en
Feedback
የሀዋሳ ታቦር ሰባተኛ ቀን አድቬንቲስት አለም አቀፍ ቤተክርስቲያን (Hawassa Tabour 7th day Adventist INternational Church

የሀዋሳ ታቦር ሰባተኛ ቀን አድቬንቲስት አለም አቀፍ ቤተክርስቲያን (Hawassa Tabour 7th day Adventist INternational Church

Open in Telegram

እግዚአብሄርን ለመገናኘት ተዘጋጅ

Show more
1 071
Subscribers
+224 hours
+167 days
+3930 days
Posts Archive
በጌታ የተወደዳችሁ ቤተሰብ ሰላም ለእናንተ ይሁን! በጌታ ጸጋ ዛሬ የተለቀቀች ሁለተኛ መጽሐፌን ሳጋራችሁ እጅግ ደስ ይለኛል። ርዕስዋ “ወደ ልቡም ተመልሶ” ይሰኛል። ምናልባት የመጀመሪያዋን አጋፔን - አሁን ላይ የታተመችዋ ገበያ ላይ ስለሌለች - እስካሁን ካላገኛችኋት በሚል እርስዋንም አንድ ላይ በዚህ መልዕክት አጋርቻችኋለሁ። በማንበብ እና በነጻም ለብዙዎች በማዳረስ አብረን እንደምናገለግል ተስፋ አደርጋለሁ! ተባረኩ ወንድማችሁ አትክልት ኢሳይያስ

መርዶ
ቀን 18/3/18 የቤ/ያን አባል የሆኑት አቶ ለገሠ ለምቤቦ እና ወ/ሮ ታገሠች ለምቤቦ እህታቸውን አስቀብረው ትላንት ተመልሰዋል፣ ስለዚህ ምዕመናን ቤተሰቦቻቸውንና ወዳጅ ዘመዶቻቸውን እንድታጽናኑ እያሳሰብን ቤተክርስቲያናችን ለምዕመኑ፣ለቤተሰቦቻቸው እና ወዳጅ ዘመዶቻቸው መጽናናትን ትመኛለች!! አድራሻ:- የታቦር ክ/ከ ማዘጋጃ አጠገብ (ከአድቬንቲስት ት/ቤት ከፍ ብሎ) አቶ ለገሰ ላምቤቦ 0916024311

የቀብር ስነ ስርዓት ዛሬ ሀሙስ ህዳር 11/2018 ዓ.ም ከ10፡00 ጀምሮ ይፈፀማል በመሆኑም የቤተክርስቲያናችን አባላት በሙሉ እንድትገኙ ቤተ ክርስቲያን ታሳስባለች። እግዚአብሔር ለቤተሰብ ለወዳጅ ዘመዶች ሁሉ መጽናናትን እንዲሰጣቸው ቤተ ክርስቲያን ትመኛለች። አድራሻ፡ ከጤና ቢሮ ፊት ለፊት መኖሪያ ቤት

የሀዘን መግለጫ
ህዳር 11/2018 ዓ.ም የቤተ ክርስቲያናችን አባል እና የቤተክርስቲያንቱ የፅዳት ክፍል ሠራተኛ የሆኑት  ወ/ሮ አስቴር ሌንዳዶ ከዚህ አለም ድካም አርፈዋል ቤተክርስቲያናችን በሞታቸው የተሰማትን ሀዘን እየገለፀች ሁላችንን ሀዘን ቦታ በመገኘት እንድናፅናና ቤተክርስቲያን ታሳስባለች!!! አድራሻ:- ጤና ቢሮ ፊትለፊት አስፓልት ላይ ማሳሰቢያ፤ የቀብሩን ሁኔታ አጣርተን የምንገልፅ ይሆናል።

💀 ስለዚህ ውድ የእግዚያብሔር ልጆች ዛሬ እኛን የደረቅን አጥንቶችን ሕይወት ሊዘራብን ስጋ ሊያለብሰን ወደ እርሱ ኑ ይለናል ፣ከክፉ ስራችን እንመለስ የሕይወት ምንጭ የሆነውን አምላክ እንቅረበው፣በራሳችንን ጥረት ምንም ማድረግ አንችል ፤እንታጠብ ሰውነታችንን እናንጻ ፤ የሥራችንን ክፋት ከእግዚያብሔር ፊት እናስወግዱ፤ ክፉ ማድረግን እንተዉ፥መልካም መሥራትን እንማር፥ ፍርድን እንፈልግ፥ የተገፋውን እናድን፥ ለድሀ አደጉ እንፍረድለት ስለ መበለቲቱም እንሟገት፤እሺ እንበል ለእርሱም እንታዘዝ። 💀 እግዚያብሔር ከሄድንበት ክፉ መንገድ ሰብስቦ ሊያመጣን የታመነ አምላክ ነው ብቻ ልባችንን ለዚህ አምላክ እንስጥ ወደ ምንጩ እንቅረብ ሕዝ 37፦21-29 21፤ አንተም እንዲህ ትላቸዋለህ። ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል። እነሆ፥ የእስራኤልን ልጆች ከሄዱባቸው ከአሕዛብ መካከል እወስዳለሁ ከስፍራም ሁሉ እሰበስባቸዋለሁ ወደ ገዛ ምድራቸውም አመጣቸዋለሁ፤ 22፤ በምድርም ላይ በእስራኤል ተራሮች ላይ አንድ ሕዝብ አደርጋቸዋለሁ፥ አንድ ንጉሥም በሁላቸው ላይ ይነግሣል፤ ከዚያ ወዲያ ሁለት ሕዝብ አይሆኑም፥ ከዚያ ወዲያም ሁለት መንግሥቶች ሆነው አይለዩም። 23፤ ከዚያ ወዲያም በጣዖቶቻቸውና በርኵሰታቸው በመተላለፋቸውም ሁሉ አይረክሱም፥ ኃጢአትም ከሠሩባት ዓመፅ ሁሉ አድናቸዋለሁ አነጻቸውማለሁ፤ ሕዝብም ይሆኑኛል እኔም አምላክ እሆናቸዋለሁ። 24፤ ባሪያዬም ዳዊት ንጉሥ ይሆናቸዋል፤ ለሁሉም አንድ እረኛ ይሆንላቸዋል፤ በፍርዴም ይሄዳሉ ትእዛዜንም ይጠብቃሉ ያደርጓትማል። 25፤ አባቶቻችሁም በኖሩበት ለባሪያዬ ለያዕቆብ በሰጠኋት ምድር ይኖራሉ፤ እነርሱና ልጆቻቸው የልጅ ልጆቻቸውም ለዘላለም ይኖሩባታል፤ ባሪያዬም ዳዊት ለዘላለም አለቃ ይሆናቸዋል። 26፤ የሰላምም ቃል ኪዳን ከእነርሱ ጋር አደርጋለሁ፥ የዘላለምም ቃል ኪዳን ይሆንላቸዋል፤ እኔም እባርካቸዋለሁ አበዛቸውማለሁ መቅደሴንም ለዘላለም በመካከላቸው አኖራለሁ። 27፤ ማደሪያዬም በላያቸው ላይ ይሆናል፤ እኔም አምላክ እሆናቸዋለሁ እነርሱም ሕዝብ ይሆኑኛል። " መቅደሴም ለዘላለም በመካከላቸው በሆነ ጊዜ፥ እኔ እስራኤልን የምቀድሰው እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ አሕዛብ ያውቃሉ። አሜን ዮሐንስ ዲላ ( ህዳር 05/2018 ዓ.ም)

