💦👨⚕️አስራት ወልደየስ ጤና ሳይንስ ካምፓስ👩⚕️
Open in Telegram
1 534
Subscribers
+124 hours
+197 days
+2330 days
Posts Archive
Repost from Tikvah-University
እስከ ሐምሌ 24/2018 ዓ.ም ተራዝሟል!
የብቃት ምዘና ፈተና ለመውሰድ መረጃ በማስተሳሰር ላይ የምትገኙ የጤና ሙያ ተመራቂዎች፣ የመረጃ ማስተሳሰሪያ ጊዜ-ገደቡ እስከ ሐምሌ 24/2018 ዓ.ም የተራዘመ መሆኑን ጤና ሚኒስቴር አሳውቋል።
ቀነ-ገደቡ ሐምሌ 17/2018 ዓ.ም ያበቃል ተብሎ የነበረ ቢሆንም፤ በተለያዩ ምክንያቶች መረጃ ማስተሳሰር ያላጠናቀቁ ተመራቂዎች በመኖራቸው ቀነ-ገደቡ እስከ ሐምሌ 24/2018 ዓ.ም የተራዘመ መሆኑ ተገልጿል።
በመሆኑም በ https://hple.moh.gov.et/ ላይ በመግባት የብሔራዊ መታወቂያ መለያ ቁጥር (16 Digit FAN) በማስገባት አስፈላጊ መረጃዎችን በማሟላት ለምዝገባ እንድትዘጋጁ ሚኒስቴሩ አሳስቧል።
🔔 መረጃ የማስተሳሰር ሒደት እንዳለቀ የፈተና ጣቢያ መረጣ ሒደት ይቀጥላል ተብሏል፡፡
@tikvahuniversity
በአስራት ወልደየስ ጤና ሳይንስ ካምፓስ የነጭ ጋወን ማልበስ ሥነ-ሥርዓት ተካሄደ
*************
በደብረብርሃን ዩኒቨርሲቲ አስራት ወልደየስ ጤና ሳይንስ ካምፓስ የሲ-1 የህክምና ተማሪዎችን የነጭ ጋወን ማልበስ ስነ-ስርዓት የካምፓሱ አመራሮች፣ መምህራን እና የህክምና ተማሪዎች በተገኙበት ሀምሌ 2 ቀን 2018 ዓ.ም በልዩ ዝግጅት ተካሂዷል፡፡
በካምፓሱ የህክምና ትምህርት ቤት መምህርና በሀኪም ግዛው ሆስፒታል የውስጥ ደዌ ስፔሻሊስት ሀኪም ዶ/ር አስራት ብርሃኑ በመርሃ ግብሩ መክፈቻ ላይ እንደገለጹት የነጭ ጋወን ማልበስ ሥነ-ሥርዓት በ1920ዎቹ መጀመሪያ የተጀመረ ሲሆን፣ ተማሪዎች ከፕሪ-ክሊኒካል ወደ ክሊኒካል ስልጠና መሸጋገራቸውን የሚያመለክት ክብር እና የሙያ ግዴታ ምልክት ነው። ነጭ ጋወኑ ከታካሚዎች ጋር በቅርብ የሚደረግ ግንኙነትን፣ ሙያዊ ኃላፊነትን፣ ታማኝነትን፣ ቁርጠኝነትን እና ጽናትን የሚወክል መሆኑን ገልጸዋል። በተጨማሪም ተማሪዎቹ ለዚህ ደረጃ እንዲደርሱ አስተዋጽኦ ላበረከቱ ወላጆች፣ መምህራን እና ሌሎች ድጋፍ አድራጊዎች ምስጋና አቅርበዋል።
በደብረብርሃን ዩኒቨርሲቲ አስራት ወልደየስ ጤና ሳይንስ ካምፓስ የሕክምና ትምህርትና አገልግሎት ምክትል ዳይሬክተር ዶ/ር ጌታነህ ደጀን በማጠቃለያ መልዕክታቸው እንዳሉት ተማሪዎቹ በክሊኒካል ስልጠናቸው የላቀ እውቀትን እንዲያገኙ፣ የመተባበር ባህልን እንዲያጎለብቱ፣ ሙያዊ ሥነ-ምግባርና ኃላፊነትን እንዲያ ጠናክሩ አሳስበዋል። በተጨማሪም መምህራን በትምህርትና በክሊኒካል ልምምድ ወቅት የሚያስፈልገውን ሁሉንም ድጋፍና ክትትል ለማድረግ ቁርጠኞች መሆናቸውን ገልጸዋል።
