en
Feedback
Time Secondary school official channel

Time Secondary school official channel

Open in Telegram
270
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
ሰው ለመርዳት ሰው መሆን በቂ ነው !! ➡️➡️➡️➡️➡️➡️➡️➡️➡️➡️➡️➡️➡️ የታይም ሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎችና መምህራን ለብሄራዊ ደም ባንክ በተለያየ በሽታና ድንገተኛ አደጋዎች ለሚሰቃየው ማህበ
+9
ሰው ለመርዳት ሰው መሆን በቂ ነው !! ➡️➡️➡️➡️➡️➡️➡️➡️➡️➡️➡️➡️➡️ የታይም ሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎችና መምህራን ለብሄራዊ ደም ባንክ በተለያየ በሽታና ድንገተኛ አደጋዎች ለሚሰቃየው ማህበረሰባችን እኛም ደማችን በመስጠት ለወገናችን አለኝታ ሆነናል ።    እናመሰግናለን ‼️

Time secondary school ♦️♦️♦️♦️♦️♦️♦️♦️♦️ 2016 E.c First Term Final Exam schedule ‼️ ♦️♦️♦️♦️♦️♦️♦️♦️♦️♦️
Time secondary school ♦️♦️♦️♦️♦️♦️♦️♦️♦️ 2016 E.c First Term Final Exam schedule ‼️ ♦️♦️♦️♦️♦️♦️♦️♦️♦️♦️

============================= ለተከበራችሁ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎቻችን ወላጆች / አሳዳጊዎች ‼️ ============================= የሚቀጥለው ቅዳሜ በቀን 06/04/20
============================= ለተከበራችሁ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎቻችን ወላጆች / አሳዳጊዎች ‼️ ============================= የሚቀጥለው ቅዳሜ በቀን 06/04/2016 ዓ.ም ከጠዋቱ 2:30 ሰዓት ጀምሮ እስከ 5:00 ተማሪዎች በተገኙበት ከወላጆቻቸው ጋር በውጤትና ስነ ምግባር ጉዳይ ውይይት ስለሚደረግ ሁሉም ወላጅ/አሳዳጊ በዕለቱና በሰዓቱ ተገኝቶ በልጆቹ ጉዳይ መነጋገር የወላጅ/የአሳዳጊ ግዴታ መሆኑን ተገንዝቦ እንዲገኝ እያሳሰብን በዕለቱ ባልተገኙ ወላጆችና  ተማሪዎች ላይ  ት/ቤቱ አስተማሪ ዕርምጃ እንደሚወስድና ሀላፊነቱንም ወላጆች  የሚወስዱት ይሆናል ። ⏩ ት/ቤትና ወላጆች በጋራ ሁነው በልጆቻቸው መማር ማስተማርና ስነ -ምግባር ላይ  አብረው ካልሰሩ ውጤቱ የሚሆነው የጋራ ጉዳት ነውና ለልጆቻችን ጉዳይ አብረን እንምከር ፣ እንወያይ ፣ እንነጋገር ‼️ ማሳሰቢያ ‼️ ➡️➡️➡️➡️➡️ ➡️ ተማሪዎች ሀላፊነት ወስዶ የሚያስተምራቸው / ያስመዘገባቸው አካል በዕለቱ ተገኝቶ መወያየት ካልቻለ ሰኞ ፈተና ለመፈተን የማይፈቀድለት /ላት መሆኑ በጥብቅ እናሳስባለን !!

ከ9ኛ -12ኛ ክፍል ተማሪዎች እና ለት/ቤታችን ወላጆች/ አሳዳጊዎች በሙሉ ‼️ ።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።። እንደሚታወቀው ት/ቤታችን በተማሪዎች ውጤትና ስነ- ምግባር ላይ ዘወትር የትኩረት አቅጣጫዎቹ አድርጎ እየሰራ ይገኛል ሆኖም ት/ቤት ብቻውን የተለየ ታዕምር ሊፈጥር ስለማይችል ወላጆች ዘወትር የልጆቻቸው ሁኔታ በንቃት ሊከታተል ይገባል ። ⏩ የመቅረት ሁኔታ ➡️ የማርፈድ ሁኔታ ⏩ የውጤት ሁኔታ እና ስነ -ምግባር ላይ ዘወትር ሊከታተል ይገባል ተብሎ ይታሰባል !! ♦️ በአዲሱ የት /ት ፖሊሲ የወረዱ መመሪያዎች በተመለከተ 1. በሂሳብ/ በእንግሊዝኛ ት/ት በአንዱ ከ50% በታች ካመጣ/ች ወደ ቀጣዩ ክፍል ማለፍ አይችልም / አትችልም 2. በሁለት የት/ት አይነት ከ50%  በታች ካመጣ/ች አቬሬጁ/ጇ 53 ከመቶ  በላይ ካልሆነ ወደ ቀጣዩ ክፍል አያልፍም/አታልፍም 3. በሴሚስተር አስራ ሁለት /12/  ቀን ከቀረ/ ች ፈተና ላይ መቀመጥ አይችልም/አትችልም ‼️ ⏩ በዚህም መሰረት ተማሪዎቻችን ለማብቃትና ክፍተታቸው ምን እንደሆነ ለመለየት በታህሳስ ወር የሚሰጠው ከ9ኛ እስከ 11ኛ ክፍል  የማጠናከሪያ ት/ት በሳምንት ማክሰኞ ወይም ረቡዕ ሴቶች ብቻ እና በሳምንት ረቡዕ ወይም ማክሰኞ  ወንዶች ብቻ  እየተፈራረቁ ተምረው  ያላቸውን ለውጥ በመገምገም ከወላጆች ጋር በጥር / የካቲት ወር በሚኖረን ወላጅ በዓል የምንገመግመው መሆኑን በአክብሮት እንገልፃለን ። ማሳሰቢያ  ‼️ ======= 12ኛ ክፍሎች ማትሪክ ተፈታኝ በመሆናቸው   ከታህሳስ ወር ጀምሮ በተጠናከረ መልኩ የማትሪክ ጥያቄዎች በተለመደው መልኩ በመምህራኖቻቸው የሚሰጣቸው ይሆናል ። ⏩ በሚቀጥለው ቅዳሜ /06/04/12 / ከ12ኛ ክፍል ተማሪ ወላጆች ጋር ብቻ በውጤትና ስነ ምግባር ላይ ተማሪዎችና ወላጆች ባሉበት በጋራ ውይይት ይደረጋል ።

photo content
+1

photo content
+3

ታይም ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ።።።።።።።።።።።።።።።።።።። የ18ኛው ብሄር ብሄረሰቦች ቀን በድምቀት ተከበረ ‼️ ኢትዮጵያ ብዙሃ ባህል ፣ ቋንቋ እና ብሄር አካታ የያዘች ልዩነቶቿ ውበቷ እና አንድነቷ የጥንካሬዋ ምንጭ ሆና የቆየች ታላቅ ሀገር ናት ። እኛም ይህንን ለማሰብ እንደ ተቋም በስነ ምግባራቸው የታነፁ እና በውጤታቸው የዳበሩ ዜጎች እንድናፈራ ከተሰጠን ተልዕኮ ጎን ለጎን የብሄር ብሄረሰቦች በዓል ምክንያት በማድረግ በተለያዩ ዝግጅቶች በት/ቤታችን ደማቅ በዓል አክብረናል ። ለኘሮግራሙ መሳካት ለተባበራችሁን ወላጆች ፣ ተማሪዎችና ለበዓሉ ኤሸንት አቅራቢዎች በሙሉ በት/ቤቱ ስም እናመሰግናለን ። ➡️ 6:45 ላይ ኘሮግራማችንን ጨርሰን ተማሪዎቻችን ሸኝተናል ።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሰላምና ጸጥታ ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሊዲያ ግርማ በበኩላቸው በአዲስ አበባ ከተማ የተለያዩ የጸጥታ ችግሮችን ለመፍጠር የሚፈልጉ አካላት ትምህርት ቤቶች ዋነኛ የብጥብጥ ማዕከል እንዲሆኑ ትኩረት አድርገው እንደሚንቀሳቀሱ ጠቁመው ችግሩ የመማር ማስተማር ስራውን እንዳያውክ የትምህርት ማህበረ ሰቡ በቂ ግንዛቤ እንዲኖረው ማድረግ እንደሚገባ በመግልጽ የጸጥታው ክፍልም በጉዳዩ ተሳታፊ የሚሆኑ አካላትን በህግ ተጠያቂ የማድረግ ኃላፊነቱን በአግባቡ የሚወጣ መሆኑን አስታውቀዋል። መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ! You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ... TikTok፡- tiktok.com/@aaeducationbureau Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication Blog: - http://www.aacaebc.wordpress.com/ Website: - aaceb.gov.et Email;- aacaebc@gmail.com Instagram: - https://www.instagram.com/aacaeb/