በእኔ ኑሩ
" እኔ የወይን ግንድ ነኝ እናንተም ቅርንጫፎች ናችሁ። ያለ እኔ ምንም ልታደርጉ አትችሉምና በእኔ የሚኖር እኔም በእርሱ፥ እርሱ ብዙ ፍሬ ያፈራል።" ዮሐ 15:5 ወገኖቼ ከምንጩ ተለይተን የት እየኖርን ይሁን??? ፨ ያለ ምንጩ መኖር ከባድ ነው ፨ ሁላችንም ዛሬ ግን ከዚህ ምንጭ ተለይተን እየተቅበዘበዝን እንገኛለን ፨ አሳቤ እንደ አሳባችሁ መንገዳችሁም እንደ መንገዴ አይደለምና ይላል እግዚአብሔር፤ ሰማይ ከምድር ከፍ እንደሚል፥ እንዲሁ መንገዴ ከመንገዳችሁ አሳቤም ከአሳባችሁ ከፍ ያለ ነው። ኢሳ 55፦ 8-9 ታዲያ ይሄ ሕዝብ ርቆ የት ነው የሄደው??? ፨ ሁላችን ይጠቅመናል ይበጀናል ባልነው በአለም መንገድ እየሄድን ነው ፨ ስጋችንን ለማስደሰት ከእግዚያብሔር ሀሳብ ወተን በገዛ ምኞታችን በአለም እየተቅበዘበዝን ነዉ " እኛ ሁላችን እንደ በጎች ተቅበዝብዘን ጠፋን፤ ከእኛ እያንዳንዱ ወደ ገዛ መንገዱ አዘነበለ። ኢሳ 53:6 ነቢዩ ኤርሚያስ ሕዝቡ ምን ያህል ከእግዚያብሔር እንደራቀ በምዕራፍ 24 ስናገር ፨ አባቶቻችሁ ከእኔ ዘንድ የራቁ፥ ከንቱነትንም የተከተሉ፥ ከንቱም የሆኑ ምን ክፋት አግኝተውብኝ ነው? ፨ ከግብጽ ምድር ያወጣን፥ በምድረ በዳም በባድማ ጒድጓድም ባለበት ምድር፥ በውኃ ጥምና በሞት ጥላ ምድር፥ ማንም በማያልፍበትና ማንም በማይቀመጥበት ምድር የመራን እግዚአብሔር ወዴት አለ? ይላል ፨ ፍሬዋንና በረከትዋንም ትበሉ ዘንድ ወደ ፍሬያማ ምድር አገባኋችሁ፤ ነገር ግን በገባችሁ ጊዜ ምድሬን አረከሳችሁ፥ ርስቴንም አጐሳቈላችሁ። ፨ በውኑ አማልክት ያልሆኑትን አማልክቱን የለወጣቸው አንድ ሕዝብ አለን? ነገር ግን ሕዝቤ ክብሩን ለማይረባ ነገር ለወጠ። ፨ ሕዝቤ ሁለቱን ክፉ ነገሮች አድርገዋልና፤ እኔን የሕያውን ውኃ ምንጭ ትተውኛል፥ የተቀደዱትንም ጒድጓዶች፥ ውኃውን ይይዙ ዘንድ የማይችሉትን ጒድጓዶች፥ ለራሳቸው ቆፍረዋል። ፨ የሜምፎስና የጣፍናስ ልጆች አስነወሩሽ አላገጡብሽም። ፨ ይህ ሁሉ የሆነብሽ እኔን ስለ ተውሽ አይደለምን? ይላል እግዚአብሔር አምላክሽ። ፨ እኔ የተመረጠች ወይን ፍጹምም እውነተኛ ዘር አድርጌ ተክዬሽ ነበር፤ አንቺ ግን ክፉ የእንግዳ ወይን ግንድ ሆነሽ እንዴት ተለወጥሽብኝ? ፨ በእንዶድ ብትታጠቢም፥ ለራስሽም ሳሙና ብታበዢ፥ በእኔ ፊት በኃጢአትሽ ረክሰሻል ይላል ጌታ እግዚአብሔር። ፨ አንቺስ። አልረከስሁም በአሊምንም አልተከተልሁም እንዴት ትያለሽ? በቈላ ያለውን መንገድሽን ተመልከቺ፥ ያደረግሽውንም እወቂ፤ በመንገድም ላይ እንደ ተለቀቀች እንደ ፈጣን ግመል ሆነሻል። ፨ ግንዱን።አንተ አባቴ ነህ፤ ድንጋዮንም። አንተ ወለድኸኝ ይላሉ፤ ፊታቸውንም ሳይሆን ጀርባቸውን ሰጡኝ፥ በመከራቸው ጊዜ ግን። ተነሥተህ አድነን ይላሉ። ፨ በውኑ ቆንጆ ጌጥዋን ወይስ ሙሽራ ዝርግፍ ጌጥዋን ትረሳለችን? ሕዝቤ ግን የማይቈጠር ወራት ረስቶኛል። 💀 ወገኖቼ ዛሬ የእያንዳዳችን ሕይወት ቢመዘን ከዚህ የተለየ አይደለም፤ በእግዚያብሔር ቤት ሆነን ቤቱን ያረከስን ከምንጩ የተለየን ነን፤የቆምን የሚመስለን ነገር ግን የወደቅን ነን፣ አለምን እና ምኞቷን የሚናሳድድ ነን፣ እላያችን በበግ ለምድ የተሸፈ ውስጣችን ግን ነጣቂ ተኩላዎች ነን፣እላያችን በሚያምር ቀለም የተዋበ ውስጣችን ግን የተለሰነ መቃብር ነን፣ ሀሳባችን ከሀሳቡ የራቀ በዚህች ጊዜያዊ ምድር ጠዋት ታይቶ ከሰዓት እንደሚጠፋ ጠዛዎች ነን። ፨ ወገኖቼ እናስተውል ወደ ምንጩ እንቅረብ ፨ ምንም እንኳ ከእርሱ የራቅን ቢሆን እንኳ አሁንም ወደ እኔ ኑ ይለናል በእኔ ኑሩ ይለናል ፨ ምንም ያህል ኋጥያተኞች ቢንሆን እንኳ፣በቤቱ እየኖርን በብዙ ያሻገረንን አምላክ የካድን ቢሆን እንኳ፣ በማስመሰል ሕይወት አለምን እና ጣኦቷን እያመክን ቢሆን እንኳ ኑ ይለናል እግዚያብሔር " ኑና እንዋቀስ ይላል እግዚአብሔር፤ ኃጢአታችሁ እንደ አለላ ብትሆን እንደ አመዳይ ትነጻለች፤ እንደ ደምም ብትቀላ እንደ ባዘቶ ትጠራለች። " ኢሳ 1:18 💀 የእግዚያብሔር ቃልኪዳን እስራኤል ለመታደግ ( የደረቁ አጥንቶችን ወደ ሕይወት ለመመለስ) በባህሪያው ሕዝቀል አማካኝነት ( ሕዝ ምዕራፍ 37 ላይ ) እግዚያብሔር መልዕክት ስሰጠው እናያለን በዚህ ምዕራፍ 37 ላይ ስናገር 1፤ የእግዚአብሔርም እጅ በላዬ ነበረ እግዚአብሔርም በመንፈሱ አወጣኝ አጥንቶችም በሞሉባት ሸለቆ መካከል አኖረኝ። 2፤ በእነርሱም አንጻር በዙሪያቸው አሳለፈኝ፤ እነሆም፥ በሸለቆው ፊት እጅግ ብዙ ነበሩ፥ እነሆም፥ እጅግ ደርቀው ነበር። 3፤ እርሱም። የሰው ልጅ ሆይ፥ እነዚህ አጥንቶች በሕይወት ይኖራሉን? አለኝ። እኔም። ጌታ እግዚአብሔር ሆይ፥ አንተ ታውቃለህ አልሁ። 4፤ እርሱም እንዲህ አለኝ። በእነዚህ አጥንቶች ላይ ትንቢት ተናገር እንዲህም በላቸው። እናንተ የደረቃችሁ አጥንቶች ሆይ፥ የእግዚአብሔርን ቃል ሰሙ። 5፤ ጌታ እግዚአብሔር ለእነዚህ አጥንቶች እንዲህ ይላል። እነሆ፥ ትንፋሽን አገባባችኋለሁ በሕይወትም ትኖራላችሁ። 6፤ ጅማትም እሰጣችኋለሁ ሥጋንም አወጣባችኋለሁ በእናንተም ላይ ቁርበትን እዘረጋለሁ ትንፋሽንም አገባባችኋለሁ በሕይወትም ትኖራላችሁ፤ እኔም እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ታውቃላችሁ። 7፤ እንዳዘዘኝም ትንቢት ተናገርሁ፤ ስናገርም ድምፅ ሆነ፥ እነሆም፥ መናወጥ ሆነ፥ አጥንቶችም አጥንት ከአጥንት ጋር ተቀራረቡ። 8፤ እኔም አየሁ፥ እነሆም፥ ጅማት ነበረባቸው ሥጋም ወጣ ቁርበትም በላያቸው ተዘረጋ፥ ትንፋሽ ግን አልነበረባቸውም። 9፤ እርሱም። የሰው ልጅ ሆይ፥ ትንቢት ተናገር፥ ለነፋስ ትንቢት ተናገር፥ ለነፋስም። ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል። ነፋስ ሆይ፥ ከአራቱ ነፋሳት ዘንድ ና፥ እነዚህም የተገደሉት በሕይወት ይኖሩ ዘንድ እፍ በልባቸው በል አለኝ። 10፤ እንዳዘዘኝም ትንቢት ተናገርሁ፥ ትንፋሽም ገባባቸው ሕያዋንም ሆኑ፥ እጅግም ታላቅ ሠራዊት ሆነው በእግራቸው ቆሙ። 11፤ እርሱም እንዲህ አለኝ። የሰው ልጅ ሆይ፥ እነዚህ አጥንቶች የእስራኤል ቤት ሁሉ ናቸው፤ እነሆ። አጥንቶቻችን ደርቀዋል ተስፋችንም ጠፍቶአል ፈጽመንም ተቈርጠናል ብለዋል። 12፤ ስለዚህ ትንቢት ተናገር እንዲህም በላቸው። ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል። ሕዝቤ ሆይ፥ እነሆ፥ መቃብራችሁን እከፍታለሁ ከመቃብራችሁም አወጣችኋለሁ፥ ወደ እስራኤልም ምድር አገባችኋለሁ። 13፤ ሕዝቤ ሆይ፥ መቃብራችሁን በከፈትሁ ጊዜ ከመቃብራችሁም ባወጣኋችሁ ጊዜ፥ እኔ እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ታውቃላችሁ። 14፤ መንፈሴንም በውስጣችሁ አሳድራለሁ፥ እናንተም በሕይወት ትኖራላችሁ፥ በገዛ ምድራችሁም አኖራችኋለሁ፤ እኔም እግዚአብሔር እንደ ተናገርሁ እንዳደረግሁም ታውቃላችሁ፥ ይላል እግዚአብሔር። ዛሬም እኛም እንደ እስራኤላዊያን የደረቅን አጥንቶች ነን

