en
Feedback
የሀዋሳ ታቦር ሰባተኛ ቀን አድቬንቲስት አለም አቀፍ ቤተክርስቲያን (Hawassa Tabour 7th day Adventist INternational Church

የሀዋሳ ታቦር ሰባተኛ ቀን አድቬንቲስት አለም አቀፍ ቤተክርስቲያን (Hawassa Tabour 7th day Adventist INternational Church

Open in Telegram

እግዚአብሄርን ለመገናኘት ተዘጋጅ

Show more
1 070
Subscribers
No data24 hours
+157 days
+3930 days
Posts Archive
ውድ ምዕመናን፣ በ2018 ዓ.ም በታቦር ሰባተኛ ቀን አድቬንቲስት ቤተክርስቲያን ለማገልገል የተመረጡትን ወንድሞችና እህቶች ስም ዝርዝር እንደሚከተለው ቀርቧል። የተመረጣችሁ አገልጋዮች በዚህ ዓመት በተ
+2
ውድ ምዕመናን፣ በ2018 ዓ.ም በታቦር ሰባተኛ ቀን አድቬንቲስት ቤተክርስቲያን ለማገልገል የተመረጡትን ወንድሞችና እህቶች ስም ዝርዝር እንደሚከተለው ቀርቧል። የተመረጣችሁ አገልጋዮች በዚህ ዓመት በተሰጣችሁ ኃላፊነት በታማኝነት እንድታገለግሉ እግዚአብሔር ጥበብና ኃይል እንዲሰጣቸው ቤተክርስቲያን ትፀልያለች። ውድ የተከበራችሁ የቤተክርስቲያናችን ምዕመናንም እንደተለመደው ይህን በመረዳት በጸሎትና በትብብር ከእነርሱ ጋር እንድትቆሙ በጌታ ፍቅር እንጠይቃችኋለን። "እንዲሁ ሰው እኛን እንደ ክርስቶስ ሎሌዎችና እንደ እግዚአብሔር ምሥጢር መጋቢዎች ይቍጠረን። እንደዚህም ሲሆን፥ በመጋቢዎች ዘንድ የታመነ ሆኖ መገኘት ይፈለጋል። '' (1ኛ ቆሮንቶስ 4:1-2) እግዚአብሔር ቤተክርስቲያናችንን እና ሀገራችንን ይባርክ። ሲድራቅ የቤተክርስቲያኒቱ ዋና ወንጌላዊ የካቲት 30,2018 ዓ.ም ሀዋሳ

የሀዘን መግለጫ😭😭😭 ቀን የካቲት 29,2018 😭 የቤተክርስቲያናችን የዲያቆን ዘርፍ አገልጋይ የሆኑት የአቶ ድራጎ ቱሚዬ የበኩር ልጅ በህክምና ስትረዳ ቆይታ ትናንት አርፋለች። 💒 በልጃችን ህልፈት ቤተክርስቲያን እጅግ ማዘኗን እየገለፀች ለቤተሰባቸውና ለመላው የቤተክርስቲያናችን ምዕመናን መፅናናትን ትመኛለች። 🪦 የቀብር ሥነ- ሥርዓት ዛሬ እሁድ የካቲት 29,2018 ዓ.ም ሚሽን መካነ መቃብር ከረፋዱ 5 :00 ሰዓት ይፈፀማል!! 📇አድራሻ:- ከጤና ቢሮ ወደ ታቦር አድቬንቲስት ቤተክርስቲያን ሲሄዱ ኢቫን ትምህርት ቤት አካባቢ(ፓስተር ዮሴፍ መኖሪያ ቤት አጠገብ)

ሰላም ቤተሰብ! መልካም ሰንበት ይሁንላችሁ! ፓ/ር ዌስ ፔፐርስ እና ቤተሰቡ በሀዋሳ አርሲ ነጌሌ ... ከ ኢት ኢስ ሪትን ቡድን ጋር ጌታን ብዙ እንዳገለገሉ ለብዙዎችም መጠመቅ ምክንያት እንደሆኑ ይታወቃል። ዛሬ ደግሞ ማታ በእኛ አቆጣጠር ከምሽቱ 1፡00 ሰዓት ላይ ትንሿ ልጃችን ስለምትጠመቅ በቅርብ ያላችሁ በአካል በሩቅ ያለንም በቀጥታ ስርጭት የሚከተለውን ማስፈንጠሪያ በመጠቀም ታደሙልኝ ብለዋችኋል። https://southbaysda.org/livestream ተባረኩ!