በሰላማዊ መማር ማስተማር ዙሪያ በከተማ አስተዳደሩ ከሚገኙ የመንግስትና የግል 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሳነ መምህራን ጋር ውይይት ተካሄደ። (ህዳር 21/2016 ዓ.ም) ውይይቱን የአዲስ አበባ ከተ
+3
በሰላማዊ መማር ማስተማር ዙሪያ በከተማ አስተዳደሩ ከሚገኙ የመንግስትና የግል 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሳነ መምህራን ጋር ውይይት ተካሄደ። (ህዳር 21/2016 ዓ.ም) ውይይቱን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ከአዲስ አበባ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ ጋር በመተባበር ያዘጋጀው ሲሆን በውይይቱ በሰላማዊ የመማር ማስተማር አተገባበርን በተመለከተ የተዘጋጀ የመወያያ ሰነድ በአዲስ አበባ ከተማ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ አማካሪ በአቶ ማስረሻ ሀብቴ ቀርቦ ውይይት ተካሂዷል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ዘላለም ሙላቱ በመርሀ-ግብሩ ባስተላለፉት መልዕክት በትምህርት ተቋማት ከጸጥታ ጋር የሚስተዋሉ አዝማሚያዎች የመማር ማስተማር ሂደቱ ላይ ችግር እንዳይፈጥሩም ሆነ በተቋማቱ የሚገኙ ንብረቶች ላይ ጉዳት እንዳያደርሱ በአመቱ መጀመሪያ ቢሮው ከሰላምና ጸጥታ ቢሮ ጋር በመሆን ባለድርሻ አካላትን በማወያየት ወደ መማር ማስተማር ስራ መግባቱን አስታውቀዋል። ዶክተር ዘላለም አክለውም ትምህርት ቤቶች ከማንኛውም የፖለቲካም ሆነ ሀይማኖታዊ እንቅስቃሴዎች ነጻ ሆነው መደበኛ የመማር ማስተማር ስራቸውን በአግባቡ ተግባራዊ ማድረግ እንዲችሉ ከባለድርሻ አካላት ጋር በየደረጃው ውይይት እንደሚካሄድ ጠቁመው በትምህርት ተቋማት የሚስተዋሉ የጸጥታ ችግሮች ከመንግስት ትምህርት ቤቶች ባሻገር በአንዳንድ በግል ትምህርት ቤቶችም እየተስተዋሉ በመሆናቸው የትምህርት ቤት ባለቤቶችና አመራሮች ለጉዳዩ ትኩረት ሰጥተው መንቀሳቀስ እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል።

ለት/ቤታች ተማሪ ወላጆች /አሳዳጊዎች በሙሉ :- ========================= በ2016 ዓ.ም የአዲሱ ስርዓተ ትምህርት በሁሉም ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤቶች ተግባራዊ መሆኑን ሆኖም የተማሪዎች መማርያ መፅሀፍ ታትሞ አለመቅረቡ በተማሪዎች መማር ማስተማር ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ፈጥሯል የሚል አስተያየቶች ከወላጆች መቅረቡ ይታወቃል ። አሁን መንግስት መፅሀፎቹን አሳትሞ ለግል ትምህርት ቤቶች መንግስት በተመነው ዋጋ እያከፋፈለ በመሆኑ ሁሉም ወላጆች ለልጆቻችሁ መፅሀፍ በክፍያ እንድትገዙ በጥብቅ እያሳሰብን ወላጆች ት/ቤት መጥታችሁ / በልጆቻችሁ በኩል/ በስልክ በአስቸኳይ መረጃ እንድትሰጡ በአክብሮትእንገልፃለን ። ማሳሰቢያ ‼️ ።።።።።።። ➡️ ሁሉም ተማሪ መፅሀፍ አሟልቶ መገኘት ግዴታው ነው ። ➡️ ት/ቤቱም ለተማሪዎች መፅሀፍ የሚያገኙበት አማራጭ መዘርጋትና ማመቻቸት ግዴታው ነው ።

ለታይም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ፣ መምህራን ፣ ወላጆችና አሳዳጊዎች ‼️ ።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።። በነገው ዕለት ከተመረጡ ተማሪዎች ፣ መምህራንና ከተማሪ ወላጆች ጋር በትምህርት ቤት መሻሻል እና ደረጃ ምደባ መረሀ ግብር ላይ በት/ቤቱ ተዘጋጅቶ የሚሰጥ ስልጠና ስለሚኖር መደበኛ ትምህርት የሚኖረው እስከ 6:30 ድረስ በመሆኑ እስከ ምሳ ረፍት ያሉት ክፍለ ጊዜ ያሉ የማስታወሻ ደብተሮቻችሁ ብቻ እንድትይዙና ወላጆችም ልጆቻችሁን በዚሁ ልክ እንድትከታተሉ በአክብሮት እንገልፃለን ።