አማኞቹ
ሉቃ 18፦9-13 ጻድቃን እንደ ሆኑ በራሳቸው ለሚታመኑና ሌሎቹን ሁሉ በጣም ለሚንቁ ይህን ምሳሌ ነገራቸው፤ እንዲህ ሲል። ሁለት ሰዎች ሊጸልዩ ወደ መቅደስ ወጡ፥ አንዱ ፈሪሳዊ ሁለተኛውም ቀራጭ። ፤ ፈሪሳዊም ቆሞ በልቡ ይህን ሲጸልይ። እግዚአብሔር ሆይ፥ እንደ ሌላ ሰው ሁሉ፥ ቀማኞችና ዓመፀኞች አመንዝሮችም፥ ወይም እንደዚህ ቀራጭ ስላልሆንሁ አመሰግንሃለሁ፤ በየሳምንቱ ሁለት ጊዜ እጦማለሁ፥ ከማገኘውም ሁሉ አሥራት አወጣለሁ አለ። ቀራጩ ግን በሩቅ ቆሞ ዓይኖቹን ወደ ሰማይ ሊያነሣ እንኳ አልወደደም፥ ነገር ግን። አምላክ ሆይ፥ እኔን ኃጢአተኛውን ማረኝ እያለ ደረቱን ይደቃ ነበር። ፨ ፈሪሳዊው ራሱን እንደ ፃዲቅ የሚቆጥር፣ ሌሎችን በንቀት ዐይን የሚመለከት፣ ወደ ቤተ መቅደስ የሚመጣው ኋጥያተኛ መሆኑ ተሰምቶት ሳይሆን የአድናቆት ሽልማቱን ተስፋ በማድረግ ነው፣ ሌሎች ክርስቲያኖች ስለ እርሱ ኋይማኖኝነት እንድያወሩ የሚፈልግ፣ የሌሎችን ኋጥያት ከእርሱ ጽድቅ ጋር የሚያነፃፅር፣ በሰውም በእግዚያብሔርም ፊት ሞገስን ለማግኘት የሚጣጣር ውጭያዊ ታይታ ላይ ብቻ ትኩረት የሚያደርግ፣ ሌሎች ሰዎች የእግዚያብሔር ሕግ ተላላፊዎች እንደሆኑ የሚያውጅ፣ ሌሎችን የሚለካው በራሱ መስፈርት ነው ፨ ነገር ግን ቀራጩ ራሱን ከሌሎች ያላነፃፀረ ፣ በህሊና ወቀሳ ውስጥ ተውጦ በእግዚያብሔር ፊት ብቻሁን የቆመ፣ ምኞቱ ይቅርታና ምህረት ማግኘት ብቻ የሆነ፣ ኋጥያተኛ መሆኑ የገባው። ፨ ታሪኩን ስንመለከተው ከእግዚያብሔር ቀራጩ ምህረት አግኝቶ ሄደ 💀 ዛሬ እኛ ከየትኞቹ አማኞች ውስጥ እንሆን ይሁን?? ፨ መጽሐፍ ቅዱስ ላይ የሐዋርያው ጳውሎስ የአገልግሎት ታሪክ ስንመለከት አገልግሎት የጀመረ ጊዜ በራሱ የሚመካ፣ ክርስቶስ በክህደት ተላልፎ ከመሰጠቱ አስቀድሞ ኢየሱስ ለደቀመዛሙርቱ ሁላችሁም ትክዱኛላችሁ ብሎ በተናገረበት ወቅት ጰጥሮስ በልበ ሙሉነት ሌሎች ሁሉ ቢሰናከሉ እንኳ እኔ አላደርገውም ብሎ ነበር ፨ ነገር ግን በራስ መተማመኑ መኩራቱ በተሳሳተ መንገድ መራው ፣ በራሱ ፈተናን የሚቋቋም መሰለው ነገር ግን በአጭር ጊዜ ውስጥ ፈተናውን ወደቀ 3ት ጊዜ ካደው " ኢየሱስም። እውነት እልሃለሁ፥ ዛሬ በዚች ሌሊት ዶሮ ሁለት ጊዜ ሳይጮኽ ሦስት ጊዜ ትክደኛለህ አለው።" የማር 14:30 ፨ ዶሮ ስጮህ የክርስቶስ ቃላቶች ትዝ አለው ያ ሁላ መታበዩ መኩራራቱ በራስ መተማመኑ ክርስቶስን ከመካድ አላዳነውም ፨ ጰጥሮስ እንደቀራጩ ገባው የት እንደነበረ ማን እንደሆነ አስተዋለ ንስሀ ገባ አለቀስ ምህረትም አገኘ፣ ነገሮችን በአድስ የሚጀምርበት ነጥብ ላይ ደረሰ ፨ ከዛ በኋላ ራስ መተማመኑ መኩራራቱ ከእርሱ ስለተለየ የድሮ ጉረኝነቱ ላይመለሰ ከሕይወቱ ተለየ ፨ ከትንሳኤ በኋላ ክርስቶስ ጰጥሮስን 3ት ጊዜ ፈተነው ነገር ግን በዚህ ጊዜ ያ የድሮ ማንነቱ ስለተለየው ፈተናውን በድል ተሻገረ ዮሐ 21፦ 15-17 15፤ ምሳ ከበሉ በኋላም ኢየሱስ ስምዖን ጴጥሮስን። የዮና ልጅ ስምዖን ሆይ፥ ከእነዚህ ይልቅ ትወደኛለህን? አለው። አዎን ጌታ ሆይ፥ እንድወድህ አንተ ታውቃለህ አለው። ግልገሎቼን አሰማራ አለው። 16፤ ደግሞ ሁለተኛ። የዮና ልጅ ስምዖን ሆይ፥ ትወደኛለህን? አለው። አዎን ጌታ ሆይ፥ እንድወድህ አንተ ታውቃለህ አለው። 17፤ ጠቦቶቼን ጠብቅ አለው። ሦስተኛ ጊዜ። የዮና ልጅ ስምዖን ሆይ፥ ትወደኛለህን? አለው። ሦስተኛ። ትወደኛለህን? ስላለው ጴጥሮስ አዘነና። ጌታ ሆይ፥ አንተ ሁሉን ታውቃለህ፤ እንድወድህ አንተ ታውቃለህ አለው። ኢየሱስም። በጎቼን አሰማራ። ፨ ጉረኛ የነበረ ከዚህ ቀደም እራሱንና ደቀመዝሙርን ያዋረደ ችኩል የነበረን ራሱን ለሀያሉ ጌታ ስሰጥ መልሶ ሰው አረገው ለወጠው እውነተኛ አማኝ አረገው ፨ ጰጥሮስ በሕይወቱ በራሱ መታመን ጉራ በሰይጣን በብዙ እየተፈተነ የነበረን ጌታ ግን ከለለው ልቡን ስለከፈተ ዳግም ሕይወት ዘራበት ሉቃ 22፦ 31-32 ጌታም። ስምዖን ስምዖን ሆይ፥ እነሆ፥ ሰይጣን እንደ ስንዴ ሊያበጥራችሁ ለመነ፤ እኔ ግን እምነትህ እንዳይጠፋ ስለ አንተ አማለድሁ፤ አንተም በተመለስህ ጊዜ ወንድሞችህን አጽና አለ። ፨ ስለዚህ የእግዚያብሔር ውዶች ልክ እንደ ቀራጩ ማንነታችን እጅግ ኋጥያተኛ መሆናችንን ማወቅ ያስፈልገናል ለደከመው ብርታትን የሚሰጠውን መተማመን ያስፈልገናል ያ የፈሪሳዊ አማኝ ባህሪን ከማንነታችን እንድያስወግድልን ዘወትር መፀለይ ያስፈልገናል " ለደካማ ኃይልን ይሰጣል፥ ጕልበት ለሌለውም ብርታትን ይጨምራል። " ኢሳ 40:2 1ኛ ዮሐ 1፦6-10 ከእርሱ ጋር ኅብረት አለን ብንል በጨለማም ብንመላለስ እንዋሻለን እውነትንም አናደርግም፤ ነገር ግን እርሱ በብርሃን እንዳለ በብርሃን ብንመላለስ ለእያንዳንዳችን ኅብረት አለን፥ የልጁም የኢየሱስ ክርስቶስ ደም ከኃጢአት ሁሉ ያነጻናል፤ ኃጢአት የለብንም ብንል ራሳችንን እናስታለን፥ እውነትም በእኛ ውስጥ የለም፤ በኃጢአታችን ብንናዘዝ ኃጢአታችንን ይቅር ሊለን ከዓመፃም ሁሉ ሊያነጻን የታመነና ጻድቅ ነው።፤ ኃጢአትን አላደረግንም ብንል ሐሰተኛ እናደርገዋለን ቃሉም በእኛ ውስጥ የለም። 💀 ወገኖች እንፀፀት የተለምዶ የማስመሰል ንስሀ ይቅርብን የእይታ እምነት ይቅርብን ዮሐ 3፦ 17-19 ሀብታም ነኝና ባለጠጋ ሆኜአለሁ አንድም ስንኳ አያስፈልገኝም የምትል ስለ ሆንህ፥ ጐስቋላና ምስኪንም ድሀም ዕውርም የተራቆትህም 18መሆንህን ስለማታውቅ፤ ባለ ጠጋ እንድትሆን በእሳት የነጠረውን ወርቅ፥ ተጐናጽፈህም የራቁትነትህ ኃፍረት እንዳይገለጥ ነጭ ልብስን፥ እንድታይም ዓይኖችህን የምትኳለውን ኵል ከእኔ ትገዛ ዘንድ እመክርሃለሁ፤ እኔ የምወዳቸውን ሁሉ እገሥጻቸዋለሁ እቀጣቸውማለሁ፤ እንግዲህ ቅና ንስሐም ግባ። 💀 እግዚያብሔር የምንፀፀት ንስሀ ከልብ የምንገባ የቀራጩ አይነት ልብ ያለን አማኝ ያርገን አሜን ዮሐንስ ዲላ