በመጨረሻም የነጭ ጋወን ማልበስ ሥነ-ሥርዓቱ በተሳካ ሁኔታ ተጠናቆ፣ ለፕሮግራሙ ስኬት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላበረከቱ መምህራንና የተማሪ ተወካዮች የምስክር ወረቀትና የእውቅና ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።
******
የሕዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ቡድን
ታዓማኝ እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት:-
የጤና ባለሙያዎች የሙያ ፈቃድ ፈተና በነሐሴ ወር 2018 ዓ.ም ይሰጣል። - ጤና ሚኒስቴር
ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በመጀመሪያ ዲግሪ ለተመረቃችሁ የጤና ባለሙያዎች የሙያ ፈቃድ ፈተና በነሐሴ ወር 2018 ዓ.ም ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የጤና ሚኒስቴር ገልጿል።
በመሆኑም መረጃችሁን ወደ ሲስተም ያላስገባችሁ ነባር እና አዲስ ተመዛኞች ከሰኔ 30 እስከ ሐምሌ 17/2018 ዓ.ም ድረስ ብቻ https://hple.moh.gov.et/ ላይ በመግባት የብሔራዊ መታወቂያ መለያ ቁጥር (FAN 16 Digit) በማስገባት አስፈላጊ መረጃዎችን በማሟላት ለምዝገባ እንድትዘጋጁ ሚኒስቴሩ አሳስቧል፡፡
መረጃ የማስተሳሰር ሂደት እንዳለቀ የፈተና ጣቢያ መረጣ ሂደት እንደሚቀጥል ተገልጿል፡፡
🔔 በሰኔ 2018 ዓ.ም የመውጫ ፈተና ተፈትናችሁ ያለፉችሁ ተመዛኞች የስም ዝርዝራችሁን በተማራችሁበት ተቋም አማካኝነት ወደ ሲስተም ማስጫን ይጠበቅባችኋል ተብሏል።
@tikvahuniversity
ለመላው የካምፓሳችን ተማሪዎች በሙሉ
ከት/ት ሚኒስቴር በመጣ መመሪያ መሰረት ማንኛውም ተማሪ 5ሚሊዮን ኮደርስ ስልጠና ወስዶ ሰርቲፊኬት ካላመጣ clearance እንደማይሰጠው እናሳስባለን።
የተማሪዎች አገልግሎት ዲን
+1
35 A+ ያመጣው ተማሪ
ብሩክ ደግነት ከደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ የፕ/ር አስራት ወልደየስ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የፋርማሲ ትምህርት ክፍል ተመራቂ ነው።
ብሩክ ከወሰዳቸው አጠቃላይ ኮርሶች 35 A+ በማምጣት እና 3.97 ውጤት በማስመዝገብ የሜዳልያ እና የዋንጫ አሸናፊ ሆኗል። 👏👏
ከሴቶች የከፍተኛ ውጤት ባለቤቷ
ተማሪ ትርንጎ ገዛኸኝ ከደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ የማኔጅመንት ትምህርት ክፍል በላቀ ማዕሰግ ተመርቃለች።
