጢአታቸውም ጠፉ። 20፤ ከሕልም እንደሚነቃ፥ አቤቱ፥ ስትነቃ ምልክታቸውን ታስነውራለህ። 21፤ ልቤ ነድዶአልና፥ ኵላሊቴም ቀልጦአልና፤ 22፤ እኔ የተናቅሁ ነኝ አላውቅሁምም፥ በአንተ ዘንድም እንደ እንስሳ ሆንሁ። 23፤ እኔ ግን ዘወትር ከአንተ ጋር ነኝ፥ ቀኝ እጄንም ያዝኸኝ። 24፤ በአንተ ምክር መራኸኝ፤ ከክብር ጋር ተቀበልኸኝ። 25፤ በሰማይ ያለኝ ምንድር ነው? በምድርስ ውስጥ ከአንተ ዘንድ ምን እሻለሁ? 26፤ የልቤ አምላክ ሆይ፥ ልቤና ሥጋዬ አለቀ፤ እግዚአብሔር ግን ለዘላለም እድል ፈንታዬ ነው። 27፤ እነሆ፥ ከአንተ የሚርቁ ይጠፋሉና ከአንተ ርቀው የሚያመነዝሩትንም ሁሉ አጠፋኻቸው። 28፤ ለእኔ ግን ወደ እግዚአብሔር መቅረብ ይሻለኛል፤ መታመኛዬም እግዚአብሔር ነው በጽዮን ልጅ በሮች ምስጋናህን ሁሉ እናገር ዘንድ። ፨ በሚልክያስም መጽሐፍ የገባቸው እግዚያብሔርን ያስተዋሉ እንዲህ አሉ ሚል 3:16 " የዚያን ጊዜ እግዚአብሔርን የሚፈሩ እርስ በእርሳቸው ተነጋገሩ፤ እግዚአብሔርም አደመጠ፥ ሰማም፥ እግዚአብሔርንም ለሚፈሩ ስሙንም ለሚያስቡ የመታሰቢያ መጽሐፍ በፊቱ ተጻፈ። " ፨የእግዚያብሔር ውዶች ምንም እንኳ በተመቻቼ ሁኔታ ውስጥ ባንገኝም፣ በብዙ ውጣወረድ እያለፍን ብንሆንም፣ ነገሮች እንዳሰብነው ባይሄዱም ፣ኋጥያትን ፈልገውና አቅደው የሚያደርጉ ለጊዜው የተመቻቼላቸው መስሎ ቢሰማንም ፣ የክርስትና ጉዞ ቢከብደንም ሁል ጊዜ በእግዚያብሔር ተስፋ ማድረጋችንን አንተው ከአገልግሎታችን አንሽሽ ልባችንን ከእርሱ አይራቅ ምክንያቱም እግዚያብሔር እያለፍን ያለውን ነገር ይረሳ ዘንድ ሰው አይደለም ዕብ 6:-10-12 10፤ እግዚአብሔር፥ ቅዱሳንን ስላገለገላችሁ እስከ አሁንም ስለምታገለግሉአቸው፥ ያደረጋችሁትን ሥራ ለስሙም ያሳያችሁትን ፍቅር ይረሳ ዘንድ ዓመፀኛ አይደለምና። 11-12፤ በእምነትና በትዕግሥትም የተስፋውን ቃል የሚወርሱትን እንድትመስሉ እንጂ ዳተኞች እንዳትሆኑ፥ ተስፋ እስኪሞላ ድረስ እያንዳንዳችሁ ያን ትጋት እስከ መጨረሻ እንድታሳዩ እንመኛለን። እግዚያብሔር ሁሌም በእርሱ ተስፋ ማድረግ እንዳንተው ይርዳን አሜን። ዮሐንስ ዲላ

አሳፍ
፨ በዳዊት ንግስና ዘመን የአምልኮ መሪ የነበረ፣ የመዘመራን አለቃ፣ የመዝሙር ፀሐፊ፣ ትውልዱ ሁሉ በመዝሙር እና አምልኮ የሚታወቅ፣ ዕድመውን ሁሉ በእግዚያብሔር ቤት ያሳለፈ፣ ከመዝሙረ ዳዊት መጽሐፍ ውስጥ መዝ 50፣መዝ 73 እስከ መዝ 83 ያሉትን ምዕራፎች የፃፈ ሰው ነው ነው ፨ ነገር ግን የዛሬ ትኩረቴ ይሄ ዘማሪ በመዝሙር 73 ስለዘመረው መዝሙር ነው ፨ መዝሙር 73:-1-14 ስናነብ በዚህ ክፍል ላይ አሳፍ ቀንቼ ነበር ይላል የቀናውም 💀 "የኃጢአተኞችን ሰላም አይቼ በዓመፀኞች ቀንቼ ነበርና። 💀 ለሞታቸው መጣጣር የለውምና፤ ኃይላቸውም ጠንካራ ነውና። 💀 እንደ ሰው በድካም አልሆኑም፥ ከሰው ጋርም አልተገረፉም። 💀 እንደ ሰው በድካም አልሆኑም፥ ከሰው ጋርም አልተገረፉም። 💀 ዓይናቸው ስብ ስለ ሆነ ወጣ፤ ልባቸውም ከምኞታቸው ይልቅ አገኘ። 💀 አስበው ክፉ ነገርን ተናገሩ ከፍ ከፍ ብለውም በዓመፃ ተናገሩ። 💀 እግዚአብሔር እንዴት ያውቃል? በልዑልስ ዘንድ በውኑ እውቀት አለ? ይላሉ። 💀 እነሆ፥ እነዚህ ኃጢአተኞች ይደሰታሉ፥ ሁልጊዜም ባለጠግነታቸውን ያበዛሉ። ፨ ወገኖቼ አሳፍ ይህን አይቶ ቀና መቅናት ብቻ አይደለም በእግዚያብሔር ማመኑ፣ በቤቱ ማገልገሉ ከንቱ እና ዋጋ ቢስ እንደሆነ አሰበ እንዲህም አለ መዝ 73:13  " እንዲህም አልሁ። በውኑ ልቤን በከንቱ አጸደቅሁ፥ እጆቼንም በንጽሕና በከንቱ አጠብሁ።" ፨ በእግዚያብሔር ተስፍ ቆረጠ ልቡን ማጽደቁ ከንቱ እንደ ሆነ አሰበ ንጹ ሆኖ መገኘቱ ቆጨው እንደ ኋጥያተኞች መሆንን ተመኘ ፨ ወዳጆቼ እንዲህ ተሰምቷቹ አያቅም??? ፨ በተመሳሳይ በ ሚሊ 3:-13-15

ማስታወቂያ 📢 🥮🧁ኩኩ ጣፋጭ ኩኪስና ዶናት KuKu Sweet Cookies and Donuts 🥮 ለቤትዎ ለርስዎና ለልጆችዎ 🍦 ለቤቢ ሻወር 🍰 ለልደት 🧈 ለግብዣ 🍩 ለሱፐርማርኬት 🍪 ለበዓ
+4
ማስታወቂያ 📢 🥮🧁ኩኩ ጣፋጭ ኩኪስና ዶናት KuKu Sweet Cookies and Donuts 🥮 ለቤትዎ ለርስዎና ለልጆችዎ 🍦 ለቤቢ ሻወር 🍰 ለልደት 🧈 ለግብዣ 🍩 ለሱፐርማርኬት 🍪 ለበዓልና ለተለያዩ ዝግጅቶች እናቀርባለን 👉🏻 የጣፋጭ ኬተሪንግ አገልግሎትም እንሰጣለን 💕 ኩኩ ጣፋጭ ኬክና ኩኪስ በእርግጥም ይለያል!! 🚐ይዘዙን ያሉበት እናደርሳለን!! አድራሻችን- 0911739995 ሀዋሳ

ይዋጣልን(እንተያይ)
💀 ዖዝያን እና አሜስያስ የተባሉትን (ልጅና አባት) የይሁዳ ንጉሶች ታሪክ ስትመረምሩ " ትዕቢት ውድቀትን ትቀድማለች ለምለው የመጽሐፍ ቅዱስ ቃል ሁነኛ ማሳያ ናቸው። እስኪ ታሪካቸውን በጨረፍታ እንይ 💀 ንጉስ አሜስያስ (2ተኛ ነገ 14,2ተኛ ዜና 25) ፨ ይሄ ንጉስ መንገስ ከጀመረ በኋላ በእግዚያብሔር ፊት ቅን ነገርን አደረገ። ፨ እግዚያብሔር መንግስቱን ስያፀናለት፣ ሲረዳው አባቱን የገደሉትን በመሉ ገደለ፣ በመቀጠል የጨው ሸለቆ በተባለ ቦታ 10,000 ኤዶማዊያንን ድል አደረገ ፨ በዚህ ድል የሰከረው ንጉስ አሜስያስ በትዕቢት እና በእብሪት ተሞልቶ ወደ ንጉስ ዮአስ እንዲህ ብሎ መልዕክተኞችን ላከ " ና እርስ በርሳችን ፊት ለፊት እንተያይ ብሎ ወደ እስራኤል ንጉሥ ወደ ኢዩ ልጅ ወደ ኢዮአካዝ ልጅ ወደ ዮአስ መልእክተኞችን ላከ። " ፨ የእስራኤልም ንጉስ ዮአስም እንዲህ ብሎ መለሰለት "ኤዶምያስን በእውነት መታህ፥ ልብህንም ከፍ ከፍ አደረግህ፤ በዚያ ተመካ፥ በቤትህም ተቀመጥ፤ አንተ ከይሁዳ ጋር ትወድቅ ዘንድ ስለ ምን መከራ ትሻለህ? ብሎ ወደ ይሁዳ ንጉሥ ወደ አሜስያስ ላከ።" ፨ ትዕቢተኛው አሜስያስ ግን አልሰማም በመጨረሻም ራሱ ቆስቁሶ ባነደደው የግጭት እሳት ወላፈን ሽንፈትን ተከናንቦ ህይወቱን አጣ( በራስ ትዕቢት ያለ እግዚያብሔር ምሪት ህይወቱን አጣ) 💀 ንጉስ ዖዝያን( 2ተኛ ዜና 26) ፨ ንጉስ አሜስያስ ከወደቀ በኋላ ልጁ ዖዝያን የእስራኤል ንጉስ ሆነ። ፨ የንግስናው ጅማሬ ላይ አባቱ አሜስያስ እንዳደረገው በእግዚያብሔር ፊት ቅን ነገር አደረገ ፨ እግዚያብሔርም በብዙ ነገር ድል ሰጠው ፨ ነገር ግን በበረታ ጊዜ ለጥፋት ልቡ ታበየ፥ አምላኩንም እግዚአብሔርን በደለ፤ ወደ መቅደስ ገብቶ በዕጣን መሠዊያ ላይ ዐጠነ። ፨ ንጉሡንም ዖዝያንን እየተቃወሙ። ዖዝያን ሆይ፥ ዕጣን ማጠን የተቀደሱት የአሮን ልጆች የካህናቱ ሹመት ነው እንጂ ለእግዚአብሔር ታጥን ዘንድ ለአንተ አይገባህም፤ በድለሃልና ከመቅደሱ ውጣ፤ ከአምላክህም ከእግዚአብሔር ዘንድ ክብር አይሆንልህም አሉት። " ፨ ዖዝያን ግን አሻፈረኝ አለ በትዕቢት ተሞልቶ በእግዚያብሔር ቤተመቅደስ ላይ ድፍረትን አደረገ ፨ በመጨረሻም በለምፅ በሽታ ተይዞ ሞተ ፨ የቀረውንም የፊተኛውንና የኋለኛውን የዖዝያንን ነገር ነቢዩ የአሞጽ ልጅ ኢሳይያስ ጽፎታል። " 2ተኛ ዜና 26:22 ፨ የሚገርማችሁ ነገር ኢሳያስ ስለ ዖዝያን የፃፈው የሚረባ ነገር የለውም በኋጥያት እና ትዕቢት ምክንያት እንደት ዋጋ እንደከፈለ ነው።(ኢሳ 1) ፨ ወገኖቼ የእግዚያብሔር ቃል ደጋግሞ ትዕቢት ለውርደት እና ጥፋት እንደሚዳርግ ሲናገር " ትዕቢት ከመጣች ውርደት ትመጣለች፤ በትሑታን ዘንድ ግን ጥበብ ትገኛለች። " (መጽሐፈ ምሳሌ 11:2) " እግዚአብሔር የትዕቢተኞች ቤት ይነቅላል፤ የባልቴትን ዳርቻ ግን ያጸናል። " (መጽሐፈ ምሳሌ 15:25) " ትዕቢት ጥፋትን፥ ኵሩ መንፈስም ውድቀትን ይቀድማል። " (መጽሐፈ ምሳሌ 16:18) " ሰው ሳይወድቅ በፊት ልቡ ከፍ ከፍ ይላል፥ ትሕትናም ክብረትን ትቀድማለች። " (መጽሐፈ ምሳሌ 18:12) " ሰውን ትዕቢቱ ያዋርደዋል፤ መንፈሱን የሚያዋርድ ግን ክብርን ይቀበላል። " (መጽሐፈ ምሳሌ 29:23) 💀 ስለዚህ የእግዚያብሔር ውዶች ትምክሕታችን የአምላካችን የእግዚያብሔር ስም ይሁን ፨ ስንት ጊዜ ይሁን ባለን እና በሆነልን ነገር ተማምነን የወደቅን ፨ ስንት ጊዜ ይሁን ተስፋ ባደረግናቸው ሰዎች ተስፋ የቆረጥነው ፨ ስንት ጊዜ ይሁን እግዚያብሔር ካቃናልን ነገሮችን ካሰመረልን በኋላ ወደ ትዕቢት ያደላን ፨ ስንት ጊዜ ይሁን የተደረገልንን ረስተን በራስ የተመካን ፨ ስለዚህ ቢደላንም ቢከፋንም መታመኛችን እርሱ ይሁን መዝ 146:-3-5 3፤ ማዳን በማይችሉ በሰው ልጆችና በአለቆች አትታመኑ። 4፤ ነፍሱ ትወጣለች ወደ መሬቱም ይመለሳል፤ ያን ጊዜ ምክሩ ሁሉ ይጠፋል። 5፤ የያዕቆብ አምላክ ረዳቱ የሆነ ተስፋውም በአምላኩ በእግዚአብሔር የሆነ ሰው ምስጉን ነው፤ ኤርምያስ 17:-5-8 5፤ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል። በሰው የሚታመን ሥጋ ለባሹንም ክንዱ የሚያደርግ ልቡም ከእግዚአብሔር የሚመለስ ሰው ርጉም ነው። 6፤ በምድረ በዳ እንዳለ ቍጥቋጦ ይሆናል፥ መልካምም በመጣ ጊዜ አያይም፤ ሰውም በሌለበት፥ ጨው ባለበት ምድር በምድረ በዳ በደርቅ ስፍራ ይቀመጣል። 7፤ በእግዚአብሔር የታመነ እምነቱም እግዚአብሔር የሆነ ሰው ቡሩክ ነው። 8፤ በውኃ አጠገብ እንደ ተተከለ፥ በወንዝም ዳር ሥሩን እንደሚዘረጋ ሙቀትም ሲመጣ እንደማይፈራ ቅጠሉም እንደሚለመልም፥ በድርቅ ዓመትም እንደማይሠጋ ፍሬውንም እንደማያቋርጥ ዛፍ ይሆናል። ፨ ወገኞቼ መታመኛችን አንድ ብቻ ነው እርሱም እግዚያብሔር ነው እንድንታመነው ሁላችንንም ይርዳን። ዮሐንስ ዲላ