ያለፈውን እርሱት
" ወንድሞች ሆይ፥ እኔ ገና እንዳልያዝሁት እቈጥራለሁ፤ ነገር ግን አንድ ነገር አደርጋለሁ፤ በኋላዬ ያለውን እየረሳሁ በፊቴ ያለውን ለመያዝ እዘረጋለሁ፥" ፊልጵ 3:13 በምንኖረው የህይወት ጎዳና ፈተና ያለ ጉዳይ ነው ፨ ያከበርከው ያዋርድሀል፣የሚወድህ ይጠላሀል፣የቀረብከው ይሸሽሀል፣ያጀበህ ይበተናል፣ያመንከው ይከዳሀል፣የተማመንከው ምርኩዝ ይሆነኛል ያልከው ባዶ ሜዳ ላይ ጥሎህ ይሄዳል፣በክፉ ቀን የደረስክለት በቸገረክ ጊዜ ዞር ብሎ አያይህም ፨ በህይወት ጎዳና በትዳር፣በስራ፣በኑሮ፣በቤተክርስቲያን፣በሰፈር፣በቤተሰብ ብቻ በብዙ መንገድ እንፈተናለን ሰዎች ያሳዝኑናል በአእምሯችንና በልባችን የማይሽር ጠባሳ ያስቀምጣሉ። ፨ ይሄ እያንዳዳችን የማይቀርልን ጉዳይ ነው ፨ ብዙዎቻችን የትላንት በደል እስረኞች ነን፣የትላንት ትዝታ እስረኞች ነን ፨ በዚህም ምክንያት ወደፊት መሄድ አልቻልንም፣ የትላት የበደል እስረኛና የትዝታ እስረኛ መሆናችን በክርስቲና ወደፊት እንዳንራመድ አድርጎናል። ፨ ኢየሱስን ማመናችን ሁሉ ጎዳና የቀና እና የተመቻቸ እንዲሆን አስበን ከሆነ ተሳስተናል የዚህ ምድር ጉዞ የቀና አይደለም ለዚህም ነው የትላንት ትዝታ የትላንት በደል እስረኞች መሆን የለሌብን " በዚች ሕይወት ብቻ ክርስቶስን ተስፋ ያደረግን ከሆነ፥ ከሰው ሁሉ ይልቅ ምስኪኖች ነን።" 1ኛ ቆሮ 15:19 ፨ በሁኔታዎች ላይ እራሳችንን ማቆም የለብንም፣ የገጠመንን እያሰላሰልን መቆየት የለብንም። ፨ የቱንም ያህል በሰዎች እንዲሁም በልዩ ልዩ ሁኔታ ፈተና ቢገጥመን ወደ ኋላ ማየት እና ማሰላሰሉን ትተን ወደፊት እንሂድ ኢዮብን ተመልከቱ ፨ በጓደኞቹ የተከዳ ፨ እንደ ኋጥያተኛ የተቆጠረ ፨ በምስቱ ብዙ የተባለ ፨ ሁሉ ነገሩ የጨለመበት ፨ ያለውን ሁሉ ያጣ በ ኢዮብ 23፦8-9(እራሱ ኢዮብ ተፈትኖ እንዲህ አለ 8፤ እነሆ፥ ወደ ፊት እሄዳለሁ፥ እርሱም የለም፤ ወደ ኋላም እሄዳለሁ፥ እኔም አላስተውለውም፤ 9፤ ወደሚሠራበት ወደ ግራ ብሄድ አልመለከተውም፤ በቀኜም ይሰወራል፥ አላየውምም። ፨ ነገር ግን ኢዮብ ፈተና እንዳለ ገብቶት እንዲህ አለ ኢዮብ 23፦10 የምሄድበትን መንገድ ያውቃል፤ ከፈተነኝም በኋላ እንደ ወርቅ እወጣለሁ። ፨ ኢዮብ እግዚያብሔር ሰውን እንደሚትን ገብቶታል እግዚያብሔር ፨ ትዕግስታችንን ይፈትናል፣እምነታችንን ይፈትናል፣ታማኝነታችንን ይፈትናል፣ፅናታችንን ይፈትናል፣ትህትናችንን ይፈትናል፣ባህሪያችንን ይፈትናል ፨ በአጠቃላይ ህይወት በሁሉ መንገድ ፈተና ነች " ወንድሞቼ ሆይ፥ የእምነታችሁ መፈተን ትዕግሥትን እንዲያደርግላችሁ አውቃችሁ፥ ልዩ ልዩ ፈተና ሲደርስባችሁ እንደ ሙሉ ደስታ ቍጠሩት" ያዕ 1:2-3 " በፈተና የሚጸና ሰው የተባረከ ነው፤ ከተፈተነ በኋላ ለሚወዱት ተስፋ ስለ እርሱ የሰጣቸውን የሕይወትን አክሊል ይቀበላልና።" ያዕ 1:12 ፨ ስለዚህ ውድ የእግዚያብሔር ልጆች በህይወታችን በብዙ መንገድ ብንፈተን ሰዎች ቢያሳዝኑንም ከኋላ ያለውን እየረሳን መልካሙን እያሰብን ከትዝታ እስረኝነት ነፃ ሆነን እንዲህ ተደረኩ ከሚል ሀሳብ ወተን የፊቱን ለመያዝ እጃችንን እንዘርጋ " የፊተኛውን ነገር አታስተውሉ፥ የጥንቱንም ነገር አታስቡ።" ኢ4 3:18 ፨ ዳዊት የተረሳ፣የተናቀ፣ የተተወ ሰው ነበር ነገር ግን መርሳትን ያውቃል ፨ እንደምናውቀው ሳሙኤል ንጉስ ሊቀባ ወደ እሰይ ቤት(የዳዊት አባት) በመጣ ጊዜ መጠራት የነበረበት ዳዊት አልተጠራም ነበር ነገር ግን በመጨረሻም የዳዊት መምጣት ግድ ሲሆን ዳዊት ቀድሞ ለምን አልተጠራሁም ብሎ ለምን አላለም ያለፈውን ረሳ ተወ ፨ ስለዚህ ሁላችንም በምንም ሁኔታ እያለፍን ቢሆን እንኳ ያመነው ሰው ቢከዳን ቢያሳዝነን እንኳ በውስጣችን ቂም አይኑረን ያለፈውን ሁሉ እንርሳ እኛ ሩጫችን ከዚህ ምድር ነገር ጋር አይደለም 1ኛ ቆሮ 9፦24-27 በእሽቅድምድም ስፍራ የሚሮጡት፥ ሁሉ እንዲሮጡ ነገር ግን አንዱ ብቻ ዋጋውን እንዲቀበል አታውቁምን? እንዲሁም ታገኙ ዘንድ ሩጡ፤ የሚታገልም ሁሉ በነገር ሁሉ ሰውነቱን ይገዛል፤ እነዚያም የሚጠፋውን አክሊል ሊያገኙ ነው፥ እኛ ግን የማይጠፋውን፤ ስለዚህ እኔ ያለ አሳብ እንደሚሮጥ ሁሉ እንዲሁ አልሮጥም፥ ነፋስን እንደሚጎስም ሁሉ እንዲሁ አልጋደልም፤ ነገር ግን ለሌሎች ከሰበክሁ በኋላ ራሴ የተጣልሁ እንዳልሆን ሥጋዬን እየጎሰምሁ አስገዛዋለሁ። ፨ ያለፈውን እያሰብን ለቤዛ ቀን የታተምንበትን መንፈስ ቅዱስ አናሳዝን ስለዚህ ያለፈውን እንተው የበደል እስረኛ አንሁን ኤፌ 4፦ 30-32 ለቤዛም ቀን የታተማችሁበትን ቅዱሱን የእግዚአብሔርን መንፈስ አታሳዝኑ፤ መራርነትና ንዴት ቁጣም ጩኸትም መሳደብም ሁሉ ከክፋት ሁሉ ጋር ከእናንተ ዘንድ ይወገድ፤ እርስ በርሳችሁም ቸሮችና ርኅሩኆች ሁኑ፥ እግዚአብሔርም ደግሞ በክርስቶስ ይቅር እንዳላችሁ ይቅር ተባባሉ። ፨ ያለፈውን መተው ያለፈውን መርሳት እንድንችል እግዚያብሔር ይርዳን አሜን ዮሐንስ ዲላ

