የሀዋሳ ታቦር ሰባተኛ ቀን አድቬንቲስት አለም አቀፍ ቤተክርስቲያን (Hawassa Tabour 7th day Adventist INternational Church
Open in Telegram
1 070
Subscribers
No data24 hours
+157 days
+3930 days
Posts Archive
ማስታወቂያነገ እሁድ ጥር 24/2018 ዓ.ም በታቦር 7ተኛ ቀን ቤ/ክርስቲያን ከ 3:00 ሰዓት ጀምሮ ቢዝነስ ሚቲንግ [Bussines Meeting] ስላለ ሁላችሁም የቤ/ክርስቲያኒቱ ምዕመናል እንድትገኙ ቤ/ክርስቲያን ታሳስባለች::
ያጠነክረናል
የእግዚአብሔር ቅዱስ መንፈስ በሕይወታችን ከሚሰራቸውሥራዎች መካከል አንደኛው በውስጡ ሰውነታችን እንጠነክር ዘንድ በኃይል በመሙላት ይጠብቀናል። ሐዋርያው ጳውሎስ ይህንን የመንፈስ
ቅዱስ ሥራ አስመልክቶ ሲጸልይ እንዲህ ይላል፦
““በውስጥ ሰውነታችሁ እንድትጠነክሩ፣ ከክብሩባለጠግነት በመንፈሱ በኩል ኀይል እንዲሰጣችሁ እጸልያለሁ፤” ኤፌ 3፡ 16
ይህ በመንፈስ ቅዱስ ኃይል የምንጠነክርበትና በጠላት
ግፍተራ ወደ ጥፋት ገደል እንዳንወድቅ የምንጠበቅበትን መንገድ ጳውሎስ ጨምሮ ሲገልጽ እንዲህ ይላል፦
“እግዚአብሔር በሰጠን በመንፈስ ቅዱስ ፍቅሩንበልባችን አፍስሷልና።” ሮሜ 5፡ 5
መንፈስ ቅዱስ በልባችን የሚያፈሰው የእግዚአብሔር
ፍቅር ከእርሱ ጋር ባለን ግንኙነት የሚያሳድገን እንዲሁም በምንም አይነት ሁኔታ ውስጥ ብናልፍ ጠንክረን እንድንቆም የሚያደርገንየኃይላችን ምንጭ ነው። ከዚህ ፍቅሩ የተነሳ በጠላታችን በዲያቢሎስ ላይ ድል ነሺዎች መሆን እንችላለን።
“ከክርስቶስ ፍቅር የሚለየን ማን ነው? ችግር
ነው ወይስ ሥቃይ፣ ወይስ ስደት፣ ወይስ ራብ፣ ወይስ ዕራቍትነት፣ ወይስ አደጋ፣ ወይስ ሰይፍ? … ምንም አይለየንም፤በዚህ ሁሉ በወደደን በርሱ ከአሸናፊዎች እንበልጣለን። ይህን ተረድቻለሁ፤ ሞትም ይሁን ሕይወት፣ መላእክትም ይሁኑ
አጋንንት፣ ያለውም ይሁን የሚመጣው፣ ወይም ማንኛውም ኀይል፣ ከፍታም ይሁን ጥልቀት ወይም የትኛውም ፍጥረት፣በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ካለው ከእግዚአብሔር ፍቅር ሊለየን አይችልም።”
ሮሜ 8፡ 35-39
አዎ፣ በመንፈስ ቅዱስ የእግዚአብሔር ፍቅር በልባችን
ሲፈስ በውስጡ ሰውነታችን እንጠነክራለን፤ ምንም ነገር ከእርሱ ፍቅር ሊለየን አይችልም። ነፍሳችን በመንፈስ ቅዱስ ኃይል የተጠበቀችትሆናለች።
አባት ሆይ፣ በመንፈስ ቅዱስ በልባችን በምታፈሰው
በፍቅርህ ኃይል ሁልጊዜ ስለምትጠብቀን እናመሰግንሃለን። አሜን።
በ ኤልሮኢ ደስታ
አስቸኳይ የቦርድ ስብሰባ ጥሪሠላም ይብዛላችሁ የቤተ ክርስቲያን የቦርድ አባላት በሙሉ ! ነገ ጥር 16 2018 ዓ.ም ከቀኑ 11፡00 አስቸኳይ የቦርድ ስብሰባ ስለሚኖረን በቦርድ መሰብሰቢያ አዳራሽ እንድትገኙ በጌታ ፍቅር እንጠይቃለን። ተባረኩ!! ወ/ዊ ሲድራቅ ብርሃኑ የቤተ ክርስቲያኒቱ ወንጌላዊ