የ2018/2019 የታቦር ቤተ ክርስቲያን የቦርድ መማክርት 1.ወንጌላዊ ሲድራቅ - ሰብሳቢ 2. ወንጌላዊ ውቅያኖስ አሰፋ - ምክትል ሰብሳቢ 3. ዋና ፀሐፊ - አቶ ዱሬሳ የመመ 4. ረዳት ፀሐፊ -አቶ አረጋ ሂቦሮ 5. ገንዘብ ያዥ  - ወ/ሮ ኤደን ይስሀቅ 6.ኦዲተር - አቶ ቹቹ አንባዬ  7. ሽማግሌ ዘርፍ      አቶ ጰጥሮስ ጎደቦ - ዋና ሽማግሌ     አቶ ሰለሞን ፀጋዉ     አቶ ዮሴፍ ሜላ        አቶ ግርማ ጉዬ      ዶ/ርአላዛር ኤርገና      ፓ/ር አደራ አቢጤ      አቶ ሚሊክያስ ቢትሬ 8. ወጣት ዘርፍ - አቶ ውብሸት ማርቆስ 9. ግንኙነት ዘርፍ - አቶ ናትናኤል ሚሊዮን 10. ቤትና ቤተሰብ - አቶ አፈወርቅ ባረና 11. ፍቃደኛ ወንጌላዊ - አቶ ዮሴፍ ኤርጌጤ 12. መጋቢነት - አቶ ሰንበቶ ሌጃጎ 13. ሰንበት ት\ት- አቶ አበበ ለጋሶ 14. በጎ አድራጎት - ዶ/ር አየነው አበራ 15. ፀሎት ዘርፍ - ወ/ሮ ታሪኳ ቦርኮ 16. እህቶች ዘርፍ - ወ/ሮ ይመኙሻል ጌታቸዉ 17. ወንድ ዲያቆን - አቶ ምንዳዬ ዮሐንስ 18. ሴት ዲያቆን - ወ/ሮ እልፍነሽ ሳሙኤል 19. ሙዚቃ ዘርፍ - አቶ ዘውዴ አሳሞ  20. መዘመራን ዘርፍ - ወ/ሪት መታሰቢያ ገብርሃና 21. ጤና ዘርፍ - ዶ/ር ፀደይ ዘካርያስ 22. ልጆች አገልግሎት ዘርፍ - አስናቀች ቆርጋ 23. ጎዳና ፈላጊ - ውድነሽ ዳና  24. ሙስሊም ክርስቲያን ዘርፍ - ታማኝ ታረቀኝ መልካም የአገልግሎት አመት ይሁንላችሁ!!!