ማስታወቂያ
የዛሬ ቅዳሜ መደበኛው ኘሮግራም በታቦር ቤተክርስቲያን እንደሚካሄድ ቤተ ክርስቲያን ትገልፃለች።

የሀዘን መግለጫ ጥቅምት 26/02/2018 ዓ.ም የቤተ ክርስቲያናችን ፓስተር የሆኑት ፓ/ር ዮሴፍ ቡጤ ከዚህ አለም ድካም አርፈዋል ቤተክርስቲያናችን በሞታቸው የተሰማትን ሀዘን እየገለፀች የቀብር ስነ
የሀዘን መግለጫ ጥቅምት 26/02/2018 ዓ.ም የቤተ ክርስቲያናችን ፓስተር የሆኑት ፓ/ር ዮሴፍ ቡጤ ከዚህ አለም ድካም አርፈዋል ቤተክርስቲያናችን በሞታቸው የተሰማትን ሀዘን እየገለፀች የቀብር ስነ ስርዓት ሚፈፀመው ነገ በቱላ ክ/ ከተማ በ6:00 ሲሆን የሽንት ፕሮግራም ሚደረገው በሀዋሳ ታቦር ቤተ ክርስቲያን በ4:00 ይሆናል:: እግዚአብሔር ሁላችንን በመፅናናቱ ይጎብኘን!!

ተጨማሪ መረጃ
የቀብር ስነ ስርዓት ሚፈፀመው ነገ በቱላ ክ/ ከተማ በ6:00 ሲሆን የሽንት ፕሮግራም ሚደረገው በሀዋሳ መኖሪያ ቤታቸው ይሆናል:: እግዚአብሔር ሁላችንን በመፅናናቱ ይጎብኘን!!

ተጨማሪ መረጃ
የቀብር ስነ ስርዓት ሚፈፀመው ነገ በቱላ ክ/ ከተማ በ6:00 ሲሆን የሽንት ፕሮግራም ሚደረገው በሀዋሳ መኖሪያ ቤታቸው ይሆናል:: እግዚአብሔር ሁላችንን በመፅናናቱ ይጎብኘን!!

ተጨማሪ መረጃ
የቀብር ስነ ስርዓት ሚፈፀመው ነገ በቱላ ክ/ ከተማ በ6:00 ሲሆን የሽንት ፕሮግራም ሚደረገው በሀዋሳ መኖሪያ ቤታቸው ይሆናል:: እግዚአብሔር ሁላችንን በመፅናናቱ ይጎብኘን!!

የሀዘን መግለጫ
ጥቅምት 26/02/2018 ዓ.ም የቤተ ክርስቲያናችን ፓስቴር የሆኑት ዮሴፍ ቡጤ ከዚህ አለም በሞቱ ስለተለዩ ቤተክርስቲያናችን የተሰማትን ሀዘን እየገለፀች የቤ/ያን አባላት በሙሉ በስፍራው እንድትገኙ እና ቤተሰቦቹን እንድታጽናኑ እናስታውቃለን። አድራሻ፡ ጤና ቢሮ ወረድ ብሎ

