የሀዋሳ ታቦር ሰባተኛ ቀን አድቬንቲስት አለም አቀፍ ቤተክርስቲያን (Hawassa Tabour 7th day Adventist INternational Church
Open in Telegram
1 071
Subscribers
+224 hours
+167 days
+3930 days
Posts Archive
Adult Sabbath Sch Q1 2026.pdf7.46 MB
ለEnglish ሰንበት ትምህርት ተጠቃሚዎች
GC Calendar of Events 2026 and 2027
GC Calendar of Events 2026 and 2027
Songs_by_Seventh_Day_Adventist_singers_in_Ethiopian_Languages_Progress.zip8.00 MB
የኢትዮጵያ ሰባተኛ ቀን አድቬንቲስት ዝማሬዎች ስብስብን በተመለከተ አጭር ማስታወሻ
ታህሳስ 22 / 2018 ዓ.ም. (Dec. 31 / 2025)
ሰላም ሰላም ውድ ቤተሰብ!
በጌታ ጸጋ በኢትዮጵያ ሰባተኛ ቀን አድቬንቲስት ዘማሪያን የተዘመሩ ዝማሬዎችን ለግልም ሆነ ለጉባዔ አምልኮ በነጻ እንዲታደሉ በማሰብ በመተግበሪያ (application) መልኩ ለማዘጋጀት ከተወሰኑ ጊዜያት በፊት እንቅስቃሴዎች መጀመራቸው ይታወሳል።
ሂደቱ አስደናቂ የሆነ የበረከት ልምምድ ነበር።
ብዙዎቹን ዝማሬዎች ከራሳቸው ከዘማሪያኑ ያገኘን ሲሆን ሌሎቹን ደግሞ በተለያዩ ጊዜያት በግል ማስታወሻቸው ካሰባሰቡ ወገኖች የተወሰኑቱንም ደግሞ በቀጥታ ከካሴት እየሰሙ የዚህ ፕሮጀክት ተባባሪዎች ጽፈዋል።
የመተግበሪያ ዝግጅት ቡድንም ስራውን ተግቶ እየሰራ ያለ ሲሆን በቅርቡ መተግበሪያውን ያደርሰናል ብለን ተስፋ እናደርጋለን።
የሆነ ሆኖ ግና ዛሬ ላይ እነዚህን ዝማሬዎች አሁን ባሉበት ሁኔታ (በ word, excel & pdf) ስንለቅ የተወሰኑ ነጥቦችን ልናነሳላችሁ ወደድን፡-
- እስካሁን በ9 ቋንቋዎች የተለያየ ብዛት ያላቸውን ዝማሬዎች ለማሰባሰብ ተችሏል። ቋንቋዎቹም፦ አማርኛ ፣ ኦሮሚኛ ፣ ትግርኛ ፣ ወላይትኛ ፣ ሀዲይኛ ፣ ከምባትኛ ፣ ጉራጊኛ ፣ ኑዌርኛ ፣ ሲዳሚኛ ናቸው።
በኑዌር ቋንቋ በፒዲኤፍ ያለው ግን ከዚህ ማሰባሰብ ቀድሞ በሌላ ወገኖች የተዘጋጀ እንደነበር መግለጽ እንወድዳለን።
- ሀሳቡን በተወሰኑ ወገኖች ልብ አስነስቶ ሌሎች ደግሞ በሙያቸው ፣ ጊዜያቸው . . . ስራውን እንዲደግፉ ያደረገ እና እስካሁን ያደረሰ ነገም ይልቅ የሚያሰፋልን እግዚአብሔር ይባረክ!
- በመጀመሪያ ዝማሬዎቹን ከጌታ ዘንድ ተቀብለው በጉባኤ በመዘመርም ሆነ በካሴቶች በማሳተም በረከቶቻችን የሆኑ ዘማሪያን ወንድም እህቶቻችንን እግዚአብሔር ይባርካችሁ ልንል እንወድዳለን።
- በመቀጠልም በዚህ ስራ ላይ እስካሁን በተለያዩ ስራዎች የለፉ እና በቀጣይም ይህንን ፕሮጀክት በማበልጸግ ፣ በአርትኦት ፣ ተጨማሪ በዚህ ያልተካተቱ ዝማሬዎችን በእነዚህ ቋንቋዎችም ሆነ በሌሎች አዳዲስ ቋንቋዎች በማበርከት የሚያግዙንን ወገኖቻችንን እግዚአብሔር ይባርክልን ለማለት እንወድዳለን።
ጌታ ፈቅዶ በቅርቡ ቀጣይ እትም (version) ላይ በዝርዝር በዝማሬ ማሰባሰብ እንዲሁም መተግበሪያ ዝግጅት ውስጥ የተሳተፉ ወገኖችን በስም ጠቅሰን ለማመስገን (acknowledge ለማድረግ) ዕቅዱ አለን።
- ከላይ እንደተጠቀሰው የዝማሬ መተግበሪያ ዝግጅት ቡድን ስራውን ጀምሮ በጥሩ ደረጃ ላይ የሚገኝ ሲሆን እነዚህን የዝማሬ ስብስቦች በመጠቀም ሌሎች መተግበሪያዎችን ማዘጋጀት አይፈቀድም።
ምናልባት ግን የመተግበሪያ ዝግጅት ሙያ እና ልምድ ያላችሁ እንዲሁም በእነዚህ ስራዎች ላይ በበጎ ፈቃድ ላይ የተመሰረተ አስተዋጽኦ ለማድረግ ፈቃደኝነቱ ያላችሁ ወገኖች መጨረሻ ላይ በምታገኟቸው አድራሻዎች (በኢሜይል ፣ ቴሌግራም ፣ ዋትስአፕ . . .) ብትጽፉልን በዚህ ፕሮጀክት ላይ የተጀመሩ ስራዎችን በማገዝም ሆነ በሌሎች አዳዲስ መንፈሳዊ ስራዎች ላይ እንድታግዙን ለማመቻቸት ደስተኞች ስለሆንን እባካችሁ ጻፉልን።
- ይህ የዝማሬዎች ስብስብ (በእርግጥ አንድ ዙር ዝማሬዎቹ ላይ የአርት ኦት ስራ / editing መስራት) (የሚስተካከለው ፊደል ፣ ዝማሬን ከዘማሪ ስም ጋር በትክክል ማገናኘት ፣ ቋንቋው የሚጠቀመው ኦፊሴላዊ ፊደል ላቲን ሆኖ በሳባ ፊደላት የተጻፉትን ወደ ላቲን መቀየር . . . ሊሆኑ ይችላሉ) እንደሚቀር የሚሰማን ቢሆንም ያንን አድርገው ለሚጠቀሙ ወገኖች ፣ ለግል አምልኮዎች ፣ በጉባኤ ለሚደረጉ አምልኮዎች ፣ ዝማሬዎቹን ኮፒ አድርገው በፓወር ፖይንት ለጉባኤ እየለቀቁ ለማዘመር ለሚፈልጉ የዝማሬ አምልኮ መሪዎች ፣ ፕሪንት አድርገው በማረሚያ . . . ላሉ ወገኖች ለማበርከት ለሚፈልጉ . . . ታላቅ በረከት ይሆናል ብለን ተስፋ እናደርጋለን!
በሀዋሳ ማረሚያ ተቋም በምትገኘዋ የሰ/ቀ/አ/ቤ/ክ በወገኖች ድጋፍ ጥቂት የአማርኛ እና የሲዳሚኛ ዝማሬ ስብስቦችን ፕሪንት አድርገን እና ጠርዘን ከተወሰኑ ወራት በፊት ያስቀመጥን ሲሆን አሁን ላይ እጅግ በመልካም ሲጠቀሙባቸው አይተናል።
እናንተም እንዲሁ ፕሪንት አድርጋችሁ በተመሳሳይ ማረሚያ . . . አካባቢ ላሉ ብታደርሱ በረከቱ ብዙ እንደሚሆን አንጠራጠርም!