ኢሳይያስ ምዕራፍ 41፡- 1-14 1፤ ደሴቶች ሆይ፥ በፊቴ ዝም በሉ፤ አሕዛብም ኃይላቸውን ያድሱ፤ ይቅረቡም በዚያን ጊዜም ይናገሩ፤ ለፍርድ ለአንድነት እንቅረብ። 2፤ ከምሥራቅ አንዱን ያስነሣ በጽድቅም ወደ እግሩ የተጠራው ማን ነው? አሕዛብንም አሳልፎ በፊቱ ሰጠው፥ ነገሥታትንም አስገዛለት፤ ለሰይፉ እንደ ትቢያ ለቀስቱም እንደ ተጠረገ እብቅ አድርጎ ሰጣቸው። 3፤ አሳደዳቸው፥ እግሮቹም አስቀድመው ባልሄዱባት መንገድ በደኅነት አለፈ። 4፤ ይህን የሠራና ያደረገ፥ ትውልድንም ከጥንት የጠራ ማን ነው? እኔ እግዚአብሔር፥ ፊተኛው በኋላኞችም ዘንድ የምኖር እኔ ነኝ። 5፤ ደሴቶች አይተው ፈሩ፥ የምድርም ዳርቾች ተንቀጠቀጡ፤ ቀረቡም ደረሱም። 6፤ ሁሉም እያንዳንዱ ባልንጀራውን ይረዳው ነበር፥ ወንድሙንም። አይዞህ ይለው ነበር። 7፤ አናጢውም አንጥረኛውን፥ በመዶሻም የሚያሳሳውን መስፍ መችውን አጽናና፥ ስለ ማጣበቅ ሥራውም። መልካም ነው አለ፤ እንዳይንቀሳቀስም በችንካር አጋጠመው። 8፤ ባሪያዬ እስራኤል፥ የመረጥሁህ ያዕቆብ፥ የወዳጄ የአብርሃም ዘር ሆይ፥ 9፤ አንተ ከምድር ዳርቻ የያዝሁህ ከማዕዘንዋም የጠራሁህና። አንተ ባሪያዬ ነህ፥ መርጬሃለሁ አልጥልህም ያልሁህ ሆይ፥ 10፤ እኔ ከአንተ ጋር ነኝና አትፍራ፤ እኔ አምላክህ ነኝና አትደንግጥ፤ አበረታሃለሁ፥ እረዳህማለሁ፥ በጽድቄም ቀኝ ደግፌ እይዝሃለሁ። 11፤ እነሆ የሚቆጡህ ሁሉ ያፍራሉ፥ ይዋረዱማል፤ የሚከራከሩህም እንዳልነበሩ ይሆናሉ፥ ይጠፉማል። 12፤ የሚያጣሉህንም ትሻቸዋለህ አታገኛቸውምም፥ የሚዋጉህም እንዳልነበሩና እንደ ምናምን ይሆናሉ። 13፤ እኔ አምላክህ እግዚአብሔር። አትፍራ፥ እረዳሃለሁ ብዬ ቀኝህን እይዛለሁና። 14፤ አንተ ትል ያዕቆብ የእስራኤልም ሰዎች ሆይ፥ አትፍሩ፤ እረዳሃለሁ፥ ይላል እግዚአብሔር፥ የሚቤዥህም የእስራኤል ቅዱስ ነው።

የተቀጠቀጠን ሸምበቆ አይሰብርም
" የተቀጠቀጠን ሸምበቆ አይሰብርም፥ የሚጤስንም ክር አያጠፋም። " ኢሳ 42:3 ሸምበቆ - በቀላሉ የሚሰበር ነገር ነው፣ የተቀጠቀጠ ሸምበቆ ደግሞ ምንም አይነት ጥንካሬ የሌለው ነገር ነው፣ የሚጤስ ክር ብዙም ርቀት የማያበራ ወዲያው ተቀጣጥሎ የሚጠፋ ነው። እስክ የተወሰኑ ታሪኮችን አብረን እንይ 1. የአመንዝራይቱ ታሪክ( ዮሐ 8:-1-11) ፨ ተስፋ የቆረጠች ፨ በምንዝር ወንጀል እጅ ከፍንጅ የተያዘች ፨ ከአሁን አሁን የድንጋይ ናዳ እንደሚወርድባት የሚትጠብቅ ፨ እራሷን እንደ ተቀጠቀጠ ሸንበቆ የቆጠረች 2. ጰጥሮስ ፨ ኢየሱስን በፍፁም እንደማይከዳው ደጋግሞ ስምልና ስገዘት የነበረ ፨ ከባዷ ሰዓት ስትመጣ ያን ሁሉ ረስቶ በገረድ ፊት