ፀዊረ መስቀል
የየእለቱ ወንጌል ክፍል የየበዓላቱ ሥርዓተ ዋዜማ ፤ ሥርዓተ ማኅሌት ፤ #ወረብ፤ መዝሙራት እና ምስባክ በጽሑፍ እና በድምጽ የሚቀርበት ቻናል ነው ሼር እያደረጉ ሃይማኖታዊ ድርሻዎን ይወጡ። https://t.me/tsewire @tsewire DM @faya6
Show more📈 Analytical overview of Telegram channel ፀዊረ መስቀል
Channel ፀዊረ መስቀል (@tsewire) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 19 643 subscribers, ranking 4 085 in the Religion & Spirituality category and 1 715 in the Ethiopia region.
📊 Audience metrics and dynamics
Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 19 643 subscribers.
According to the latest data from 11 July, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by -125 over the last 30 days and by -11 over the last 24 hours, overall reach remains high.
- Verification status: Not verified
- Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 0.99%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 0.59% reactions from the total number of subscribers.
- Post reach: On average, each post receives 194 views. Within the first day, a publication typically gains 116 views.
- Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 2.
📝 Description and content policy
The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
“የየእለቱ ወንጌል ክፍል የየበዓላቱ ሥርዓተ ዋዜማ ፤ ሥርዓተ ማኅሌት ፤ #ወረብ፤ መዝሙራት እና ምስባክ በጽሑፍ እና በድምጽ የሚቀርበት
ቻናል ነው ሼር እያደረጉ ሃይማኖታዊ ድርሻዎን ይወጡ።
https://t.me/tsewire
@tsewire
DM @faya6”
Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 12 July, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Religion & Spirituality category.
እንግዲህ በነቢዩ በዳንኤል የተባለውን የመፍረሱን የርኵሰት ምልክት በተቀደሰ ቦታ ቆሞ ባያችሁት ጊዜ አንባቢው ያስተውል። ያንጊዜ በይሁዳ ያሉ ወደ ተራሮች ይሽሹ። "በሰገነት ያለም በቤት ውስጥ ያለውን ያነሣ ዘንድ አይውረድ። በእርሻም ያለ ልብሱን ይወስድ ዘንድ ወደ ኋላው አይመለስ። "ነገርግን በዚያ ወራት ለፀነሱና ለሚያጠቡ ወዮላቸው! "ነገር ግን ሽሽታችሁ በክረምት ወይም በሰንበት እንዳይሆን ጸልዩ። “ያንጊዜ ዓለም ከተፈጠረ ጀምሮ እስከ ዛሬ ያልተደረገ፥ ከእግዲህም ወዲያ የማይደረግ ታላቅ መከራ ይሆናል። "እነዚያ ቀኖችስ ባያጥሩ ኖሮ ሥጋ የለበሰ ሁሉ ባልዳነም ነበር፤ ነገር ግን ስለ ተመረጡት እነዚያ ቀኖች ያጥራሉ። "ያንጊዜ እነሆ፥ ክርስቶስ በዚህ አለ፤ ወይም በዚያ አለ የሚላችሁ ሰው ቢኖር አትመኑ። ሐሰተኞች መሢሖችና ሐሰተኞች ነቢያት ይነሣሉና፤ ቢቻላቸውስ የተመረጡትን እንኳ ለማሳት ታላላቅ ተአምራትንና ድንቅ ሥራን ይሠራሉ። እነሆ፥ አስቀድሜ ነገርኋችሁ። እነሆ፥ በምድረበዳ አለ ቢሉአችሁ አትውጡ፤ እነሆም፥ በቤት ውስጥ ነው ቢሉአችሁ አትመኑ። መብረቅ ከምሥራቅ እንደሚወጣ፥ እስከ ምዕራብም እንደሚታይ የሰው ልጅም መምጣት እንዲሁ ይሆናል። ገደላ ባለበት አሞሮች በዚያ ይሰበሰባሉ።
“ከእነዚያም ቀኖች መከራ በኋላ፥ ወዲያውኑ ፀሐይ ይጨልማል፤ ጨረቃም ብርሃኑን አይሰጥም፤ ከዋክብትም ከሰማይ ይወድቃሉ፤ የሰማያት ኀይልም ይናወጣል። በዚያም ወራት የሰው ልጅ ምልክት በሰማይ ይታያል፤ ያንጊዜም የምድር አሕዛብ ሁሉ ያለቅሳሉ፤ የሰው ልጅንም በኀይልና በብዙ ክብር በሰማይ ደመና ሲመጣ ያዩታል። መላእክቱንም ከታላቅ የመለከት ድምፅ ጋር ይልካቸዋል፤ የተመረጡትንም ከሰማይ ዳርቻ እስከ ዳርቻው ከአራቱ መዐዝን ይሰበስቧቸዋል።
“ምሳሌውንም ከበለስ ዕወቁ፤ ጫፍዋ የለሰለስ፥ ቅጠልዋም የለመለመ እንደሆነ እነሆ መከር እንደ ደረሰ ታውቃላችሁ። "እንዲሁ እናንተ ይህን ሁሉ ባያችሁ ጊዜ፥ እንደ ቀረበና በዳጃፍ እንዳለ ዕወቁ። "እውነት እላችኋ ለሁ፤ ይህ ሁሉ እስኪደረግ ድረስ ይቺ ትውልድ አታልፍም። ሰማይና ምድር ያልፋሉ፥ ቃሌ ግን አያልፍም.......