የሶስቱ መላዕክት መልዕክት አብሳሪዎች ሚኒስትሪ ከደቡብ ኢትዮጵያ ሰበካ ጋር በመተባበር “ወንጌልን እንዴት እንስበክ?” በሚል ርዕስ ጥር 2 (ቅዳሜ ከሰዓት) ከ9 ሰዓት ጀምሮ እና ጥር 3 እሁድ ከጠዋት እስከ 8 ሰዓት በሀዋሳ ከተማ እና በዙሪያዋ ከሚገኙ አጥብያዎች ለመጡ ወጣቶች በታቦር ቤ/ክ ልዩ ስልጠና ሰጥተናል።
በስልጠናው ወቅት ከሰበካው ወ/ዊ ውቂያኖስ (የሰበካው ዋና ፀሀፊ)፣ ወ/ዊ መኮንን (የሰበካው ወጣቶች ዘርፍ ዳይሬክተር) እና አቶ መብራቱ (የሰበካው ኮሚኒኬሽን ዘርፍ ዳይሬክተር) የተገኙ ሲሆን፣ እሁድ ቀን ከወጣቶቹ ጋር የሰበካው ወጣቶች ዘርፍ አስተባባሪ በቀጣይ የወንጌል ስራ ሂደት ውይይት አድርገዋል።
በሁለቱ ቀናት ስልጠናውን በድምሩ ከ80 የሚበልጡ ወጣቶች የታደሙት ሲሆን፣ ብዙዎች በጣም ደስተኛ እንደነበሩና ጠቃሚ ትምህርት እንዳገኙበት ተናግረዋል።
ምስጋና፡-
1. በነገር ሁሉ የረዳንን ያገዘንን ጌታ እግዚአብሔርን ከልብ እናመሰግናለን፣ ክብር ሁሉ ለስሙ ይሁን።
2. የደቡብ ኢትዮጵያ ሰበካ ስላደረጉልን ጥሪ፣ ስላሳዩን መልካምነት ጌታ እግዚአብሔር ይባርካችሁ ለማለት እንወዳለን።
3. የሀዋሳ ከተማ አቀፍ ዞን መሪዎችንና የታቦር 7ኛ ቀን አድቬንቲስት ቤ/ክ ቦርድ አስተዳደር ክፍሎችን በሙሉ ከልብ እናመሰግናለን።
4. በሁለቱም የስልጠናው ቀናት የተገኙትን ወጣቶች ከልብ እናመሰግናለን።
ፀሎት፡- ጌታ ቢፈቅድ በዲላ ከተማ ለሚደረገው የወንጌል ስርጭትና በደቡብ ኢትዮጵያ ሰበካ ለሚሰራው የወንጌል ስራ እንቅስቃሴ ሁሉ እንድትፀልዩ በጌታ ፍቅር እንጠይቃችኋለን።
መርዶ
ጥር 2,2018
እህታችን አማረች (የአቶ ታደገ ሎደሞ ባለቤት አባታችውን አስቀብረው ነገ እሁድ 8:00 ወደ ቤታቸው የሚመለሱ በመሆኑ ምዕመናን በመድረስ እንድታፅናኑ ቤተክርስቲያን ታሳስባለች።
ቤተክርስቲያንም እግዚአብሔር ለቤተሰቡና ለዘመዶች መፅናናትን እንዲሰጥ ትፀልያለች
አድራሻ:- ታቦር ሰባተኛ ቀን አድቬንቲስት ቤተክርስቲያን ግቢ ውስጥ
📢 የምስራች በሀዋሳ ከተማ እና አካባቢዋ ለምትገኙ ወጣቶች በሙሉ!
📖 ልዩ የወንጌል ዘመቻ ስልጠና
📍 ቦታ፡ በሀዋሳ ታቦር ሰባተኛ ቀን አድቬንቲስት ቤተ/ያን ⛪️
🗓 ቀን እና ሰዓት፡ 👉 ጥር 02 ቅዳሜ፥ ከሰዓት 9:00 ሰዓት ጀምሮ ⏰
👉 ጥር 03 እሁድ፥ ማለዳ ከ2:00 - 6:00 ሰዓት ☀️
🙌 ሁላችሁም ተጋብዛችኋል! 🙌
መርዶ30/4/18 የቤተ ክርስቲያናችን አባል የሆኑት የጋሽ አስፋው አኒቶ፣ አዲሴና ጌቱ አኒቶ ወንድማቸው ከዚህ ዓለም ድካም ስላረፉ፣ አስቀብረው ነገ ዓርብ (01/5/18) ከቀኑ 9፡00 ላይ ወደ ሀዋሳ የሚመለሱና በአቶ አዲሴ አኒቶ ቤት (አማካይ ሥፍራ ላይ) የሚቀመጡ ሲሆን የቤተ ክርስቲያናችን አባላት ለቅሶ እንድትደርሱ እናስታውቃለን። አድራሻ፡ ጎድጓዳ ሰፈር ጋሽ አስፋው አኒቶ +251916861024