የካደው ፨ በክህደቱ ምክንያት ኢየሱስን ለማየት ያቃተው በዚህም ምክንያት ተስፋ መቁረጥ ውስጥ የገባ ፨ ራሱን ተቀጣጥሎ እንደሚጠፋ ክር የቆጠረ ፨ በአደባባይ ከተገለጠው ደካማነቱ የተነሳ ኢየሱስ ከሞት በመነሳቱ ደስ ቢለውም ቀድሞ የቆመበትን ቦታ እንደማያገኝ ያመነ 3. ሽባው ሰውዬ( ዮሐ 5:-1-15) ፨ ከሠላሳ ስምንት ዓመት ጀምሮ የታመመ ፨ ኢየሱስ ልትድን ትወዳለህ ሲለው እንኳ ተስፋ በመቁረጥ "ጌታ ሆይ፥ ውኃው በተናወጠ ጊዜ በመጠመቂያይቱ ውስጥ የሚያኖረኝ ሰው የለኝም ነገር ግን እኔ ስመጣ ሳለሁ ሌላው ቀድሞኝ ይወርዳል ብሎ ተስፋ መቁረጡን ያወጀ ሰው ነበር 💀 ወገኖቼ የሰራነው ኋጥያት ስከብድብን ይህን እግዚያብሔር ይቅር አይለንም ብለን የምናስብ ብዙዎች ነን ፨ ነገር ግን ሁሉም ድንጋይ ስወረውሩባት ልያጠፏትና ታሪኳን በሞት ልቋጩ የተሰበሰቡ እና የተማማሉ ሰዎችን ዝም አሰኝቶ ልጠፋ የሚጤስን ክር እየበራ እንድቆይ የሚያረግ ተስፋ በሌለበት ተስፋን የሰጣት አምላክ ደረሰላት ፨ ታሪኳን ቀይሮ ተስፋ መቁረጧን አስወግዶ ኋጥያቷን ይቅር ብሎ ዳግም ኋጥያት አትስሪ ብሎ ሸኛት ፨ ተስፍ የቆረጠውን ጰጥሮስን በገረድ ፊት የካደውን ጰጥሮስን ከዚህ በኋላም ተስፋ የለኝም እንደ ቀድሞ ወደ እሱ አያስጠጋኝም ብሎ ያመነን ጰጥሮስን ይቅር ብሎ የሰው አጥማጅ የወንገል አርበኛ አረገው ፨ ሽባው ሰውዬ ለብዙ ጊዜያት ውኃው በተናወጠ ጊዜ በመጠመቂያይቱ ውስጥ የሚያኖረውን ሰው በማጣት ተስፍ የቆረጠ ፨ ነገር ግን ልትድን ትወዳለህ ብሎ ሰው ያላየውን በተስፋ መቁረጥ ውስጥ የነበረውን የተቀጠቀጠን ሸንበቆ የማያጠፍው ኢየሱስ ተነስተህ አልጋህን ተሸክመህ ሂድ አለው 💀 ውድ ወገኖቼ ምንም እንኳን ጌታን የሚያስደስት የመዓዛ ሽቶ ባንሸትም፣ በብዙ በተለማመድነው ኋጥያት ውስጥ ብንገኝም፣ በህይወት ውጣ ወረድ የታመምን የተቸገርን ሰው ያጣን ያልደላን ተስፋ የቆረጥኝ ቢንሆን ሁሌም የተቀጠቀጠን ሸምበቆ የማይሰብር፥ የሚጤስንም ክር የማያጠፋ በወደቅንበት ቦታ ትቶን የማይሄድ ታማኝ እና አዛኝ አምላክ አለን ስለዚህ ወደዚህ ጌታ እንቅረብ " ኃጢአተኞችን ሊያድን ክርስቶስ ኢየሱስ ወደ ዓለም መጣ የሚለው ቃል የታመነና ሁሉ እንዲቀበሉት የተገባ ነው፤ ከኃጢአተኞችም ዋና እኔ ነኝ፤" 1ኛ ጢሞ1:15 ፨ስለዚህ ተስፋን የሰጠ አምላክ የታመነ ነው በምን ሁኔታ ውስጥ ቢንሆንም እርሱ ካለንበት እንደሚያወጣን እንመን፣ አምላክ ለሁላችን እምነትን ይስጠን። ዮሐንስ ዲላ

የ2017 የፓዝፋይንደር ሰልጣኞች የክብር እንግዳው ማስተር ስዩም ዓለሙ በተገኙበት ዛሬ ተመርቀዋል!! እንኳን ደስ አላችሁ!

የቤተክርስቲያን ማስታወቂያ ጥቅምት 8,2018 1. የከተማ አቀፍ የእህቶች አገልግሎት አባል የሆናቸሁ ነገ ጥቅምት 9,2018 ከጧቱ 1:30 ጀምሮ ታቦር ሰባተኛ ቀን አድቬንቲስት ቤተክርስቲያን እንድትገኙ፣ 2. የወንዶች መረዳጃ ዕድር ስብሰባ ነገ ከቀኑ 7:30 የሚደረግ ስለሆነ አባላት እንድትገኙ ይሁን መልካም ሰንበት!