- ይህንን የዝማሬ ስብስብ ለማዘጋጀትም ሆነ ለሌላ ተያያዥ እንቅስቃሴዎች እስካሁን ምንም ዓይነት ገንዘብ ያልተሰበሰበ እና ወደፊትም የማይሰበሰብ ሲሆን ስራው ሙሉ ለሙሉ በበጎ ፈቃድ ላይ የተመሰረተ መንፈሳዊ እንቅስቃሴ አካል ሆኖ ይቀጥላል።
- ይህንን ማሰራጨታችን ብዙ ሊደግፉን የሚችሉ (በዝማሬ ማሰባሰብ ፣ አርትኦት ፣ የተላኩልንን በወግ በማደራጀት . . . ) ወዳጆችን እንደሚያመጣልን እና በቅርቡም በብዙ መልኩ የተሻለ ሁለተኛ ዙር የምንለቀው እትም / version እንደሚኖረን ተስፋ እናደርጋለን።
- ምንም እንኳን ሁሉም በግል ዘማሪያንም ሆነ በኳየሮች በሁሉም ቋንቋዎች የተዘጋጁ ዝማሬዎች የተባረኩ እና ጌታ ቢፈቅድ ወደፊት ሁሉንም ወደማሰባሰብ የመግባት ተስፋ ያለን ቢሆንም ለአሁን ግን ለአሰራር እንዲመች የዚህ ስብስብ አዘጋጆች ዝማሬዎችን ለማካተት የተጠቀሙበት መስፈርት “በሰባተኛ ቀን አድቬንቲስት ዘማሪያን የተዘመሩ ሆነው በተቻለ መጠን ሁሉንም በካሴት / ሲዲ ብቻ በአጠቃላይ በስቱዲዮ የተሰሩ ለሆፕ ቻናል ወይም ዩ-ቲዩብም ሊሆን ይችላል እንዳይቀሩ ምናልባት ደግሞ ስቱዲዮ ላይ ባይሰሩም በህዝባችን ዘንድ በስፋት የሚታወቁ ዝማሬዎችን" ለማካተት ታቅዶ ሲሰራ ነበር።
ነገር ግን እንደሚታወቀው ይህንን መስፈርት ያሟሉ እና ሊካተቱ ሲገባቸው ያልተካተቱ በርካታ ዝማሬዎች አሉ።
የአርትኦቱን አስተዋጽኦ ከእናንተ በቀጣይ ትንሽ ሰብሰብ ባሉ ዝማሬዎቻችን ላይ የምንጠይቅ ሆኖ አሁን ግን አዳዲስ / በዚህ ያልተካተቱ ዝማሬዎችን እስካሁን በተጀመሩ ወይንም አዳዲስ የኢትዮጵያ ቋንቋዎች በወርድ ፋይል እያደረጋችሁ ቴሌግራም / ዋትስአፕ ወይንም ኢሜይል ላይ ብትልኩልን እጅግ ደስ ይለናል።
የፋይሉን ስም ለምሳሌ “አዳዲስ የሀዲይኛ መዝሙሮች / New Oromiffa songs” . . . ብታደርጉት በቀጥታ ለዚያ ቋንቋ ዝማሬ አሰባሳቢዎች ለመላክ ይመቸናል።
በተቻለ መጠን መካተት የሚገባቸው መረጃዎች፦ ሙሉ መዝሙሩ (ቢቻል ላቲንን በኦፊሴላዊነት ለሚጠቀሙ ቋንቋዎች በላቲን ካልሆነም በሳባ ፊደል ሊሆን ይችላል) ፣ ዘማሪያኑን ቢቻል ደግሞ ሌሎች ኤክሴል ላይ ያሉ ዝማሬዎች የያዟቸውን መረጃዎች ሁሉ ይያዙ።
ይህ አስተዋጽኦ በተቻለ መጠን ፈጥኖ ቢመጣ ቀጣዩን ስብስብ (version) ቶሎ ለመስራት ያግዘናል።
“በክርስቶስ በሰማያዊ ስፍራ በመንፈሳዊ በረከት ሁሉ የባረከን የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክና አባት ይባረክ” (ኤፌ. 1:3)
ጌታ ይባርካችሁ!
ወንድሞቻችሁ
አትክልት ኢሳይያስ - atuesu@gmail.com / +251911714976
ትዕግስቱ ዘለቀ - abushabeki@gmail.com / +251913882262