1 ቆሮንጦስ 15:33-45 1 ዮሐንስ 2:20-ፍጻሜ ሐዋ፡ሥራ 16:14-18👉 ቅዳሴ ዘሐዋርያት
ምስባክ መዝሙር 55:13-ፍጻሜእስመ አድኀንካ ለነፍስየ እሞት ወለአዕይንትየኒ እም አንብዕ ወለእገርየኒ እምዳህፅ
1 ተሰሎንቄ 4:13-ፍጻሜ 2 ጴጥሮስ 1:1-13 ሐዋ.ሥራ 23:10:16ምስባክ መዝሙር 18:3 አልቦ ነገር ወአልቦ ነቢብ ዘኢተሰምዐ ቃሎሙ ውስተ ኩሉ ምድር ወጽአ ነገሮሙ ወእስከ አጽናፈ ዓለም በጽሐ ነቢቦሙ
ምሳም ከበሉ በኋላ ጌታችን ኢየሱስ፦ ስምዖን ጴጥሮስን፥ “የዮና ልጅ ስምዖን ሆይ፥ ከእነዚህ ይልቅ ትወደኛለህን?” አለው፤ እርሱም፥ “አዎን፥ ጌታዬ ሆይ፥ እኔ እንደምወድህ አንተ ታውቃለህ” አለው፤ ጌታችን ኢየሱስም፥ “በጎቼን ጠብቅ” አለው። ዳግመኛም፥ “የዮና ልጅ ስምዖን ሆይ፥ ትወደኛለህን?” አለው፤ እርሱም፥ “አዎን፥ ጌታዬ ሆይ፥ እኔ እንደምወድህ አንተ ታውቃለህ” አለው፤ “ጠቦቶቼን አሰማራ” አለው። ሦስተኛ ጊዜም፥ “የዮና ልጅ ስምዖን ሆይ፥ ትወደኛለህን?” አለው፤ ጴጥሮስም ሦስት ጊዜ ትወደኛለህን? ስላለው ተከዘ፤ “ጌታዬ ሆይ፥ አንተ ሁሉን ታውቃለህ፤ እኔም እንደምወድህ አንተ ታውቃለህ” አለው፤ “እንኪያስ ግልገሎቼን ጠብቅ” አለው። “እውነት እውነት እልሃለሁ፤ አንተ ጐልማሳ ሳለህ በገዛ እጅህ ወገብህን ታጥቀህ ወደ ወደድኸው ትሄድ ነበር፤ በሸመገልህ ጊዜ ግን እጆችህን ትዘረጋለህ፤ ወገብህንም ሌላ ያስታጥቅሃል፤ ወደማትወደውም ይወስድሃል።” "በምን ሞት እግዚአብሔርን ያከብር ዘንድ እንዳለው ሲያመለክት ይህን ተናገረ፤ ይህንም ብሎ ተከተለኝ አለው.....
1 ተሰሎንቄ 4:13-ፍጻሜ 2 ጴጥሮስ 1:1-13 ሐዋ.ሥራ 23:10:16ቅዳሴ ዘ፫፻ (ግሩም)
ምስባክ መዝሙር138:17-18ወኀቤየሰ ፈድፋደ ክቡራን አዕርክቲከ እግዚኦ ወፈድፋደ ፀንዑ እምቀደምቶሙ እኌልቆሙ እምኆፃ ይበዝኁ
ትርጉምአቤቱ ወዳጆችህ በእኔ ዘንድ እጅግ የከበሩ ናቸው ከቀደምቶቻቸውም እጅግ ጸኑ እቈጥራቸዋለሁ ከአሸዋም ይልቅ ይበዛሉ፤
ሌላ ምሳሌ ስሙ፤ ባለቤት ሰው ወይንን ተከለ፤ ቅጥርም ቀጠረለት፤ መጭመቂያም አስቈፈረለት፤ ግንብም ሠራለት፤ ለገባሮችም ሰጥቶአቸው ሄደ። የሚያፈራበት ወራት በደረሰ ጊዜም፥ ከወይኑ ፍሬ ያመጡለት ዘንድ አገልጋዮችን ወደ ገባሮቹ ላከ። ገባሮቹም አገልጋዮቹን ይዘው፥ አንዱን በበትር ደበደቡት፤ አንዱንም ገደሉት፤ ሌላውንም በድንጋይ መቱት። ከዚያም በኋላ ከቀደሙት የሚበዙ ሌሎች አገልጋዮችን ላከ፤ እነርሱንም እንዲሁ አደረጉባቸው። በኋላም ልጄንስ ይፈሩት ይሆናል ብሎ ልጁን ላከ። ገባሮቹም ልጁን ባዩት ጊዜ እርስ በርሳቸው፦ እነሆ፥ ወራሹ ይህ ነው፤ ኑ እንግደለውና ርስቱን እንውረስ ተባባሉ። ይዘውም ከወይኑ ቦታ ወደ ውጭ አውጥተው ገደሉት። “እንግዲህ የወይኑ ቦታ ባለቤት በመጣ ጊዜ እነዚህን ገባሮች ምን ያደርጋቸዋል?” "እነርሱም፥ “ክፉዎችን በክፉ ያጠፋቸዋል፤ ወይኑንም በየጊዜው ፍሬውን ለሚሰጡት ለሌሎች ገባሮች ይሰጣል” አሉት። «ጌታችን ኢየሱስም እንዲህ አላቸው፥ “በመጻሕፍት ያለውን ያነበባችሁበት ጊዜ የለምን? ግንበኞች የናቁአት ድንጋይ የማዕዘን ራስ ሆነች፤ ይህቺም ከእግዚአብሔር ዘንድ ሆነች፤ ለዐይኖቻችንም ድንቅ ናት። ስለዚህም እላችኋለሁ፤ የእግዚአብሔር መንግሥት ከእናንተ ትወሰዳለች፤ ፍሬዋንም ለሚያደርጉ ለአሕዛብ ትሰጣለች። በዚያችም ድንጋይ ላይ የሚወድቅ ይቀጠቀጣል፤ በላዩ የምትወድቅበትንም ትፈጨዋለች።”
የካህናት አለቆችና ፈሪሳውያንም ምሳሌዎቹን በሰሙ ጊዜ፥ ስለ እነርሱ እንደተናገረ ዐወቁ። ሊይዙትም ሲፈልጉ ሕዝቡን ፈሩአቸው፤ በእነርሱ ዘንድ እንደ ነቢይ ነበርና....
ዕብራውያን 11:32-ፍጻሜ 2 ጴጥሮስ 1:19-ፍጻሜ ሐዋ.ሥራ 10:37-ፍጻሜቅዳሴ ዘወልደ ነጎድጓድ
ምስባክ መዝሙር 43:1-2እግዚኦ ሰማዕነ በእዘኒነ ወአበዊነሂ ዜነዉነ ግብረ ዘገበርከ በመዋዕሊሆሙ በመዋዕለ ትካት
ትርጉምአቤቱ በጆሮአችን ሰማን አባቶቻችንም ነገሩን በዘመናቸው በቀድሞ ዘመን የሠራኸውን ሥራ
“ወንድምህ አንተን ቢበድልህ፥ ሄደህ ብቻህን ሆነህ፥ ብቻውን አድርገህ ምከረው፤ ቢሰማህ ወንድምህን ጠቀምኸው። "ባይሰማህ ግን በሁለተኛው ጊዜ ከአንተ ጋር አንድ ወይም ሁለት ምስክር ያዝ፤ ነገር ሁሉ በሁለት ወይም በሦስት ምስክር ቃል ይጸናልና። እነርሱን ባይሰማቸው ግን ለቤተ ክርስቲያን ንገራት፤ ቤተ ክርስቲያንንም ባይሰማት እንደ አረማዊና እንደ ቀራጭ ይሁንልህ። እውነት እላችኋለሁ፤ በምድር የምታስሩት በሰማይ የታሰረ ይሆናል፤ በምድርም የምትፈቱት በሰማይ የተፈታ ይሆናል። ዳግመኛም እላችኋለሁ፤ ከእናንተ ሁለቱ በምድር ላይ ስለሚለምኑት ነገር ሁሉ ቢተባበሩ፥ በሰማያት ባለው አባቴ ዘንድ ይደረግላቸዋል። ሁለት ወይም ሦስት በስሜ በሚሰበሰቡበት እኔ በዚያ በመካከላቸው እኖራለሁና”.........