ተሻግሮ ወራጅ አለ
በየቀኑ የምንሰማት "ተሻግሮ ወራጅ አለ" የምትለዋ አጭር አረፍተ ነገር የሰውን ልጅ የኑሮ እና የህይወት ጉዞ ትገልጻለች። ታክሲዋ ዓለም ናት እኛ ደግሞ ተጓዦች። ታክሲ ውስጥ አንዳችን ሌላችንን ሳናውቅ በተለያየ የኑሮ ደረጃ እና ስሜት ውስጥ ሆነን አብረን እንነጉዳለን። ሆኖም ግን ምንም ያህል ብንቀራረብና ብናወራም የመውረጃ ፌርማታችን ግን የግል ነው። ሌላው ባልደረሳበት ቦታ ላይ አንዱ "ወራጅ አለ!" ብሎ ይወርዳል።ሞትም ይሁን የሕይወት ምዕራፍ ለውጥ፣ ሁላችንም የየግላችን መውረጃ ሰዓት እንዳለን ያሳየናል። ሰው "ተሻግሮ" ወራጅ አለ ሲል አሁን ካለበት ቦታ ጥቂት ራቅ ብሎ የሚታየው መዳረሻ ላይ መድረሱን ማወጁ ነው። በሕይወት ፍልስፍናም "መሻገር" ማለት ካለፉበት ምዕራፍ ወጥቶ ወደማያውቁት አዲስ ዓለም መግባት ነው። ታክሲዋ ቆማ እኛ ስንወርድ፣ ለታክሲዋ የቀረነው ተሳፋሪዎች ዉስጧ ብንቆይም የወረደው ሰው ግን አዲስ መንገድ ይጀምራል። ጊዜው ሲደርስ ረዳቱ "መጨረሻ!" ይላል። መጀመሪያ ላይ በሰው ተሞልታ፣ በጫጫታና በሳቅ ደምቃ የነበረችው ታክሲ፣ መጨረሻ ላይ ጭር ትላለች። ይህ የሚያሳየን ጊዜያዊነትን እና ማንም በዚህች ዓለም ውስጥ ለዘላለም እንደማይኖር ነዉ።ባዶነት ዓለም ከመምጣታችን በፊት ነበረች፣ ከሄድን በኋላም ትኖራለች። እኛ ግን ለተወሰነ ደቂቃ መቀመጫ ተከራይተን የምናልፍ እንግዶች ብቻ ነን። ሕይወት ልክ እንደ አዲስ አበባ ታክሲ ናት። መጨናነቅ፣ መገፋፋት፣ አንዳንዴም ሳቅና ጨዋታ አለ ግን ደግሞ ሁልጊዜም ቢሆን "ተሻግሮ" ወራጅ አይጠፋም። ዋናው ቁምነገር መውረጃችን ሲደርስ የምንወርድበት ቦታ ሰላምና ደስታ የሚገኝበት መሆኑ ላይ ነው። አዳነ ባደቦ እንደፃፈው

የቤትና ቤተሰብ ሳምንት
ጊዜ: የካቲት 29- መጋቢት 5 ቦታ: ታቦር ቤ/ክ ሰዓት: 12:00

12 እግዚአብሔርም ለምድርህ በወራቱ ዝናብ ይሰጥ ዘንድ፥ የእጅህንም ሥራ ሁሉ ይባርክ ዘንድ መልካሙን መዝገብ ሰማዩን ይከፍትልሃል፤ ለብዙ አሕዝብም ታበድራለህ፥ አንተ ግን ከማንም አትበደርም። 'ኦሪት ዘዳግም 28:12' https://play.google.com/store/apps/details?id=com.nippt.bible.free&hl=en

የሀዘን መግለጫ 08/06/2018 የቤተ ክርስቲያናችን አባል እና መስራች የሆኑት የፓስተር አደራ አቢጤ( ወንድም) ከዚህ አለም ድካም አርፈዋል ቤተ ክርስቲያናችን በወንድሙ ማረፍ የተሰማትን ሀዘን እየገለፀች ለቤተሰቡና ወዳጅ ዘመዶቹ መፅናናትን ትመኛለች። የቀብር ስነ ስርዓት ዛሬ እሁድ 08\06/2018 ዓ.ም በቱላ ከተማ በ 6 ሰዓት ይፈፀማል። አድራሻ፡ ቱላ 7ተኛ ቀን አድቬንቲስት ቤተ ክርስቲያን ወረድ ብሎ