የእግዚያብሔር ክንድ
፨ በእና ውስን አእዕምሮ የእግዚያብሔር ወሰን የለሽ ክንድ ለመረዳት ሲያቅተን ብዙ ጊዜ እንፈተናለን ፨ ከዚያም የተነሳ ይህ ፈፅሞ ሊሆን አይችልም ብለን የደመደምነው ጊዜ ብዙ ነው፣ በዚህም ምክንያት ሌላ መፍትሔ የሚሰጥ ነገር ፍለጋ የሄድነው በጣም ብዙ ጊዜ ነው ፨ በዘኁልቁ ምዕራፍ 11 ላይ እግዚያብሔር በድንቅ ያሻገራቸው መናን የመገባቸው ሕዝቦች ሙሴን ጨምሮ በእግዚያብሔር ላይ አማረሩ በግብፅ ያለው ነገር አማራቸው ዘኍልቍ 11፦ 5-6 በግብፅ ያለ ዋጋ እንበላው የነበረውን ዓሣ፥ ዱባውንም፥ በጢኹንም፥ ኩራቱንም፥ ቀዩንም ሽንኩርት፥ ነጩንም ሽንኩርት እናስባለን፤ አሁን ግን ሰውነታችን ደረቀች፤ ዓይናችንም ከዚህ መና በቀር ምንም አታይም አሉ። 💀 ሙሴ ድንቁን የእግዚያብሔርን ክንድ ዘንግቶ ፨ ባህር ከፍሎ በድንቅ ያሻገረውን ረስቶ ፨ ተቃጥሎ በማይጠፋ ቁጥቋጦ ክብሩን ያሳየውን እግዚያብሔርን ረስቶ ፨ እጅግ ብዙ ታምራትን ያሳየው እግዚያብሔርን ረስቶ እንዲህ አለ ዘኍልቍ 11 ሙሴም። እኔ በመካከላቸው ያለሁ ሕዝብ ስድስት መቶ ሺህ እግረኛ ናቸው፤ አንተም። ወር ሙሉ የሚበሉትን ሥጋ እኔ እሰጣቸዋለሁ አልህ፤ እነርሱን የሚያጠግብ የበሬና የበግ መንጋ ይታረድን? ወይስ የባሕርን ዓሣ ሁሉ ያጠግባቸው ዘንድ ይሰበሰብላቸዋልን? አለ። 💀 ነገር ግን እግዚያብሔር ለሙሴ እንዲህ አለው " እግዚአብሔርም ሙሴን። በውኑ የእግዚአብሔር እጅ አጭር ሆነ? አሁን ቃሌ ይፈጸም ወይስ አይፈጸም እንደ ሆነ አንተ ታያለህ አለው። " ዘኍልቍ 11:23 በእርግጥ የእግዚያብሔር ክንዶች ሁሉን ማድረግ እነንደሚችሉ ማመን አለብን ፨ በዕድሜ ብዛት የማይዝሉ ፨ በዕድሜ ብዛት የማያረጁ ፨ በቀን ሆነ በሌሊት የማይደክሙ ፨ የማይሰለቹ ፨ ቀጠሮ የማይሰጡ ፨ በዝምታ የሚሰሩ ፨ ሰውን በማንነት የማይለዩ ዘላለማዊ ክንዶች ናቸው ፨ ለዚህም እግዚያብሔር ማረጋገጫ ሲሰጥ እንዲህ አለ " በውኑ ለእግዚአብሔር የሚሳነው ነገር አለን? ዘፍጥረት 18:14 " ለእግዚአብሔር የሚሳነው ነገር የለምና።" ሉቃስ 1:37 " እርሱ ግን። በሰው ዘንድ የማይቻል በእግዚአብሔር ዘንድ ይቻላል አለ።" ሉቃስ 18:27 " ኢየሱስም። ቢቻልህ ትላለህ፤ ለሚያምን ሁሉ ይቻላል አለው።" ማርቆስ 9:23 " እኔ ከአንተ ጋር ነኝና አትፍራ፤ እኔ አምላክህ ነኝና አትደንግጥ፤ አበረታሃለሁ፥ እረዳህማለሁ፥ በጽድቄም ቀኝ ደግፌ እይዝሃለሁ። ኢሳይያስ 41:10 ፨ ስለዚህ የእግዚያብሔር ውዶች ምንም እንኳን ተስፋ የሚያስቆርጥ ሁኔታ ውስጥ ቢንሆን እንኳን፣ ምንም እንኳ በለስም ባታፈራ፥በወይንም ሐረግ ፍሬ ባይገኝ፥የወይራ ሥራ ቢጐድል፥ እርሾችም መብልን ባይሰጡ፥በጎች ከበረቱ ቢጠፉ፥ላሞችም በጋጡ ውስጥ ባይገኙ፥ ሁሉ ነገር ቢጨልምብን እንኳ ሁሌም የእግዚያብሔር ዘላለማዊ ክንዶች አይተውኑም ለዚህ ሁሌም ይሄን ክንድ እንመነው እንዲህም እንበለው ኢዮብ 42 ፦ 2 ሁሉን ታደርግ ዘንድ ቻይ እንደ ሆንህ፥ አሳብህም ይከለከል ዘንድ ከቶ እንደማይቻል አወቅሁ። ፨ ይሄን እምነት ለሁላችን ይስጠን አሜን ዮሐንስ ዲላ