ቲቶ 3:8-ፍጻሜ 1 ጴጥሮስ 3:15-ፍጻሜ ሐዋ.ሥራ 20:28-31ቅዳሴ ዘቄርሎስ
ምስባክ መዝሙር 21:22-23እነግሮሙ ስመከ ለአኃውየ ወበማዕከለ ማኅበር እሴብሐከ እለ ትፈርህዎ ለእግዚአብሔር ሰብሕዎ
ትርጉምስምህን ለወንድሞቼ እነግራቸዋለሁ በጉባኤም መካከል አመሰግንሃለሁ እግዚአብሔርን የምትፈሩ አመስግኑት
እነሆም አንድ ጐልማሳ መጥቶ፥ “ቸር መምህር ሆይ የዘለዓለም ሕይወትን እወ ርስ ዘንድ ከበጎ ሥራ ወገን ምን ላድርግ?” አለው። እርሱም፥ “ለምን ቸር ትለኛለህ? ከአንዱ እግዚአብሔር በቀር ማንም ቸር የለም፤ ወደ ሕይወት ልትገባ ብትወድድስ ትእዛዛትን ጠብቅ” አለው። እርሱም፥ “የትኞቹን?” አለው፤ ጌታችን ኢየሱሱም አለው፥ “አትግደል፥ አታመንዝር፥ አትስረቅ፥ በሐሰትም አትመስክር፥ "አባትህንና እናትህን አክብር፤ ባል ንጀራህንም እንደ ራስህ ውደድ።” ያም ጐልማሳ፥ “ይህን ሁሉ ከሕፃንነቴ ጀምሬ ጠብቄአለሁ፤ እንግዲህ የቀረኝ ምንድን ነው?” አለው። ጌታችን ኢየሱስም እንዲህ አለው፥ “ፍጹም ልትሆን ብትወድስ፥ ሂድና ያለህን ሁሉ ሸጠህ ለድኾች ሰጥ፤ ሰማያዊ ሀብትንም ታገኛለህ፤ መጥተህም ተከተለኝ።” ጐልማሳውም ይህን ነገር ሰምቶ ሀብቱ ብዙ ነበርና እያዘነ ሄደ። ጌታችን ኢየሱስም ለደቀ መዛሙርቱ እንዲህ አላቸው፥ “እውነት እላችኋለሁ፤ ባለጸጋ ወደ መንግሥተ ሰማያት ይገባ ዘንድ ጭንቅ ነው። ዳግመኛም እላችኋለሁ፦ ባለጸጋ ወደ እግ ዚአብሔር መንግሥት ከሚገባ ይልቅ ግመል በመርፌ ቀዳዳ ቢያልፍ ይቀላል።” ደቀ መዛሙርቱም ይህን በሰሙ ጊዜ፥ “እንግዲያ ማን ሊድን ይችላል?” እያሉ እጅግ ተደነቁ። ጌታችን ኢየሱስም አያቸውና፥ “በሰው ዘንድ ይህ አይቻልም፤ በእግዚአብሔር ዘንድ ግን ሁሉ ይቻላል” አላቸው
ከዚህም በኋላ ጴጥሮስ መልሶ፥ “እኛ ሁሉን ትተን ተከተልንህ፤ እንግዲህ ምን እናገኛለን?” አለው። ጌታችን ኢየሱስም እንዲህ አላቸው፥ “እውነት እላችኋለሁ፤ የተከተላች ሁኝ እናንተ በዳግም ልደት የሰው ልጅ በክብሩ ዙፋን በተቀመጠ ጊዜ እናንተም በዐሥራ ሁለት ዙፋን ትቀመጣላችሁ፤ በዐሥራ ሁለቱም ነገደ እሥራኤል ትፈርዳላችሁ። ስለ ስሜም ቤትን፥ ወይም ወንድሞችን፥ ወይም እኅቶችን፥ ወይም አባትን፥ ወይም እናትን፥ ወይም ሚስትን፥ ወይም ልጆችን፥ ወይም ርስትን የተወ ሁሉ መቶ ዕጥፍ ዋጋ ያገኛል፤ የዘለዓለም ሕይወትንም ይወርሳል። ነገር ግን ብዙዎች ፊተኞች ኋለኞች ይሆናሉ፤ ኋለኞችም ፊተኞች ይሆናሉ......
1 ቆሮንጦስ 9:1-13 ይሁዳ 1:17-ፍጻሜ ሐዋ.ሥራ 5:17-33ዘሐዋርያት (ዘበደኀሪ)
ምስባክ መዝሙር 64:9-10ሐወጽካ ለምድር ወአርወይካ ወአብዛኅኮ ለብዕላ ፈለገ እግዚአብሔር ምሉዕ ማያተ
ትርጉምምድርን ጐበኘሃት አረካሃትም ብልጽግናዋንም እጅግ አበዛህ የእግዚአብሔር ወንዝ ውሆችን የተመላ