ወቅታዊ መረጃ፡ ስለ ሰባተኛ ቀን አድቬንቲስት ቤተክርስቲያን የቦታ ይገባኛል ጥያቄ ትላንት በነበረው ሁኔታ፣ የሰባተኛ ቀን አድቬንቲስት ቤተክርስቲያን ወንጌላውያን እና ምዕመናን በቤተክርስቲያናችን ይዞታ ላይ ለተነሳው ቅሬታ አቤቱታ ለማሰማት በከተማው ከንቲባ ጽሕፈት ቤት ተገኝተናል። የከንቲባው ምላሽ፦ ክቡር ከንቲባው ጩኸታችንን ሰምተው ጉዳዩን በአፋጣኝ እንደሚመለከቱትና ምላሽ እንደሚሰጡበት ቃል ገብተውልናል። ክቡር ከንቲባው ለፍትህ ባላቸው ቁርጠኝነትና በመልካም አስተዳዳሪነታቸው ጉዳያችንን በአግባቡ እንደሚፈቱት ሙሉ እምነት አለን። ለጸሎት፦ ወደፊት በሚኖሩት ሂደቶች ሁሉ እግዚአብሔር ጣልቃ እንዲገባና ፍትህ እንዲነግስ በጸሎት እንድታስቡን እንጠይቃለን። ለምስጋና፦ በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ ሀገር ሆናችሁ በማህበራዊ ሚዲያ ድምፅ በመሆን፣ መረጃዎችን በማጋራት (Share) እና ከጎናችን በመቆም አጋርነታችሁን ላሳያችሁ ሁሉ እግዚአብሔር ይባርካችሁ። ቀጣዩን ሂደት እና ዝርዝር መረጃዎችን በጽሑፍ በቅርቡ የምናሳውቅ መሆኑን እንገልጻለን።

ወቅታዊ መረጃ፡ ስለ ሰባተኛ ቀን አድቬንቲስት ቤተክርስቲያን የቦታ ይገባኛል ጥያቄ ትላንት በነበረው ሁኔታ፣ የሰባተኛ ቀን አድቬንቲስት ቤተክርስቲያን ወንጌላውያን እና ምዕመናን በቤተክርስቲያናችን ይዞታ ላይ ለተነሳው ቅሬታ አቤቱታ ለማሰማት በከተማው ከንቲባ ጽሕፈት ቤት ተገኝተናል። የከንቲባው ምላሽ፦ ክቡር ከንቲባው ጩኸታችንን ሰምተው ጉዳዩን በአፋጣኝ እንደሚመለከቱትና ምላሽ እንደሚሰጡበት ቃል ገብተውልናል። ክቡር ከንቲባው ለፍትህ ባላቸው ቁርጠኝነትና በመልካም አስተዳዳሪነታቸው ጉዳያችንን በአግባቡ እንደሚፈቱት ሙሉ እምነት አለን። ለጸሎት፦ ወደፊት በሚኖሩት ሂደቶች ሁሉ እግዚአብሔር ጣልቃ እንዲገባና ፍትህ እንዲነግስ በጸሎት እንድታስቡን እንጠይቃለን። ለምስጋና፦ በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ ሀገር ሆናችሁ በማህበራዊ ሚዲያ ድምፅ በመሆን፣ መረጃዎችን በማጋራት (Share) እና ከጎናችን በመቆም አጋርነታችሁን ላሳያችሁ ሁሉ እግዚአብሔር ይባርካችሁ። ቀጣዩን ሂደት እና ዝርዝር መረጃዎችን በጽሑፍ በቅርቡ የምናሳውቅ መሆኑን እንገልጻለን። ፍትህ ለቤተክርስቲያናችን!