ጥቅምት 7,2018 መልካም ሰንበት የታቦር ሰባተኛ ቀን አድቬንቲስት ቤተክርስቲያን የነፀብራቅ የጎዳና ፈላጊዎች ቡድን የምስጋናና የምረቃ ፕሮግራም ነገ ጥቅምት 8,2018 በመደበኛ አምልኮ ፕሮግራም ሁ
+3
ጥቅምት 7,2018 መልካም ሰንበት የታቦር ሰባተኛ ቀን አድቬንቲስት ቤተክርስቲያን የነፀብራቅ የጎዳና ፈላጊዎች ቡድን የምስጋናና የምረቃ ፕሮግራም ነገ ጥቅምት 8,2018 በመደበኛ አምልኮ ፕሮግራም ሁላችሁም እንድትገኙ ተጋብዛችኋል አገልጋይ - ወ/ዊ ስዩም

ሀዘንተኛዋ ሴት
ይችህ ሴት እንደሌሎች ባል አግብታ ልጆች ወልዳ ከብራ ከብዳ መኖር የምትፈልግ ሴት ነበረች ነገር ግን ፨ የሀዘን ታሪክ ያላት ሴት ሆነች ፨ የመከራ ታሪክ ያላት ሴት ሆነች ፨ በብዙ ተስፋ መቁረጥ ውስጥ የተዘፈቀች ሴት ሆነች ፨ ቤቷን ትዳሯን አጽንታ የማትይዝ ሴት ሆነች ፨ ማንም ሰው ቦታ የማይሰጣት ክብር የማይሰጣት ሴት ሆነች ፨ ነገር ሁሉ የጨለመባት ሴት ሆነች ፨ የሕይወቷን ጥም ሊያረካ የቻለ አንድም ነገር ያላገኘች ተስፋ ቆርጣ ሰው በለሌበት ሰዓት በቀትር የምትወጣ ሴት ሆነች በዚህ ምክንያት ይችህ ሴት ውሀ በቀትር ትቀዳ ነበር ለምን በቀትር ሄደች?? ፨ በሰው ምክንያት ሀፍረት የሚሰማት ስለነበረች ፨ በብዙ ነገር የምትጨነቀች ስለነበረች ፨ በሰው መሳቂያና መጠቋቀሚያ ስለነበረች © ነገር ግን ከዚህ መከራና ሀፍረት መውጣት የምትፈልግ ሴት ስለነበረች በዛ በቀትር የሕይወት ውሃ ምንጭ የሆነው ኢየሱስን አገኘች። ታሪኩ ዮሐ 4::-4-29 ይገኛል ፨ ዛሬ የብዙዎቻችን ታሪክ የሀዘን ሰው ታሪክ ነው ሁላችንም በብዙ ነገር የተጨነቅን ሀፍረት የሚሰማን ማንም በማያየን በቀትር የምንወጣ ሰዎች ነን ፤ በጓዳችን ብዙ ነገር ደብቀን የምንኖር በኋጥያት ተዘፍቀን የምንኖር ሰዎች ነን። ፨ከዚህ ጭንቀት ለመውጣት ከኋጥያት እስር ለመውጣት እውነተኛ የሕይወት ውሃ ያላገኘን ሰዎች ነን ፨ በብዙ ነገር ሕይወት ተስፋ ያስቆረጠችን የምንይዘውን የምንጨብጠውን ነገር እስካይኖር ጨለማ የሸፈነን ሰዎች ነን ፨ ዛሬም ቢሆን ይህችን ተስፋ የቆረጠች ሀዘንተኛዋን ሳምራዊቷን ሴት ያገኛት አምላክ የሕይወት ውሃ የሰጣት አምላክ ለእኛም ይህን የሕይወት ውሃ ይስጠን ሁላችን በብዙ ነገር የተሰበርን ነን ፨ የተሰበረውን የሚያቀናው ፨ የዛለውን የሚያበረታው ፨ ያዘነውን የሚያበረታው ፨ ተስፋ ለቆሰጠ ተስፋ የሚሰጥ ፨ የተገፋውን የሚያስጠጋ ፨ ለጨለመበት የሚያበራ ፨ የተጣለውን የሚያነሳ ፨ የተራበውን የሚያበላ ፨ የታረዘውን የሚያለብስ ፨ መጠለያ ላጣ ከለላ የሚሆን ፨ የጠፋሁን የሚፈልግ ፨ የደከመውን የሚያጠነክር ፨ ኋጥያተኛውን የሚፈልግ ፨ ደካማውን የሚሸከም ፨ ለተጠማ የሕይወት ውሃ የሚሰጥ እርሱ አለ ኢየሱስ አለ እርሱን እንመነው ተስፋ እናድርገው ለዚህም ነው መዝ 34:- 10 " እግዚአብሔር ልባቸው ለተሰበረ ቅርብ ነው፥ መንፈሳቸው የተሰበረውንም ያድናቸዋል።" ኢሳ 42:-3 " የተቀጠቀጠን ሸምበቆ አይሰብርም፥ የሚጤስንም ክር አያጠፋም፤ በእውነት ፍርድን ያወጣል። " ስለዚህ ሁላችን ምንም እንኳ እግዚያብሔርን በብዙ ነገር ያሳዘንን ቢንሆንም፣ ሕይወት በብዙ መንገድ የፈተነችን ቢንሆንም፣ በብዙ ድብቅ ኋጥያት የተዘፈቅን ቢንሆን የተቀጠቀጠውን ሸንበቆ የማይሰብር የሚጤስንም ክር የማያጠፋ አምላክ ሁሌም ሊቀበለን ከወደቅንበት ሊያነሳን ኑ ይለናል ልክ እንደ ሳምራዊቷ ሴት ልባችንን ከፍተን ይሄን የሕይወት ውሃ የሚሰጠውን አምላክ ወደ ሕይወታችን እንጋብዘው። ሳምራዊቷን ያገኘ አምላክ ሁላችንንም ያግኘን አሜን!!! ዮሐንስ ዲላ