የማያዮ ዓይኖች የማይሰሙ ጆሮዎች
" ልባችሁስ ደንዝዞአልን? ዓይን ሳላችሁ አታዩምን? ጆሮስ ሳላችሁ አትሰሙምን? ትዝስ አይላችሁምን?" ማር 8:18 ፨ ከላይ የተጠቀሰው ደቀ መዛሙርቱ እንዲህ ዓይነት ችግር በታየባቸው ጊዜ ጌታ ኢየሱስ የተናገራቸው ሀሳብ ነው ፨ " እርሱም። ተጠንቀቁ፤ ከፈሪሳውያንና ከሄሮድስ እርሾ ተጠበቁ ብሎ አዘዛቸው።" ማር 8:15 ፨ ኢየሱስ እያወራ ያለው ስለ መንፈሳዊ እይታ ሆኖ ሳለ ፨ አብረሁት ሆነው የሚያስቡት ስለ እንጀራ እንደሆነ ኢየሱስ አውቆ ተናገራቸው በተጨማሪም ብዙ ተዓምር ያዩ የኢየሱስን ድንቅ ስራ የተመለከቱ ቀድሞ ያደረገውን ነገር ረሱት በዚህም ምክንያት ኢየሱስ አዝኖ ልባችሁስ ደንዝዞአልን? ዓይን ሳላችሁ አታዩምን? ጆሮስ ሳላችሁ አትሰሙምን? ትዝስ አይላችሁምን አላቸው። ፨ ጌታ ኢየሱስ ስጋን ለብሶ በምድር በተመላለሰበት ጊዜ መጽሐፍትን ያውቃሉ የሚባሉት ብዙዎቹ አልተቀበሉትም ነበር ፨ እንዲያው በመንገዱ ላይ ወጥመድ በማስቀመጥ አገልግሎቱን ለማደናቀፍ የሰይጣን መጠቀሚያ የሆኑበት ሁኔታ እንመለከታለን ነገር ግን ይሄን ያደርጉ የነበረው በጌታ ቤት ሆነው ነበር ክርስቲያን ነን ባዮች ነበሩ ለዚህም ነው ልባችሁስ ደንዝዞአልን? ዓይን ሳላችሁ አታዩምን? ጆሮስ ሳላችሁ አትሰሙምን? ትዝስ አይላችሁምን ያላቸው ፨ ከዚህ እውርነት ይጠብቀን ፨ ሁላችንም በጌታ ቤት ሆነን የእርሱ ተከታይ ነን እያለን ነገር ግን ዓይናችን የተጨፈነ ጆሯችን የደነቆረ ሆኗል ጌታ በቃሉ ሲናገር ማቴ 13፦13-15 ስለዚህ እያዩ ስለማያዩ እየሰሙም ስለማይሰሙ ስለማያስተውሉም በምሳሌ እነግራቸዋለሁ፤ መስማት ትሰማላችሁና አታስተውሉም፥ ማየትም ታያላችሁና አትመለከቱም፤ በዓይናቸው እንዳያዩ፥ በጆሮአቸውም እንዳይሰሙ፥ በልባቸውም እንዳያስተውሉ፥ ተመልሰውም እንዳልፈውሳቸው፥ የዚህ ሕዝብ ልብ ደንድኖአልና ጆሮአቸውም ደንቁሮአል ዓይናቸውንም ጨፍነዋል የሚል የኢሳይያስ ትንቢት በእነርሱ ይፈጸማል። ፨ እግዚያብሔር ከእንደዚያ አይነት መደንደን ይጠብቀን ፨ ይሁዳን ተመልከቱ አብሮት ኖሮ ከእግሩ ስር ተመግቦ ነገር ግን የተጨፈነ አይን የደነቆረ ጆሮ የደነደነ ልብ ይዞ ለዛ ክብር ሳይታደል ቀረ ያሳዝናል ሐዋ 1፦17 " ከእኛ ጋር ተቈጥሮ ነበርና፥ ለዚህም አገልግሎት ታድሎ ነበርና። ፨ ለእስራኤል ልጆች " እግዚአብሔር ግን አስተዋይ ልብ፥ የሚያዩ ዓይኖች፥ የሚሰሙም ጆሮች እስከ ዛሬ ድረስ አልሰጣችሁም።" ይላል ዘዳ 29:4 ፨ ምክንያቱም የተደረገላቸውን ታላቅ ነገር ማየት ስላልቻሉ፣ መስማት ስላልፈቀዱ የግብፅን ሽንኩርት ተመኙ 40 ዓመት በምድረ በዳ ተንከራቱቱ ወደ ታሰበላቸው ከነዓን ሳይገቡ በምድረ በዳ ረገፉ እንደ ይሁዳ ከእኛ ጋር ተቈጥሮ ነበርና፥ ለዚህም አገልግሎት ታድለው ነበርና ተባሉ ኢሳ 42፦ 18-20 እናንተ ደንቆሮች፥ ስሙ፤ እናንተም ዕውሮች፥ ታዩ ዘንድ ተመልከቱ፤ ከባሪያዬ በቀር ዕውር ማን ነው? እንደምልከው መልእክተኛዬስ በቀር ደንቆሮ የሆነ ማን ነው? እንደ ፍጹሙ ወይስ እንደ እግዚአብሔር ባሪያ ዕውር የሆነ ማን ነው? ፤ ብዙ ነገርን ታያላችሁ ነገር ግን አትጠባበቁትም፤ ጆሮአችሁም ተከፍተዋል፥ ነገር ግን አትሰሙም። ዮሐ 12፦37-40 ነገር ግን ይህን ያህል ምልክት በፊታቸው ምንም ቢያደርግ፤ ነቢዩ ኢሳይያስ። ጌታ ሆይ፥ ማን ምስክርነታችንን አመነ? የእግዚአብሔርስ ክንድ ለማን ተገለጠ? ብሎ የተናገረው ቃል ይፈጸም ዘንድ በእርሱ አላመኑም፤ ኢሳይያስ ደግሞ። በዓይኖቻቸው እንዳያዩ፥ በልባቸውም እንዳያስተውሉ፥ እንዳይመለሱም፥ እኔም እንዳልፈውሳቸው፥ ዓይኖቻቸውን አሳወረ ልባቸውንም አደነደነ ብሎአልና ስለዚህ ማመን አቃታቸው። 💀 ዛሬ ጌታችን የእኛን ልምምድ ቢፈትሽ ከዚህ የተለየ ይሆን??? 💀 ሁላችን ልናስተውል ያስፈልጋል ተደላድለን የቆምንበትን ክርስትናችንን ልንፈትሽ ያስፈልጋል፣ ማንም የቆመ ሚመስለው እንዳይወድቅ ይጠንቀቅ እንደተባለው ሁላችን የቆምንበትን ነገር መፈተሽ ያስፈልገናል፣ እንደ ይሁዳ ተቆጥሮ ነበረና ብቻ ተብለን ታሪካችን በዚያ የሚያበቃ መሆን የለብንም 💀 ውድ ወገኖቼ የመዳን ቀን ዛሬ ነው የምናስተውልበት ሰዓት አሁን ነው ራሳችንን እንፈትሽ የበግ ለምድ ለብሰን ነገር ግን በውስጣችን ነጣቂ ተኩላ ባህሪያችንን እንፈትሽ በጌታ ቤት ሆነን ነገር ግን በድብቅ ኋጥያት ምክንያት ጌታን ማየት ያቃተን ጌታን መስማት የተሳነን ልባችን ወደ ድንጋይ የተቀየረብን እንደ ዳዊት እንዲህ ብለን መጸለይ ይገባናል " ዓይኖቼን ክፈት፥ ከሕግህም ተኣምራትህን አያለሁ።" መዝ 119:18 ፨ ለሁላችን ጌታ ማስተዋሉን ይስጠን፣ ድንጋዩን ልብ ቀይሮ በፊቱ ዝቅ የሚል ልብ ይስጠን፤ አጥርቶ የሚያይ ዓይን ይስጠን፣ የሚሰማ ጆሮ ይስጠን አሜን ዮሐንስ ዲላ

መርዶ ሰላም ይብዛላችሁ የቤ/ያን አባል የሆኑት አቶ ሻጳ ሻዶ (የወ/ሮ አበበች አልቤ ባሌቤት) እናቱን አስቀብሮ ነገ ጥቅምት 23/2018 ዓ.ም ይመለሳል ስለሆነም አመሻሽ 12፡00 ጀምሮ ቤተ ክርስቲያን የማፅናኛ ፕሮግራም ስለምታካህድ የቤ/ያን አባላት በሙሉ በስፍራው እንድትገኙ እናስታውቃለን። አድራሻ፡ 07 ዶ/ር ሙላት ህክምና ክሊኒክ አከባቢ / ከትሩፋት ከፍ ብሎ