በኢትዮጵያ ከአንድ ክፍለ ዘመን በላይ ያስቆጠረው የሰባተኛ ቀን አድቬንቲስት ቤተክርስቲያን፤ በሲዳማ ክልል ሐዋሳ ከተማ የሚገኝ ታሪካዊ ይዞታው ለግለሰቦች ተላልፎ ተሰጥቷል። ይህ ደግሞ "ግልጽ ያልሆነ የመብት ጥሰት" ነው። ይህ ይዞታ ከንጉሠ ነገሥቱ ዘመን ጀምሮ ቤተክርስቲያኒቱ ስትጠቀምበት የቆየችው፣ የመኖሪያ ቤቶች፣ አጥር እና የእንግዳ ማረፊያዎችን የያዘ ግቢ ነው። ይህ ስፍራ ለብዙ ዓመታት ለቤተክርስቲያኒቱ ማህበራዊ እና መንፈሳዊ አገልግሎቶች ሲውል የቆየ ቢሆንም፣ አሁን ግን ባልታወቀ ምክንያት ለግለሰብ እንዲሰጥ ተወስኗል። አድቬንቲስት ቤተክርስቲያን በኢትዮጵያ ከመንፈሳዊ አገልግሎት ባለፈ፤ ዘመናዊ የጤና ተቋማትን (ሆስፒታሎችን) በመክፈት፣ በርካታ ምሁራንን ያፈሩ ኮሌጆችንና ትምህርት ቤቶችን በማቋቋም፣ እንዲሁም ሰፊ የበጎ አድራጎት ሥራዎችን በመሥራት ለአገር ባለውለታ መሆኗን የሚታወቅ ነው። የቤተክርስቲያኒቱ መሪዎችና ምእመናን ጉዳዩን ለሚመለከታቸው የመንግሥት አካላት አቤቱታ እያቀረቡ ይገኛሉ። እኛም የቤተክርስቲያን አባሎች በፀሎት፣ በመረጋጋት የሕግ የበላይነት እንዲከበር ጥሪያችንን አናቀርባለን።
በመሆኑም ነገ ጠዋት 2:30 ለሚመለከተውን አካል ቅሬታ ለማቅረብ በሀዋሳ ከተማ ከንቲባ ጽህፈት ቤት (ወልደ አማኑኤል) የቤተክርስቲያን አባሎች እድንገኝ ሲል ቤተክርስቲያን በጌታ ፍቅር ትጠይቃለች

የመጨረሻው ፈተና " እግዚአብሔር ለእያንዳንዱ ሰው የመጨረሻውን ፈተና የሚሰጥበት ጊዜ በቅርቡ ይመጣል። ሰዎች የአውሬውን ምልክት እንድንቀበል ሊያስገድዱን ይሞክራሉ። ~ በእምነታቸው ደካማ የሆኑ ሰዎች ምልክቱን እንዲቀበሉ ለሚያስገድዷቸው መሪዎች ይታዘዛሉ። ~ ቀስ በቀስ እነዚህ ሰዎች የሰውን ሀሳብ እና ህግጋት ይከተላሉ። ስድብን፣ እስራትን እና ሞትን ይፈራሉ፣ ስለዚህ የአውሬውን ምልክት በቀላሉ ይቀበላሉ። ~ . . .“በዚያን ጊዜ ኢየሱስን ከልባቸው የሚያገለግሉት እነማን እንደሆኑ እንመለከታለን። የኢየሱስ እውነተኛ ተከታዮች ከእርሱ ጋር ይቆማሉ። ከእነዚህ ተከታዮች መካከል ብዙዎቹ ለእግዚአብሔር ለመቆም ይፈሩ የነበሩ ናቸው፤ ብዙም ድፍረት አልነበራቸውም። አሁን ግን ከኢየሱስ እና ከእውነት ጎን መሆናቸውን ያስታውቃሉ። ~ እጅግ ደካማ እና ፈሪ የነበሩ አባላት እንደ ንጉሥ ዳዊት ደፋር ይሆናሉ። እነዚህ አባላት እግዚአብሔርን ሙሉ በሙሉ ያገለግላሉ። ~ ነገሮች እየከፉ በሄዱ ቁጥር፣ የእግዚአብሔር ሕዝቦች ይበልጥ እንደ ከዋክብት ደምቀው ያበራሉ። ሰይጣን ይዋጋቸዋል፣ ይጎዳቸዋልም። ይሁን እንጂ የእግዚአብሔር ታማኝ ተከታዮች ተጋድሎውን በኢየሱስ ስም ያሸንፋሉ።”—ኤለን ጂ. ዋይት፣ የቤተክርስቲያን ምክሮች፣ ጥራዝ 5፣ ገጽ 81, 82 በገዛኸኝ ግርማ