ከዘንድሮ ሴት ተመራቂዎች ከፍተኛ የሆነውን 3.96 አጠቃላይ ውጤት በማስመዝገብ የክብር ዋንጫ ተሸላሚ ሆናለች። 👏👏
ለካምፓሳችን አጠቃላይ አገልግሎቶች መሻሻል እንዲሁም እድገት መልካምም ሆነ መሻሻል ያለባቸውን ለመለየት ይህን መጠይቅ ሁሉም የካምፓሱ ተማሪዎች ልንሞላ ያስፈልጋል።
https://forms.gle/ZgmxWBMN8GBh25RXA
ለተመራቂ ተማሪዎች “Employability and Job Readiness” በሚል ርዕሰ ጉዳይ ስልጠና ተሰጠ
=================================
ሰኔ 15 ቀን 2018 ዓ.ም(አ/ወ/ጤ/ሳ/ካ)፡፡ በደብረብርሃን ዩኒቨርሲቲ አስራት ወልደየስ ጤና ሳይንስ ካምፓስ ለተመራቂ ተማሪዎች “Employability and Job Readiness” በሚል ርዕስ ስልጠና ተሰጠ።
ስልጠናው ከ82 በላይ ተማሪዎችን ያሳተፈ ሲሆን፣ ዓላማውም የተማሪዎችን የሙያ እና የአመራር ክህሎቶች በማጎልበት በሥራ ገበያው ተወዳዳሪ እንዲሆኑ፣ የተሻሉ የሥራ ዕድሎችን እንዲያገኙ እና በማህበረሰቡ ላይ አዎንታዊ ተፅዕኖ እንዲያሳድሩ ማገዝ ነው።
በካምፓሱ የተማሪዎች ሙያ ማሻሻያ ኦፊሰር ዶ/ር እየሩሳሌም ዳመና እንደገለጹት ስልጠናው ተመራቂ ተማሪዎች በአገር ውስጥና በዓለም አቀፍ የጤና ዘርፍ የሥራ ገበያ ተወዳዳሪ እንዲሆኑ፣ ለሙያ ሕይወታቸው የሚያስፈልጉ ክህሎቶችን እንዲያዳብሩ እና ለቀጣይ የሥራ ሕይወታቸው በቂ ዝግጅት እንዲያደርጉ ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑን ገልጸዋል። በተጨማሪም ስልጠናው ተግባር ተኮር በሆኑ ልምምዶች እና በእርስ በርስ የልምድ ልውውጥ የተደገፈ መሆኑን ጠቅሰዋል።
በስልጠናው የተካተቱት ዋና ዋና ርዕሰ ጉዳዮች የሙያ ተኮር ራስን መገምገም (Career-Focused Self-Assessment)፣ የሥራ ዓለምን መረዳት (Understanding the Employment World)፣ መሰረታዊ የቅጥር ብቃትና ሶፍት ስኪሎች (Essential Employability and Soft Skills)፣ የስረራ ማመልከቻ ደብዳቤና የሲቪ (CV) አዘገጃጀት እንዲሁም የቃለ መጠይቅ ክህሎቶች ናቸው ተብሏል፡፡
በስልጠናው ማጠቃለያ ላይ የአስራት ወልደየስ ጤና ሳይንስ ካምፓስ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ዶ/ር ቴዎድሮስ ክፍለዮሐንስ እና የሕክምና አገልግሎት፣ ትምህርትና ጥራት ኮርፖሬት ዳይሬክተር ዶ/ር ኤርሚያስ እንደውነት ተገኝተው ከተመራቂ ተማሪዎች ጋር ውይይት አድርገዋል።
በውይይቱ ወቅት ተማሪዎች በስልጠናው ያሳዩት ተሳትፎ፣ የመማር ማስተማር ሂደቱ ያሉት ጠንካራና ደካማ ጎኖች፣ እንዲሁም ወደፊት መሻሻል የሚገባቸው ጉዳዮች ላይ ጥያቄዎችና አስተያየቶች ቀርበው ሰፊ ውይይት ተካሂዷል።