የሀዘን መግለጫ 😭
መስከረም 20, 2018 ዓ.ም የቤተክርስቲያናችን አባል የሆኑት ወ/ሮ ድንቅነሽ ሃ/ገብርኤል ዳቃቦ ከዚህ አለም ድካም አርፈዋል። ቤተክርስቲያናችን በእናታችን ሞት ጥልቅ ሀዘን የተሰማት መሆኗን እየገለፀች ለቤተሰቦቻቸው እና ለወዳጅ  ዘመዶቻቸው መጽናናትን ትመኛለች። የቀብር ሥነ ሥርዓት ዛሬ ማክሰኞ በ7፡00 ይፈፀማል። አድራሻ፡ ከሴንተራል ሆቴል ጎን

📣 Church Event Announcement 📣 🕊️ በእግዚአብሔር ፍቅር የተሞላ የበረከት ቀን ነው! 🕊️ በመስከረም 24, 2018 ዓ.ም. የ2018 ዓ.ም. የመጀመሪያው ቅዱስ ቁርባን በቤተ ክ
📣 Church Event Announcement 📣 🕊️ በእግዚአብሔር ፍቅር የተሞላ የበረከት ቀን ነው! 🕊️ በመስከረም 24, 2018 ዓ.ም. የ2018 ዓ.ም. የመጀመሪያው ቅዱስ ቁርባን በቤተ ክርስቲያናችን ይከናወናል። 🙏 በረከት የሞላው ዕድልን አትታለፉ፤ ተዘጋጅታችሁ የበረከቱ ተካፋይ ይሁኑ! 🙌

እግዚያብሔር ዝም ስል
፨ወገኖቼ ሕይወት የተሰመረ መስመር አይደለም፣በሕይወት የተለያዩ ወቅቶች አሉ። ለዚህም ሰለሞን በመጽሐፉ ሲናገር መክብብ 3:-1-8 ለሁሉ ዘመን አለው፥ ከሰማይ በታችም ለሆነ ነገር ሁሉ ጊዜ አለው፤ ለመወለድ ጊዜ አለው፥ ለመሞትም ጊዜ አለው፤ለመትከል ጊዜ አለው፥ የተተከለውንም ለመንቀል ጊዜ አለው፤ ለመግደል ጊዜ አለው፥ ለመፈወስም ጊዜ አለው፤ ለማፍረስ ጊዜ አለው፥ለመሥራትም ጊዜ አለው፤ ለማልቀስ ጊዜ አለው፥ ለመሳቅም ጊዜ አለው፤ ዋይ ለማለት ጊዜ አለው፥ ለመዝፈንም ጊዜ አለው፤ ድንጋይን ለመጣል ጊዜ አለው፥ ድንጋይንም ለመሰብሰብ ጊዜ አለው፤ ለመተቃቀፍ ጊዜ አለው፥ ከመተቃቀፍም ለመራቅ ጊዜ አለው፤ ለመፈለግ ጊዜ አለው፥ ለማጥፋትም ጊዜ አለው፤ ለመጠበቅ ጊዜአለው፥ለመጣልም ጊዜ አለው፤ ለመቅደድ ጊዜ አለው፥ ለመስፋትም ጊዜ አለው፤ ዝም ለማለት ጊዜ አለው፥ ለመናገርም ጊዜ አለው፤ለመውደድ ጊዜ አለው፥ ለመጥላትም ጊዜ አለው፤ ለጦርነት ጊዜ አለው፥ ለሰላምም ጊዜ አለው። ፨እኛ ሰዎች ለእነዚህ ነገሮች ሁሉ እንደሁኔታው ከጊዜው ጋር ነገሮቻችንን እናስማማለን፤ እንደዛው እኛ ክርስቲያኖች አስተሳሰባችንን ከእግዚያብሔር ጊዜ ጋር ማስማማት አለብን። እንዳለመታደል ሆኖ ሁላችን እግዚ/ር ስሰራ እኛ እንቀመጣለን እግዚ/ር ስቀመጥ(ዝም ስል) እኛ እንነሳለን። ፨ ለማይቀረው ወቅት እራሳችንን ማዘጋጀት አለብን(በእግዚ/ር ጊዜ) እግዚያብሔር ዝም ስል ፨ቀኑ አጭር ይሆንብናል፣ምሽቱ ደግሞ ረዥም፣ብቸኝነት ይሰማናል፣በልተን ይርበናል፣ጠጥተን ይጠማናል፣ተስፋ እንቆርጣለን፣መውጫ መግቢያ ይጠፋናል። ፨ዝም ያለን ሰው ሳይሆን የሕይወታችን ምንጭ የማንነታችን መሰረት የሆነ አምላክ ሲሆን ይጨንቃል ያንገበግባል ግራ ያጋባል በዚህም ምክንያት በነገሮቻችን ሁሉ ላይ ተስፋ እንቆርጣለን ሁሉ ነገር ያስጠላናል አልፎም በእግዚያብሔር ላይ እናማራለን፣በእግዚ/ር ላይ ተስፋ እንቆርጣለን፣የተወለድንበትን ቀን እንረግማለን። ፨ የሚገርመው ከዚህ በፊት መገኘቱ እርዳታው ቅርብ እንዳልነበር እስክንረሳ ድረስ፤ስንት ጊዜ የጥያቄዎቻችንን መልስ እንዳላገኘን እስክንረሳ ድረስ በዝምታው ተስፋ እንቆርጣለን። ፨ሁሉን ላንተ ትተን፣ካንተ ጋር ተጣብቀን፣አንተን እያገለገልን፣ዘወትር እየተጋን፣የእንጀራ ልጅ እስክንመስል ለምን ዝም አልክ? የታለህ? እንቅልፍ እስክናጣ የእግ/ር እጅ ከማዳን አላጠረችም ብለን አንተ ግን ለምን ዝም አልክ?? ፨ ወገኖቼ እዮብ እንዲህ አለ በተስፋ መቁረጥ ሆኖ ኢዮብ 23፦8-9 እነሆ፥ ወደ ፊት እሄዳለሁ፥ እርሱም የለም፤ ወደ ኋላም እሄዳለሁ፥ እኔም አላስተውለውም፤ ወደሚሠራበት ወደ ግራ ብሄድ አልመለከተውም፤ በቀኜም ይሰወራል፥ አላየውምም። ፨ ነቢዩ ዕንባቆምም በዙርያው ያለውን ነገር ባየ ጊዜ ግራ በመጋባት እና ተስፋ በመቁረጥ ውስጥ ሆኖ እግ/ር የታል አለ ዕንባቆም 1:-2-4 አቤቱ፥ እኔ ስጮኽ የማትሰማው እስከ መቼ ነው? ስለ ግፍ ወደ አንተ እጮኻለሁ፥ አንተም አታድንም። ፤ በደልንስ ስለ ምን አሳየኸኝ? ጠማምነትንስ ስለ ምን ትመለከታለህ? ጥፋትና ግፍ በፊቴ ነው፤ ጠብና ክርክር ይነሣሉ፤ ስለዚህ ሕግ ላልቶአል፥ ፍርድም ድል ነሥቶ አይወጣም፤ ኃጢአተኛ ጻድቅን ይከብባልና፤ ስለዚህ ፍርድ ጠማማ ሆኖ ይወጣል። ፨ ነገር ግን እዮብም ዕንባቆምም የእግዚያብሔርን ዝምታ ሲረዱ እንዲህ አሉ ኢዮብ 23፦10 የምሄድበትን መንገድ ያውቃል፤ከፈተነኝም በኋላ እንደ ወርቅ እወጣለሁ። ዕን 2:-20 " እግዚአብሔር ግን በተቀደሰ መቅደሱ አለ፤ ምድርም ሁሉ በፊቱ ዝም ትበል። ፨ እግዚያብሔር ዝም ስል የመጣል የመረሳት ጊዜ ሳይሆን የመሰራት ጊዜ ነው ፨ ዝምታው የዝግጅት ጊዜ ነው ፨ ዝምታው የመማረር ጊዜ ሳይሆን ለእግ/ር ሀሳብ የመማረክ ጊዜ ነው። ፨ወገኖቼ እግዚያብሔር ግን በተቀደሰው መቅደሱ አለ ምንም እንኳ የተመቻቼ ሁኔታ ውስጥ ባንገኝም፣ ነገሮች ባይመቹንም፣ የምናየው የምንሰማው ተስፋ የሚያስቆርጥ ቢሆንም፣ ወዳጅ ዘመድ ጓደኛ ቢሸሸንም፣ የምንይዘው የምንጨብጠው ቢጠፋ ፣ዝምታው ስዳስሰን ባይሰማንም እግ/ር ግን በተቀደሰው መቅደሱ አለ ያየናል፣ይራራልናል፣ይሰማናል። ስለዚህ ልክ እንደ ዕንባቆም የእግዚያብሔር ዝምታው ሲገባን ይህን ልናውጅ ይገባል ዕንባቆም 3፦17-19 ምንም እንኳ በለስም ባታፈራ፥በወይንም ሐረግ ፍሬ ባይገኝ፥የወይራ ሥራ ቢጐድል፥ እርሾችም መብልን ባይሰጡ፥በጎች ከበረቱ ቢጠፉ፥ላሞችም በጋጡ ውስጥ ባይገኙ፥እኔ ግን በእግዚአብሔር ደስ ይለኛል፤በመድኃኒቴ አምላክ ሐሤት አደርጋለሁ፤ ጌታ እግዚአብሔር ኃይሌ ነው፤እግሮቼን እንደ ዋላ እግሮች ያደርጋል፤በከፍታዎችም ላይ ያስሄደኛል። አባቴ ሆይ ዝምታህን እንድንረዳ፣ ሁለም በተቀደሰ መቅደስህ እንዳለክ እንዲሰማን፣እንደ ዕንባቆም በመጠበቂያዬ ላይ እቆማለሁ፥ በአምባ ላይም እወጣለሁ፤ የሚናገረኝንም፥ ስለ ክርክሬም የምመልሰውን አውቅ ዘንድ እመለከታለሁ። "(ዕንባ 2:-1) እንድንል እርዳን አሜን።

Dear My beloved SDA Church fellows, As we celebrate the arrival of the 2018 Ethiopian New Year, I want to share a heartfelt wish for each of you. May this New Year bring you success and fruit in all dimensions of life. Reflecting on the words of (Isaiah 43:19) "See, I am doing a new thing! Now it springs up; do you not perceive it? I am making a way in the wilderness and streams in the wasteland." This verse reminds us that God is always at work, bringing renewal and hope into our lives. May you embrace the new beginnings this year offers, and may God bless you with love, joy, and prosperity. Wishing you a blessed and fulfilling New Year!