ሩጫን ጨርሶ መሮጥመሪ ጥቅስ ዕብራውያን 12 1-2 እንግዲህ እነዚህን የሚያህሉ ምስክሮች እንደ ደመና በዙሪያችን ካሉልን፥ እኛ ደግሞ ሸክምን ሁሉ ቶሎም የሚከበንን ኃጢአት አስወግደን፥ የእምነታችንንም ራስና ፈጻሚውን ኢየሱስን ተመልክተን፥ በፊታችን ያለውን ሩጫ በትዕግሥት እንሩጥ፤ እርሱ ነውርን ንቆ በፊቱም ስላለው ደስታ በመስቀል ታግሦ በእግዚአብሔር ዙፋን ቀኝ ተቀምጦአልና። በህይወት ብዙ ምንሮጥባቸው ነገሮች አሉን በስራችን እንሮጣለን፤ በትዳራችን እንሮጣለን፤ በልጆቻችንእንሮጣለን፤ በአገልግሎት እንሮጣለን .... ነገር ግን በሩጫ ውስጥ ድካም፣ መዛል ፣ መቁሰል ሊኖር ይችላል ደግሞም አለ ነገር ግን 💪 በድካም ውስጥ ሩጫን አለማቋረጥ፤ 👣 በመዛል ውስጥ አለመውደቅ 😭 ብንቆስልም ሩጫን አለማቋረጥ ያስፈልጋል
ሩጫን ለመጨረስ1. ክብደትን ማስወገድ 2. አይንን በኢየሱስ ላይ ማድረግ 3. መፍጠናችን ሳይሆን በታማኝነት መጨረሳችን ማሠብ 4. ለብቻችን እየሮጥን እንዳይደለ ማወቅ ስንሮጥ ሁሌም ከልባችን መጥፋት የሌለበት ነገር
"ከኃጢአት በቀር በነገር ሁሉ እንደ እኛ የተፈተነ ነው እንጂ፥ በድካማችን ሊራራልን የማይችል ሊቀ ካህናት የለንም።" ሮሜ 4:15አሜን ፓር መስፍን ማንደፍሮ
የፃድቁና የክፉው ዕጣ ፈንታበክፉዎች ላይ አትቅና፥ ዓመፃንም በሚያደርጉ ላይ አትቅና፤ እንደ ሣር ፈጥነው ይደርቃሉና፥ እንደ ለመለመ ቅጠልም ይረግፋሉና። በእግዚአብሔር ታመን፥ መልካምንም አድርግ፥ በምድርም ተቀመጥ፥ ታምነህም ተሰማራ። በእግዚአብሔር ደስ ይበልህ፥ የልብህንም መሻት ይሰጥሃል። መንገድህን ለእግዚአብሔር አደራ ስጥ፥ በእርሱም ታመን፥ እርሱም ያደርግልሃል። ጽድቅህን እንደ ብርሃን፥ ፍርድህንም እንደ ቀትር ያመጣል። ለእግዚአብሔር ተገዛ ተስፋም አድርገው። መንገድም በቀናችለትና ጥመትን በሚያደርግ ሰው አትቅና። ከቁጣ ራቅ መዓትንም ተው፤ እንዳትበድል አትቅና። ክፉ አድራጊዎች ይጠፋሉና፤ እግዚአብሔርን ተስፋ የሚያደርጉ ግን እነርሱ ምድርን ይወርሳሉ። ገና ጥቂት፥ ኃጢአተኛም አይኖርም፤ ትፈልገዋለህ ቦታውንም አታገኝም። ገሮች ግን ምድርን ይወርሳሉ፥ በብዙም ሰላም ደስ ይላቸዋል። ኃጢአተኛ ጻድቁን ይመለካከተዋል፥ ጥርሱንም በእርሱ ላይ ያንገጫግጫል። እግዚአብሔር ይሥቅበታል፥ ቀኑ እንደሚደርስ አይቶአልና። ኃጢአተኞች ሰይፋቸውን መዘዙ፥ ቀስታቸውንም ገተሩ ድሀውንና ችግረኛውን ይጥሉ ዘንድ ልበ ቅኖችንም ይወጉ ዘንድ፤ ሰይፋቸው ወደ ልባቸው ይግባ፥ ቀስታቸውም ይሰበር። ለጻድቅ ያለው ጥቂት ከብዙ ከኃጢአተኞች ሀብት ይበልጣል። የኃጥአን ክንድ ትሰበራለችና፤ እግዚአብሔር ግን ጻድቃንን ይደግፋቸዋል። የንጹሓንን መንገድ እግዚአብሔር ያውቃል፥ ርስታቸውም ለዘላለም ነው፤ በክፉ ዘመንም አያፍሩም በራብ ዘመንም ይጠግባሉ። ኅጥአን ግን ይጠፋሉ፥ የእግዚአብሔር ጠላቶች በከበሩና ከፍ ከፍ ባሉ ጊዜ እንደ ጢስ ይጠፋሉ። ኃጢአተኛ ይበደራል አይከፍልምም፤ ጻድቅ ግን ይራራል ይሰጣልም። እርሱን የሚባርኩት ምድርን ይወርሳሉና፤ የሚረግሙት ግን ይጠፋሉ። የሰው አካሄድ ከእግዚአብሔር ዘንድ ይጸናል፥ መንገዱንም ይወድዳል። ቢወድቅም ለድንጋጤ አይጣልም፥ እግዚአብሔር እጁን ይዞ ይደግፈዋልና። ጐለመስሁ አረጀሁም፤ ጻድቅ ሲጣል፥ ዘሩም እህል ሲለምን አላየሁም። ሁልጊዜ ይራራል ያበድርማል፥ ዘሩም በበረከት ይኖራል። ከክፉ ሽሽ፥ መልካምንም አድርግ፤ ለዘላለምም ትኖራለህ። እግዚአብሔር ፍርዱን ይወድዳልና፥ ቅዱሳኑንም አይጥላቸውምና፤ ለዘላለምም ይጠብቃቸዋል ለንጹሓንም ይበቀልላቸዋል፤ የኅጥኣን ዘር ግን ይጠፋል። ጻድቃን ምድርን ይወርሳሉ፥ በእርስዋም ለዘላለም ይኖራሉ። የጻድቅ አፍ ጥበብን ያስተምራል፥ አንደበቱም ፍርድን ይናገራል። የአምላኩ ሕግ በልቡ ውስጥ ነው፥ በእርምጃውም አይሰናከልም። ኃጢአተኛ ጻድቁን ይመለከተዋል፥ ሊገድለውም ይወድዳል። እግዚአብሔር ግን በእጁ አይተወውም፥ በተፋረደውም ጊዜ አያሸንፈውም። እግዚአብሔርን ደጅ ጥና፥ መንገዱንም ጠብቅ፥ ምድርንም ትወርስ ዘንድ ከፍ ከፍ ያደርግሃል፤ ኃጢአተኞችም ሲጠፉ ታያለህ። ኃጥአን ከፍ ከፍ ብሎ እንደ ሊባኖስ ዝግባም ለምልሞ አየሁት። ብመለስ ግን አጣሁት፤ ፈለግሁት ቦታውንም አላገኘሁም። ቅንነትን ጠብቅ፥ ጽድቅንም እይ፤ ለሰላም ሰው ቅሬታ አለውና። በደለኞች በአንድነት ይጠፋሉ። የኃጢአተኞች ቅሬታ ይጠፋል። የጻድቃን መድኃኒታቸው ከእግዚአብሔር ዘንድ ነው፤ በመከራቸውም ጊዜ መጠጊያቸው እርሱ ነው። እግዚአብሔር ይረዳቸዋል፥ ያድናቸዋልም፥ ከኃጢአተኞችም እጅ ያወጣቸዋል፥ ያድናቸዋል፥ በእርሱ ታምነዋልና። አሜን
የፃድቁና የክፉው ዕጣ ፈንታበክፉዎች ላይ አትቅና፥ ዓመፃንም በሚያደርጉ ላይ አትቅና፤ እንደ ሣር ፈጥነው ይደርቃሉና፥ እንደ ለመለመ ቅጠልም ይረግፋሉና። በእግዚአብሔር ታመን፥ መልካምንም አድርግ፥ በምድርም ተቀመጥ፥ ታምነህም ተሰማራ። በእግዚአብሔር ደስ ይበልህ፥ የልብህንም መሻት ይሰጥሃል። መንገድህን ለእግዚአብሔር አደራ ስጥ፥ በእርሱም ታመን፥ እርሱም ያደርግልሃል። ጽድቅህን እንደ ብርሃን፥ ፍርድህንም እንደ ቀትር ያመጣል። ለእግዚአብሔር ተገዛ ተስፋም አድርገው። መንገድም በቀናችለትና ጥመትን በሚያደርግ ሰው አትቅና። ከቁጣ ራቅ መዓትንም ተው፤ እንዳትበድል አትቅና። ክፉ አድራጊዎች ይጠፋሉና፤ እግዚአብሔርን ተስፋ የሚያደርጉ ግን እነርሱ ምድርን ይወርሳሉ። ገና ጥቂት፥ ኃጢአተኛም አይኖርም፤ ትፈልገዋለህ ቦታውንም አታገኝም። ገሮች ግን ምድርን ይወርሳሉ፥ በብዙም ሰላም ደስ ይላቸዋል። ኃጢአተኛ ጻድቁን ይመለካከተዋል፥ ጥርሱንም በእርሱ ላይ ያንገጫግጫል። እግዚአብሔር ይሥቅበታል፥ ቀኑ እንደሚደርስ አይቶአልና። ኃጢአተኞች ሰይፋቸውን መዘዙ፥ ቀስታቸውንም ገተሩ ድሀውንና ችግረኛውን ይጥሉ ዘንድ ልበ ቅኖችንም ይወጉ ዘንድ፤ ሰይፋቸው ወደ ልባቸው ይግባ፥ ቀስታቸውም ይሰበር። ለጻድቅ ያለው ጥቂት ከብዙ ከኃጢአተኞች ሀብት ይበልጣል። የኃጥአን ክንድ ትሰበራለችና፤ እግዚአብሔር ግን ጻድቃንን ይደግፋቸዋል። የንጹሓንን መንገድ እግዚአብሔር ያውቃል፥ ርስታቸውም ለዘላለም ነው፤ በክፉ ዘመንም አያፍሩም በራብ ዘመንም ይጠግባሉ። ኅጥአን ግን ይጠፋሉ፥ የእግዚአብሔር ጠላቶች በከበሩና ከፍ ከፍ ባሉ ጊዜ እንደ ጢስ ይጠፋሉ። ኃጢአተኛ ይበደራል አይከፍልምም፤ ጻድቅ ግን ይራራል ይሰጣልም። እርሱን የሚባርኩት ምድርን ይወርሳሉና፤ የሚረግሙት ግን ይጠፋሉ። የሰው አካሄድ ከእግዚአብሔር ዘንድ ይጸናል፥ መንገዱንም ይወድዳል። ቢወድቅም ለድንጋጤ አይጣልም፥ እግዚአብሔር እጁን ይዞ ይደግፈዋልና። ጐለመስሁ አረጀሁም፤ ጻድቅ ሲጣል፥ ዘሩም እህል ሲለምን አላየሁም። ሁልጊዜ ይራራል ያበድርማል፥ ዘሩም በበረከት ይኖራል። ከክፉ ሽሽ፥ መልካምንም አድርግ፤ ለዘላለምም ትኖራለህ። እግዚአብሔር ፍርዱን ይወድዳልና፥ ቅዱሳኑንም አይጥላቸውምና፤ ለዘላለምም ይጠብቃቸዋል ለንጹሓንም ይበቀልላቸዋል፤ የኅጥኣን ዘር ግን ይጠፋል። ጻድቃን ምድርን ይወርሳሉ፥ በእርስዋም ለዘላለም ይኖራሉ። የጻድቅ አፍ ጥበብን ያስተምራል፥ አንደበቱም ፍርድን ይናገራል። የአምላኩ ሕግ በልቡ ውስጥ ነው፥ በእርምጃውም አይሰናከልም። ኃጢአተኛ ጻድቁን ይመለከተዋል፥ ሊገድለውም ይወድዳል። እግዚአብሔር ግን በእጁ አይተወውም፥ በተፋረደውም ጊዜ አያሸንፈውም። እግዚአብሔርን ደጅ ጥና፥ መንገዱንም ጠብቅ፥ ምድርንም ትወርስ ዘንድ ከፍ ከፍ ያደርግሃል፤ ኃጢአተኞችም ሲጠፉ ታያለህ። ኃጥአን ከፍ ከፍ ብሎ እንደ ሊባኖስ ዝግባም ለምልሞ አየሁት። ብመለስ ግን አጣሁት፤ ፈለግሁት ቦታውንም አላገኘሁም። ቅንነትን ጠብቅ፥ ጽድቅንም እይ፤ ለሰላም ሰው ቅሬታ አለውና። በደለኞች በአንድነት ይጠፋሉ። የኃጢአተኞች ቅሬታ ይጠፋል። የጻድቃን መድኃኒታቸው ከእግዚአብሔር ዘንድ ነው፤ በመከራቸውም ጊዜ መጠጊያቸው እርሱ ነው። እግዚአብሔር ይረዳቸዋል፥ ያድናቸዋልም፥ ከኃጢአተኞችም እጅ ያወጣቸዋል፥ ያድናቸዋል፥ በእርሱ ታምነዋልና። አሜን
በሲኦል ሆድ ውስጥ" በመከራዬ ሳለሁ ወደ አምላኬ ወደ እግዚአብሔር ጮኽሁ፥ እርሱም ሰማኝ፤ በሲኦልም ሆድ ውስጥ ሆኜ ጮኽሁ፥ ቃሌንም አዳመጥህ። " ትንቢተ ዮናስ 2:3 ፨ እግዚያብሔር ዮናስን ተነሥተህ ወደዚያች ወደ ታላቂቱ ከተማ ወደ ነነዌ ሂድ፥ ክፉታቸውም ወደ ፊቴ ወጥቶአልና በእርስዋ ላይ ስበክ አለው። ፨ ነገር ግን ዮናስ የእግዚያብሔርን ትዕዛዝ አሻፈረኝ ብሎ ከእግዚአብሔር ፊት ወደ ተርሴስ ይኰበልል ዘንድ ተነሣ፤ ወደ ኢዮጴም ወረደ፥ ወደ ተርሴስም የምታልፍ መርከብ አገኘ፤ ከእግዚአብሔርም ፊት ኰብልሎ ከእነርሱ ጋር ወደ ተርሴስ ይሄድ ዘንድ ዋጋ ሰጥቶ ወደ እርስዋ ገባ። 💀 ወገኖቼ ዮናስ የእግዚያብሔርን ነገር ትቶ ወደ ማይገባው ቦታ ለመሄድ ዋጋ ሰጠ ( በስኦል ሆድ ውስጥ በዛ ድቅድቅ ጨለማ መሆንን መረጠ) ፨ ዛሬም እኛ ሁላችንም ከእግዚያብሔር ሀሳብ፣ ከእግዚያብሔር መንገድ ወተን በአለም ሀሳብና ትርምስ በስኦል ሆድ ውስጥ በአስፈሪው ጨለማ ውስጥ ነን ፨ እግዚያብሔር ሁላችንንም ከዚህ ጨለማ ከስኦል ሆድ ውስጥ ልያወጣን ይፈልጋል ነገር ግን ከዚያ ጨለማ ለመውጣት እንደ ዮናስ በስኦል ሆድ ውስጥ ሆነን መጮህ አለብን። ፨ በሉቃስ ምዕራፍ 15 ከቁጥር 11 ጀምሮ የጠፋውን ልጅ ታሪክ ስንመለከት ከሁለቱ ታናሹ አባቱን ፤አባቴ ሆይ፥ ከገንዘብህ የሚደርሰኝን ክፍል ስጠኝ አለው፣ገንዘቡንም አካፈላቸው። ከጥቂት ቀንም በኋላ ታናሹ ልጅ ገንዘቡን ሁሉ ሰብስቦ ወደ ሩቅ አገር ሄደ ( ወደ ስኦል ሆድ ውስጥ ገባ) ፨ ክፉውን መንገድ መርጦ በአለም ጨለማ በስኦል ሆድ ውስጥ ተቅበዘበዘ። ፨ ነገር ግን ወደ ልቡም ስመለስ እንዲህ አለ፣ እንጀራ የሚተርፋቸው የአባቴ ሞያተኞች ስንት ናቸው? እኔ ግን ከዚህ በራብ እጠፋለሁ፤ ተነሥቼም ወደ አባቴ እሄዳለሁና፣ አባቴ ሆይ፥ በሰማይና በፊትህ በደልሁ፤ ወደ ፊትም ልጅህ ልባል አይገባኝም፤ከሞያተኞችህ እንደ አንዱ አድርገኝ እለዋለሁ፤ ተነሥቶም ወደ አባቱ መጣ። እርሱም ገና ሩቅ ሳለ አባቱ አየውና አዘነለት፥ ሮጦም አንገቱን አቀፈውና ሳመው ከስኦል ሆድ ውስጥ ከድቅድቅ ጨለማ አወጣው። 💀 ውድ የጌታ ልጆች ካለንበት ጨለማ ከስኦል ሆድ ውስጥ መውጣት አለብን አለምን አትርፈን ነብሳችንን ብናጣ ምን ይጠቅመናል? ቃሉ በስኦል ሆድ ውስጥ ያለንን እኛን እንዲህ ይላል ኢሳ 1፦ 2-20 2፤ እግዚአብሔር ተናግሮአልና ሰማያት ስሙ፥ ምድርም አድምጪ፤ ልጆችን ወለድሁ አሳደግሁም፥ እነርሱም አመጹብኝ። 3፤ በሬ የገዢውን አህያም የጌታውን ጋጣ አወቀ፤ እስራኤል ግን አላወቀም፥ ሕዝቤም አላስተዋለም። 4፤ ኃጢአተኛ ወገንና በደል የተሞላበት ሕዝብ፥ የክፉዎች ዘር፥ ርኵሰትን የምታደርጉ ልጆች ሆይ፥ ወዮላችሁ! እግዚአብሔርን ትተዋል የእስራኤልንም ቅዱስ አቃልለዋል ወደ ኋላቸውም እየሄዱ ተለይተዋል። 5፤ ደግሞስ ዓመፃ እየጨመራችሁ ለምን ገና ትቀሰፋላችሁ? ራስ ሁሉ ለሕመም ልብም ሁሉ ለድካም ሆኗል። 6፤ ከእግር ጫማ አንስቶ እስከ ራስ ድረስ ጤና የለውም፤ ቍስልና እበጥ የሚመግልም ነው፤ አልፈረጠም፥ አልተጠገነም፥ በዘይትም አልለዘበም። 7፤ ምድራችሁ ባድማ ናት፤ ከተሞቻችሁ በእሳት ተቃጠሉ፤ እርሻችሁንም በፊታችሁ ሌሎች ይበሉታል፤ ባዕድ እንዳፈረሳት ምድር ባድማ ሆነች። 8፤ የጽዮንም ሴት ልጅ በወይን ቦታ እንዳለ ዳስ፥ በዱባ አትክልትም እንዳለ ጎጆ፥ እንደተከበበችም ከተማ ሆና ቀረች። 💀 ስለዚህ እንመለስ ከስኦል ሆድ ከዚያ አስፈሪ ጨለማ እንውጣ ኢሳ 1፦ 16-20 16፤ ታጠቡ ሰውነታችሁንም አንጹ፤ የሥራችሁን ክፋት ከዓይኔ ፊት አስወግዱ፤ ክፉ ማድረግን ተዉ፥ 17፤ መልካም መሥራትን ተማሩ፥ ፍርድን ፈልጉ፥ የተገፋውን አድኑ፥ ለድሀ አደጉ ፍረዱለት ስለ መበለቲቱም ተምዋገቱ። 18፤ ኑና እንዋቀስ ይላል እግዚአብሔር፤ ኃጢአታችሁ እንደ አለላ ብትሆን እንደ አመዳይ ትነጻለች፤ እንደ ደምም ብትቀላ እንደ ባዘቶ ትጠራለች። 19፤ እሺ ብትሉ ለእኔም ብትታዘዙ፥ የምድርን በረከት ትበላላችሁ፤ 20፤ እምቢ ብትሉ ግን ብታምፁም፥ ሰይፍ ይበላችኋል፤ የእግዚአብሔር አፍ ይህን ተናግሮአልና። ፨ እግዚያብሔር ከዚያ አስፈሪ ጨለማ ከስኦል ሆድ ውስጥ መዉጣት እንድንችል ይርዳን አሜን ዮሐንስ ዲላ
"A pastor who doesn't get wet in the baptistry dries out in the ministry."