በቀጣይ የሚሰጡ ስልጠናዎች የተማሪዎችን ፍላጎትና የክህሎት ማጎልበቻ ፍላጎቶች መሰረት ያደረጉ እንደሚሆኑ የስራ ሀላፊዎቹ ገልጸዋል።
ስልጠናው ተመራቂ ተማሪዎችን ለሥራ ዓለም በተሻለ ሁኔታ ለማዘጋጀት እና በሙያቸው ውጤታማ እንዲሆኑ የሚያግዝ ጠቃሚ መድረክ መሆኑ ተገልጿል።
************
#አስራት_ደም_ለጋሾች_ክበብ
#ASRAT_BLOOD_DONATOR'S_CLUB
ክበባችን #አስራት_ደም_ለጋሾች_ክበብ የደም ልገሳ መርሐ ግብር ከፊታችን ቅዳሜ ማለትም 13/10/2017 እስከ ሰኞ 14/10/2017 ዓ.ም ያደርጋል ስለሆነም የተለመደ ትብብራችሁን እንዲሁም አንድም እናት ወይም ማንኛውም ሰው ደም አስፈልጎት በ ደም እጥረት ምክንያት ልናጣው አይገባም በሚል ከ ልብ የመነጨ ርህራሄ ችሮታችሁን እንድትለግሱ ስንል በትህትና እንጠይቃለን።
#በጓደኛ
#በዲፓርትመንት
#በዶርም ሁሉንም በማስተባበር ደም እንዲለገስ የማድረግ የሁሉም ጤና ባለሞያ ኃላፊነት ነው።☺️
#የሚለግሱት_ደም_ሕይወት_መታደግ_እንደሚችል_የሚያውቁ_ሁሉ_የማይቀሩበት_መርሐግብር_ነው፡፡😊
ቀን:13/10/2018 እስከ 14/10/2018
ቦታ፡ መመገብያ ካፌ አካባቢ
"Donate blood save life"‼️
https://t.me/asrat_HSC
Join and share👆👆👆👆
ተ/ኅብረት
የሊጉ ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪዎች
አስራት ሊግ/ASRAT LEAGUE
Please Join and Share
👇👇👇👇👇👇👇👇
https://t.me/Asrat_League
እባክዎ ሊንኩን ለ ሌሎች ያጋሩ ይቀላቀሉ
ተወዳጁ የአስራት ሊግ ሊጠናቀቅ 1 ጨዋታ ብቻ ቀረ 🎉🎉🎉
💥የ2018 ዓ.ም የአስራት ሊግ ቶርናመንት የፍፃሜ ጨዋታ 💥
ነገ
Medicine Vs HO 1-3RD YR
9:00 LT
ቀበሌ 05 ሜዳ
ማን ያሸንፋል??
ነገ ቀበሌ 05 ሜዳ አይቀርም።✨✨
አስራት ሊግ/ASRAT LEAGUE
Please Join and Share
👇👇👇👇👇👇👇👇
https://t.me/Asrat_League
እባክዎ ሊንኩን ለ ሌሎች ያጋሩ ይቀላቀሉ
ነገ Exit Exam የምትወስዱ የጊቢያችን ተማሪዎች በሙሉ መልካም ፈተና ይሁንላችሁ ። እንደስከዛሬው ሁሉ በድል እንደምትወጡት እርግጠኞች ነን። ተረጋግታችሁ መስራት ብቻ በቂ ነው።
መልካም እድል!!!
Share: t.me/asrat_HSC
የመልካም ምኞት መግለጫ
በካምፓሳችን የህክምና ት/ት ክፍል Qualification የቃል ፈተና በመውሰድ ላይ ያላችሁ ተማሪዎች መልካም ፈተና እንዲሆንላችሁ እንመኛለን።
ፈጣሪ ይርዳችሁ!!!!
የተማሪዎች ኅብረት
Join & Share: t.me/asrat_HSC
Join & Share: t.me/asrat_HSC
Join & Share: t.me/asrat_HSC