"በመጥመቅያ ውስጥ እርጥብ የማይሆን ፓስተር በአገልግሎት ይሞታል."
©️ Pastor Erton Kohler
አዲስ የተጋቡ ሙሽሮች አዲስ ወደገዙት ቤት ከገቡ ሰንበትበት ብለዋል ይላል ታሪኩ። በአንዱ ቀን ሙሽሪት ቁርስ እያቀራረበች ወደ መስኮቱ ስትመለከት ጎረቤቷ ልብስ እያሠጠች ትመለከታለች ከዛ አይኗን ማመን ተሳናት ባለቤቷን ጠርታው "ተመልከት ይቺ ገረቤታችንን ምንም የማታውቅ፣ በደንብ ሳታጠራ ልብስ እያሰጠች ትለዋለች" ተያት ነበር መልሱ ብዙ ቀኖችን ስታያት ተመሳሳይ አይነት አስተጣጠብ ነበር። አንድ ቀን ግን ተዓምር ሆነ ንፁህ ልብስ አሰጠች ሙሽሪት ደስ ብሏት ባለቤቷን ጠርታው "ዛሬ ማን እንደነገራት አላውቅም ግን በደንብ አጥባለች፣ ንፁህ ልብስ እኮ ነው ያሰጠችው" ትለዋለች
ባል ረጋ ብሎ "የኛ መስታወት ነበር የቆሸሸው፣ በጠዋት ተነስቼ አፅድቼው ነው" አላት።
ሰው በጌታ ከሆነ በኃላ ሊቀየሩ ከሚገቡ ነገሮች መሃል አንዱ ዕይታ ነው። ምክንያቱም "የሰውነት መብራት ዓይን ናት። ዓይንህ እንግዲህ ጤናማ ብትሆን፥ ሰውነትህ ሁሉ ብሩህ ይሆናል፤ ዓይንህ ግን ታማሚ ብትሆን፥ ሰውነትህ ሁሉ የጨለመ ይሆናል። እንግዲህ በአንተ ያለው ብርሃን ጨለማ ከሆነ፥ ጨለማውስ እንዴት ይበረታ! " ማቴ 6:22-23
አባት ሆይ ሌሎችን የምናይበት ዕይታ ፍፁም ርህራሄን የተሞላበት ይሆን ዘንድ እርዳን!
መረዶህዳር 28/2018 የቤ/ያን አባል የሆኑት ወ/ሮ አለምፀሃይ ሾንዴ (የአብነት ዮሃንስ ባሌቤት) አባቷን አስቀብራ ዛሬ እሁድ ትመለሳለች ስለሆነም ከሰዓት 9:00 ጀምሮ ቤተ ክርስቲያን የማፅናኛ ፕሮግራም ስለምታካሂድ የቤ/ያን አባላት በሙሉ በስፍራው እንድትገኙ እናስታውቃለን። አድራሻ፡ 05 አድቬንቲስት ግቢ
📌ሐዋሳ
⏰ ማለዳ 3:00-6:30 የጥምቀት እና የቃለ እግዚአብሔር ጊዜ
⏰ ከሰዓት 9:00-11:00 የምስክርነት እና የምርቃት መርኃ ግብር
📌ሐዋሳ መነሃሪያ ቤተ ክርሰቲያን
⏰ ማለዳ 3:00-6:30 የጥምቀት እና የቃለ እግዚአብሔር ጊዜ
⏰ ከሰዓት 9:00-11:00 የምስክርነት እና የምርቃት መርኃ ግብር
ወደ_ልቡም_ተመልሶ_Having_returned_to_his_heart_December,_2025_By_Atkilt.pdf18.20 MB
